Get Mystery Box with random crypto!

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ለማስጀመር የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ | Ministry of Education Ethiopia

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ለማስጀመር የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሲከታተሉ የነበሩ መምህራን ተመረቁ
.............................................................................................................................................................................................................
ታህሳስ 06/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ለማስጀመር የአቅም ግንባታ ሥልጠና በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሲከታተሉ የነበሩ መምህራን አጋሮችና ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ማክሰኞ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ዓ/ም በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተመርቀዋል።

ከተለያዩ የኢትዮጵያ የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተውጣጡ 32 መምህራን ለ8 ወራት በአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሜሪ ሉ ፉልተን መምህራን ኮሌጅ በInstructional Design and Performance Improvement ስልጠናቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ሲሆን በዕለቱ በግራጁዌት ሰርተፊኬት ተመርቀዋል፡፡

በተጨማሪም በዕለቱ የዲጂታል ትምህርት አዘገጃጀት የአሰልጣኞች ስልጠናን በኮሌጁ ሲከታተሉ የቆዩ 19 መምህራንም ተመርቀዋል፡፡

ሙሉ ዜናው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0MS6LL9gEFvmdEyZBoaAKhZaKQ4qpSz849cWYrDXhnsRy5sBhjJXqUVEErbkWezvyl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO