Get Mystery Box with random crypto!

EMS Mereja

የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja
የሰርጥ አድራሻ: @emsmereja
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.57K
የሰርጥ መግለጫ

👉 መረጃዎች፣ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና የማስታወቂያ ስራ ለማሰራት ከፈለጉ በዚህ ያናግሩን👉 t.me/infoetrobot
👉 የዕለታዊ ዝግጅቶችና ዜናዎች በተባባሪ አቅራቢዎች እንዲደርሷችሁ👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@HAQMEDIA12
Subscribe ያድርጉ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-30 14:11:49
ዛሬ EMS 1ኛ ዓመት የምስረታ በዓል እያከበርን እንገኛለን።
@emsmereja
3.4K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 13:56:34 ዕድሜያቸው 18 ዓመት የሞላቸውና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ለሁለት ዓመት ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደውን አዲስ አዋጅ ፀደቀ
የተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ውትድርና አገልግሎት አዋጅ አፀደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕድሜያቸው 18 ዓመት የሞላቸውና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ወታደራዊ ስልጠና ወስደው ለሁለት ዓመት ብሔራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደውን አዲስ አዋጅ አፀደቀ፡፡

ምክር ቤቱ ከትናንት በስቲያ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ መንግስት አዘጋጅቶ ያቀረበውን የተሻሻለ የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል፡፡

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጪ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ዲማ ኖህ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ተማሪዎች በፈቃዳቸው በመደበኛ መከላከያ ሰራዊት ወይም የብሔራዊ ተጠባባቂ ሃይል አባል የሚሆኑ ከሆነ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ተያያዥ መብቶችንና ጥቅሞች እንዲጠብቁላቸው ያደርጋል ብለዋል፡፡

በመንግስት ተዘጋጅቶ የቀረበው የተሻሻለ የመከላከያ ሰራዊት ረቂቅ አዋጅ፣ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት ነፃ ሆኖ የተጣለበትን ሀገርን የመጠበቅ ተልክኮ በአስተማማኝ ሁኔታ ለመወጣት እንዲችል ያደርገዋል ተብሏል፡፡

በመንግስት የተሻሻለውና ከትናንት በስቲያ በምክር ቤቱ የፀደቀው ይህው አዋጅ የሰራዊቱ አባላት የጡረታ መውጫ የእድሜ ጣሪያ አወሳሰን እንዲሁም የአገር ህልውና ከባድ አደጋ ላይ በሚወድቅ ጊዜ ከሰራዊቱ የተገለሉ አባላት መቀጠር የሚችሉበትን ሁኔታ ሁሉ አካቶ መያዙም ተገልጿል፡፡
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
3.4K views10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 13:52:17 ኢትዮጵያና ቱርክ በሱዳን ያለውን ግጭት ለመፍታት የሽምግልና ሥራ ሊጀምሩ ነው ተባለ

በሱዳን በአገሪቱ የጦር መሪ ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን እና በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች መሪ መሃመድ ሀምዳን ዳጋሎ አለመግባባት ምክንያት የተጀመረው ጦርነት እንዲያበቃ ኢትዮጵያ እና ቱርክ የሽምግልና ሥራ ሊጀምሩ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜብሉት ካቩሶግሉ፤ ኹለቱ አገራት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ አነሳሽነት በሱዳን ያለውን ግጭት ለመፍታት የሽምግልና ሥራ እንደሚጀምሩ ማስታወቃቸውን የቱርኩ ዕለታዊ ጋዜጣ ደይሊ ሳባህ ዘግቧል፡፡

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ አወድሰው፣ በሱዳን ላለው ችግር አላቂ መፍትሄ ለማምጣት በሚቀጥለው ሳምንት የቱርክ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወደ ሱዳን እንደሚያቀኑም ተገልጿል።

ይሁን እንጂ ይህ የሽምግልና ሥራ መቼ እንደሚጀመር እና በምን መልኩ እንደሚካሄድ በዝርዝር የተገለጸ ነገር የለም፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ባሳለፍነው አርብ በሱዳን ግጭት ተፋላሚ የሆኑት ኹለቱ ኃይሎች ልዩነቶቻቸውን በመግባባት እንዲፈቱ እና ለአገራቸው መረጋጋትን ማምጣት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ከመሪዎች ጋር በስልክ መወያየታቸውን ገልጸዋል።

አስራ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የሱዳን የእርስ በእርስ ግጭት በመቶ ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሱዳናውያን አገራቸውን ጥለው ወደ ጎረቤት አገራት የተሰደዱ ሲሆን፤ በርካታ የመሰረተ ልማት ውድመት መድረሱም እየተነገረ ይገኛል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት በካርቱም ውስጥ ከሚገኙ የጤና ተቋማት 16 በመቶው ብቻ አገልግሎት እንደሚሰጡ የገለጸ ሲሆን፤ በዚህም በበሽታ፣ በምግብ፣ በውሃ እና በሕክምና አገልግሎት እጥረት፣ የበርካታ ሰዎች ህልፈት ሊመዘገብ እንደሚችል አስጠንቅቋል።

የሱዳን የጤና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ በግጭቱ ከ500 በላይ ሰዎች እንደተገደሉ እና ከ4 ሺሕ በላይ የሚሆኑት ደግሞ እንደቆሰሉ አሳውቋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
3.4K viewsedited  10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 19:49:22 ቅዳሜ ምሽት! ሚያዝያ 21/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ብሄራዊ ባንክ የውጭ ኩባንያዎች በባንክ ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችላቸውን የሕግ ማዕቀፍ በኹለት ወራት ውስጥ አዘጋጅቶ ለፓርላማ እንደሚያቀርብ መናገሩን ሪፖርተር እስነብቧል። ባንኩ በረቂቁ የሕግ ማዕቀፍ ዙሪያ ቀደም ሲል ከአገር ውስጥ ንግድ ባንኮች አስተያየት የተቀበለ ሲሆን፣ ከዓለማቀፍ ባንኮችና የፋይናንስ ተቋማትም አስተያየት ለመቀበል ዝግጁ መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። የባንኩ ገዥ ማሞ ምኅረቱ ባንኩ ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ የገንዘብ መገበያያ ዘዴ "ኤምፔሳ" በቀጣዮቹ ኹለት ሳምንታት ውስጥ ፍቃድ እንደሚሰጥ ሰሞኑን ባንድ መድረክ ላይ መናገራቸውን ዜና ምንጩ ጨምሮ ጠቅሷል። ሚንስትሮች ምክር ቤት የውጭ ባንኮች በአገሪቱ የባንክ ዘርፍ እንዲሠማሩ የፈቀደው ከስምንት ወራት በፊት ነበር።

2፤ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠቅላላ ሃብቱ 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር መድረሱን ዛሬ አስታውቋል። ባንኩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ123 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ ተቀማጭ ገንዘብ እንደሰበሰበ ገልጧል። ባንኩ በዲጂታል የባንክ አገልግሎቱ በኩል ባለፉት ዘጠኝ ወራት 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር እንደተንቀሳቀሰም በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል።

3፤ ከሱዳኑ ግጭት የሚሸሹ በርካታ የውጭ ዜጎች በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባት ቀጥለዋል። የኬንያ መንግሥት ከሱዳን በመተማ በኩል በተሽከርካሪ ጎንደር ከተማ የደረሱ 184 ዜጎቹን ትናንት በአውሮፕላን ወደ ናይሮቢ ማጓጓዙን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኬንያዊያን በመተማ በኩል ወደ አገራቸው ሲመልሱ የትናንቱ ለሦስተኛ ጊዜ ነው።

4፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ደጋሎ ለፊት ለፊት ንግግር ተወካዮቻቸውን ወደ ጅዳ ወይም ጁባ ለመላክ ፍቃደኛ መኾናቸውንና ተወካዮችን መምረጣቸውን በሱዳን የተመድ ልዩ መልዕክተኛ ቮከር ፔርቴዝን ጠቅሶ ሮይተርስ ዘግቧል። ኾኖም ፔርቴዝ ኹለቱ ጀኔራሎች ተወካዮቻቸውን ወደ ጅዳ ወይም ጁባ ስለመላካቸውና ንግግር መጀመር ስለመቻላቸው ዋስትና የለም ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ጀኔራል ቡርሃንና ጀኔራል ደጋሎ ውጊያው መቀጠል የለበትም የሚል አቋም እንዳላቸውም ፔርቴዝ ገልጸዋል ተብሏል። ጅዳ ለቴክኒካዊ ወታደራዊ ጉዳዮች የተመረጠች ሲሆን፣ ጁባ ደሞ ለፖለቲካዊ ንግግር እንደተመረጠች ዘገባው አመልክቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ከትናንት እኩለ ሌሊት ጀምሮ የተራዘመው የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም እንዳልተከበረና ካርቱም በድሮንና ከባድ መሳሪያ ድብደባ ስትናጥ እንደዋለች ከአገሪቱ የሚወጡ ዜናዎች አመልክተዋል።

5፤ አሜሪካ በዛምቢያ እና ማላዊ የሕንድ ውቅያኖስ ዳርቻ ብሄራዊ የጠረፍ ጠባቂ ተጠባባቂ ዘቦቿን ለማሠማራት ከኹለቱ አገራት ጋር የጋራ የትብብር ስምምነት ላይ መድረሷን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። አሜሪካ በኹለቱ አገራት የባሕር ዳርቻዎች ተጠባባቂ ዘቧን የምታሠማራው፣ የአገራቱን የድንበርና ወደብ ደኅንነት ለማጠናከር፣ ለተፈጥሮ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠትና ከአገራቱ ጋር ያላትን የጸጥታ ትብብር ይበልጥ ለማጎልበት መኾኑን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። አሜሪካ በአኹኑ ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት ጋር የፈረመቻቸው 16 ተመሳሳይ የጋራ ትብብር ስምምነቶች አሏት። አሜሪካ በዚህ ዓይነት የትብብር ስምምነት በተለያዩ አገራት የምታሠማራቸው ተጠባባቂ ዘቦች፣ ከአንድ ወይም ከዚያ በላይ የአሜሪካ ግዛቶች ተጠባባቂ ዘቦች የሚውጣጡ ናቸው። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.1K views16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 06:41:12 ቅዳሜ ማለዳ! ሚያዝያ 21/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ብሄራዊ የጋራ ደኅንነት ግብረ ኃይል በአማራ ክልል የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ ግርማ የሺጥላ ግድያን ተከትሎ በክልሉ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ "ጽንፈኛ ኃይሎች" ላይ "አስፈላጊና ሕጋዊ ርምጃ" መውሰድ ጀምሬያለኹ ማለቱን የመንግሥት ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ግብረ ኃይሉ የክልሉ ጽንፈኛ ኃይሎች በውስጥና በውጭ ከሚገኙ አካላት ጋር በመቀናጀትና "የራሳቸውን ኅቡዕ አደረጃጀት" በመፍጠር "ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በማፍረስ ክልላዊ ሥልጣን ለመቆጣጠር" እንቅስቃሴ እያደረጉ መኾኑን መግለጡን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። በክልሉ በርካታ የጽንፈኛ ኃይሎች አባላት በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መኾኑንም ግብረ ኃይሉ ጨምሮ ገልጧል ተብሏል።

2፤ የጀርመን መራኄ መንግሥት ዖላፍ ሹልት በሚቀጥለው ሳምንት ኢትዮጵያን ሊጎበኙ መኾኑን የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ማስታወቁን ዶይቸቨለ ዘግቧል። መራኄ መንግሥት ዖላፍ ሹልት በቀጣዩ ሐሙስ ከርዕሰ ብሄር ሳሕለወርቅ ዘውዴ፣ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እና ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ጋር እንደሚወያዩ ዘገባው አመልክቷል። ሹልት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጣዩ ቀን ወደ ኬንያ ያቀናሉ ተብሏል።

3፤ በሱማሊያ የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ተልዕኮ በቀጣዩ ሰኔ ወር 2 ሺህ ሰላም አስከባሪ ወታደሮቹን ከሱማሊያ እንደሚያስወጣ ወታደር ያዋጡ አገራት መሪዎች ሰሞኑን ካምፓላ ውስጥ ባካሄዱት ስብሰባ አስታውቀዋል። የኅብረቱ ሰላም ተልዕኮ እስከ ቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት በታኅሳስ ወር ድረስ ሰላም አስከባሪ ወታደሮቹን ሙሉ በሙሉ ከአገሪቱ ለማስወጣት የያዘው እቅድ እንደተጠበቀ መኾኑ በመሪዎቹ ስብሰባ ላይ ተገልጧል። ሱማሊያ የኅብረቱ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ቆይታ ከቀጣዩ የፈረንጆች ዓመት ታኅሳስ በኋላ እንዲራዘም ፍላጎቷ መኾኑ በቅርቡ ተዘግቦ ነበር። በመሪዎቹ ስብሰባ የኢትዮጵያው ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ፣ የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ሙሴቪኒ፣ የኬንያው ፕሬዝዳንት ሩቶ፣ የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ጌሌህ፣ የቡሩንዲው ፕሬዝዳንት ንዳሺማዬ እና የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሞሐመድ ተገኝተዋል።

4፤ የአሜሪካ ሕግ አውጭ ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር የአሜሪካ ወታደሮችን ከሱማሊያ እንዲያስወጣ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ ማድረጉን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ውድቅ ያደረገው በ321 የተቃውሞና በ102 የድጋፍ ድምጽ እንደኾነ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። የአሜሪካ ወታደሮች ከሱማሊያ እንዲወጡ ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ ያቀረቡት የፍሎሪዳ ግዛት እንደራሴ ማት ጋዕዝ ናቸው። ጋዕዝ በሱማሊያ የሠፈሩ 900 አሜሪካዊያን ወታደሮች ሊያመጡ የሚችሉት ለውጥ እንደሌለና የሱማሊያን ጸጥታ ለአፍሪካ ኅብረት ብቻ መተው እንደሚሻል ጠቅሰው ተከራክረው እንደነበር ተገልጧል።

5፤ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ከአገሪቱ ጦር ሠራዊት አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ለንግግር ለመቀመጥ ዝግጁ መኾናቸውን ትናንት ለቢቢሲ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ኾኖም ጀኔራል ደጋሎ ለውይይት የሚቀመጡት በቅድሚያ ግጭቱ ከቆመ ብቻ መኾኑን ገልጸዋል። ኸለቱ ተፋላሚ ወገኖች ከትናንት እኩለ ሌሊት ጀምሮ ተኩስ አቁሙን ለተጨማሪ 72 ሰዓታት ቢያራዘመም፣ በካርቱም የከባድ መሳሪያ ተኩስ ልውውጡና የአየር ድብደባው እንደቀጠለ መኾኑን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
1.2K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 20:14:27
ከአቶ ግርማ የሺጥላ ጋር አብረው የተገደሉ ፖሊሶች እስካሁን ቁጥራቸው 6 ደርሷል። በመሃል ሜዳ እየታከሙ ያሉም አሉ።
#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
2.9K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 20:08:18 የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ተጨማሪ 22 ሚሊዮን ዩሮ እርዳታ ሰጠ
የገንዘብ ድጋፉ በግጭት እና ድርቅ ለተጎዱ ሰዎች ድጋፍ ይውላል ተብሏል
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ ተጨማሪ 22 ሚሊዮን ዩሮ እርዳታ ሰጠ፡፡
የአውሮፓ ህብረት ለአልዐይን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ተጨማሪ 22 ሚሊዮን የሮ ወይም ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል፡፡
ህብረቱ በመግለጫው እንዳለው ከዚህ በፊት ለኢትዮጵያ ለሰብዓው ድጋፎች የሚውል 60 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር መስጠቱን ገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያወጣውን መግለጫ ውድቅ አደረገች
ህብረቱ አሁን ከለገሰው 22 ሚሊዮን ዩሮ ጋር በተያዘው የፈረንጆቹ 2023 ዓመት ውስጥ በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ የረዳው ገንዘብ መጠን 4 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ይደርሳልም ብሏል፡፡
በኢትዮያ ባለፉት ዓመታት የነበረው ጦርነት፣ ድርቅ እና መፈናቀል ምክንያቶች የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር ከፍ ማለቱ እርዳታ ለማድረግ እንዳነሳሳውም አስታውቋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም በሶማሊያ በግጭት ምክንያት የተሻለ ደህንነት ፍለጋ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ዜጎችን ቁጥር 890 ሺህ ከፍ አድርጎታል ብሏል፡፡
በህብረቱ የቀውስ አስተዳድር ኮሚሽነር ጃኔዝ ሊናርሲስ እንዳሉት “ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር መጨመሩ ተጨማሪ ድጋፍ ለማድረግ ተወስኗል” ብለዋል፡፡
“በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ ባለሙያዎቻችን ሁኔታዎችን እየተከታተሉ ነው” ያሉት ኮሚሽነሯ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው ዜጎች ጎን መሆናቸውንም አክለዋል፡፡ BBC #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
2.9K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 19:41:38 ዓርብ ምሽት! ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የፓርላማው አባላት ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ተጠርጣሪዎችን በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት እንደማያቀርብና የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንደማያከብር ጠቅሰው ተችተዋል። የፓርላማ አባላቱ ትችቱን ያቀረቡት፣ ፌደራል ፖሊስ ሕገወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድ፣ ሕገወጥ የሰው ዝውውርና ሌሎች ከባድ ወንጀሎችን እየመረመረ መኾኑን ትናንት ለሕግና ፍትህ ኮሚቴ ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው። ፌደራል ፖሊስ ግን፣ የፍርድ ቤት ትዕዛዞችን ማክበር ለፖሊስ "ቀይ መስመር" መኾኑን ገልጦ ትችቱን ያስተባበለ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቶችም በጉዳዩ ላይ ያቀረቡት ቅሬታ እንደሌለ ተናግሯል። ፌደራል ፖሊስ በተለይ በቁጥጥር ስር የዋሉ ጋዜጠኞች ከውጭ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደደረግላቸውና "በስውር መዋቅር ተደራጅተው" እንደሚንቀሳቀሱ ለፓርላማ አባላቱ አብራርቷል።

2፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ልዩነቶቻቸውን በመግባባት ለመፍታትና ለሱዳን መረጋጋት ማስፈን በሚችሉበት ኹኔታ ዙሪያ ከኹለቱም ጋር በስልክ መወያየታቸውን ዛሬ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። በኹለቱ የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች መካከል ከኹለት ሳምንት በፊት ውጊያ ከተቀሰቀሰ ወዲህ፣ ዐቢይ ከጀኔራል ቡርሃንና ጀኔራል ደጋሎ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ በስልክ መነጋገራቸውን ሲገልጹ የዛሬው የመጀመሪያቸው ነው።

3፤ የኢትዮጵያ መንግሥት በግጭት ከምትታመሰው ሱዳን የሚመነጩ የጸጥታና ሰብዓዊ ቀውስ ስጋቶች ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጋቡ የሚከላከልና መፍትሄ የሚሰጥ ግብረ ኃይል ማቋቋሙን የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ መለስ ዓለም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠት ጋዜጣዊ መግለጫ መናገራቸውን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ግብረ ኃይሉ፣ ዜጎቻቸውን በአስቸኳይ ከሱዳን ለማስወጣት የአየር ክልልና አውሮፕላን ማረፊያ ፍቃድ ለሚጠይቁ አገራት ምላሽ የሚሰጥ፣ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ስደተኞችና የውጭ ዜጎች አቀባበልና ሽኝት የሚያደርግ ጭምር መኾኑን መለስ መናገራቸውን ዘገባዎች አመልክተዋል። መለስ ስንት ኢትዮጵያዊያን ከሱዳን ወደ አገራቸው እንደተመለሱ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ መልስ ሳይሰጡ ቀርተዋል ተብሏል።

4፤ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም መንግሥት በኦሮሚያ፣ ሱማሌና ደቡብ ክልሎች ድርቅና ጎርፍ ላስከተለው ጉዳት ዳተኛና ከሚጠበቀው ደረጃ በታች የኾነ ምላሽ ሰጥቷል ሲል በክልሎቹ ያደረገውን የቁጥጥር ሪፖርት ትናንት ለጋዜጠኞች ባብራራበት ወቅት ተችቷል። ተቋሙ፣ በክልሎች የምግብ ዕርዳታ ክምችት አለመኖሩና ፍትሃዊ የዕርዳታ ሥርጭት አለመስፈኑ አንድ ከጠቀሳቸው ችግሮች መካከል ይገኙበታል። በድርቁ ሳቢያ ከቦረና ዞን ከ59 ሺህ በላይ ተጎጂዎች በ20 መጠለያዎች እንደሚገኙ የገለጠው ተቋሙ፣ በዞኑ ድርቁ ከ1 ሚሊዮን 300 በላይ የቁም እንስሳትን መግደሉን ገልጧል። ከደቡብ ኦሞ ዞን ኹለት ወረዳዎች 64 ሺህ የሚጠጉ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውንና ከሱማሌ ክልል ዳዋ ዞን ደሞ ከአራት ወረዳዎች ከ16 ሺህ 300 በላይ ተፈናቃዮች በአራት መጠለያዎች ተጠልለው እንደሚገኙ ጠቅሷል።

5፤ ታንዛኒያ 206 ዜጎቿን በኢትዮጵያዋ የጠረፍ ከተማ መተማ በኩል በተሽከርካሪ ከሱዳን ማስወጣቷን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። በመተማ በኩል ከሱዳን ወጥተው በቦሌ ዓለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ አገራቸው ከተመለሱት ታንዛኒያዊያን መካከል፣ በሱዳን የአገሪቱ አምባሳደር ሲሊማ ሐጂ እና የጉዞ ሰነድ የሌላቸው የአገሪቱ ዜጎች እንደሚገኙበት ዘገባዎቹ አመልክተዋል። በመተማ በኩል ከሱዳን የወጡት አብዛኛዎቹ ታንዛኒያዊያን በሱዳን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎች ናቸው ተብሏል። ስመ ጥሩ በኾኑት የሱዳን ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በርካታ አፍሪካዊያን ተማሪዎች እንደሚማሩ ይታወቃል።

6፤ ኹለቱ የሱዳን ተፋላሚ ኃይሎች ከትናንት እኩለ ሌሊት ጀምሮ በድጋሚ ያራዘሙትን የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም ሳያከብሩ እንደቀሩ የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ካርቱም ዛሬም በከባድ መሳሪያ ተኩስ ስትናጥ እንደዋለች ዘገባዎቹ አመልክተዋል። በምዕራብ ዳርፉር ግዛት በኹለቱ ወገኖች መካከል የቀጠለው ግጭት ደሞ፣ የጎሳ ግጭት መቀስቀሱን ተመድ ገልጧል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ1517 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2347 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ5557 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ8468 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ8647 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ0620 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
2.9K views16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 14:08:42 በአጣዬ ዙሪያ ባለው የጸጥታ ስጋት ምክንያት አርሶ አደሮች ሰብላቸውን መሰብሰብ አለመቻላቸው ተገለጸ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አጣዬ ዙሪያ ኤፍራታ ግድም ወረዳ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት አርሶ አደሮች ሰብላቸውን መሰብሰብ አለመቻላቸውን ለአዲስ ማለዳ ገለጹ፡፡

በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ እና በኤፍራታ ግድም ወረዳ አዋሳኝ ቦታዎች ያለው የፀጥታ ችግር አርሶ አደሮች የደረሰ ሰብላቸውን እንዳይሰበስቡ እና መሬታቸውን ለመጭው የዘር ወቅት እንዳያዘጋጁ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል፡፡

ባሳለፍነው ረቡዕ ወደቆላ ወርደው የደረሰ ስብል ለመሰብሰብ የሞከሩ የኤፍራታና ግድም ወረዳ አርሶ አደሮች ከጅሌ ጥሙጋ በኩል ተኩስ እንደተከፈተባቸውና አንድ ሰው መቁሰሉን ገልጸዋል፡፡

በዚህም በተለይ አላላ በሚባል ቀበሌ የሚገኙ አርሶ አደሮች ሰብል መሰብሰብ ሳይችሉ መቅረታቸውን አንስተው፤ ሰሞኑን እየዘነበ ባለው ዝናብ የደረሱ ሰብሎች እየረገፉ ነው ብለዋል፡፡

በአካባቢው የመከላከያ ሠራዊት መግባቱን ተከትሎ አገርሽቶ የነበረው የጸጥታ ችግር ለጊዜው በቁጥጥር ሥር የዋለ ቢሆንም፤ አሁንም ገበሬዎች ያለስጋት ሰብል መሰብሰብና የግብርና ሥራዎችን ማከናወን የማይችሉ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

በኹለቱ አዋሳኝ ወረዳዎች የሚከሰተው የጸጥታ ችግር ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ የሚከሰት መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን በተለይም ችግር እየተፈጠረበት ባለው ጅሌ ጥሙጋ ወረዳ የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ከማህበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ በመሆናቸው ነዋሪዎቹ ስጋታቸው መጨመሩን ገልጸዋል፡፡

በአጣዬ ከተማ አሁንም የፀጥታ ስጋት በመኖሩ፤ በማህበረሰቡ የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ እና በንግድ እንቅስቃሴው ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ እየተገለጸ ይገኛል፡፡

የከተማዋና የአካባቢው የጸጥታ ሁኔታ በየቀኑ እንደሚለዋወጥ እና በአጣዬ ከተማ ያለው የንግድ እንቅስቃሴ በከፊል ብቻ መሆኑም ታውቋል፡፡ #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
3.8K viewsedited  11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 07:11:32 ዓርብ ማለዳ! ሚያዝያ 20/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአማራ ክልላዊ መንግሥት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊና የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባል ግርማ የሺጥላ በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጓሳ በተባለ አካባቢ የተገደሉት "በታጠቁ ጽንፈኛ ኃይሎች" ነው ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። "የጽንፈኛ ኃይሎችን የሽብር ድርጊት" ለማስቆም ርምጃ እንደሚወስድ የገለጠው የክልሉ መንግሥት፣ የግድያውን ፈጻሚዎች ለፍርድ አቀርባለኹ በማለት ቃል ገብቷል። ግርማ የተገደሉት፣ ከመንግሥትና የድርጅት ሥራ መልስ ከመሃል ሜዳ ከተማ ወደ ደብረ ብርሃን ከተማ ሲጓዙ እንደኾነ የክልሉ መንግሥት ጨምሮ ገልጧል።

2፤ አብን በአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ ግርማ የሺጥላ ላይ የተፈጸመው ግድያ "የአገሪቱን ሰላምና መረጋጋት አደጋ ላይ የሚጥል የዜሮ ድምር ፖለቲካዊ ሽብር ውጤት" መኾኑን ገልጧል። አብን ቀደም ሲል በክልሉ አመራሮች ላይ የተፈጸመው የግድያ ወንጀል "ተሸፋፍኖ መቅረቱና ተጠያቂነት አለመስፈኑ"፣ አኹንም የአመራሮች ግድያ "ተባብሶ እንዲቀጥል" ምክንያት መኾኑን አምናለኹ ብሏል። አብን ግድያው ሳይጣራና የገዳዮች ማንነት ሳይታወቅ፣ ከድርጊቱ "ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ሲባል በአደባባይ የሚደርጉ ፍረጃዎችንና መግለጫዎችን" እንደሚያወግዝም ገልጧል። የግድያው ፈጻሚዎች ማንነት እንዲጣራና ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ አብን ጨምሮ ጠይቋል።

3፤ ዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ካለፈው ዓርብ ጀምሮ ከ3 ሺህ 500 በላይ የበርካታ የውጭ አገራት ዜጎች በግጭት ከምትናጠው ሱዳን በመተማ የድንበር ከተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን አስታውቋል። የውጭ ዜጎቹ አብዛኞቹ ቱርካዊያን፣ ኡጋንዳዊያን፣ ኢትዮጵያዊያን፣ ቻይናዊያን፣ ሱዳናዊያንና ሱማሊያዊያን እንደኾኑ ድርጅቱ ገልጧል። ቱርክ ከ1 ሺህ 600 በላይ ዜጎቿ በመተማ በኩል ወደ ኢትዮጵያ መግባታቸውን ከኹለት ቀናት በፊት መግለጧ ይታወሳል።

4፤ በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ እና የተወሰኑ ዲፕሎማቶች ገዳሪፍ ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ተዛውረው ሥራቸውን እያከናወኑ መኾኑን ኤምባሲው በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል። ኾኖም ኢምባሲው የተወሰኑ ባልደረቦቹ ኢምባሲው ውስጥ እንዲቆዩ እንደተደረገ ጠቅሷል። አምባሳደሩና የተወሰኑ ዲፕሎማቶች ወደ ገዳሪፍ የተዛወሩት፣ ኢምባሲው የሚገኝበት የካርቱም ክፍል "የውጊያ ቀጠና" በመኾኑ እንደኾነ ገልጧል።

5፤ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ባለፈው ማክሰኞ ያወጁት የ72 ሰዓት ተኩስ አቁም ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ አብቅቷል። ተመድ እና የተለያዩ አገራት ተኩስ አቁሙ ለተጨማሪ 72 ሰዓታት እንዲራዘም ያቀረቡትን ጥሪ፣ የጦር ሠራዊቱ አዛዥ ጀኔራል ቡርሃንና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ እንደተቀበሉት የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.2K views04:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ