Get Mystery Box with random crypto!

EMS Mereja

የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja E
የቴሌግራም ቻናል አርማ emsmereja — EMS Mereja
የሰርጥ አድራሻ: @emsmereja
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 14.57K
የሰርጥ መግለጫ

👉 መረጃዎች፣ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና የማስታወቂያ ስራ ለማሰራት ከፈለጉ በዚህ ያናግሩን👉 t.me/infoetrobot
👉 የዕለታዊ ዝግጅቶችና ዜናዎች በተባባሪ አቅራቢዎች እንዲደርሷችሁ👇👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@HAQMEDIA12
Subscribe ያድርጉ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-11 07:25:59 ሐሙስ ጠዋት! ግንቦት 3/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሜሪካ ሎዛንጅለስ ከተማ ከሚኖሩ የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያን ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንደሚወያዩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። አምባሳደር ሐመር፣ ከትናንት ጀምሮ እስከ ግንቦት 12 በከተማዋ በሚኖራቸው ቆይታ፣ ከአማራ፣ ኦሮሞ፣ ትግሬይና ሱማሊያ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማኅበረሰብ ተወካዮች እና ባጠቃላይ ከኢትዮዊያን አሜሪካዊያን ጋር እንደሚወያዩ መስሪያ ቤቱ ገልጧል። የአምባሳደር ሐመርና የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያኑ ውይይት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሃት መካከል ፕሪቶሪያ ላይ በተደረሰው ሰላም ስምምነት አፈጻጸ፣ በሌሎች የኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች እንዲኹም የኢትዮጵያዊያን ሴቶችን አቅም በመገንባት ዙሪያ ያተኮረ እንደሚኾን መረጃው አመልክቷል።

2፤ በአዲስ አበባ በርካታ ትምህርት ቤቶች ከ20 እስከ 100 ፐርሰንት የሚደርስ የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ለማድረግ የውሳኔ ሃሳብ ማቅረባቸውን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። የከተማዋ የትምህርትና ሥልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለሥልጣን ግን፣ የትኛውም ትምህርት ቤት ከተማሪ ወላጆች ጋር ስምምነት ላይ ሳይደርስ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ እንደማይችል ማስጠንቀቁን ዘገባው ጠቅሷል። በከተማዋ ከሚገኙት 1 ሺህ 558 ትምህርት ቤቶች መካከል፣ በቀጣዩ ዓመት የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ለማድረግ መወሰናቸውን ለባለሥልጣኑ ያሳወቁት፣ 1 ሺህ 257 ትምህርት ቤቶች እንደኾኑ ባለሥልጣኑ መናገሩን ዜና ምንጩ አመልክቷል።

3፤ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት በሱዳኑ ግጭት መጀመርያ ቀናት በፕሬዝዳንታዊ ጽሕፈት ቤቱ ላይ በፈጸመው ጥቃት የአገሪቱን ወታደራዊ መሪ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንን ለመግደል ወይም እጃቸውን ለመያዝ ተቃርቦ እንደነበር ሮይተርስ ዘግቧል። ጀኔራል ቡርሃንም ክላሽንኮቭ አንስተው እንደተዋጉና በጥቂት ቀናቶች ውጊያ ከ30 በላይ የጀኔራል ቡርሃን የግል ጠባቂዎች እንደተገደሉ ከግል ጠባቂዎቻቸው መስማቱን ዜና ምንጩ ጠቅሷል። የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ተዋጊዎች ባኹኑ ወቅት የአገር ውስጥ ጉዳይ፣ የፖሊስ መስሪያ ቤቱን እና ሌሎች ተቋማትን ሕንጻዎች ተቆጣጥረውና የካርቱም መውጫና መግቢያ መንገዶች ላይ ኬላዎችን አቁመው ቁጥጥር በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ሮይተርስ ጨምሮ ዘግቧል።

4፤ የዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፌሊክስ ቲሽስኬዴ በምሥራቃዊ ኮንጎ የሠፈረውን የምሥራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጦር አፈጻጸም ክፉኛ መተቸታቸውን የፈረንሳዩ ዜና ወኪል ዘግቧል። በቀጠናዊው ጦር እና በኮንጎ አማጺያን መካከል "መቻቻል ይታያል" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ባሁኑ ወቅት የቀጠናው ጦር እና አማጺው "ኤም-23" ባንድ ላይ እየኖሩ ነው ማለት ይቻላል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። የቀጠናው ጦር በሰኔ ከኮንጎ ሊወጣ እንደሚችልም ፕሬዝዳንቱ ፍንጭ ሰጥተዋል ተብሏል። ካለፈው ኅዳር እስከ መጋቢት፣ ኬንያ፣ ቡሩንዲ፣ ኡጋንዳና ደቡብ ሱዳን ከአገሪቱ መንግሥት ጋር ወግነው አማጺዎችን ለመውጋት በምሥራቅ ኮንጎ ወታደሮቻቸውን ማስፈራቸው ይታወሳል። የደቡባዊ አፍሪካ ቀጠናዊ ማኅበረሰብ መሪዎች የቀጠናውን ጦር ለተመሳሳይ ተልዕኮ በምሥራቅ ኮንጎ ለማስፈር ሰሞኑን መወሰናቸው ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
3.3K views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 22:27:07
ሌብነት ባልጠበቅነው መልኩ ባህሪውን እየቀያየረ ብዙዎችን እያከሰረ ነው
የዛሬውን የአንድ ነጋዴ ገጠመኝ አንብቡት
."ዛሬ ሱቄ ኣንድ ሰው ሞባይል ሊገዛ ይመጣል እናም ሲመጣ የቤት መኪና ፣ ህፃን ልጁንና ለመውለድ የተቃረበች ሚስቱን ይዞ ነበር ....... እናም ሚስቱን መኪናው ውስጥ ኣስቀምጧት ህፃን ልጁን ይዞ ወደ ሱቄ ይገባና #iphone14  ስልክ ኣሳየኝ ብሎኝ ካሳየሁት በኃላ ዋጋውን ሲጠይቀኝ 165ሺ ኣልኩት እሱም እባክህ ሚስቴ ስላማራት ነው ቀንስልኝ ሲለኝ እሺ ብዬ 2ሺ ብር ስቀንስለት ተስማማን..............  ከዛም ባለቤቴን ከለር ላስመርጣት ብሎ ሶስት የተለያዩ ከለር ያላቸውን iphone 14 ስልኮች ልጁን ሱቄ ጥሎ ይዞ ወጣ............. ያው እኔም ልጁን እዛው ስለተውና እርጉዝ ሴት ስላየው ይመለሳል በሚል እሳቤ ሰጥቼው ትኩረቴን ሌሎች ደንበኞች ላይ ኣደረኩኝ............. ከዛም ብጠብቅ ምንም የለም  ወጣ ብዬ ስመለከትም መኪናዋም እነሱም የሉም ..............ከዛ ወደሱቅ ተመልሼ ፈላውን ስጠይቀው ከጎዳና ላይ ጠዋት ኣንስተውት ልብስ ገዝተውለት ፤ ፀጉሩን ኣሰሰተካክለው ፤ ገላውን ምናምን ኣጥበው እንዳመጡት ነገረኝ ማለት ነው" 165K * 3 = 495 ሺ አነደዱኝ ማለት ነው።
ከእኔ ተማሩ ለጥንቃቄ ይህንን መልዕክቴን #ሼር አድርጉ ተብላቹሃል።

ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
3.6K viewsedited  19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:08:38 ረቡዕ ምሽት!ግንቦት 2/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌደሬሽን (ኢሠማኮ) በሠራተኞች ጥያቄዎች ዙሪያ ከጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ጋር ለመወያየት ጥያቄ ማቅረቡን ሪፖርተር ዘግቧል። ኢሠማኮ፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ለመጣው የሠራተኛው የኑሮ ኹኔታ መፍትሄ ለመፈለግ "ብቸኛው አማራጭ ጠቅላይ ሚንስትሩን ማነጋገር ነው" ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። ኢሠማኮ፣ የሠራተኞች የደመወዝ ግብር እንዲቀነስ፣ ከታክስ ነጻ የደመወዝ ወለል ከ600 ብር ከፍ እንዲልና አነስተኛ የምግብ ፍጆታዎች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲኾኑ ለገንዘብ ሚንስቴር ደብዳቤ መጻፉም በዘገባው ተመልክቷል። ኢሠማኮ በዓለም ወዛደሮች ቀን ላይ የሠራተኞችን ጥያቄ ለማስተጋባት የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ አስተዳደር እንዳገደው መግለጡ ይታወሳል።

2፤ ምርጫ ቦርድ በትግራይና ምርጫ ባልተካሄደባቸው የሌሎች ክልሎች አካባቢዎች ለሕዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች ምርጫ ለማካሄድ ለመንግሥት የበጀት ጥያቄ አቅርቤያለሁ ማለቱን ሪፖርተር ዘግቧል። ቦርዱ ከትግራይ በተጨማሪ፣ በኦሮሚያ፣ አማራና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ለክልል እና ፌደራል ምክር ቤቶች ምርጫ ባልተካሄደባቸው የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች በቀጣዩ ዓመት ምርጫ ለማካሄድ መወሰኑን መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ቦርዱ በተጠቀሱት ክልሎች በሚገኙ ምርጫ ክልሎች በአገራዊው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት ምርጫ ሳያካሂድ የቀረው፣ በጸጥታ መጓደልና በፖለቲካዊ ምክንያቶች እንደነበር በወቅቱ መግለጡ ይታወሳል።

3፤ መንግሥት "በሽብር ወንጀል" እፈልጋቸዋለኹ ያላቸው አንጋፋው ተቃዋሚ ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው ክስ ከተመሠረተብኝ ክሱን ለመከላከል ከአሜሪካ "ወደ አገር ቤት እመለሳለኹ" ማለታቸውን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ልደቱ እስከ ትናንት ድረስ ክስ እንዳልተመሠረተባቸው ከጠበቃዬ ተረድቻለኹ ማለታቸውን የጠቀሰው ዘገባው፣ ባኹኑ ወቅት አሜሪካ ውስጥ የሕክምና ክትትል ላይ እንደኾኑ መግለጣቸውን ጠቅሷል። ልደቱ፣ መንግሥት የሽብር ክስ ሊመሠርትብኝ የፈለገው በፍራቻ ወደ አገሬ እንዳልመለስ ለማድረግ ነው ማለታቸውንም ዘገባው ጨምሮ አመልክቷል። የጸጥታና ደኅንነት ግብረ ኃይል፣ በውጭ የሚገኙ ተጠርጣሪዎችን ከዓለማቀፉ የፖሊስ ተቋም ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረት አደርጋለኹ ማለቱ ይታወሳል።

4፤ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከጅቡቲ ተያዘ የተባለውን የበይነ መረብ ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይን ጨምሮ በስድስት የሽብር ወንጀል ተጠርጣሪዎች ላይ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት መፍቀዱን "ኢትዮጵያ ኢንሳይደር" ዘግቧል። ችሎቱ የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ያደረገው፣ መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ባስተባበሩት "የሽብር ድርጊት በርካታ ንጹሃን ዜጎች እንዲሞቱና ንብረት እንዲወድም ኾኗል" በማለት ያቀረበውን አቤቱታ ግምት ውስጥ በማስገባት እንደኾነ ዘገባው ጠቅሷል።

5፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት በካርቱም ተከታይ የአየር ድብደባ መፈጸሙንና ውጊያው ተባብሶ መቀጠሉን የውጭ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት፣ የሱዳን አየር ኃይል በፕሬዝዳንታዊ ጽሕፈት ቤቱ ላይ የአየር ድብደባ ፈጽሟል በማለት ከሷል። በከተማዋ ሕግና ሥርዓት መፍረሱንና ዝርፊያ መንሠራፋቱንም የተለያዩ የዜና ምንጮች አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ጣይብ ኤርዶጋን አገራቸው በተፋላሚ ወገኖች መካከል የሚካሄድ ኹሉን ዓቀፍ ንግግር ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኗን ለሱዳን ጦር ሠራዊት ዋና አዛዥ ጀኔራል ቡርሃን በስልክ እንደገለጡላቸው ተዘግቧል። ኹለቱ ተፋላሚ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ መስመሮችን ስለመክፈት ቅዳሜ'ለት ጅዳ ውስጥ የጀመሩት ንግግር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ አልተቋጨም።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2086 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2928 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ3068 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ6129 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ5048 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ60 ብር ከ6949 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
3.7K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 07:16:52 ረቡዕ ጠዋት! ግንቦት 2/2015 ዓ.ም የEMS ዋናዋና ዜናዎች

1፤ ሕገመንንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመገልበጥ አሲረዋል ተብለው በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ ትናንት መርማሪ ፓሊስ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 14 ተጨማሪ ቀናት እንዲሰጠው መጠየቁን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በበኩላቸው፣ መርማሪ ፖሊስ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያቀረበውን ምክንያት ደግሞ አቅርቦታል በማለት፣ ችሎቱ ጥያቄውን እንዳይቀበል እንዲኹም የጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ክስ በመገናኛ ብዙኀን አዋጅ መሠረት እንዲታይ እንደጠየቁ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ችሎቱ ግራ ቀኙን መርምሮ ዛሬ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል። ትናንት ችሎት ከቀረቡት መካከል፣ ጅቡቲ ላይ ተያዘ የተባለው የበይነ መረብ ጋዜጠኛው ጎበዜ ሲሳይ እና ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው ይገኙበታል።

2፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት እስካለፈው ሰኞ 15 ሺህ ከሱዳኑ ግጭት የሸሹ ሰዎች በመተማ በኩል ኢትዮጵያ መግባታቸውን በትዊተር ገጹ አስታውቋል። ድርጅቱ ወደ ኢትዮጵያ ለሚገቡ ሰዎች የተለያዩ ድጋፎችን እየሰጠ መኾኑን ገልጦ፣ ድጋፉን አጠናክሮ ለመቀጠል ግን ተጨማሪ የገንዘብ ዕርዳታ እንደሚፈልግ ገልጧል። ከሱዳን በመተማ በኩል የሚገቡት፣ ኢትዮጵያዊያን ተመላሾች፣ ሱዳናዊያን ስደተኞችና የሌሎች አገራት ዜጎች እንደኾኑ ድርጅቱ ቀደም ሲል ማስታወቁ ይታወሳል።

3፤ የሳፋሪኮም ኩባንያ የሞባይል መገበያያ ዘዴ "ኤምፔሳ" ገንዘብ ላኪዎች ስማቸውንና ስልክ ቁጥራቸውን ከገንዘብ ተቀባዩ እንዲደብቁ የሚያስችል አሠራር ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የኬንያው ቢዝነስ ደይሊ ድረገጽ ዘግቧል። ኩባንያው አዲሱን አሠራር የጀመረው፣ በ"ኤምፔሳ" ላይ የሚፈጸሙ የዲጂታል ማጨበርበርና የግል መረጃ ሥርቆት ወንጀሎችን ለመከላከል እንደኾነ መግለጡን ዘገባው አመልክቷል። ኾኖም የአዲሱ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ተጨማሪ የገንዘብ መላኪያ ታሪፍ እንደሚከፍሉ ተገልጧል። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ፣ "ኤምፔሳ" ኢትዮጵያ ውስጥ አገልግሎቱን እንዲጀምር በቅርቡ ፍቃድ እንደሚሰጥ ባለፈው ሳምንት መናገራቸው ይታወሳል።

4፤ ዓለማቀፉ የፍልሰት ድርጅት ሱማሊያ ውስጥ በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ ለሚያልፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ አፍሪካዊያን ፍልሰተኞች ከሰኔ በፊት 3 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ እንደሚያስፈልገው ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፉን ካላገኘ፣ በሱማሊያ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት ለሚሻገሩ በዓመት 50 ሺህ ያህል ፍልሰተኞች የምግብ፣ ሕክምናና ሕይወት አድን ድጋፎችን መስጠት እንደማይችልና ቦሳሶ እና ሐርጌሳ የሚገኙ ማዕከሎቹንም ለመዝጋት እንደሚገደድ ገልጧል። በሱማሊያ በኩል ወደ ባሕረ ሰላጤው አገራት የሚሻገሩት ሕገወጥ ፍልሰተኞች አብዛኞቹ ኢትዮጵያዊያን ናቸው።

5፤ የሱማሊያዋ ፑንትላንድ ወታደሮች "ደመወዝ አልከፈለንም" በማለት በራስ ገዟ መንግሥት ላይ ማደማቸውን ጋሮዌ ድረገጽ ዘግቧል። አድመኞቹ ወታደሮች የፑንትላንድ ዋና ከተማ ጋሮዌን መውጫና መግቢያ ከፊል መንገዶችንና ጋሮዌን ከቦሳሶ ወደብ ጋር የሚያገናኘውን አውራ ጎዳና መዝጋታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ወታደሮቹ አድማ የመቱት፣ የሥልጣን ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት የራስ ገዟ ፕሬዝዳንት አብዱላሂ ደኒ ከአካባቢ ምርጫና ከሕገመንግሥታዊ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ከተቃዋሚ ፖለቲከኞችና ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ከፍተኛ ውጥረት በገቡበት ወቅት ላይ ነው። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.1K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:22:24 ማክሰኞ ምሽት! ግንቦት 1/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በክልሉ የሚካሄደውን ግጭት በድርድርና በሰላማዊ አማራጭ ለመፍታት ዝግጁ መኾኑን ዛሬ የክልሉ ኮምንኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ መናገራቸውን ዶይቸቨለ ዘግቧል። ኾኖም የቢሮ ኃላፊው፣ ታንዛኒያ ውስጥ በፌደራል መንግሥቱ እና በአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት መካከል በቅርቡ ስለተካሄደው የመጀመሪያ ዙር የፊት ለፊት ድርድር ሂደትና ውጤቱ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ቀጥተኛ መልስ ሳይሰጡ እንደቀሩ ዘገባው ጠቅሷል። ኹለቱ ወገኖች ቀጣይ ድርድር በማድረግ አስፈላጊነት ላይ እንደተስማሙ መግለጣቸው ይታወሳል። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የመንግሥት ጦር ትናንት በምዕራብ እና ምሥራቅ ሸዋ በኩል አዲስ ጥቃት ከፍቶብኛል ሲል ዛሬ ማለዳ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

2፤ ኢትዮጵያ የኬንያን የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት በመሳብ ከምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ኡጋንዳንና ታንዛኒያን በመብለጥ ቀዳሚውን ደረጃ መያዟን ደይሊ ኔሽን አስነብቧል። ከአንድ ዓመት በፊት በነበረው መረጃ፣ የኬንያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ገበያ ያፈሰሱት ሙዓለ ንዋይ ከ600 ሚሊየን ዶላር በላይ ደርሶ እንደነበር ዘገባው ጠቅሷል። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና የኬንያ ኩባንያዎች ቀጥተኛ የውጭ ኢንቨስትመንት መዳረሻ በመኾን ታንዛኒያ ቀዳሚዋ እንደነበረች ዘገባው አመልክቷል። ኢትዮጵያ የኬንያ ኩባንያዎች ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት መዳረሻ በመኾን የቀዳሚነቱን ደረጃ የያዘችው፣ የኬንያው ሳፋሪኮም የቴሌኮም ኩባንያ በኢትዮጵያ ሙዓለ ንዋዩን ማፍሰስ ከጀመረ ወዲህ ነው።

3፤ የግብጽ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሳሜ ሽኩሪ ዛሬ ጁባ መግባታቸውን የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል። ሽኩሪ ጁባ የገቡት፣ የሱዳኑን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ከሱዳን ጎረቤት አገራት የሰላም ጥረቶችን ለማስተባበር እንደኾነ ሚንስቴሩ ገልጧል። ሽኩሪ ለሱዳኑ ግጭት መፍትሄ በማፈላለግ ዙሪያ፣ ከደቡብ ሱዳኑ አቻቸው እንዲኹም ከአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ይወያያሉ ተብሏል።

4፤ በሱዳኑ ግጭት ሳቢያ ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ወደ 700 ሺህ ማሻቀቡን ዓለማቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት ዛሬ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል። እስካለፈው ሳምንት ድረስ በግጭቱ የተፈናቀሉ ተፈናቃዮች ብዛት 334 ሺህ ገደማ የነበረ ሲኾን፣ ባለፉት ጥቂት ቀናት ግን ውጊያው ጋብ ማለቱን ተከትሎ በርካቶች የውጊያ ቀጠና ከኾኑ ቀየዎቻቸው እንደለቀቁ ተገልጧል። ከ100 ሺህ በላይ ሱዳናዊያን ደሞ ወደ ጎረቤት አገራት በተለይም ወደ ደቡብ ሱዳን፣ ቻድና ግብጽ እንደተሰደዱ ድርጅቱ በሪፖርቱ ጠቅሷል። ተፋላሚዎቹ የሰብዓዊ ዕርዳታ መተላለፊያ መስመሮችን ለመክፈት ጅዳ ውስጥ ቅዳሜ'ለት የጀመሩት ንግግር እንደቀጠለ ሲኾን፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ንግግሩ ምን ውጤት እንዳስገኘ የታወቀ ነገር የለም።

5፤ በደቡባዊ ኬንያ ፖል ማካንዚ የተባለ የፕሮቴስታንት ሰባኪ "እየሱስ ክርስቶስን ለመገናኘት ራሳቸውን አስርበው እንዲሞቱ" ካደረጋቸው ከመቶ በላይ ተከታዮቹ የተወሰኑ አስከሬኖች ላይ አንዳንድ የሰውነት ክፍሎች እንደተወሰዱ በምርመራ መረጋገጡን የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስትሩ ኪቱሪ ኩንዲኪ ድርጊቱን "በከፍተኛ ደረጃ የተደራጀ ወንጀል" በማለት እንደፈረጁት የጠቀሱት ዘገባዎቹ፣ ዛሬን ጨምሮ የሰባኪው ቤተክርስቲያን በሚገኝበት ጫካ በተደረገ አሰሳ 133 አስከሬኖች በጅምላ መቃብሮች ውስጥ እንደተገኙ አመልክተዋል። መርማሪ ፖሊስ፣ ድርጊቱ ከሰውነት ክፍሎች ንግድ ጋር የተያያዘና በርካታ ተዋናዮች የተሳተፉበት ወንጀል ሳይኾን እንደማይቀር መግለጡና፣ በሰባኪው ላይ የ"ሽብር ወንጀል" ክስ እመሠርታለኹ ማለቱ ተገልጧል። መንግሥት ወንጀሉን የሚመረምር ገለልተኛ ኮሚሽን አቋቁሟል።

6፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ2048 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2889 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ5404 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ8512 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ8855 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ0832 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.1K views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 07:36:30 ማክሰኞ ጠዋት! ግንቦት 1/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የመንግሥት ጦር ሠራዊት በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ላይ በሁለት ግንባሮች ትናንት ማለዳ ላይ አዲስ ጥቃት ከፍቷል ሲሉ የቡድኑ ቃል አቀባይ ኦዳ ታርቢ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል። የመንግሥት ጦር በቡድኑ ላይ ጥቃት የከፈተው፣ በምዕራብ ሸዋ ዞን ጀልዱ እና በምሥራቅ ሸዋ ዞን አዳሚ ቱሉ በኩል መኾኑን ቃል አቀባዩ ገልጸዋል። ቃል አቀባይ ኦዳ ታርቢ ጨምረውም፣ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ተዋጊዎች ጥቃትቱን መክተዋል ብለዋል። በመንግስት በኩል ስለጉዳዩ የተባለ ነገር የለም:: በኦሮሞ ነጻነት ሠራዊትና በመንግስት በኩል በታንዛንያ ድርድር ተደርጎ ያለስምምነት የተቋጨው ባለፈው ሳምንት ነበር።

2፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እና የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በታንዛኒያዋ ዛንዚባር ውስጥ ያደረጉት የመጀመሪያ ዙር ድርድር ያለ ውጤት የተበተነው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ማዕቀፍ ስር ለመነጋገር ፍቃደኛ ባለመኾኑ እንደኾነ ከምንጮች መስማቱን ጠቅሶ ሪፖርተር ዘግቧል። የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ድርድሩ ሁሉንም ፖለቲካዊ ልዩነቶች በሚፈታ መንገድ ያለ ገደብ መካሄድ አለበት የሚል አቋም ስለማንጸባረቁ ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። ባንጻሩ መንግሥት ድርድሩ በአገሪቱ ሕገ መንግሥት ማዕቀፍ ስርና ሁለቱ ወገኖች ብቻ በባለቤትነት የሚይዙት መኾን አለበት የሚል አቋም ይዞ ነበር ተብሏል። የሁለቱ ወገኖች ድርድር ያተኮረው፣ ድርድሩ ወደፊት በሚመራበት ማዕቀፍ ዙሪያ እንደነበር ዘገባው ጠቅሷል።

3፤ ሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ጅዳ ውስጥ እያደረጉት የሚገኙት ንግግር አወንታዊ ርምጃ እንዳልታየበት ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች የሳዑዲ ዲፕሎማቶችን ጠቅሰው ዘግበዋል። ሁለቱም ተፋላሚ ወገኖች ውጊያውን እናሸንፋለን የሚል እምነት እንዳላቸው ምንጮች መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ሁለቱ ወገኖች የሰብዓዊ ዕርዳታ መስመሮችን ማስከፈት ዓላማው ያደረገ ተኩስ አቁም ማድረግ በሚቻልበት ኹኔታ ዙሪያ ስምምነት ላይ ለመድረስ በአሜሪካና ሳዑዲ ዓረቢያ አስተባባሪነት ቅዳሜ'ለት የጀመሩት ንግግር፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ አልተጠናቀቀም።

4፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ ቡርሃን "ካርቱም ላይ ዘላቂ ተኩስ አቁም ካልተደረገ በስተቀር ጅዳ ላይ እየተደረገ ያለው የአገሪቱ ተፋላሚ ወገኖች ንግግር ፋይዳ የለውም" በማለት ባንድ ቃለ ምልልስ ላይ መናገራቸውን የሱዳን ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኾኖም ቡርሃን ፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ከመንግሥታዊ ተቋማትና ከሲቪሎች መኖሪያዎች ለቆ ከወጣ፣ ችግሩን በፖለቲካዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ መኾናቸውን ገልጸዋል ተብሏል። የፈጥኖ ደራሹ ሠራዊት ከተቋማትና ሲቪል ሠፈሮች መውጣት፣ ለተኩስ አቁም ቅድመ ሁኔታ መኾኑን ቡርሃን መግለጣቸው ተነግሯል። ቡርሃን ካርቱም ውስጥ ክፍፍሎች ከተፈጠሩ፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርስ ጦርነት ሊቀጣጠል ይችላል በማለት ማስጠንቀቃቸውም ተዘግቧል።

5፤ ቀጠናዊው የደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ አባል አገራት የመሪዎች ጉባኤ በምሥራቅ ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ የቀጠናው የተውጣጣ ሠራዊት ለማሠማራት የሚያስችለውን ውሳኔ ትናንት አሳልፏል። የኮንጎ መንግሥት እና ዋናው አማጺ ቡድን "ኤም-23" መካከል ያገረሸው ግጭት ተባብሶ እንደቀጠለ ነው። ውሳኔውን ከደገፉት የቀጠናዊው ማኅበረሰብ አባል አገራት መካከል፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ታንዛኒያ እና አንጎላ ይገኙበታል። ባለፉት ጥቂት ወራት፣ የምሥራቅ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ አባል አገራት ከኮንጎ መንግሥት ጋር ወግነው የሚዋጉ ወታደሮቻቸውን በቀጠናዊው ማኅበረሰብ ማዕቀፍ ስር በምሥራቅ ኮንጎ ማሠማራታቸው ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.4K views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:13:32
ቪድዮ ፦ በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፤ " የጋፋት የህዋ ምህንድስ እና ልማት ማዕከል " ከ20 ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ መጓዝ የሚችል ሮኬት አስወንጭፏል።

ዩኒቨርሲቲው " አፄ ቴዎድሮስ 2015 " የሚል ስያሜ የተሰጣትን ሮኬት ከ20 ሺህ ጫማ ከፍታ በላይ በማስወንጨፍ ስኬታማ ሙከራ ማድረጉን አሳውቋል።

" የጋፋት የህዋ ምህንድስና ልማት ማዕከል " ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ ሙክራ ያደረገ ሲሆን ይኸኛው ሙከራ ግን ከዚህ በፊት ከተደረጉ ሙከራዎች የተሻለ ምርምር የተደረገበት መሆኑን አሳውቋል።

ቪድዮ ፦ አሚኮ

#ደብረታቦር_ዩኒቨርሲቲ #አፄቴዎድሮስ2015

#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.2K viewsedited  18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 20:08:41 ሰኞ ምሽት! ሚያዝያ 30/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ የኢሰመኮ ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ በአማራ ክልል ውስጥ ባኹኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው "ወታደራዊ እንቅስቃሴ" እና "የዘፈቀደ እስሮች" አሳሳቢ ኾነዋል ሲሉ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት የኮሚሽኑ የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ላይ መግለጣቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል። በክልሉ እየተወሰደ ካለው የጸጥታ ርምጃ "በእስር ወቅት የሚደርስ ተገቢ ያልኾነ አያያዝ"፣ "በተቃውሞ ሰልፎች ላይ ጸጥታ ኃይሎች የሚወስዱት ተመጣጣኝ ያልኾነ የኃይል ርምጃ"፣ "በጋዜጠኞች፣ በሚዲያ፣ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችና ተቃዋሚ ድምጾች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት" እና "በመንቀሳቀስ መብት ላይ የተጣሉ የዘፈቀደ ገደቦች" ጭምር አሳስቢ እንደኾኑ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል። የመንግሥት ርምጃ በሰብዓዊ መብት ላይ ያለው አንድምታ የሚያሰጋ መኾኑንም ዳንኤል ጨምረው ገልጸዋል።

2፤ በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን የሐሩካ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት ከፍተኛ ሃላፊ ኡመር ለማ ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች ትናንት እንደተገደሉ በክልሉ የፓርቲው ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። ኡመር በጥይት የተገደሉት፣ ከአዳማ ወደ አዋሽ በሚወስደው መንገድ ላይ በተሽከርካሪ ሲጓዙ በተከፈተባቸው ተኩስ እንደኾነ የገለጠው ፓርቲው፣ የግድያውን ፈጻሚዎች "አሸባሪዎች" በማለት ጠርቷቸዋል። ዶይቸቨለ በበኩሉ፣ ኡመርን ከአንድ ወንድማቸው ጋር በሩምታ ተኩስ ወለንጪቲ ከተማ አካባቢ አካባቢ ልዩ ስሙ አረቦና በሚባል ቦታ የገደሏቸው 30 የሚደርሱ ታጣቂዎች እንደኾነ ከሟቹ ቤተሰቦች መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። ከጥቂት ቀናት በፊት ታጣቂዎች የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ ግርማ የሺጥላን ሰሜን ሸዋ ውስጥ መገደላቸው ይታወሳል።

3፤ ንግድ ባንክ ከነገ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ አካባቢዎች በነዳጅ ማደያዎች የ"ሲቢኢ ብር" የኤሌክትሮኒክ ክፍያ አገልግሎት እንደሚጀምር አስታውቋል። ባንኩ "ቀላልና ፈጣን" ያለውን የ"ሲቢኢ ብር" የሞባይል ስልክ መገበያያ አገልግሎት ዘዴን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማደያዎች መስጠት የጀመረው ከሚያዝያ 16 ጀምሮ ነው። የነዳጅ ደንበኞሽ፣ *847# በመደወል ወይም "ነዳጅ" የተሰኘውን ባንኩ ያበለጸገውን መተግበሪያ በሞባይል ስልካቸው ላይ በመጫን ነዳጅ መቅዳት እንደሚችሉ ባንኩ ገልጧል።

4፤ የሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች ተወካዮች በሳዑዲ ዓረቢያና አሜሪካ አስተባባሪነት ጅዳ ውስጥ ቅዳሜ'ለት የጀመሩት ንግግር፣ ለቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት እንደሚቀጥል የሳዑዲ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መግለጡን የውጭ ዜና ወኪሎች ዘግበዋል። የንግግሩ ዓላማ፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ መተላለፊያ መስመሮችን ለመክፈት የሚያስችል "የአጭር ጊዜ ተኩስ አቁም" ላይ ለመድረስ ብቻ እንደኾነ ተፋላሚዎቹ የገለጡ ሲኾን፣ ሳዑዲና አሜሪካ ግን "ለዘላቂ ተኩስ አቁም" ንግግር እንዲደረግ በመወትወት ላይ እንደኾኑ ሚንስቴሩ ገልጧል ተብሏል። በጅዳው ንግግር እየተሳተፉ ከሚገኙት መካከል፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ ጄክ ሱሊቫን ይገኙበታል። ውጊያው ግን ዛሬም እንደቀጠለ ነው።

5፤ የሱማሌላንድ ራስ ገዝ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ "የፑንትላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ታጣቂዎች የግጭት ማዕከል ከኾነችው ላስ አኖድ ከተማ እስካልወጡ ድረስ ግጭቱ አይቆምም" በማለት ለራስ ገዟ ፓርላማ መናገራቸውን የሐርጌሳ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። የሱማሌላንድ ወታደሮች ካለፉት ጥቂት ወራት ወዲህ፣ ፑንትላንድ የይገባኛል ጥያቄ በምታነሳባት የላስ አኖድ ከተማና ሱል አውራጃ የጎሳ ሚሊሻዎች ጋር ግጭት ውስጥ ናቸው። ሱማሌላንድ ግን፣ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት ሠራዊት፣ የፑንትላንድ አስተዳደርና የአልሸባብ ታጣቂዎች ተባብረው እየወጉኝ ነው ትላለች። ፑንትላንድ በበኩሏ፣ ታጣዎቿን ወደ ላስ አኖድ እንዳላስገባሽ በተደጋጋሚ አስተባብላለች።

6፤ የኡጋንዳ ሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ጫትን ከአደንዛዥ ዕጽ ተርታ የሚፈርጀው ሕግ እንደሻረው የአገሪቱ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ፍርድ ቤቱ ሕጉን የሰረዘው፣ ፓርላማው ሕጉን ያጸደቀበት ውሳኔ ምልዓተ ጉባዔ ያልተሟላበት ሕጋዊ ያልኾነ ውሳኔ ነው በማለት እንደኾነ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው፣ የአገሪቱ ጫት አምራች ገበሬዎች ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት ነው። የኡጋንዳ ፓርላማ ከሰባት ዓመታት በፊት ያጸደቀው ሕግ፣ ጫት ማምረት፣ መሸጥ፣ ማከፋፈልና መጠቀምን የሚከለክል ነበር። በምሥራቅ አፍሪካ ጫት ለውጭ ገበያ በማቅረብ የመሪነቱን ደረጃ የያዙት፣ ኢትዮጵያ እና ኬንያ ናቸው።

7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 54 ብር ከ1967 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ2806 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 65 ብር ከ0182 ሳንቲም እና መሸጫው 66 ብር ከ3186 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ59 ብር ከ9090 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ61 ብር ከ1072 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.3K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 07:19:04 ሰኞ ጠዋት! ሚያዝያ 30/2015 ዓ.ም የEMS ዐበይት ዜናዎች

1፤ ብሄራዊ ባንክ ያቋቋመው የተቀማጭ ገንዘብ መድኅን ፈንድ እስከ 200 ሺህ ብር በባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ላስቀመጡ አካላት የዋስትና ሽፋን ሊሰጥ መኾኑን ብሄራዊ ባንክ መናገሩን ሪፖርተር ዘግቧል። ውሳኔው አብዛኞቹን ገንዘብ አስቀማጮች ተጠቃሚ እንደሚያደርግ የጠቀሰው ባንኩ፣ ባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ለአስቀማጮች የመድኅን ዋስትና ለማስገኘት ከተቀማጭ ገንዘባቸው ውስጥ 0 ነጥብ 2 በመቶውን በየዓመቱ ለተቀማጭ ገንዘብ መድኅን ፈንድ ማስገባት እንዳለባቸው መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። ብሄራዊ ባንክ ፈንዱ እንዲቋቋም የወሰነው፣ ባንኮችና ማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት አደጋ በሚያጋጥማቸው ጊዜ ለገንዘብ አስቀማጮቻቸው ዋስትና ለመስጠት በማሰብ ነው።

2፤ የኤርትራ መንግሥት በሱዳኑ ግጭት አጣብቂኝ ውስጥ የገቡ ስደተኛ ዜጎችን በኃይል ወደ ኤርትራ እየመለሰ መኾኑን ጋርዲያን ጋዜጣ ዘግቧል። የሱዳኑ ግጭት ከተቀሰቀሰ ወዲህ፣ ባትንሹ 3 ሺህ 500 ኤርትራዊያን ስደተኞች በግዳጅ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንደተደረገ መረዳቱን ዘገባው አመልክቷል። ዜና ምንጩ ለመረጃው በምንጭነት የተጠቀመው፣ ሱዳን ውስጥ የሚገኙ ኤርትራዊያን የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን እንደኾነ ገልጧል። በሱዳን የጠረፍ ግዛቶች ከሚገኙ የተመድ ስደተኛ መጠለያዎች አካባቢ ወደ ኤርትራ ታፍነው ከተወሰዱት ስደተኞች መካከል፣ ከውትድርና አገልግሎት ያመለጡትን ጨምሮ 95ቱ መታሠራቸውን ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

3፤ የሱዳን ጦር ሠራዊት እና ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት ተወካዮች ጅዳ ውስጥ ንግግር ላይ እንደኾኑ ዓለማቀፍ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኹለቱ ወገኖች በተኩስ አቁም ላይ ለመነጋገር ጅዳ ላይ እንዲገናኙ ያስተባበሩትና ንግግሩን እየመሩት ያሉት፣ አሜሪካ እና ሳዑዲ ዓረቢያ ናቸው። ግጭቱ ከተጀመረ ወዲህ፣ ኹለቱ ተፋላሚዎች ለፊት ለፊት ንግግር ሲቀመጡ የአኹኑ የመጀመሪያቸው ነው። ኾኖም የንግግሩ ሂደት ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ፣ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የታወቀ ነገር የለም። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ግጭቱ በካርቱምና ሌሎች አካባቢዎች ተባብሶ እንደቀጠለ ነው።

4፤ በደቡብ ሱዳን የተመድ ተቆጣጣሪ ቡድን አገሪቱ ጸጥታው ምክር ቤቱ የጣለባትን የጦር መሳሪያ ግዢ ማዕቀብ በመጣስ የተለያዩ አዳዲስ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን ሳትገዛ አልቀረችም በማለት ከሷል። ቡድኑ ክሱን ያቀረበው፣ ደቡብ ሱዳን በምስራቅ አፍሪካ ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ጥላ ስር በምሥራቃዊ ዲሞክራሲያዊት ኮንጎ ካዘመተቻቸው ሰላም አስከባሪዎች ጋር የላከቻቸውን 10 አዳዲስ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች በማየት እንደኾነ ገልጧል። ኾኖም ቡድኑ አዲሶቹ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች የት እንደተገዙ ገና እንዳላወቀ አመልክቷል። የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በአገሪቱ ላይ የጦር መሳሪያ ግዢ ማዕቀብ የጣለው ክ5 ዓመት በፊት ነበር። #ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.7K viewsedited  04:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 00:29:14
ሀሰት ነው ተባለ

#ሼር በማድረግ ተባበሩን


ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ

                                  
@emsmereja
4.6K viewsedited  21:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ