Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_moe — Ministry of Education Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81.50K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-02-12 17:17:28
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚተገበሩ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች እውቀት-መር እና አሳታፊ በሆነ አግባብ መተግበር እንዳለባቸው ተገለጸ።

………………………………………. // ……………………………….
የካቲት 4/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚተገበሩ የማህበረሰብ አገልግሎት እና ማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ለሁሉም ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ጉድኝት የስራ ኃላፊዎች ስልጠና እየሠጠ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር የምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ሥራ አሥፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር ሥልጠናውን ሲከፍቱ ባስተላለፉት መልዕክት በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተደራሽነት ላይ ትኩረት ተሰጥቶ የተሰራ ቢሆንም ከምርምር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች አንጻር የተሻለ ስራ መስራት የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ዶ/ር ሰለሞን አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች ልዩ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ የህግ ማዕቀፎችን በማዘጋጀት እና የአቅም ግንባታ ስራዎች በማከናወን ላይ መሆኑን ጠቅሰው የዚህ ስልጠና ዓላማም በተለይም በማህበረሰብ ጉድኝት ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሻለ አሰራር ስራ እንዲዘረጉና እንዲተገብሩ ለማስቻል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ስልጠናው በኮሎራዶ ስቴት ዩኒቨርሲቲ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አሠፋ ገብረ-አምላክ የተሰጠ ሲሆን በሀገራችን የሚተገበሩ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች ከአለም-አቀፍ ተሞክሮ አንጻር መቃኘት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

ሙሉ ዜናው https://www.facebook.com/share/p/KwN95ba3WXkQaw9h/?mibextid=2JQ9oc
35.0K views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-11 21:31:40
የመላው ጥቁር ሕዝቦች የድልና ነፃነት ዓርማ ፣ የአፍሪካ ኩራት፣ የኢትዮጵያ ጀግኖች መታሰቢያ የሆነው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቆ በመመረቁ እንኳን ደስ አለን!

ትምህርት ሚኒስቴር!

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
38.6K views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-09 19:57:58
#ማስታወቂያ

በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ በ2016 በጀት አመት የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅም ለማጎልበት የሚያግዝ ልዩ የስልጠና መረሃግብር ለማዘጋጀት እየሰራ ይገኛል።

በዚሁ መሰረት ስልጠናው የመምህራንን የስልጠና ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ከሚገኙ መምህራን መርጃ ለመሰብስብ የሚያስችል የበይነ መረብ መጠይቅ ተዘጋጅቷል።

በመሆኑም በማንኛውም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሒሳብ፣ እንግሊዘኛና የተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዓይነቶችን የምታስተምሩ መምህራን
https://forms.office.com/r/B8GAUYUg4H

ላይ በመግባት የተዘጋጀውን መጠይቅ እንድትሞሉና ለሚዘጋጀው ስልጠና ጥራት አስተዋፅኦ እንድታደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የትምህርት ሚኒስቴር!
15.8K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-09 12:09:04
የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች “ ስልጡን አገልጋይነት ለሁለንተናዊ ስኬታማነት “በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት አደረጉ፡፡
...................................................

የካቲት 1/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) "ከእዳ ወደምንዳ" በሚል ሀገራዊ መልዕክት እንደ ሀገር በተዘጋጁ የውይይት ሰነዶች ላይ ለትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ለሁለት ቀናት የተሰጠው ስልጠናና ውይይት ተጠናቋል፡፡

“ ስልጡን አገልጋይነት ለሁለንተናዊ ስኬታማነት “በሚል ርዕስ በቀረበው ሰነድ የሪፎርሙ መዋቅር ከተቋማት ባህሪና ተልእኮ አንጻር የተቃኘ መሆኑ ፣ ብቃትን ማዕከል ያደረገ፣ ነጻ ፣ ገለልተኛና አካታች ሲቪል ሰርቪስ መገንባት፣ ግልጽና የማትጊያ ሂደቶችንም የተከተለ ስርዓት ማበጀትን ዓላማው ያደረገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በመሆኑም በትምህርቱ ዘርፍ ለሚተገበሩ የሪፎርም ስራዎች ስኬታማነት በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና ሰራተኞች ለውጤታማነቱ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ሊወጡ እንደሚገባ በከፍተኛ አመራሩ ተገልጿል ፡፡

በመድረኩ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ አስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ ( ዶ/ር ) “ ስልጡን አገልጋይነት ለሁለንተናዊ ስኬታማነት “በሚል ርዕስ ሲቪል ሰርቪስን የተመለከተ የመወያያ ሰነድ አቅርበዋል፡፡

በቀረበው ሰነድ መነሻ በትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የአጠቃለይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴና የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ኮራ ጡሹኔ መሪነት ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ዝርዝሩ

https://www.facebook.com/share/p/hyLBGNab4wnKpsoS/?mibextid=9R9pXO
16.0K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-08 11:13:02
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች በሀገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እካሄዱ፡፡
====================
ጥር 30/2016(ትምህርት ሚኒስቴር) ከ”እዳ ወደ ምንዳ” በሚል መሪ መልዕክት እንደ ሀገር በተዘጋጀው የውይይት ሰነድ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች ውይይት እያካሄዱ ይገኛሉ፡፡

የውይይቱ አላማ ሰራተኛው በሀገራዊና ክልላዊ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም የሰላም ሁኔታ ላይ በመወያየትና በመመካከር የተሻለ ግንዛቤ በመፍጠር መሆኑ ተገልጿል።

ውይይቱ በመጀመርያ ቀን ውሎው ሀብት የመፍጠር ጉዟችን፣ እያጋጠሙን ያሉ ተግዳሮቶችና ቀጣይ አቅጣጫዎች በሚል ርእስ የተዘጋጀ የውይይት መነሻ ሰነድ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራአስፈፃሚ ኤባ ሚጅና(ፒኤችዲ) ቀርቧል።

በቀረበው ሰነድ መነሻ በትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የአጠቃለይ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት አየለች እሸቴና በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ኮራ ጡሹኔ መሪነት ውይይት ተደርጎበታል፡፡

ውይይቱ ዛሬም አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ብልፅግና በሚል ርእስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
19.6K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-08 07:48:19
#ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

ለድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ

የካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና  ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የ ድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍቃል (Password) ከታችበተዘረዘሩት አማራጮች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

1. በምዝገባ ወቅት በሞላችሁት email በኩል

2.  https://exam.ethernet.edu.et  ላይ በመግባት የከፈላችሁበትን Transaction Number በማስገባት እንዲሁም

3. ከተመደባብችሁብት የመፈተኛ ተቋም ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ
• ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች የይለፍቃል (Password) የምታገኙት ከምትማሩበት ወይም ከተመደባብችሁበት የመፈተኛ ተቋም ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን።

• ሁሉም ተፈታኞች የሞዴል ፈተናን እስከ  የካቲት 5/2016 ዓ.ም መውሰድ ይኖርባቸዋል።

ትምህርት ሚኒሰቴር !

የትምህርት ሚኒስቴርን መረጃዎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
19.7K views04:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-06 12:36:53
ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ በትግራይ ክልል ከትምህርት አንጻር በርካታ ስራዎች መስራታቸው ተገለጸ
.............................................................
ጥር 28/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የፌዴራል መንግስት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካደረጉት የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ በትግራይ ክልል ከትምህርት አንጻር በርካታ ስራዎች መስራታቸውን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ፒኤችዲ)  ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን  የተናገሩት በ16ኛው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ለተጠየቁ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከፕሪቶሪያው ስምምነት በፊት ትግራይ ውስጥ ትምህርት መቋረጡን ገልጸው አሁን ሁሉም ዩኒቨርስቲዎችና ከሞላ ጎደል ሁሉም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስራ ጀምረዋል ብለዋል።

ይህንንም ለማሳካት የፌዴራል መንግስት፣ ትምህርት ሚኒስቴርና የክልሉ ትምህርት ቢሮ በትብብር በርካታ ስራ መስራታቸውን አስታውሰዋል።

በትምህርት ጥራት፣  መስፋፋት፣ በመጽሀፍት አቅርቦት እንደማንኛውም አካባቢ ክፍተት ሊኖር እንደሚችል የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባጠቃላይ ግን  ትምህርት መጀመሩ አስደሳች መሆኑን ገልፀዋል።

በትግራይ ክልል በአራቱም ዩኒቨርስቲዎች ትምህርት እየተሰጠ ሲሆን በሁለተኛ ደረጃ  ትምህርት የ2015 ዓ.ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናም መሰጠቱ ይታወሳል።
16.0K views09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-06 11:28:19
15.2K views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-05 14:31:54
#የቀን ለውጥ ማስታወቂያ

ረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት ለመስጠት ሀሙስ የተጠራው ስብሰባ ወደ አርብ የካቲት 1/2016 ዓ.ም ጠዋት 3:30 ሰዓት መሸጋገሩን ስለማሳወቅ

የትምህርት ሚኒስቴር: -

1. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣
2. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣
3. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ መምህራን ምልመላና መረጣ የአፈጻጸም መመሪያ፣ የሚሉ 3 መመሪያዎችን አዘጋጅቷል።

መመሪያዎቹ በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አስተያየት ሰጥተውባቸው የዳበሩ ሲሆን የፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2012 ክፍል 2 ንዑስ ክፍል 2 አንቀጽ 10 መሰረት የሚዘጋጁ መመሪያዎች ከመጽደቃቸው በፊት ማንኛውም ሰው የሚሳተፍበት የውይይት መድረክ ማዘጋጀትና ግብዓት መሰብሰብ እንዳለበት ስለሚደነግግ ሚኒስቴሩ የውይይት መድረከ አዘጋጀቷል።

በዚህም መሰረት አርብ የካቲት 01/2016 ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በትምህርት ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ለባለድርሻ አካላት የገለጻና የውይይት መድረክ ስለተዘጋጀ በተጠቀሰው ጊዜና ቦታ በመገኘት አስተያየት እንድትሰጡ ተጋብዛችኋል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et ይከታተሉ
14.3K viewsedited  11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-04 14:31:09
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአደንዛዥ እጽና መድሃኒቶች ሥርጭት ለመከላከል በትኩረት መሰራት እንዳለበት ተገለፀ።
----------------- //--------------------
ጥር 26/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በአደዛዥ እጽና መድሃኒቶች ሥርጭት ዙሪያ ውይይት ተደርጓል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአስተዳደር ጉዳዮች ዴስክ ኃላፊ አቶ አብዶ ናስር በዩኒቨርሲቲዎች የአደንዛዥ እጽና መድሃኒቶች ተጠቃሚነት ችግሮችን ለመከላከል ሥራዎች ሲሰሩ የቆዩ ቢሆኑም ከችግሩ ስፋትና ባህሪ አንጻር የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ ገልጸዋል፡፡

አቶ አብዱናስር አክለውም ችግሩን ለመፍታትም አደንዛዥ እጾችና መድሃኒቶች ወደ ተቋማቱ እንዳይገቡ ከባለድርሻ አካላት ጋር የቁጥጥር ስራዎችን ከመስራት ጎን ለጎን በጉዳዩ አሳሳቢነት ዙሪያ መንስኤዎችን፣ልምዶችንና መፍትሄዎችን መሠረት ያደረጉ የባህሪ ለውጥ ሊያመጡ በሚችሉ የተማሪ ሥልጠናዎች ላይ ማተኮር እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጤንነቱ የተጠበቀ ትውልድ ለመቅረፅ ፤ ስብዕናን በመገንባትና ግንዛቤ በመፍጠር የባህሪ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት መሰረት እንደሚገባም ገልጸዋል።

ሀላፊው አክለውም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት በችግሩ አሳሳቢነት ልክ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅንጅትና በትኩረት ሊሠሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0qG8vx8mBtALovuwLTZfPpvKo8BoYHqjmH92H9sLYGDN6JnYwLev3nr6YofkgzwxTl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
15.9K views11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ