Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 82.27K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-08-25 11:31:47
የቻይና መንግስት በሰጠው የነፃ ትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ ተማሪዎች ሽኝት ተደረገ።
--------------------------------------------------
ነሐሴ 19/2015 (የትምህርት ሚኒስቴር) የቻይና መንግስት  በሰጠው የነጻ የትምህርት እድል አሸናፊ ለሆኑ 26 ተማሪዎች አዲስ አበባ በሚገኘው የቻይና ኢምባሲ  ትናንት ሽኝት ተደርጓል።

በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ የቻይና አምባስደር ዣዎ ዚዩአን  ሀገራቸው በኢትዮጵያ የሚደረገውን የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግርን  በዘላቂነት እንደምትደግፍ ገልጸዋል።

አምባሳደሩ አያይዘውም በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያና ቻይና መካከል ያለው ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂካዊ ትብብር  የጋራ በሆኑ ጉዳዮች በዘላቂነት ለመስራት እንደሚያስችል አብራርተዋል።

በትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት አለማቀፋዊነትና ስኮላርሺፕ ዴስክ ሀላፊ ዶ/ር ኢዶሳ ተርፋሳ በበኩላቸው  በኢትዮጵያ የሰለጠነ የሰው ሀይል ግንባታ ሂደት ውስጥ የቻይና መንግስት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ተማሪዎች ተጨባጭ እውቀት በመቅሰምና ወደ ሀገራቸው በመመለስ በእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር  ግምባታ የበኩላቸውን አስተዋጾ እንዲያደርጉም አሳስበዋል።

በተደረገው የሽኝት መርሃ ግብር ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሀላፊዎችና ቀደም ሲል በቻይና ትምህርታቸውን ተከታትለው የተመለሱ ምሁራን ልምዳቸውን አካፍለዋል።
12.9K views08:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-15 17:10:38
በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሮግራሞች አከፋፈት  የዩኒቨርስቲዎችን የትኩረትና ተልእኮ ልየታ የተከተለ እንዲሆን አቅጣጫ ተሰጠ::
……………………………………………………………………………………………………………………………………………………………

ነሃሴ 09/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር ) በ2016 የትምህርት ዘመን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሮግራሞች አከፋፈት  የዩኒቨርስቲዎችን የትኩረትና ተልእኮ ልየታ የተከተለ እንዲሆን  በትምህርት ሚኒስቴር ነሃሴ 09/2015ዓ. ም በተጻፈ ደብዳቤ አቅጣጫ ተሰጥቷል።

እስካሁን  በመሰጠት ላይ ያሉ የቅድመና ድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች በ2016 ዓ.ም በዝርዝር ተፈትሸውና  ተገምግመው  ከዩኒቨርስቲዎች ልየታ ጋር መጣጣማቸውን የማረጋገጥ ስራ እንደሚሰራም ተገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ለሁሉም ዩኒቨርስቲዎች በጻፉት ደብዳቤ የታቀዱ አዳዲስ ፕሮግራሞች ለመክፈት የሚደረጉ ጥናቶች ባሉበት እንዲቆዩ፣ መጪው የትምህርት ዘመን የመንግስት  ዩኒቨርስቲዎች በአዳዲስ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እንዳይቀበሉ እንዲሁም  በቦርድ በጸደቁና በትምህርት ሚኒስቴር በተመዘገቡ አዳዲስ ፕሮግራሞችም ዩኒቨርስቲዎች ተማሪ መቀበል እንዳይጀምሩ አሳስበዋል።

አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ባሉበት እንዲቆዩ የተወሰነው የትምህርት ፕሮግራሞች ተገምግመው ከዩኒቨርስቲዎች ተልዕኮና ትኩረት ጋር መጣጣማቸው  እስኪረጋገጥ ድረስ አዳዲስ ፕሮግራሞችን የመክፈት ስራ መግታት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል።

ደብዳቤውን ያገኙታል

https://rb.gy/apntp
21.8K views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-13 12:13:30
“የደብረ ታቦር ህዝብ ደጀን በመሆን ትክክለኛውን ኢትዮጵያዊ ማንነታችንን ስላሳዬ አመሰግናለሁ” ዶ/ር አነጋግረኝ ጋሻው-የደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት

.............................................

ነኅሴ 07/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የ2015 ዓ.ም 12ኛ ክፍል ፈተና ከመላው ኢትዮጵያ ወደ ደብረታቦር ዩኒቨርስቲ የተመደቡ ሁሉ በሰላም ወደመጡበት ተሸኚተዋል።

የደብረታቦር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አነጋግረኝ ጋሻው ቦታው ግጭት የተቀሰቀሰበት እንደመሆኑ ህዝቡ ደጀን በመሆን ትክክለኛውን ኢትዮጵያዊ ፍቅር እና ማንነታችንን ባያሳይ ኖሮ በታሪክ ተወቃሽ የምንሆንበት መጥፎ አጋጣሚ ሊፈጠር ይችል ነበር ብለዋል።

የመጨራሻዎቹ ሶስት ቀናት ግጭቱ እየተካሄደ ነው ፈተና ስንፈትን የነበረው ያሉት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዩኒቨርስቲዉ የህዝብ ነው፤ እገዛውን የጠየቅነውም ህዝቡን ነዉ ፤ በመሆኑም ህዝቡ ከጎናችን ሆኖ በጊዜው  በዩኒቨርስቲው የነበሩ 6,743 ተማሪዎች፣ 300 የፈተና አስታባባሪዎችና 88 የፌዴራል ፖሊስ አባላት ሁሉም በሰላም ወደመጡበት ተመልሰዋል ብለዋል።

ተማሪዎችንም ሆነ የጸጥታ አካላትን  በሰላም ስንሸኝ የሀይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ከፊትና ከኋላ በመሆን የኢትዮጵያ ባንዲራ ይዘው መንገድ በማስከፈት፣ በአባታዊ ምክር እና በፍጹም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ወደየመጡበት እንድንሸኝ አድርገዋልና ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል።

የደብረ ታቦር እና የደቡብ ጎንደር ዞን ማህበረሰብ የጊዜውን ድንቅ ታሪክ በኢትዮጵያዊነት ደማቅ ቀለም በክብር ጽፋችኋልና ልትኮሩ ይገባችኋል በማለት አድናቆታቸውን ገልፀው የኢትዮጵያ ሰላም ለማረጋገጥ ቆሞ ከማየት የበኩልን ድርሻ በግልም በቡድንም መወጣት እንድንችል አስተማሪ ይሆናል ብለው እንደሚያምኑም ጨምረው ገልፀዋል።
18.5K views09:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-12 15:46:09
በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ነፃ ትምህርት እድል ላገኙ 273 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሽኝት ተደረገ።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ነሐሴ 6/2015(የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በሠጠው የነፃ ትምህርት እድል  አሸናፊ ለሆኑ 273 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ሽኝት አድርጓል።

ዛሬ ሽኝት የተደረገላቸው ተማሪዎች በ2014 ዓ.ም በተሠጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ እና በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የሚገኙ 10  ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች የሠጡትን ፈተና ያለፉ ናቸው።

የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልእክት ተማሪዎቹ አስፈላጊውን እውቀት ከገበዩ በኋላ ወደ ሀገራቸው በመመለስ ህዝባቸውን እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ ጥያቄ መሠረት የተገኘው የነጻ የትምህርት እድል  በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች መካከል ያለውን  የወዳጅነት ደረጃ ትልቅነትን ያመላከተ ነው።
16.3K views12:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-08-11 19:59:35
15.2K views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-09 17:31:50
ለትምህርት ጥራት መሻሻል የትምህርት ቤት አመራሮች ሚና ወሳኝ መሆኑ ተገለጸ
.........................................................

ሰኔ 02/2015ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ Education Development Trust (EDT ) የተባለ ድርጅት ባዘጋጀው አውደ-ጥናት ሲከፍቱ እንደተናገሩት ለትምህርት ጥራት መጠበቅ የርዕሳነ መምህራን ሚና የላቀ ነው።

የትምህርት ቤት አመራሮች ሚና ለማሳደግም ለርዕሳነ መምህራን ስልጠና የሚሰጥ የርዕሳነ መምህራን ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት እንደሚቋቋም ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

የትምህርት ጥራቱን ለማስጠበቅ ፍላጎትና አቅም ያላቸውን ርዕሳነ መምህራንን ከማሰልጠን ባሻገር በአስተሳሰብ ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚገባም ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል በየደረጃው በሚገኙ ሁሉም የትምህርት ተቋማት ማለፊያ ነጥብ 50 በመቶና ከዚያም በላይ እንዲያድግ መደረጉን ጠቁመዋል።

በዩኒቨርስቲ በተሰጠው የ2014 የ12ኛ ክፍል ፈተና የትምህርቱ ዘርፍ ያለውን ችግር አጉልቶ ያሳየ እንደነበረም ሚኒስትሩ በዚሁ ጊዜ እስታውሰዋል።

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኤምባሲ የሰው ሀብት ልማት ቡድን መሪ ሚስተር ፊል ኤሌክስ በበኩላቸው የትምህርት ቤት አመራሮችን ማብቃት ለትምህርቱ ልማት እድገት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

ብቃት ያላቸውን አመራሮች ለማፍራት ለሚደረገው ጥረት EDT የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል ።

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02V8yuuL8gYsmjyqRh27DRJKSoZRtcL7XaXhR3Db7rX1WGh2WQV1kQwj2Dbc7yipRcl&id=100064682287722&mibextid=Nif5oz
9.2K views14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 18:23:22
የተባበሩት አረብ ኤምሬት ስኮላርሽፕ ተወዳዳሪ ተማሪዎች የመለያ ፈተና ተፈተኑ፡፡
————————-//——
ግንቦት 30/2015ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የተባበሩት አረብ ኤምሬት የትምህርት ዘርፉ ልዕካን ቡድን በትምህርት ሚኒስቴር ተገኝተው ከትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡

በውይይቱም ልዑካን ቡድኑ በቅርቡ ከተባበሩት አረብ ኤምሬት በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የሀገራችን ተማሪዎች የተሰጠው እስካላርሽፕ አንዱ መስፈርት የሆነውን ፈተና የፈተኑ መሆኑን ጠቅሰው ውጤቱንም በቅርቡ እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል፡፡

ልዑካን ቡድኑ ፈተናውን ከወሰዱ 500 ተማሪዎች መካከል 275 ተማሪዎች የስኮላርሺፕ እድሉን የሚያገኙ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብረሃኑ ነጋ በፈተናው ውጤት መሰረት የስኮላርሽፕ እድሉን የሚያገኙ ተማሪዎች ወደሚመደቡበት ተቋማት ከመሄዳቸው በፊት ትምህርት ሚኒስቴር ያዘጋጀላቸው የማጠናከሪያ ትምህርት መኖሩን ጠቅሰው ጊዜውን ለመጠቀም ይቻል ዘንድ በአረብ ኤምሬት መንግሥት በኩል የሚሠራው የፈተናው ውጤት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊደርስ እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

በውይይቱም በሁለቱም ወገን በኩል አብሮ የመሥራት ፍላጎት እንዳለ የተገለጻ ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት በከፍተኛ ትምህርት ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ትምህርት ዘርፉም የመግባቢያ ሰነድ በመፈራረም አብሮ ለመሥራት የታቀደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
12.1K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 19:15:24
በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አማካኝነት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት ስኮላርሺፕን በተመለከተ:-
..................................................

ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው በ2014 የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሠዱትና ከፍተኛ ውጤት ካስመዝገቡት ውስጥ 273 ተማሪዎች ስኮላርሺፕ እንደሚሠጥ መገለጹ ይታወቃል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ:-

1. የተማሪዎች ቁጥር (ተፈታኞች)ለምን ከ273 በላይ ሆነ

2 .ከፍተኛ ውጤት ያለመጡ ተማሪዎች እንዴት ለፈተና ተቀመጡ የሚሉ ጥያቄዎች እየቀረቡ ይገኛል።

ስለሆነም ይሄን ጉዳይ ግልጽ ማድረግ ስለሚያስፈልግ

1. ለፈተና የተጠሩትን ቁጥር በተመለከተ:-

ስኮላርሺፑን የሠጡት የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ባላቸው አሠራር መሠረት 273 ለስኮላርሽፕ ብቁ የሚሆኑ ተማሪዎች ለማግኘት ከፍ ያለ ቁጥር ማለትም 500 የሚሆኑ ተማሪዎች(ተፈታኞች) ለፈተና እንዲቀመጡ ስለጠየቁ ከ273ቱ ቀጥሎ ያሉ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለፈተና እንዲቀርቡ የተደረገ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡

2.ከዚህ በመንግስት ለመንግስት ከተገኘው ስኮላርሽፕ ውጭ አዲስ አበባ በሚገኘው የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ኢምባሲ በኩል ስኮላርሺፕ የተመቻቸላቸው ሌሎች ተማሪዎች ያሉ ሲሆን ይህም በመንግስት በኩል ከተገኘው የ273 ስኮላርሽፕ ውጭ መሆኑን እንዲታወቅ እንፈለጋለን፡፡

በመጨረሻም ለሁለቱም አይነት ስኮላርሽፕ እድሎች የተለዩት እጩዎች በጋራ ፈተና እየወሰዱ እንደሆነ ማህበረሰቡ እንዲረዳ እንፈልጋለን፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር !

ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም.
9.1K views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 17:17:23
13.5K views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 17:17:19
ሀገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን ተከበረ
-------------------------------------

ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (የትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር ከቅን ኢትዮጵያ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ፣ ሰላም ሚኒስቴርና ከሌሎች ሴክተር መስሪያ ቤቶች ጋር አመታዊ ሀገር አቀፍ የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀንን በሚሌኒየም አዳራሽ በተለያዩ መርሃግብሮች አክብሯል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ፋንታ ማንደፍሮ (ዶ/ር) ሚኒስቴር መ/ቤቱ የነገው ሀገር ተረካቢው ትውልድ በስነ-ምግባር የታነጸና መመሰጋግንና መደናነቅን ዕሴቱ ያደረገ ሆኖ እንዲቀረጽ የግብረገብ ትምህርትን በስርዓተ ትምህርት በማካተት የመደበኛ ትምህርት አካል አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር ፋንታ አክለውም መምህራን የትውልድን ብሎም የሀገርን እጣ ፋንታን በመወሰን ረገድ የሚጫወቱትን ሚና ጠቅሰው ለመምህራን ያላቸው አድናቆት፣ምስጋናና፣አክብሮት እጅግ በጣም ከፍተኛ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የቅን ኢትዮጵያ ማህበር መስራች ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና ወላጆች ለልጆቻቸው ፍቅርን፣ ሰላምን ፣ ትጋትን፣ ትዕግስትን ፣ቅንነትን ፣ማመስገንንና ማስተዋልን እንዲመክሩና ለልጆቻቸው አርኣያ ይሆኑ ዘንድም ራሳቸውም እንዲተገብሩት ጠይቀዋል፡፡

ተማሪዎች ቴክኖሎጂን በአግባቡ እና በስርዓት በመጠቀም እራሳቸውን እና ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የመመሰጋገንና የመደናነቅ ቀን በየአመቱ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮችና ትምህርት ቤቶች ይከበራል።
13.5K views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ