Get Mystery Box with random crypto!

EMS Mereja

የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja
የሰርጥ አድራሻ: @emsmereja
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.57K
የሰርጥ መግለጫ

👉 መረጃዎች፣ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና የማስታወቂያ ስራ ለማሰራት ከፈለጉ በዚህ ያናግሩን👉 t.me/infoetrobot
👉 የዕለታዊ ዝግጅቶችና ዜናዎች በተባባሪ አቅራቢዎች እንዲደርሷችሁ👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@HAQMEDIA12
Subscribe ያድርጉ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-27 20:06:43
ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ

በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የብልፅግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባል እና በምክትል ርዕሰ  መስተዳደር ማዕረግ  የብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የተከበሩ አቶ ግርማ የሺጥላ እና የግል ጥበቃዎቻቸው ላይ  የመንግሥትና የድርጅት ሥራዎችን በሰሜን ሸዋ ዞን  ሠርተው ከመሀል ሜዳ ወደ ደብረ ብርሀን ሲመለሱ  ልዩ ቦታው መንዝ ጓሳ አካባቢ በታጠቁ  ፅንፈኛ ሃይሎች በደረሰባቸው ጥቃት ሕይወታቸው አልፏል::

በደረሰው ልብ ሰባሪ ጥቃት የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰማውን መሪር ሀዘን ይገልጻል፡፡  እነዚህ ፅንፈኛ ሀይሎች በሀሳብ ትግል ማሽነፍ ያልቻሉትን በኀይል ለማስፈፀም  ያደረሱት ጥቃት ዓላማውን ማሳካት የማይችልና ጊዜው ያለፈበት፣  ዘመኑን ያልዋጀ የጥፋት መንገድ ስለሆነ አምርረን የምንታገለው ተግባር  ነው፡፡

እነዚህ ፅንፈኛ ሃይሎች በክልሉ ውስጥ የሚፈጽሙትን ስርዓት አልበኝነትና የሽብር ድርጊት ለመከላከል፤ ለመቆጣጠርና ሕግ ለማስከበር የክልሉ መንግሥት እርምጃ ይወስዳል:: የጥቃቱን አድራሾችም ለሕግ ያቀርባል፡፡ ማንኛውም በጥቃቱ የተሳተፉ ሃይሎችንንና ተባባሪዎችን ሁሉ ከያሉበት ለሕግ በማቅረብ አስፈላጊው ፍትሕ እዲረጋገጥ ይደረጋል፡፡

የጥፋት ኃይሎች ከዚህ በላይ ዓላማ ያላቸው እና ክልሉን የማፍረስ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ በኋላ የክልሉ መንግሥት እንደማይታገስ እና ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ እናረጋግጣለን፡፡

የክልሉ መንግሥት ለቤተሰቦቻቸው፤ ወዳጆቻቸው፤ ለስራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የክልላችን ሕዝብ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ይገልጻል፡፡ ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያሳርፍልን!
#ሼር በማድረግ ተባበሩን
ለወሳኝ መረጃዎች    @emsmereja
4.5K viewsedited  17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 20:02:04 ሐሙስ ምሽት! ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በአማራ ክልል የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የኾኑት ግርማ የሺጥላ ዛሬ "በነውጠኛ ጽንፈኞች" መገደላቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። ዐቢይ በዚኹ መልዕክታቸው፣ "በሐሳብ የተለየን ኹሉ በጠመንጃ ለማሳመን መነሳት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው" ብለዋል። ግድያው "አስነዋሪና አሰቃቂ" መኾኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚንስትሩ፣ ጽንፈኝነትን በጊዜ ካልተወገደ "ወደመጨራረስ እንደሚወስደን ጉልህ ማሳያ ነው" በማለትም ድርጊቱን አውግዘዋል። ግርማ ዛሬ የተገደሉት በተወለዱበት ሰሜን ሸዋ አካባቢ መኾኑንም ዐቢይ ጨምረው ገልጸዋል።

2፤ የኹሉም ክልላዊ መንግሥታት ርዕሰ መስተዳድሮች፣ የአዲስ አበባና ድሬዳዋ ከተሞች ከንቲባዎችና የፌደራል መንግሥቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የተካተቱበት ልዑካን ቡድን ዛሬ በትግራይ ክልል ጉብኝት ማድረጉን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ልዑካን ቡድኑን የመሩት የገዥው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አደም ፋራህ መኾናቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ልዑካን ቡድኑ፣ በውቅሮ ከተማ ሰማያታ የእብነበረድ ፋብሪካና ሸባ የቆዳ ፋብሪካን እንደጎበኘና ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ እና ከሌሎች የአስተዳደሩ ባለሥልጣናት ጋር እንደተወያየ ዘገባው አመልክቷል። በጉብኝቱ ወቅት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ለትግራይ ክልል መልሶ ማቋቋሚያ 1 ቢሊዮን ብር እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል ተብሏል።

3፤ ታንዛኒያ ውስጥ በኢትዮጵያ መንግሥትና በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል እየተካሄደ ያለው ድርድር አሸማጋዮች ኬንያ እና ኖርዌይ እንደኾኑ ዘ ኢስት አፍሪካን ዘግቧል። አጀንዳ በመቅረጽ ላይ ያተኮረው የአኹኑ ድርድር ወደፊት ለሚካሄድ ሁሉን ዓቀፍ ድርድር መንደርደሪያ እንደሚኾን የአማጺው ቡድን ቃል አቀባይ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ድርድሩ ወደፊት ከቀጠለ፣ አሜሪካ፣ አውሮፓ ኅብረት እና ኢጋድ የድርድር ሂደቱ አካል ይኾናሉ መባሉን ዘገባው አመልክቷል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ፣ መንግሥት ድርድር እየተካሄደ ስለመኾኑ ያለው ነገር የለም።

4፤ የፌደራሉ እንባ ጠባቂ ተቋም በኦሮሚያ፣ ሱማሌና ደቡብ ክልሎች በድርቅ ሳቢያ "አንድም ሰው እንዳልሞተ" አረጋግጫለሁ ሲል ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ መናገሩን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ተቋሙ በድርቁ የሰው ሕይወት እንዳላለፈ አረጋግጫለሁ ያለው፣ በሦስቱ ክልሎች በድርቁ በከፍተኛ ደረጃ በተጎዱ የኦሮሚያው ቦረና፣ የሱማሌው ዳዋ እና የደቡቡ ደቡብ ኦሞ ዞኖች ባለፈው መጋቢት መገባደጃ ያከናወነውን ክትትል መሠረት በማድረግ መኾኑን መግለጡን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ተቋሙ፣ ከሦስቱ ክልሎች በድርቁ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት የኦሮሚያው ቦረና ዞን መኾኑን ማረጋገጡን በመግለጫው አመልክቷል ተብሏል።

5፤ በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ሰላማጎ ወረዳ በቦዲ እና ደሚ ጎሳዎች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት 11 ሰዎች ተገድለው ስድስት ሰዎች እንደቆሰሉ ዶይቸቨለ ከዓይን እማኞችና ከወረዳው አስተዳደር መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። የኹለቱ ጎሳዎች ግጭት ወደ ወረዳው መቀመጫ ከተማ ሐና ተዛምቶ ሴቶችና ሕጻናት ጭምር እንደተገደሉ የጠቀሰው ዘገባው፣ የግጭት መነሻ አንድ የወረዳው አመራር ገጠር ውስጥ ለሥራ በመጓዝ ላይ ሳሉ በድንገተኛ ጥቃት ከተገደሉ በኋላ መኾኑን ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል።

6፤ ኢጋድ የኢጋድ አሸማጋይ መሪዎች ቡድን አባል የኾኑት የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል-ቡርሃንን እና ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎን ለማሸማገል ጥረት መጀመራቸውን ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ፕሬዝዳንት ኪር ዛሬ እኩለ ሌሊት የሚያበቃው የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የ72 ሰዓታት ተኩስ አቁም ለተጨማሪ 72 ሰዓታት እንዲራዘምና ኹለቱ ወገኖች ሽምግልና እንዲጀምሩ እያደረጉት ባለው ጥረት የደረሱበትን ደረጃ፣ ትናንት ለድርጅቱ አባል አገራት መሪዎች ማሳወቃቸውንም ኢጋድ ገልጧል።

7፤ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ጁባ ውስጥ ተገናኝተው በዘላቂ ግጭት ማቆም ዙሪያ እንዲነጋገሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ዘ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ዘግቧል። የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን የፕሬዝዳንት ኪርን ግብዣና የተኩስ አቁም ማራዘም ጥሪ እንደተቀበሉት ዘገባው ጠቅሷል። የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ግን፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ገና ምላሽ አልሰጡም ተብሏል። የተኩስ አቁሙ ቀነ ገደብ ባይጠናቀቅም፣ የሱዳን ጦር ሠራዊት ዛሬ ካርቱም ውስጥ የባላንጣውን ይዞታዎች በአየር እንደደበደበና በምዕራብ ዳርፉር ከባድ ውጊያ እየተካሄደ መኾኑን የዘገቡት ደሞ የውጭ ዜና ወኪሎች ናቸው።

8፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ1547 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2347 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ5557 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ8468 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ8647 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ0620 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.3K views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 14:24:40 ዜና!!

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ምዝገባ ነገ ሚያዚያ. 20/2015 ዓም ከቀኑ 11:30 ላይ እንደሚያበቃ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ እስካሁን ያልተመዘገቡ ተፈታኞች እስከ ነገ እንዲመዘገቡ አሳስቧል።

በማንኛውም ምክኒያት ያልተመዘገቡ ተፈታኞችን " ከነገ በኋላ አላስተናግድም " ሲል አሳውቋል።

የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጥ ሲሆን ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ ከምዝገባው መጠናቀቅ በኃላ ይፋ ይደረጋል።

የEMS ቤተሰብ አባላት የሆናችሁ ተፈታኞች እስካሁን ድረስ የመፈተኛው ቀን ይፋ #አለመደረጉን በማወቅ ከሀሰተኛ መረጃዎች በመራቅ በተረጋጋ መንፈስ ሆናችሁ ይህንን መረጃ ለወዳጅ ዘመዳችሁ ሼር በማድረግ አሳውቁ።

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.1K viewsedited  11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 14:18:45 ህገወጥ የጵጵስና ሹመት ፈጽመዋል የተባሉ አካላት የቤተክርስትያን ንብረቶችን በማሸሸና ንዋየ ቅዱሳትን በመሸጥ ላይ ናቸው ተባለ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሕገወጥ የጳጳሳት ሹመት ተሳትፈዋል ተብለው የተጠቀሱ አካላት አሁንም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሐረርጌ አገረ ስብከት ተገቢ ያልሆነ ተግባር እየፈጸሙ ነው ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ገለፁ።
ነዋሪዎች አክለውም፤ ለሀገረ ስብከቱ መንፈሳዊ አግልግሎት የሚውሉ ተሽከርካሪዎችን፣ በከብት መድለቢያ የደለቡ ሰንጋዎችን እንዲሁም የተለያዩ ንብረቶችን በማሸሽ ላይ ናቸው ብለዋል፡፡

ለአብነትም በጭሮ ከተማ ከሚገኙ አምስት አብያተክርስትያናት ሦስቱን በኃይል ሰብረው በመግባት የተቆጣጠሩት እነዚህ አካላት በምዳዬ ምጽዋት ውስጥ የሚገኙ ገንዘቦችን በመውሰድ እና የአብያተ ክርስትያናቱን ንዋየቅዱሳት አውጥተው በመሸጥ ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ይህን ተከትሎም በአካባቢው የሚኖሩ የእምነቱ ተከታዮች በቅዱስ ሲኖዶሱ ተለይተው በተወገዙ አካላት አንገለገልም በማለታቸው የቤተክርስትያን አገልግሎት እያገኙ እንዳልሆነ ጠቁመዋል፡፡

ነዋሪዎቹ ይህን ተግባር እየፈጸሙ ያሉት አካላት እየታገዙ ያለው በመንግሥት የጸጥታ አካላት መሆኑን ጠቁመው፤ ድርጊታቸውን የሚቃወሙ አካላትን የማሰርና የማዋከብ ሥራ በመንግሥት አካላት እየተፈጸመ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግሥት ህግ እንዲያስከብር በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ህገወጦችን ከማስቆም ይልቅ በተቃራኒው ጥያቄ ያቀረቡ አካላት ናቸው እስርና ወከባ እየተፈጸመባቸው ያለው ብለዋል፡፡

ስለሆነም በአካባቢው ያለው የመንግሥት መዋቅር ከቤተክርስትያን ላይ እጁን እንዲያነሳ ጠይቀዋል፡፡

የኦሮሚያና የብሔር ብሔረሰቦችን ሲኖዶስ እንመሰርታለን ያሉ አካላት ባለፈው ጥር ወር የ27 ኤጲስ ቆጶሳትን ሹመት ማከናወናቸው እና ይህን ተከትሎም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ ውግዘት እንደተላለፈባቸው ይታወቃል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.1K views11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 06:56:18 ሐሙስ ማለዳ! ሚያዝያ 19/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የአውሮፓ ኅብረት ኢትዮጵያን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ በበጎ ጎኑ እንደተቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አዲስ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መንግሥትም ከአውሮፓ ኅብረት ጋር ትብብሩን በአዲስ መልክ ለማደስ መዘጋጀቱን ሚንስቴሩ ገልጧል። ኅብረቱ በምግብ ዋስትናና ግብርና ላይ ያተኮረው የባለ ብዙ ዘርፍ የድጋፍ መርሃ ግብር እንደገና እንዲጀመር ዝግጁነቱን መግለጡንና አበዳሪ አገራት የኢትዮጵያን የውጭ ዕዳ ለማሸጋሸግ የጀመሩት ድርድር በቶሎ እንዲቋጭ ጥሪ ማድረጉን ሚንስቴሩ አድንቋል።

2፤ የኢትዮጵያ መንግሥትና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ማክሰኞ'ለት በታንዛኒያ ድርድር መጀመራቸውን ከምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። መንግሥትና አማጺው ቡድን እያንዳንዳቸው ስድስት ተደራዳሪዎችን ለድርድሩ መመደባቸውን ዘገባው ጠቅሷል። መንግሥትን ከወከሉት ተደራዳሪዎች መካከል የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን እና ፍትህ ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እንዲሁም ቡድኑን የወከሉት ደሞ የታሪክ ፕሮፌሰሩ መሐመድ ሐሰን፣ የቡድኑ ታጣቂዎች አዛዥ አማካሪ ጂሬኛ ጉደታ እና አብዲ ጣሃ እንደኾኑ ዘገባው ገልጧል።

3፤ የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው መዝገብ የክስ መዝገብ በተከፈተባቸው አምስት ግለሰቦች የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ መቅጠሩን ቪኦኤ ዘግቧል። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ከእስር እንዳይለቀቁ የፈለገበትን ምክንያቶች ለችሎቱ ያስረዳ ሲሆን፣ የተጠርጣሪ ጠበቆችም ተጠርጣሪዎቹ ዋስትና ሊያስከለክላቸው የሚችል ጉዳይ እንደሌለ ጠቅሰው መከራከራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ፖሊስ ተከሳሾቹ ላይ የክስ መዝገብ የከፈተው፣ "ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳትና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመጣል" ተንቀሳቃሰዋል በማለት ነበር። ፍርድ ቤቱ በዋስትና ጥያቄያቸው ላይ ብይን የሚሰጥባቸው ሌሎች ተጠርጣሪዎች፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ ኄኖክ ዐዲሱ፣ ሰለሞን ልመንህና የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አምሃ ዳኘው ናቸው።

4፤ በሱማሊያ ለተሠማራው የአፍሪካ ኅብረት የሰላም ተልዕኮ ሰላም አስከባሪ ወታደሮችን ያዋጡ አገራት መሪዎች ኡጋንዳ ካምፓላ ውስጥ ይመክራሉ። የሱማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በመሪዎቹ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ካምፓላ መግባታቸውን የሱማሊያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የኢትዮጵያው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀም ትናንት ካምፓላ ገብተዋል። የመሪዎቹ ጉባኤ የኅብረቱ የሰላም ተልዕኮ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር እስከ ታኅሳስ 2024 ዓ፣ም ድረስ በአገሪቱ በሚኖረው ቆይታ ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ሱማሊያ የኅብረቱ ወታደሮች ቆይታ ከቀነ ገደቡ በኋላ እንዲራዘም ፍቃደኛ መኾኗ ሰሞኑን ተዘግቧል።

5፤ ደቡብ ሱዳን ለሱዳኑ ግጭት የሰላም ሃሳብ ማቅረቧን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል። የደቡብ ሱዳን የሰላም ሃሳብ የሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል-ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል መሐመድ ደጋሎ ቀጠናዊ-መር ለኾነ የሰላም ንግግር ከቀጠናው አገሮች ጋር በቅርበት ለመተባበር ቁርጠኛ እንዲኾኑ እንደሚጠይቅ ዘገባው አመልክቷል። ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ያቀረቡት የሰላም ሃሳብ፣ ሁለቱ ወገኖች ባስቸኳይ ግጭት እንዲያቆሙ፣ የ72 ሰዓት ተኩስ አቁሙን እንዲያራዝሙና የዕርዳታ መስመሮችን እንዲከፍቱ ጭምር ይጠይቃል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
4.3K views03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 07:34:53 ረቡዕ ማለዳ! ሚያዝያ 18/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ኢጋድ የኢትዮጵያ መንግሥትና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ተወካዮች ታንዛኒያ ዛንዚባር ውስጥ ንግግር መጀመራቸውን መግለጡን ሮይተርስ ዘግቧል። ኢጋድ የኹለቱ ወገኖች ንግግር ወደ ፖለቲካዊ ስምምነት ያመራል ብሎ እንደሚጠብቅ ቃል አቀባዩ ኑር መሐመድ ሼክ መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ሮይተርስ፣ የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክሎ የሚደራደረውን ቡድን የሚመሩት የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን መኾናቸውን ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ምንጮች ሰምቻለሁ ብሏል።

2፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን ጋር ትናንት በመቀሌ ጽሕፈት ቤታቸው መወያየታቸውን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። ጌታቸው ውይይቱ ፌደራል መንግሥትና ሕወሃት በደረሱበት ሰላም ስምምነት አፈጻጸም፣ በፍትህ፣ በወንጀል ተጠያቂነት፣ በሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት መሰናክሎችና አሜሪካ በመልሶ ግንባታ መስክ ሊኖራት በሚገባ ሚና ዙሪያ እንደነበር ገልጸዋል።

3፤ ከ1 ሺህ 600 ቱርካዊያን ዜጎች ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ በአውቶብስ መጓጓዛቸውን ከዲፕሎማቲክ ምንጮች መስማቱን የቱርኩ አናዶሉ ዜና ወኪል ዘግቧል። ቱርካዊያኑ ወደ መተማ እና ከዚያም ወደ ጎንደር የተጓጓዙት በአውቶብስ መኾኑን የጠቀሰው ዘገባው፣ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በአውሮፕላን መጓጓዛቸውን መስማቱን ጠቅሷል። ቱርካዊያኑን በኢትዮጵያ በኩል ከሱዳን የማስወጣቱ ተልዕኮ እንደቀጠለ መኾኑንም ዘገባው አመልክቷል።

4፤ የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት ትናንት ምሽት በሱዳን ግጭት ዙሪያ ምክክር አካሂዷል። የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ለምክር ቤቱ ባቀረቡት ሪፖርት፣ የሱዳኑ ግጭት ወደ ጎረቤት አገራት ሊዛመት እንደሚችል እና የሱዳን ጎሳዎችና የታጠቁ ኃይሎችም በግጭቱ ጎራ ለይተው ለመዋጋት እየተዘጋጁ መኾኑን በማስጠንቀቅ፣ ሁለቱ የአገሪቱ ተፋላሚ ወገኖች ባስቸኳይ ውጊያውን እንዲያቆሙ ጥሪ አድርገዋል። በተመድ የሱዳን ተወካይ አል ሐሪት ሞሐመድም በግጭቱ ላይ ለምክር ቤቱ ማብራሪያ የሰጡ ሲኾን፣ ሱዳን በግጭቱ ዙሪያ የውጫ ጣልቃ ገብነቶችን እንደማትቀበል ገልጸዋል።

5፤ የዓለም ምግብ ፕሮግራም አውሮፓ ኅብረት በጣለው ማዕቀብ ሳቢያ ከወራት በፊት ላትቪያ ውስጥ የተወረሰ የሩሲያ ማዳበሪያን ወደ ኬንያ እየተጓጓዝ መኾኑን ሮይተርስ ዘግቧል። ወደ ኬንያ መጓጓዝ የጀመረው የመጀመሪያው ዙር 200 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ መኾኑን ዘገባው አመልክቷል። ላትቪያ ማዳበሪያውን ወደ ኬንያ የላከችው፣ የምትወርሰውን የሩሲያ ማዳበሪያ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት በኢኮኖሚያቸው ላይ ጉዳት ላደረሰባቸው አገራት በነጻ እንዲከፋፈል በወሰነችው መሠረት እንደኾነ ተገልጧል።

6፤ የደቡብ አፍሪካ ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግሬስ ደቡብ አፍሪካ ከዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት እንድትወጣ መወሰኑን ፕሬዝዳንት ሴሪል ራማፎዛ መናገራቸውን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ዓለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በርካታ የዩክሬን ሕጻናትን በግዳጅ ወደ ሩሲያ ወስደዋል በማለት ባለፈው መጋቢት የእስር ማዘዣ እንዳወጣባቸው ይታወሳል። የፍርድ ቤቱ መመስረቻ ስምምነት ፈራሚ የኾነችው ደቡብ አፍሪካ በመጭው ነሐሴ በምታዘጋጀው የብሪክስ አገራት የመሪዎች ጉባኤ ላይ፣ ፕሬዝዳንት ፑቲን የሚገኙ ሲሆን፣ ደቡብ አፍሪካም የፍርድ መመስረቻ ስምምነት ፈራሚ እንደመኾኗ ፕሬዝዳንት ፑቲንን አስራ ለፍርድ ቤቱ የማስረከብ ግዴታ አለባት።

7፤ የሱማሌላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ለተመድ ጸጥታው ምክር ቤት አቤቱታ ማስገባቱን የሱማሌላንድ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የራስ ገዟ መንግሥት ለጸጥታው ምክር ቤት ያስገባው አቤቱታ፣ በላስ አኖድ ከተማ በተቀሰቀሰው ግጭት የአልሸባብ፣ የፑንትላንድና የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት ታጣቂዎች በቀጥታ ተሳታፊ ናቸው በማለት የሚከስ መኾኑን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የሱማሌላንድ መንግሥት ሦስቱ አካላት ወረራና ጥቃት ፈጽመውብኛል በማለት ሲከስ መክረሙ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
1.7K views04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 22:38:42
የ35 የአማራ፣ 2 የአፋር ባለሃብቶችና ድርጅቶች የባንክ አካውንት ታገደ። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
2.6K views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 20:10:28 ማክሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 17/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የተሻሻለውን የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ በስድስት ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። መንግሥት አዘጋጅቶ ያቀረበው የተሻሻለ ረቂቅ አዋጅ፣ ኅብረ ብሄራዊ ተዋጽዖውን የጠበቀ ዘመናዊ የአገር መከላከያ ሠራዊት ለመገንባት ማነቆ ኾነዋል የተባሉ የሕግ ማዕቀፎችን ለማሻሻል ያስችላል ተብሏል። ተሻሽሎ የጸደቀው አዋጅ፣ የሠራዊቱ አባላት የጡረታ መውጫ የእድሜ ጣሪያን አወሳሰን፣ የ12ኛ ክፍል ወይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በፍቃዳቸው ለኹለት ዓመት ብሄራዊ አገልግሎት የሚሰጡበትን አግባብ፣ የአገር ሕልውና ከባድ አደጋ ላይ በሚወድቅበት ጊዜ ከሠራዊቱ የተገለሉ የቀድሞ አባላትን መልሶ መቅጠር የሚቻልበትና ሌሎች የሠራዊቱ መብትና ጥቅማ ጥቅሞችን እንዳካተተ ተገልጧል።

2፤ በሱዳን የኢትዮጵያ ኢምባሲ በሱዳኑ ውጊያ ቢያንስ ስምንት ኢትዮጵያዊያን እንደተገደሉና ሌሎች አራት ኢትዮጵያዊያን የመቁሰል ጉዳት እንደደረሰባቸው መናገሩን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ኢትዮጵያዊያኑ ለሞት እና ለመቁሰል አደጋ የተዳረጉት፣ በተባራሪ ጥይት እና ከባድ መሳሪያ አረሮች ፍንጣሪ ሳቢያ መኾኑን ኢምባሲው መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ከአገሪቱ መውጣት የሚፈልጉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ኢትዮጵያዊያን ዜጎች በአውቶብስ ወደ መተማ ለመሸኘት እየመዘገበ መኾኑን ኢምባሲው መግለጡን የጠቀሰው ዘገባው፣ የኢምባሲው ሠራተኞች ካርቱምን ለቀው ለኢትዮጵያ ቅርብ በኾነችው የሰሜን ሱዳኗ ገዳሪፍ ከተማ ሥራቸውን እያከናወኑ መኾኑን ጠቅሷል።

3፤ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ዛሬ መቀሌ መግባታቸውን የትግራይ ክልል ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ከልዩ መልዕክተኛ ሐመር ጋር በኢትዮጵያ የአሜሪካ ዋና ጉዳይ አስፈጻሚ ትሬሲ ጃኮብሰን አብረው መቀሌ ይገኛሉ ተብሏል። ሐመር ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባለሥልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ዘገባው አመልክቷል። ሐመር፣ ባለፈው ኅዳር የሕወሃት የሰላም ተደራዳሪዎችን በአሜሪካ ወታደራዊ አውሮፕላን አሳፍረው ወደ ፕሪቶሪያ መውሰዳቸው ይታወሳል።

4፤ ትናንት በታንዛኒያ ጉብኝት ያደረጉት ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ ዛሬ በኮሞሮስ ይፋዊ ጉብኝት በማድረግ ላይ ናቸው። ደመቀ ዛሬ ከኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ ጋር ተገናኝተው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሕወሃት ጋር በደረሰበት የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ዙሪያ ለፕሬዝዳንቱ ገለጻ እንዳደረጉላቸው ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ፕሬዝዳንት አዛሊ፣ በአፍሪካ ኅብረት አስተባባሪነት በሕዳሴ ግድብ ውዝግብ ላይ ተቋርጦ የቆየው የሦስትዮሽ ድርድር እንዲቀጥል ጥረት አደርጋለሁ በማለት ለደመቀ እንዳረጋገጡላቸው ተገልጧል። ፕሬዝዳንት አዛሊ የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበር ናቸው።

5፤ አውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዘላቂ አፈጻጸምን መሠረት በማድረግ ከመንግሥት ጋር ያቋረጠውን ግንኙነት ደረጃ በደረጃ እንደገና ወደነበረበት ለመመለስ ጥረት እንደሚያደርግ ትናንት ባወጣው መግለጫ በድጋሚ አስታውቋል። ኾኖም ኅብረቱ፣ በሰሜኑ ጦርነት ኹሉም ተፋላሚ ወገኖች የፈጸሟቸው ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችና በሰላማዊ ሰዎችና ስደተኞች ላይ የተፈጸሙ የጦር ወንጀሎች በገለልተኛ መርማሪ አካል አማካኝነት ግልጽና ገለልተኛ ምርመራ የማድረግ ጉዳይ ጊዜ የማይሰጠው እጅግ አስፈላጊ ነገር መኾኑን በመግለጫው አመልክቷል። ኅብረቱ በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች ባሁኑ ወቅት እየታዩ ያሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ውጥረቶችና ግጭቶች እንዳሳሰቡት ገልጦ፣ በአገሪቱ ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት ለማስፈንችግሮቹ በፖለቲካዊ እና ዲሞክራሲያዊ አግባብ በንግግር ብቻ እንዲፈቱ ጥሪ አድርጓል። ኅብረቱ በሰሜኑ ጦርነት ሳቢያ ለኢትዮጵያ የሚሰጠውን የበጀት ድጋፍ ያቋረጠው፣ ከኹለት ዓመት ከመንፈቅ በፊት ነበር።

6፤ የሱዳን ጦር ሠራዊትና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በአሜሪካ አደራዳሪነት ከትናንት እኩለ ሌሊት ጀምሮ የደረሱበት የ72 ሰዓታት የተኩስ አቁም ስምምነት ካርቱም ውስጥ ከሞላ ጎደል ተግባራዊ እየኾነ መኾኑን ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። በኦምዱሩማንና ሌሎች ከተሞች ግን ውጊያው እንደቀጠለ መኾኑን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የጦር ሠራዊቱ ዋና አዛዥ ጀኔራል አል ቡርሃን እና የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ሞሐመድ ደጋሎ ሳዑዲ ዓረቢያ ውስጥ ተገናኝተው ፊት ለፊት እንዲነጋገሩ ጥረቶች እየተደረጉ መኾኑን የግብጽ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ1241 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2066 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 64 ብር ከ3057 ሳንቲም እና መሸጫው 65 ብር ከ5918 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ6015 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ7935 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
3.0K views17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 20:09:31 መልሱ A~Baro ወንዝ ጋምቤላ ነው።
2.5K views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 07:24:55 ማክሰኞ ማለዳ! ሚያዚያ 17ቀን 2015 የEMS አበይት ዜናዎች

1. የመከላከያ ሠራዊት አዋጅ ዛሬ ፓርላማ ቀርቦ ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል። አዋጁ የሠራዊቱ አባላትን ጥቅም፣ የማዕረግ ዕድገት እና የምልመላ ጉዳዮችን ጭምር ይዟል። ቀደም ሲል አዋጁ ክርክር ተደርጎበት ወደ ኮሚቴ ተመልሶ ነበር።

2. በኦሮሞ ነፃነት ጦር (ኦነግ ሸኔ)ና በመንግስት መካከል ይደረጋል የተባለው ድርድር ዛሬ በታንዛኒያ እንደሚጀመር ይጠበቃል። ከድርድሩ አንድ ቀን አስቀድሞ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን ታንዛኒያ ገብተዋል። ደመቀ ታንዛንያን ጨምሮ በአራት የአፍሪቃ ሀገራት ጉብኝት የማድረግ ዕቅድ አላቸው። በታንዛኒያ ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተዋል። የደመቀ የታንዛኒያ ጉብኝት ከኦነግ ሸኔ ጋር ከሚደረገው ድርድር ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ አልተገለፀም።

3. ብሄራዊ የተሃድሶ ኮምሽን ተግባራዊ ስራ ለመጀመር መዘጋጀቱን አስታወቀ። ባለፉት ሶስት ወራት ኮምሽኑ ዓላማውን በማስተዋወቅና ግብረ መልስ በመሰብሰብ ላይ አተኮሮ ነበር። ኮምሽኑ በሀገሪቱ ያለ እስከ ሶስት መቶ ሺ የሚደርሱ ተዋጊዎችን በትኖ በመደበኛ ሕይወት የማቋቋም ሀላፊነት አለበት።

4. የኦሮምያ ሕብረት ስራ ባንክ በአዲስ አበባ ረጅሙን ፎቅ ለመገንባት መዘጋጀቱን ገለፀ። ፎርቹን እንደዘገበው ባንኩ 65 ወለል ያለው አዲስ ዋና መስሪያቤቱን ፍልውሃ አካባቢ ለመገንባት እየተዘጋጀ ነው። ከዚህ ቀደም የከተማው ረጅም ፎቅ 46 ወለል ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መስሪያቤት ሕንፃ ነው።

5. የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኀይልና የሱዳን ጦር ሰራዊት ከትናንት ዕኩለ ሌሊት ጀምሮ በመላው ሀገሪቲ ለ72 ሰዓታት የሚቆይ የተኩስ አቁምማድረጋቸውን አውጀዋል። የተኩስ አቁሙ ስምምነት የተደረሰው በአሜሪካ መንግስት አደራዳሪነት ሲሆን በዚሁ የዕፎይታ ጊዜ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግና የውጪ ሀገር ዜጎችን ለማስወጣት ታቅዷል። የኣሜሪካ የውጪጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን የተኩስ አቁሙን ዘላቂ ለማድረግ ሁሉም ወገን ጥረት እንዲያደርግ ጠይቀዋል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                   @emsmereja
3.8K views04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ