Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_moe — Ministry of Education Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81.50K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2024-01-01 08:26:15
15.4K views05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-31 09:51:58
20.5K views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-30 10:46:25
ብዝኃነትን መኖር በሚል መሪ ሐሳብ የአብሮነት ቀን ለስድስት ቀናት መከበር ጀምሯል።
.............................................
ታህሳስ 20/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) እ.አ.አ. በ1995 የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ፦ ዩኔስኮ ኅዳር 6 ቀንን  ዓለም አቀፍ የአብሮነት (Tolerance) ቀን እንዲኾን ዐውጇል፡፡

የቀኑ መታወጅ ዓላማ በኅብረተሰቡ ውስጥ የአብሮነትን ጥቅም ግንዛቤ ለመፍጠርና መቻቻል ያለዉን ፋይዳ ማስገንዘብ ነው፡፡

በኢትዮጵያም ብዝኃነትን የሚያከብር፣ አብሮነትን ገንዘብ ያደረገ፣ ኃላፊነት የሚሰማዉ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረዉን ጥረት ለማገዝ፣ ማኅበራዊ ዕሴቶቻችንን ለማሳደግና ለለውጥ ዝግጁ ዜጋና  ኅብረተሰብ ለመፍጠር ተቻችሎ መኖር አንዱ ለአንዱ አስፈላጊዉ አንደኾነ ማመንን ለማስረጽና ግንዛቤ ለማሳደግ ቀኑ ይከበራል፡፡ 

ዘንድሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበረዉ ዓለም አቀፉ የአብሮነት ቀን "ብዝኃነትን መኖር!" በሚል መሪ ሐሳብ ከታኅሣሥ 20-25 ቀን 2016 ዓ.ም እየተከበረ ይገኛል።

የአብሮነት ሳምንቱ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበር ከመርሐ ግብሩ መረዳት ተችሏል።

የበዓሉን አከባበር ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከተለያዩ የፌዴራል ተቋማትና ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመኾን ያስተባብራል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
13.8K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-29 16:35:08
በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ ጥሪና ትምህርት ማስጀመርን አስመልክቶ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

.በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ፡፡

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ክልል በተፈጠረው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ-ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አልቻሉም ነበር።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ሲያካሂድ ቆይቷል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የአስሩ ዩኒቨርስቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ትናንት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም በጉዳዩ ዙሪያ የመከሩ ሲሆን አሁን በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር እንደሚችሉ ውሳኔ ላይ ተደርሷል።

በዚህም መሰረት ከጥር 1/2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን ይጀምራሉ።

በመሆኑም በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተመደባችሁ ተማሪዎች ዩኒቨርስቲዎቹ የሚያደርጉትን ጥሪ እንድትከታተሉ እንገልጻለን።
17.6K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-29 16:35:06 Press release .docx
14.1K views13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-27 12:58:13
በትምህርት ስርዓቱ ላይ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት ትኩረት ሰጥቶ መረባረብ እንደሚገባ ተገለፀ።
…………………………………………………………………………………………………
ታህሳስ 17/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በትምህርት ዘርፍ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ኤጁኬሽን ዴቨሎፕመንት ትረስት (EDT) ሲሰራቸው የነበሩ ስራዎችን ማስቀጠል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ተካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት በትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንና ትምህርት አመራር ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ ባለፉት አራት ዓመታት Education Development Trust (EDT) በርካታ ስራዎችን ሲሰራ እንደነበር አንስተዋል።

በተለይም የትምህርት ቤት አመራር ስልጠና እንዲሁም የትምህርት መረጃ ስርዓትን ማሻሻል ላይ የሠራቸው ስራዎች አሁን በትምህርት ሚኒስቴር ቁልፍ ጉዳዮች ተደርገው ተለይተዋል ብለዋል።

በዚህም የማስተማርና የትምህርት ቤት አካባቢ የየተሟላ እውቀትና ልምድ ያላቸው የትምህርት ቤት አመራሮችን ለመፍጠር በትኩረት እየተሠራ ይገኛልም ብለዋል።

ዛሬ በትምህርት ስርዓቱ ላይ ትኩረት ሰጥተን ካልተረባረብን ነገ የሚፈለገውን ለውጥ ማምጣት አንችልም ያሉት ስራ አስፈፃሚው ያለውን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም በትምህርት ዘርፍ ለውጥ ማምጣት ይገባልም ነው ያሉት።

ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid021HYrNui4s41fbzsNK3Ds5SNPq3zt5RRPnxQRDR6hBfbmAC5YAgo8mVJHrwJkjZXol&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
22.6K views09:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-23 16:13:58
ምርምሮች ሀገራዊ የትኩረት መስኮችን ያማከሉና ችግር ፈቺ ሊሆኑ ይገባል" ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር (የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ)
...................................................
ታህሳስ 13/2016 ዓ/ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንቶች ፎረም ተጠናቀቀ።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር በፎረሙ ማጠቃለያ ምርምር ለሀገር እድገትና ልማት ያላቸውን አስተዋጾ ጠቅሰው ፎረሙ ሀገራዊ የምርምር ስራ ማነቆዎችን በመለየት በሳይንሳዊ መንገድ ግንዛቤ መፍጠር ይጠበቅበታል ብለዋል።

ዶ/ ሰለሞን ምርምሮች ሀገራዊ የትኩረት መስኮችን ያማከሉና ችግር ፈቺ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ከአፈጻጸም አንጻርም የከፍተኛ ትምህርት ፣ ቴክኒክና ሞያ ሥልጠና፣ ምርምር ተቋማትና ኢንዱሰትሪ ትስስር አዋጅ 1298/2015 ጋር እያጣጣሙ መተግበር እንደሚገባ አመላክተዋል።

የማህበረሰብ ጉድኝት ስራዎች እውቀት መር መሆን እንዳለበት የጠቀሱት መሪ ስራ አስፈጻሚው መምህራን በእውቀታቸው ማህበረሰቡን በሚያገለግሉበትና ማህበረሰቡ ጋ ያሉ ሀገር በቀል እውቀቶችንም በሚጠቀሙበት አግባብ ሊመራ እንደሚገባው ገልጸዋል።

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0HPx5wyvSEJViDxPotEobRe2NJTh48j2fVDrTgoFCZBePzLUwg4rEgx8xcm2pRRASl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
15.3K views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-22 12:31:39
የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንቶች ፎረም በቦንጋ ከተማ ተጀመረ
.............................................
ታህሳስ 12/2016 ዓ/ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንቶች ፎረም በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተጀመሯል።

በፎረሙ ማስጀመሪያ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ እንደሀገር የሚሰሩ ምርምሮች ችግር ፈቺ ፣የምርምር ስነምግባር የተከተሉና የምርምር መስፈርቶች ያሟሉ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል ።

በምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ዘርፍ ዩኒቨርስቲዎች የተሻለ ውጤታማ ለመሆን እርስ በርስና ከአለም አቀፍ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ትብብር መመስረትና ማጠናከር እንደሚገባም ተናግረዋል ።

የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጰጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ቦንጋ ዩኒቨርስቲ በምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ዘርፍ ዉጤታማ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር ፎረሙ በሁለት ቀን ውሎው በከፍተኛ ትምህርት ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ምርምር ተቋማት እና ኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅ ቁጥር 1298/2015 ፣ በከፍተኛ ትምህርት ምርምርና ማህበረሰብ ጉድኚት ማስፈጸሚያ መምሪያዎች፣ እንዲሁም የተመረጡ ዩኒቨርስቲዎች የምርምር ተግባራት አፈጻጸም ላይ ይመክራል ብለዋል።

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0WEsXBugxxedNmFW7rV4vwqkqV4nEpysY8vH3B9MKVgzywKNxhKfArKp1eS1xX9dPl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
16.6K views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-20 20:33:21
የሩሲያ መንግስት በትምህርት መስክ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለጸ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ታህሳስ 10/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የኢፊዲሪ ትምህር ሚኒስትር ክቡር ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ትምህርት ሚኒስትር እና ከሌሎች የሩሲያ የትምህርትና ምርምር ተቋማት የተውጣጡ ልኡካንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

ሚንስትሩ ከልኡካኑ ጋር በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ እና በሩሲያ ፌዴሬሽን መካከል ያለውን የቆየ የትምህርትና ሥልጠና ትብብር እንዲሁም አሁን ላይ በሀገራችን ተግባራዊ እየሆነ ያለውን የትምህርት ስርአት ፣መዋቅር እና ሰትራቴጂካዊ የትኩረት አቅጣጫዎች አስመልከቶ ገለጻ አድርገዋል።

ክቡር ሚኒስትሩ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ያለውን ርብርብ የገለጹ ሲሆን በማያያዝም በመጪዎቹ አመታት የትምህርት ዘርፉን ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ እየተከናወኑ ያሉ ሰፋፊ የሪፎርም ስራዎችን አብራርተዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሸኔ በበኩላቸው የሩሲያ መንግስት በትምህርቱ ዘርፍ ለኢትዮጵያ እያደረገ ስላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በማያያዝም የሩሲያ መንግስት የሚያደርገው ድጋፍ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እና የሰው ሀብት ልማትን ለማሳደግ ሚናው የጎላ በመሆኑ ትብብሩን በቀጣይ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሳደግ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ከፍተኛ ፍላጎት ያለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02acg4VDWqNxxqz47thaDxGhKgrT2KxK3iyJN3Kh2k49XPUNhQvcfHabBew9M59mc2l&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
16.0K views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-16 17:12:33
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ለማስጀመር የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ መምህራን ተመረቁ
.............................................................................................................................................................................................................
ታህሳስ 06/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ለማስጀመር የአቅም ግንባታ ሥልጠና በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሲከታተሉ የነበሩ መምህራን አጋሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማክሰኞ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ/ም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀዋል።

ከተለያዩ የኢትዮጵያ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ 32 መምህራን ለ8 ወራት በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሜሪ ሉ ፉልተን መምህራን ኮሌጅ በInstructional Design and Performance Improvement ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሲሆን በዕለቱ በግራጁዌት ሰርተፊኬት ተመርቀዋል፡፡

በተጨማሪም በዕለቱ የዲጂታል ትምህርት አዘገጃጀት የአሰልጣኞች ስልጠናን በኮሌጁ ሲከታተሉ የቆዩ 19 መምህራንም ተመርቀዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0MS6LL9gEFvmdEyZBoaAKhZaKQ4qpSz849cWYrDXhnsRy5sBhjJXqUVEErbkWezvyl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
17.1K views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ