Get Mystery Box with random crypto!

EMS Mereja

የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja
የሰርጥ አድራሻ: @emsmereja
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.57K
የሰርጥ መግለጫ

👉 መረጃዎች፣ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና የማስታወቂያ ስራ ለማሰራት ከፈለጉ በዚህ ያናግሩን👉 t.me/infoetrobot
👉 የዕለታዊ ዝግጅቶችና ዜናዎች በተባባሪ አቅራቢዎች እንዲደርሷችሁ👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@HAQMEDIA12
Subscribe ያድርጉ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-05 07:45:20 እስከ 40 ሺሕ የሚደርሱ የአማራ ተወላጆች ተገድለዋል ተባለ
=======#=======

በኢትዮጵያ የመንግሥት ለውጥ ከተደረገበት 2010 ወዲህ ባሉት ዓመታት ከ25 ሺሕ እስከ 40 ሺሕ የሚገመቱ የአማራ ተወላጆች በአክራሪ ብሔርተኞች መገደላቸውን ካውንተር ፓንች በድህረ ገጹ አስነብቧል።

ዘገባው አብዛኞቹ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በሚል በሚጠራው እና በመንግሥት “ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በተፈረጀው ኃይል የተገደሉ መሆናቸውን መገለጹን አዲስ ማለዳ ከድህረ ገጹ ዘገባ ተመልክታለች፡፡

ከዚህ ባለፈም፤ ከአምስት እስከ ሰባት ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች በየጊዜው በሚፈጠሩ ግጭቶች ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸው ነው የተገለጸው።

እንዲሁም በአገሪቱ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ከጊዜ ወደ ጊዜ አደጋ ውስጥ እየገባ ነው የተባለ ሲሆን፤ የመሰበሰብ፣ የሚዲያ ነጻነት እና ሌሎች ተያያዥ ዴሞክራሲያዊ መብቶች አደጋ ውስጥ መግባታቸው ተጠቅሷል።

በዚህም ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ የአገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ በግልጽ የሚናገሩ ጋዜጠኞች እና የግል የሚዲያ ተቋማት በነጻነት የመናገርና የመስራት መብታቸውን አጥተዋል ሲል የካውንተር ፓንች ዘገባ አመላክቷል።

ዘገባው መሰረቱን በአሜሪካ ያደረገ “ፍሪደም ሃውስ” የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅትን መረጃ ጠቅሶ፤ በኢትዮጵያ በስፋት መንግሥትን የሚተቹ አካላት ከእውቅናቸው ውጭ በሆነ መንገድ በመንግሥት የደህንነት አካላት በእጅ ስልካቸው ላይ ሳይቀር ሚስጥራዊ ክትትል እንደሚደረግባቸው ጠቁሟል።

በአገሪቱ የዘፈቀደ እስራት በተደጋጋሚ እንደሚፈጸም በመጥቀስም፤ ጋዜጠኞች፣ የፖለቲካ አክቲቪስቶች እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሠራተኞች ከመኖሪያ ቤታቸው፣ ከሥራ ቦታቸው ወይም ከመንገድ ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በደህንነቶች ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ እንደሚወሰዱምተገልጿል።

በአገሪቱ ሥር የሰደደ ሙስና መኖሩን የጠቀሰው ዘገባው፤ ገንዝብ ተቀብለው ፍርድ የሚያጣምሙ ዳኞች ላይ ሳይቀር ያለው ተጠያቂነትም እምብዛም ነው ብሏል።

የጋዜጠኞች መብት ተማጋች ሲፒጄ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች ነጻነት አሳፋሪ ገጽታ እንዳለው በመጠቆም፤ ባለስልጣናት የታሰሩትን ጋዜጠኞች በሙሉ ሊለቁ እንደሚገባና እስር ቤት ውስጥ በነበሩበት ወቅት በደል ወይም ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል የሚለውን መመርመር ብሎም ተጠያቂነትን ማስፈን እንደሚገባቸው ማሳሰቡ ይታወሳል።

አብዛኛው የአገሪቱ ሕዝብ ትልቅ ተስፋ ጥሎበት የነበረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስተዳደር፣ ቀስ በቀስ ራሱን ወደ አምባገነናዊ ስርዓት እየለወጠ ነው ሲልም ካውንተር ፓንች በዘገባው አመላክቷል።
ሼር አድርጉት
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
2.9K views04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-04 23:03:29
የሸዋሮቢት ከተማ የጸጥታ ኃላፊ አብዱ ሁሴን ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ሽዋ ዞን የሽዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ጸጥታ ኃላፊ አብዱ ሁሴን ከሰዓታት በፊት መገደላቸውን አዲስ ማለዳ ሰምታለች።

ኃላፊው የተገደሉት በጥይት ሲሆን፤ ግድያውን የፈጸመው አካል ማንነት ለጊዜው አልታወቀም ተብሏል።

የኃላፊውን መገደል ተከትሎ የአካባቢው መንገድ በመከላከያ ሰራዊት መዘጋቱን የከተማ ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል።

አዲስ ማለዳ ስለ ኃላፊው ግድያና በከተማዋ ስላለው አሁናዊ ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት፤ ፖሊስን ጨምሮ ለከተማዋ አመራሮች ስልክ ብትደውልም መረጃ መስጠት የሚችሉበት ሁኔታ ላይ አለመሆናቸውን በመግለጽ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ሽዋሮቢት የአካባቢው ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ የሚገደሉባት ከተማ ስትሆን፤ ከአመራሮች ግድያ በተጨማሪ በመንግሥት የጸጥታ ተቋማት ላይ ጥቃቶች ሲስነዘሩ ነበር።

አማራ ክልል በተለይ የፌደራል መንግሥት መከላከያ አሰማርቶ፤ በክልሉ በሚንቀሳቀሰው ፋኖ ላይ እርምጃ መውሰድ ከጀመረ በኋላ በየአካባቢው አመራሮች እየተገደሉ መሆኑ ይታወቃል።

ሼር አድርጉት
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
3.2K viewsedited  20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 22:19:53 የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
የጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በሜዲስን፤ ነርሲንግ፤ ጤና መኮንን፤ አንስቴዥያ፤ ፋርማሲ፤ ሜዲካል ላቦራቶሪ፤ ሚድዋይፈሪ፤ ዴንታል ሜዲስን፤ ሜዲካል ራዲዮሎጂ፤ ኢንቫይሮመንታል ሄልዝ፤ ፔዲያትሪክ ኤንድ ቻይልድ ሄልዝ፤ ሳይካትሪ ነርሲንግ፤ እና ኢመርጀንሲ ኤንድ ክሪቲካል ኬር ነርሲንግ ሙያዎች በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀው የብቃት ምዘና ፈተና ለመውሰድ በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ፈተናው ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር ከሚሰጠው የመውጫ ፈተና (Exit exam) ጋር በማቀናጀት የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን:-

1. የፈተናው አሰጣጥ ሂደት በኮምፒውተር ይሆናል።

2. የፈተናው መርሃግብር

- በ30/10/2015 ዓ.ም Nursing, Pharmacy, Public Health, Anesthesia, Medical Radiology Technology and Environmental Health, Medical Laboratory Science, Midwifery, Medicine, Dental Medicine, Pediatric and Child Health Nursing, Psychiatric Nursing and Emergency and Critical Care Nursing

3. እያንዳንዱ ተፈታኝ ከሚፈተንበት ቀን አንድ ቀን ቀደም ብሎ ማለትም ሰኔ 29/2015 ዓ.ም ከቀኑ በ 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል።

4. የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን ለመስራት፤ ወደ ፈተና የሚያስገባውን Username and Password እና የመፈተኛ ጣቢያ ለማወቅ የመረጣችሁብት ዩኒቨርስቲ ዋና ግቢ ከፈተናው አንድ ቀን በፊት ማለትም  ሰኔ 29/2015 ዓ.ም በመገኘት ከጣቢያ አስተባባሪዎች ማግኘት ትችላላችሁ።

5. በፈተናው ዕለት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ (የቀበሌ መታወቂያ፣ ፓስፖርት፣ መንጃ ፍቃድ ወይም ሌላ በግልጽ የሚታይ ህጋዊ መታወቂያ) ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

6. ከላይ ከተጠቀሱት ነገሮች ውጪ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር)፣ ቦርሳ እና ሌሎች እቃዎች፣ ምንም አይነት ማጣቀሻዎች እንዲሁም ባዶ ወረቀቶች፣ ምግብ ወይም መጠጥ (የተረጋገጠ የጤና ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡

7. ፈተናውን በድጋሚ ለምትወስዱ ተመዛኞች ወደ ፈተና ጣቢያ ስትመጡ ሲስተሙ የሚሰጠውን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No) QR code የያዘ ወረቀት /ስሊፕ/ print አድርጋችሁ መምጣት ይኖርባችኋል።

ተመዛኞች ስማቸው ከተጠቀሰበት ተቋም ውጪ በፍጹም ፈተናውን መውሰድ የማትችሉ መሆኑን እያሳሰብን ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0118275936/952 መደወል ይቻላል፡፡ መረጃው ሼር አድርጉት
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
3.9K views19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 20:12:23 ሰኞ ምሽት! ሰኔ 26/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ኢሠማኮ መንግሥት የሠራተኞችን ዝቅተኛ ደመወዝ የሚወስን የደመወዝ ቦርድ ባለማቋቋሙ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፍትሄ እንዲሰጠው ጥያቄውን ማቅረቡን መግለጡን ሪፖርተር ዘግቧል። የሥራና ክህሎት ሚንስቴር በበኩሉ፣ የደመወዝ ቦርድ ጉዳይ ጥናት እየተደረገበት እንደኾነ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። የሥራና አሠሪ አዋጅ መንግሥት ዝቅተኛ የደመወዝ ወለልን የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም ደንግጓል።

2፤ በጋምቤላ ክልል አኝዋክ ብሄረሰብ ዞን ዲማ ወረዳ በታጣቂዎች ተኩስ ሁለት ጸጥታ በማስከበር ሥራ ላይ የነበሩ የመንግሥት ጸጥታ ኃይል አባላት እንደተገደሉ ዶይቸቨለ ዘግቧል። ታጣቂዎቹ አንድ ሌላ የክልሉ መንግሥት ሚሊሺያ አባልን ማቁሰላቸውን የዲማ ወረዳ አስተዳደር ኮምንኬሽን ቢሮ መናገሩን ዘገባው ጠቅሷል። የታጣቂዎቹን ማንነት ዘገባው አልጠቀሰም። በክልሉ ይንቀሳቀስ የነበረው አማጺ ቡድን፣ በቅርብ ወራት ከመንግሥት ጋር እርቅ ፈጽሞ ወደ ሰላማዊ ኑሮ መመለሱ እንደተገለጠ ይታወሳል።

3፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ "ቦይንግ- 787-9" የተሰኘውን 10ኛውን ድሪም ላይነር አውሮፕላኑን መረከቡን አስታውቋል። አውሮፕላኑ ባለፈው ሳምንት ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፉንና የመጀመሪያ በረራውን ከአዲስ አበባና ወደ ዱባይ ማድረጉን አየር መንገዱ ገልጧል።

4፤ በቻይና ብድር የተገነባው. የኢትዮጵያ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ባለፉት አምስት ዓመታት 1 ሺህ 824 ጊዜ የመንገደኞች ማመላለሻ ባቡሮች እንደተመላለሱበት የትራንስፖርት ሚንስትሩ ዓለሙ ስሜ መናገራቸውን ጠቅሶ ዥንዋ ዘግቧል። የባቡሩ ትራንስፖርቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 530 ሺህ 900 መንገደኞችን በ6 ሺህ 133 የካርጎ ባቡር ምልልሶች ከ7 ሚሊዮን 328 ሺህ ቶን በላይ ሸቀጦችን ማጓጓዙን ሚንስትሩ መግለጣቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ዓለሙ ይህን የተናገሩት፣ በኢትዮጵያና ቻይና የቤልት ሮድ ፕሮጀክት ዙሪያ በተደረገ የጋራ ውይይት ላይ እንደኾነ ተገልጧል።

5፤ በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን አማኑኤል ከተማ ነዋሪ የኾኑ አንለይ መኩሪያ የተባሉ ጡረተኛ መምህር ልጃቸውን በ1 ሚሊዮን ብር ክፍያ ከእገታ አስለቅቄያለኹ ማለታቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። የመምህሩ ልጅ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሰኔ 10 ቀን ከታገቱት 30 ሹፌሮችና ረዳቶቻቸው አንዱ እንደነበር ዘገባው አመልክቷል። የታጋቹ ወላጅ አባት የልጃቸውን ማስለቀቂያ ገንዘብ ያሰባሰቡት ከጎረቤቶቻቸውና ከዘመድ አዝማድ እንደኾነ ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል። መምህሩ 1 ሚሊዮን ብሩን ለአጋቾቹ ያስረከቡት፣ ኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ገብረጉራቻ ከተማ ሰባት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እንደኾነ ተገልጧል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ6052 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ6973 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 66 ብር ከ1810 ሳንቲምና መሸጫው 67 ብር ከ5046 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ከ5524 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ7434 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል።
ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
3.6K views17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 14:04:49
ፓስፖርት
በኢሚግሬሽን እጅግ በርካታ ህዝብ በወረፋ ምክንያት እየተጉላላ ነው። ፓስፖርት ለማሳደስ ከ8 ወር በፊት ያመለክቱ እንዳሉ እና በቀጠሮ ቀን ሲሄዱ እስካሁን እንዳልተሰራላቸው እየገለፁ ነው። አሁንማ አቁመናል እያሉም እየመለሱን ነው። አጠቃላይ ፓስፖርት ለማሳደስ ከ20ሺ በላይ ሰው አመልክቶ እየጠበቀ ነው።
ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
3.9K views11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 07:44:55 ሰኞ ጠዋት! ሰኔ 26/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የመንግሥት ባለሥልጣናት በስማቸው ወይም በቅርብ ቤተሰባቸው የተመዘገቡ የንግድ ኩባንያዎችን ወይም የአክሲዮን ድርሻዎችን እንዲያቋርጡ ወይም ለሌላ አካል እንዲያስተላልፉ የሚያስገድድ ረቂቅ ደንብ መውጣቱን ሪፖርተር ዘግቧል። የባለሥልጣናትን የጥቅም ግጭት ማስቀረትን ዓላማው ያደረገውን ረቂቅ ደንብ ያዘጋጀው፣ የጸረ-ሙስና ኮሚሽን እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል። የመንግሥት ባለሥልጣናት ኢንቨስትመንታቸውንና የግል ኩባንያቸውን በወኪሎቻቸው አማካኝነት እንዲመሩ፣ የኩባንያቸውን ካፒታልና ትርፍ በግል ማዘዝ በማይችሉበት የባንክ ሒሳብ እንዲያስቀምጡ ወይም በኩባንያዎች የያዟቸውን ከፍተኛ ሃላፊነቶች እንዲለቁ ያስገድዳል ተብሏል።

2፤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የተመራ የቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ ልዑካን ቡድን በቅርብ ቀናት ውስጥ ወደ መቀሌ እንደሚጓዝ የቤተክርስቲያኗ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባሠራጨው መረጃ አስታውቋል። የልዑካን ቡድኑ ጉዞ ዓላማ፣ የቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልሉ ለመስጠት የወሰነውን ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማድረስና በትግራይ ከሚገኙ የቤተክርስቲያኗ ጳጳሳት ጋር "በሰላም ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር" እንደኾነ መምሪያው ገልጧል። በልዑካን ቡድኑ ውስጥ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ ያቋቋመው የሰላምና አቀራራቢ ኮሚቴ አባላት እንደተካተቱ መምሪያው ጨምሮ አመልክቷል።

3፤ ፌደሬሽን ምክር ቤት ነገ እና ከነገ ወዲያ በደቡብ ክልል ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ያካሄዱትን የክልልነት ሕዝበ ውሳኔ ውጤት ለማጽደቅ እንደሚሰበሰብ መስማቱን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ምክር ቤቱ ውጤቱን የሚያጸድቀው፣ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የሚያቀርብለትን የሕዝበ ውሳኔ ሪፖርት መሠረት በማድረግ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል። ወላይታ ዞንን ጨምሮ ስድስቱ ዞኖችና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች በሕዝበ ውሳኔው በከፍተኛ ድምጽ ከደቡብ ክልል ተነጥለው በጋራ አንድ ክልል ለማቋቋም መወሰናቸው ይታወሳል። አዲሱ ክልል "ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል" ተብሎ እንደሚሰየም ይጠበቃል።

4፤ ሰሞኑን ኢትዮጵያዊያን ዜጎችን ጨምሮ ስድስት የአይኤስ የሽብር ቡድን አባላት ፑንትላንድ ራስ ገዝ ውስጥ ለመንግሥት ጦር እጃቸውን እንደሰጡ የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። እጃቸውን ለመንግሥት ከሰጡት የቡድኑ ተዋጊዎች መካከል፣ አራቱ ኢትዮጵያዊያን እንዲኹም ሁለቱ ሱዳናዊያን እንደኮኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ተዋጊዎቹ በቡድኑ ተመልምለው ላንድ ዓመት ያህል ወታደራዊ ሥልጠና ሲወስዱ እንደቆዩ መናገራቸው ተገልጧል። ቡድኑ በተለይ ወደ ቦሳሶ ወደብ ለሥራ ወይም ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለመሻገር የሚሄዱ የውጭ ዜጎችን ለምልመላ ዒላማ በማድረግ ይታወቃል።
ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
4.1K views04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 21:23:36 ዜና
የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በጉራጌ ዞን በነዋሪዎች ላይ ግድያና እገታ እየፈጸሙ ነው ተባለ
በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን በተለይም ሶዶ ወረዳ፤ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራውና መንግሥት "ኦነግ ሸኔ" በሚል በአሸባሪነት የፈረጀው ኃይል በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ ግድያና እገታ እንደሚፈጽም ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል።

በዚህም የቡድኑ አባላት ነዋሪዎችን አግተው በመውሰድ አርደን የምንበላው ከብት ስጡን፣ የግል የጦር መሳሪያችሁን እንዲሁም ብር አምጡ በማለት በደል እንደሚፈጽሙ ተነግሯል።

ባለፈው ሃሙስ ሰኔ 22/2015 በነዋሪዎቹ ቤት በመግባት "የመንግሥት የጸጥታ አካላትን ትደብቃላችሁ እንዲሁም ያሉበትን ጥቆማ አልሰጣችሁንም" በሚል ነዋሪውን ሲያሰቃዩ እንደነበርና በዚህም ምክንያት አንድ የቀበሌው ነዋሪ የነበሩ አርሶ አደርን መግደላቸው ነው የተገለጸው።

የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች በአካባቢው ከስድስት ወር በፊት ጀምሮ በተደጋጋሚ ጥቃት እያደረሱ ነበር ያሉት ነዋሪዎቹ፤ ከባለፈው ሰኔ 20/2015 ጀምሮ ግን ግድያ እና እገታ እየፈጸሙ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

ነዋሪዎችን አግተው በመውሰድ እስከ 200 ሺሕ ብር እንደሚጠይቁ በመጥቀስም፤ በአካባቢው (በቀበሌው) በቂ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባለመኖራቸው ችግሩ ተባብሶ መቀጠሉን ተናግረዋል።

የታጣቂ ቡድኑ አባላት ወደ ቀበሌው ዘልቀው የሚገቡት ከኦሮሚያ ክልል በመንግሥት የጸጥታ አካላት ሲሳደዱ መሆኑም ተጠቁሟል።

የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር እርስቱ ይርዳው በጉዳዩ ላይ መረጃ እየተሰባሰበ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ሙሉ መረጃ ሲገኝ የምንገልጽ ይሆናል።" ገልፀዋል።
ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
4.3K views18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 13:27:18 የፌደራል መንግሥቱ በትግራይ ክልል ለወደሙ ትምህርት ቤቶች መልሶ ግንባታ ምንም ዓይነት ድጋፍ እያደረገ አይደለም ተባለ

በትግራይ ክልል ለወደሙ ትምህርት ቤቶች በፌዴራል መንግሥትም ሆነ በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ምንም ዓይነት ድጋፍ እየተደረገ አለመሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል፡፡

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኪሮስ ጉዕሽ በክልሉ ከኹለት ዓመት በላይ ሲካሄደው በነበረው ውጊያ በትምህርት ሴክተሩ ላይ ያደረሰው ውድመት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን በመግለፅ፤ የዉድመቱ መጠንም መቶ በመቶ በሚባል ደረጃ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

ሆኖም የወደሙ ትምህርት ቤቶች በተወሰነ መልኩም ቢሆን ጠግኖ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው ለመመለስ ከተወሰኑ ተቋማት በስተቀር በፌደራል መንግሥት እስካሁን የተደረገ ድጋፍ እንደሌለ ጠቅሰዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም በትምህርት ተቋማቱ ላይ የደረሰውን ጉዳት በቃላት ለመግለጽ እጅግ አዳጋች ነው ካሉ በኋላ፤ ዓለም አቀፍ ተቋማትም ጭምር ካልተረባረቡ አገሪቷ አሁን ካለችበት አቋም አንጻር ትምህርት ቤቶቹን ማደስ የማይታሰብ ነው ብለዋል።

አሁን ላይ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደት መጀመሩን ገልጸው፤ ይህም ከሚፈለገው ቁጥር አንጻር ወደ ትምህርት ገበታቸው የተመለሱ ተማሪዎች 24 በመቶ ብቻ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ይህም ተማሪዎች ቤት ከሚውሉ ይሻላል በሚል ባልተመሟላ የትምህርት ቁሳቁስ እየተማሩ እንደሚገኙ ነው የገለጹት።

እንደ ኃላፊው ገለጻ በጦርነቱ ወቅት የትምህርት ተቋማቱ የወደሙት ኢላማቸውን በሳቱ የጦር መሳሪያዎች ተመተው ሳይሆን፤ ሆነ ተብሎ ትምህርት ቤቶችን ለማውደም ድሮንን ጨምሮ የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን በመጠቀም በደረሰባቸው ድብደባ ነው።

በተጨማሪም በክልሉ የተለያዩ ወረዳዎች ስር ያሉ ትምህርት ቤቶች አሁንም በኤርትራ እና በአማራ ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መሆናቸውን የገለጹት ኃላፊው፤ "በእነዚህ አካባቢዎች በ100 ሺሕዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች አሁንም ድረስ ከትምህርት ገበታቸው ውጪ ናቸው።" ብለዋል።

አክለውም ከጦርነቱ በፊት በክልሉ ከኹለት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ላይ እንደነበሩ በመግለጽ፤ በዚህ ወቅት ትምህርት እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ቁጥራቸው ክ5መቶ ሺሕ አንደማይበልጥ አብራርተዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት በተማሪዎች፣ በመምህራን እንዲሁም በተማሪ ወላጆች ላይ የደረሰው ስነ ልቦናዊ ጉዳትም እጅግ ከፍተኛ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

       ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
4.6K views10:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 22:57:58
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ ዛሬ ሀትሪክ ሰሩ
ሼር ይደረግ


ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
4.7K viewsedited  19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 22:15:29 የኢትዮጵያ መሪዎች ራሳቸው ታግተው ካላዩት በስተቀር: የሚታገቱ ሰዎች ቤተሰቦች ጭንቀት ብዙም የሚገባቸው አይመስልም:: በተለይ በኦሮምያ; የሰው እገታ ከመሬት ሽያጭ ቀጥሎ በአቋራጭ የመክበሪያ መንገድ ሆኗል:: የጸጥታ ሃይሉም ጥቅሙን እያየ ወደ አዲሱ የስራ መስክ እየገባ ነው:: አገር ሲያረጅ...ሼር ይደረግ
fasilyenealem
ለትክክለኛ ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ተከታተሉ
http://t.me/emsmereja
4.6K views19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ