2022-07-07 10:51:52
በብልፅግና ዘመን ታጋች ሆነህ የምታገኘውን እንክብካቤ፣በወያኔ ዘመን ጠ/ሚኒስተር ሆነህ አታገኘውም።
ስለደረሰብኝ መታገት ይህችን እውነት ተናግሬ ነገ ጠዋት ልሙት !
(በላይ በቀለ ወያ) አንጋሳ ስታይል።
።
።
ምንም ውሸት የለውም!!! ሞትን ፈርቼ ሳይሆን ለቤተሰቦቼና ለወዳጆቼ ስል የምደብቃችሁ ህጋዊ ህገ ወጥ የሆኑ ተግባሮች ቢፈፀሙብኝም ከዚህ በታች የምፅፋቸው ነገሮች መቶ ፐርሰንት የተረጋገጡ እውነቶችን ነው!!! ጀመርኩ!!!
።።።።
በደረሰብኝ እገታና አፈና ምክንያት ብዙ ወዳጆቼና ጠላቶቼ "ህጋዊነትና ሰብአዊነት" ተሰምቷቸው ድምፅ ሆነውልኛል !!! አብዝተው ስላለሁበት ሁኔታ ጠይቀዋል ! ደክመዋል! አዝነዋል። ተጨንቀዋል። አልቅሰዋል።ይህን ሰብአዊ ልብ ላደላቸው ሁሉ በማስመሠል ሳይሆን በነገሮች መቀያየር ስለማይቀየረው እውነት ስል ከልቤ አልፌ ከነፍሴ አመሠግናቸዋለሁ!!! በተቃራኒው ደግሞ ህጋዊ በሚመስል ህገወጥ መንገድ በመታገቴ .."የታባቱ ይሄ የብልፅግና ውታፍ ነቃይ ፣ ሲያሽቃብጥ ከርሞ የጁን ሰጡት። እዚህ ቦታ ተገደለ ፣ እዚህ ቦታ ታርዶ አየነው ፣ ስቀሉት ፣ግደሉት ፣ ዘልዝሉት ፣ በእገሌ ብሔር እናቶች ቀልዶ ፣ የእገሌ ብሔር ተወላጆችን ሞት ደግፎ ..ምንትስ ቅብርጥስ " የሚሉ የኔ መታገት ፣ የኔ ስቃይ እና የኔ ሞት የሚያስደስታቸው የወያኔ ተረፈ ምርቶችን ተመልክቻለሁ!!! ለነዚህ ተረፈ ወያኔዎች ከዚህ በታች በተራ ቁጥር የማሰፍረውን የሀቅ ጥያቄ በወያኔ መንፈሳቸው ሳይሆን በሰውነት ህሊናቸው ለራሳቸው ይመልሱት !!
1 እኔ በላይ በቀለ ወያ ዘመን በቀባኝ ጥላሸት ልክ በዘር ሳስብ በአባቴ ጥንቅቅ ያልኩ የወለጋ ኦሮሞ በእናቴ ጥንቅቅ ያልኩ የአደዋ ትግሬ ነኝ!!! እንደ ፓርቲ የወያኔን መጥፋት ከመመኘት ውጪ የትግራይ ህዝብን መጥፋት የደገፍኩት የቱ ጋር ነው ?
2 የትግራይን ህዝብ ደግነት ፣ ቀናነትና መልካምነት የምመሰክረው እናቴ ትግሬ ስለሆነች ሳይሆን ..በመቀሌ ፣ በሽሬ ፣ በአክሱምና በአድግራት ከህዝቡ ጋር ኖሬ ስለማውቅ ነው!!! ታዲያ ይህን እንስፍስፍ ህዝብ በወያኔ ጭካኔ ልክ እንድሰፍረው ለምን ፈለጋችሁ?
3 በትግራይ ህዝብ ስም "ጦርነት ባህላዊ ጨዋታዬ ነው ። በሎም! ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦል ድረስ እወርዳለሁ ። በኔ እድሜ ኢትዮጵያ ስትፈራርስ በማየቴ ደስተኛ ነኝ ። በሚሉ ቅዠታሞች ልክ የትግራይን ህዝብ እንድሰፍረው ስለምን ፈለጋችሁ?
4 ሀይማኖተኛው ፣ ሰው አክባሪው ፣ ሩህሩህ የሆነ የትግራይን ህዝብ በጨካኙ ፣ በሰሜን እዝ ላይ በፈፀመው ግፍ " ብቻ የሰይጣን ታላቅ ወንድም " መሆኑን ካረጋገጠው ወያኔ ጋር አብሬ እንዳስበው ስለምን አሰባችሁ? (እዚህች ጋር የወያኔን የሰይጣን ታላቅ ወንድምነትን እንዳንክድ መብረቃዊ ጥቃቷ ትታሰብ)
5 ወያኔ ፓርቲ እንጂ ብሔር እንዳልሆነ ጠንቅቄ የማውቅ ሰው ነኝ!! ታዲያ "ጦርነት ባህላዊ ጨዋታዬ ነው። በሎም !!! ቅብርጥስ ምንትስ ብሎ ገጥሞ የትግራይን ወጣት ያስጨረሰ ድርጅትን መጥላትና መቃወም የትግራይን ህዝብ መጥላት የሚሆነው በምን ስሌት ነው? (ወያኔ ወዲያ የትግራይህ ህዝብ ወዲህ)
።።።
ማጠቃለያ!
በወያኔ ዘመን በመፃፌ ምክንያት አንዴ ታግቼ ተወስጃለሁ። አንዴ ታስሬ ወር ተገርፊያለሁ!!! በብልፅግና ዘመን ህጋዊ በሆነ ህገወጥነት ምክንያት መታገቴ ያስደሰታችሁ የወያኔ ተረፈ ምርቶች ሁሉ መቶ ፐርሰንት እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ ከወያኔ ህጋዊነት የብልፅግና ህገወጥነት መቶ እጥፍ እንደሚሻል ነው!!! ከብልፅግና በማልጠብቃቸው ነገሮች ጭምር ተበድያለሁ !!! የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተፈፅመውብኛል !!! በሀገሪቱ ላይ እየተፈፀሙ ባሉ ዘግናኝ ድርጊቶች በማስመሰል ሳይሆን በእውነት የምቆስልና የማዝን ሰው ነኝ!!! የሆነው ነገር ሁሉ ሆኖ አይደለም መታፈን እና ነገ ብገደል እንኳን በወያኔ ዘመን ታግቶ ከመለቀቅ በዚህ ዘመን ተገድሎ መሞት መቶ እጥፍ የተሻለ ነው !!! በወያኔ ዘመን ስንቱ ወንድ ሲኮላሽ ፣ ስንቷ ሴት በብልቷ ብረት ሲገባባት ስንቱ ብልት የሀይላንድ ውሃ ሲሸከም ፣ ስንቱ በድብቅ ሲረሸንና በጅምላ ሲቀበር ትንፍሽ ያላልክ ተረፈ ወያኔ ሁላ ዛሬ የኔ መታገት አያስደስትክ !!! በወያኔም በዚህ ዘመንም ታግቻለሁ ። እርግጠኛ ሆኜ የማረጋግጥልህ ከወያኔ አጋቾች ደግነት ይልቅ የዚህ ዘመን አጋቾች ክፋት የተሻለ ነው!!! ለግዜው የማልናገረው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ቢደርሱብኝም ጠብ የማይል ሀቅ ልንገርህ !!! በዚህ ዘመን ታጋች ሆነህ የምታገኘውን እንክብካቤ በወያኔ ዘመን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆነህ አታገኘውም !!! ከወያኔነት በላይ የትግራይ ህዝብ ጠላት እዚህ ሀገር ላይ የለም !!! አይደለም በዚህ ሀገር ላይ ዓለም ላይ ተፈልጎ አይገኝም !!!
።።።።
ማሳሰቢያ!!!
ይህ መልዕክት በደረሰብኝ አፈና ጮቤ ለረገጡ ፣ ሞቴን ለተመኙ ፣ በዚህ ዘመን የሚፈፀሙ ግፎችን ታከው የወያኔን ፃድቅነት ለመመስከር ለተጋጋጡ የወያኔ ተረፈ ምርቶች ብቻ ይሁንልኝ!!! #ሼር
በላይ በቀለ ወያ እንደፃፈው
@emsmereja
4.8K viewsedited 07:51