የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
81.50K
የሰርጥ መግለጫ
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
3
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10
2023-10-04 10:59:32
#ማስታወቂያ
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚሠጠው ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 21 ጀምሮ እስከ 25/01/2016 ዓ.ም ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።
ለመመዝገብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴሌ ብር ሱፐርአፕ
https://portal.aau.edu.et
ወይም ለዚህ ፈተና ብቻ በሚያገለግለው
https://gat.aau.edu.et
ይመዝገቡ
13.8K views07:59
2023-10-03 19:56:12
ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28-30 /2016 ዓ.ም ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይሠጣል።
...................................//……………………………….
መስከረም 22/2016 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር)
በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጠው ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28-30/2016 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሰጡ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች ለመማር የብሄራዊ ድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና መውሠድ በቅድመ ሁኔታነት መቀመጡን አብራርተዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ማሻሻያ ዴስክ ሃላፊ አቶ ሰይድ መሀመድ በበኩላቸው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚሠጠው ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 21 ጀምሮ እስከ 25/01/2016 ዓ.ም የሚቆይ ምዝገባ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አያይዘውም ከመስከረም 23-25/2016 ዓ.ም የልምምድ ፈተና (Mock Exam) የሚሰጥ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ተፈታኞች በተመዘገቡበት ዩኒቨርሲቲ በመገኘት User name እና Password በመጠቀም የልምምድ ፈተና መውሰድ ይችላሉ ብለዋል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፈተናው በተሣካ ሁኔታ እንዲካሄድ የበኩላቸውን ጥረት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
የፈተና አሰጣጡን ዝርዝር መረጃ የሚከተለውን ሊንክ በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ፣ https://shorturl.at/jKLR9
16.8K views16:56
2023-09-27 13:49:21
15.6K views10:49
2023-09-24 11:57:42
በትምህርት ሴክተሩ የሚተገበሩ ተግባራትን በህግና ስርዓት መፈፀም እንደሚገባ ተጠቆመ ።
................................................
መስከረም 13/2015 ዓ/ም (የትምህርት ሚኒስቴር) ለትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች በፌድራል አስተዳደር አዋጅ 1183/2012 ላይ ስልጠና ተሰጥቷል።
የስልጠና መድረኩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ የሚሠሩ ማናቸውም ስራዎች በህግና በሥርዓት ማስፈፀም ይገባል ብለዋል።
አክለውም በትምህርት ሴክተሩ እየተካሄዱ ያሉት ሪፎርሞች በህግ ማዕቀፍ መተግበር መቻል እንዳለባቸውም ጠቁመዋል።
በዚህም እንደ ትምህርት ሴክተር በ2015 ዓ.ም በርካታ አዋጆችና ደንቦች መውጣታቸውን አንስተው በቀጣይ በአግባቡ መተግበር ይኖርባቸዋል ብለዋል።
ስልጠናውን የሠጡት ከፍትህ ሚኒስቴር ወ/ሮ ትብለፅ ቡሽራ ይህ ስልጠና በአስፈፃሚ አካላት መካከል ያለውን የግንዛቤ ክፍተት ለመሙላት ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
እንደሀገር በፍትህ ዘርፉ ሪፎርም ከተካሄደበቸው ህጎች አንዱ መሆኑን አነስተው አመራሩ በትክክል አዋጁን ተረድቶ ማስተግበር ይኖርበታልም ብለዋል።
የትምህርት ሚኒስቴር ስራ አመራር ዋና ስራ አስፈፃሚ ይበልጣል አያሌው(ዶ/ር) በበኩላቸው አዋጆችን ተከትለው የወጡ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ሰርኩላሮች የሰዎችን መብት የሚጫኑ ከሆነ በአዋጁ መሠረት ፈጥኖ መፈተሽ እና ማስተካከል እንደሚገባ አሳስበዋል።
ስልጠናውን የትምህርት ሚኒስቴር ከፍትህ ሚኒስትር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ነው።
19.9K views08:57
2023-09-23 14:58:31
#ማስታወቂያ
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ምዝገባና ፈተና ጊዜ ተራዝሟል።
የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (Graduate Admission Test) ከመስከረም 28-30/2016 ዓ.ም ጀምሮ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ይሰጣል።
በመሆኑም የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ከመስከረም 21-25/2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፖርታል https://portal.aau.edu.et በመጠቀም እንድትመዘገቡ እንገልጻለን ።
15.6K views11:58
2023-09-22 12:03:03
H.E Professor Birhanu Nega’s impromptu speech at the United Nations conference, at a side event held on Education: a catalytic investment for development. Providing youth with the freedom to build their future.
https://media.un.org/en/asset/k19/k19z23qz0r
14.9K views09:03
2023-09-21 12:31:29
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጉባኤ ላይ የትምህርትን መሰረተ ልማት ማሻሻል የቀጣዩን ትውልድ የወደፊት እድል ማሻሻል መሆኑን ገለጹ።
---------------------------------//----------------
መስከረም 10/2016ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር ) የትምህርት ሚኒስትሩ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአሜሪካ ኒውዮርክ መስከረም 08/2016 ዓ.ም ባዘጋጀው መድረክ ላይ ተሳትፈዋል ።
መድረኩ አለም አቀፉ ማህበረሰብ ድህነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና በተለያዩ የአለም ክፍሎች የማያቋርጥ ግጭትን እና አለመረጋጋትን ጨምሮ ውስብስብ ፈተናዎች ያሉበት በመሆኑ የ2030 የዘላቂ ልማት ግብ (SDG) አጀንዳ እና ሌሎች የጋራ ተግዳሮቶችን በዘላቂ ልማት ለመቅረፍ አገሮችን አንድ ለማድረግ ያለመ ነው።
በዚህም ሚኒስትሩ የተባበሩት መንግስታት ትምህርት በዲጅታል ዘመን ውስጥ ለልማት፣ ለፍትሃዊነት፣ ለሠላምና ለደህንነት የሚያግዝ ኢንቨስትመንት በሚል በኒውዮርክ ባዘጋጀው መድረክ ላይ ተገኝተው ቁልፍ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በትምህርት ላይ በተደረገ የጎንዮሽ ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር በትምህርት ላይ ኢንቨስት ማድርግ ስለ ቀጣዩ ትውልድና አለም ኢንቨስት ማድርግ ነው ያሉ ሲሆን እንደ ሀገርና መንግስት የተለያዩ ሪፎርሞችን በትምህርት ላይ እያካሄድን እንገኛለን ብለዋል።
ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02WjS3oZmg1jvXcBisePJgZKm8rygbdcAax743BJxEAXFAhcVbY7Y8pfsATwJqWKFwl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
17.6K viewsedited 09:31
2023-09-19 12:44:05
17.4K views09:44
2023-09-16 14:02:29
የአጠቃላይ ትምህርት የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት ሀገር አቀፍ የትምህርት ካላንደር
ማሳሰቢያ :- ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ
18.8K views11:02
2023-09-14 08:24:43
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና የብሄራዊ መታወቂያ መርሃ-ግብር በጋራ ዲጂታል የተማሪዎች መለያ ስርዓት (የተማሪ መታወቂያ) ተግባራዊ አደረጉ
17.9K views05:24