Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርት ዘርፉን ሪፎርሞች ለማሳካት የትምህርት ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተ | Ministry of Education Ethiopia

የትምህርት ዘርፉን ሪፎርሞች ለማሳካት የትምህርት ባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ
-------------------------//-----------------
ጥር 25/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የ2016 በጀት አመት ዕቅድ አፈፃጸምን አስመልክቶ ምክክር ከክልልና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮዎች ጋር አካሂዷል ::

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ፤ የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመቅረፍና የትምህርት ተደራሽነትን፣ ተሳትፎንና ፍትሃዊነትን ለማሳደግ የተለያዩ የለውጥ መርሃ- ግብሮች ተቀይሰው ወደ ትግበራ መገባቱን ገልጸዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ እንደገለጹት የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ትግበራ፣ የመማሪያ መጻህፍት ህትመትና ስርጭት እንዲሁም የመምህራንና ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ ችግሮቹን ለመቅረፍ እየተሰራ ሲሆን ቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል::

ክብርት ወ/ሮ አየለች አክለውም የጀመርናቸውን የለውጥ መርሃ-ግብሮች ውጤታማ ማድረግ የሚቻለው ሁሉም የትምህርት ባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲያደርጉና የድርሻቸውን እንዲወጡ ማስተባበር ስንችል ነው ብለዋል::

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0iqwx3jhxUoV4DFe5ksu1siwUtSTpNA6Hk24Bgr55e5cKFU1GbkA3Njyksu3danHEl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO