Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zephilosophy — ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zephilosophy — ፍልስፍና ለነፃ አስተሳሰብ
የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.92K
የሰርጥ መግለጫ

"Strong minds discuss ideas, average minds discuss events, weak minds discuss people."
Rinu Ruzvelt

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-28 08:51:42 ከፍቅር ወደ አፍቃሪነት.......2

ምንጭ ፦ ነፃነት (ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ ዘላለም ንጉሴ

መፈለግ (መውደድ) ከሰዎች ታላላቅ ፍላጎቶች አንዱ ነው:: ስለዚህ ፍቅር ህልውናን ይዞ ይኖራል። የሰው ልጆች እስካሉ ድረስ የፍቅርን ያህል ትልቅ ነገር አያገኙም፡፡ በምድር ላይ የሚገኝ ግን የምድር ያልሆነ ነገር ነው:: በፀሐይ ፊት እንደንስር የምትበሩበት ክንፍ ይሰጣችኋል።

ያለ ፍቅር አክናፋት አይኖሯችሁም፡፡ እጅጉን አስፈላጊ የመንፈስ ምግብና ተፈላጊ ነገር ከመሆኑ የተነሳ በዙሪያው ችግሮች ይከቡታል፡፡ ፍቅረኛህ ወይንም ፍቅረኛሽን ነገር የራስህ /ሽ/ ማድረግ ትፈልጋላችሁ ዛሬ ውብ ነገር አሳልፋችኋል፣ ለነገ ደግሞ ትጨነቃላችሁ፡፡ ስለዚህ ትዳር ይመጣል። ፍቅረኛችን ነገ እንዳትከዳን ስለምንፈራ በማህበረሰብና በሕግ ፊት ውል እንፈርማለን። ፍፁም አስቀያሚና ዘግናኝ ነገር ነው:: ፍቅርን ወደ ውል መለወጥ፣ ህግን ከፍቅር ማስቀደም ማለት፣ ማህበረሰብን ከራስህ ህልውና ማስቀደም ማለት ነው፡፡ የፍርድ ቤቶችን የጦር ሠራዊቱን፣ የፖሊሲንና የዳኞችን ከለላ በመሻት ጥምረታችሁን የተረጋገጠ ለማድረግ መጣር ማለት ነው:: ነገ ጠዋት ማንም አያውቅም፡፡ ፍቅር እንደነፋስ ሽውታ ሆኖ ይመጣል። ድጋሚ ታገኘው ይሆናል፣ ፈጽሞ ላይመጣም ይችላል። ሳይመጣ ከቀረ በህግና በትዳር የተነሳ ብቻ፣ በማህበረሰብ ክብር ከመጨነቅ የተነሳ ብቻ፣ በዓለም ዙሪያ ያሉት ጥንዶች ሕይወት ሁሉ ማለት ይቻላል፣ ወደ ወሲብ ንግድ ይለወጣል።

ከፍቅር በስተቀር በሌላ በማንኛውም ምክንያት፣ ለደህንነት ወይንም የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት ተብሎ ከማትወዳት ሴት ጋር መኖር፣ ከማታውቂው ወንድ ጋር መኖር ኑሯችሁን የወሲብ ንግድ ያደርገዋል፡ የወሲብ ንግድ ከዓለም ሙሉ ለሙሉ እንዲጠፋ እፈልጋለሁ፡፡ ኃይማኖቶች ሁሉ የወሲብ ንግድ መኖር የለበትም ይላሉ፡፡ የሰው ልጅ አይረቤነት የሚታየው ይህን በመሳሰሉ ሁኔታዎች ላይ ነው።

ከእምነት ማጣት ውስጥ ፍቅርን የሚያበለጽግና የሚያሳድግ ምንም ነገር የለም፡፡ ከነአካቴው ያጠፋዋል። አፍቅር ግን ሁለተኛ አታጥፋው፡፡ ፍቅር ትክክለኛ የሚሆነው ነፃነትን ሲያጎናፅፍ ብቻ ነው::

ቅድመ ሁኔታው ይህ ይሁን። እውነተኛ ፍቅር የሚባለው የሌላውን ሰው ነፃነት የማይጋፋ ከሆነ ነው:: የሌላውን ሰው የግል ኑሮና ማንነቱን ያከብራል፡፡ ዳሩ ግን በዓለም ዙሪያ የምናያቸው ፍቅረኞች ጥረት ግን ምንም ነገር የግል መሆን የለበትም የሚል ነው፣ ሁሉም ምስጢሮች ሊነገራቸው ይገባል። ግላዊነትን ይጠላሉ፣ ይፈራሉ፡፡ አንዳቸው የሌላቸውን ማንነት ያጠፋሉ፣ ይህን በማድረጋቸውም ሕይወታቸው ርካታና ደስታ የተሞላበት አንደሚሆን ያስባሉ፡፡ ሰቀቀናቸው እለት እለት እየጨመረ ይመጣል::

አፍቃሪ ሁን፤ እውነተኛ ሆነ ማንኛውም ነገርም ዘወትር እንደሚለዋወጥ አስታውስ፡፡ ትክክለኛ ፍቅር ዘለዓለም ይኖራል የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ ተቀብለህ ሊሆን ይችላል። ትክክለኛ ጽጌሬዳ አበባ ዘለዓለም አትኖርም፡፡ ህያው ፍጥረት እንኳን አንድ ቀን መሞት ይኖርበታል። ሕልውና የማያቋርጥ ለውጥ ነው፡፡ ፍቅር ዘለዓለም ይኖራል የሚለው ሀሳብ እውነት ቢሆን ኖሮ  ፍቅር አንድ ቀን ቢጠፋ የምንደርስበት ምክንያታዊ ድምዳሜ፣ እውነተኛ ፍቅር አልነበረም የሚል ይሆናል፡፡

እውነተኛ ፍቅር በድንገት የሚይዝህ አንተ ስለጣርክ አይደለም:: በቃ ተፈጥሮ ስጦታ ነች:: ሲመጣ ግን አንድ ቀን እንዳመጣጡ ይሄዳል ብለህ ብትጨነቅ ኖሮ ከነአካቴው ባልተቀበልከው ነበር፡፡ ግን የሚያስጨንቅ ነገር የለም:: ምክንያቱም አንድ አበባ ሲከስም ሌላ አበባ ይፈነዳል።

ካልሆነ ግን ብዙም ሳትቆይ የሞተና የረገፈ አበባ ላይ ሙጥኝ ብለህ ትቀራለህ፡፡ እውነታውም ይኸው ነው። ሰዎች በአንድ ወቅት ህያው የነበረ የሞት ፍቅርን የሙጥኝ ብለው ይታያሉ:: አሁን ወደ ትዝታና ስቃይ ተለውጧል፡፡ ለክብርና ለህግ ካለህ ጭንቀት የተነሳም ታስረህ ትቀራለህ።

ካርል ማርክስ ለዚህ ትክክለኛውን ሀሳብ አቅርቧል፣ ይህም በኮሚኒውዝም ስርዓት ውስጥ ምንም አይነት ትዳር አይኖርም፡፡ ሩሲያ ውስጥ አብዮቱ ከፈነዳ በኋላም፣ በመጀመሪያዎቹ አራት አምስት ዓመታት ውስጥ ፍቅርን ነፃነት ለማድረግ ሞክረዋል። ግን የካርል ማርክስ ጽንሰ ሀሳብ ወደ ተግባር ሲለወጥ ችግር ተፈጠረ ምክንያቱም ትዳር ከሌለ ቤተሰብ ይጠፋል፡፡ ቤተስብ ከጠፋ ደግሞ የማህበረሰቡና የህዝቡ /ሀገር/ የጀርባ አጥንትና መሠረት ነው፡፡ ቤተሰብ ከጠፋ ሀገርም መጥፋቱ አይቀርም፡፡
ከአብዮቱ እውን መሆን ከአምስት ዓመታት በኋላ የሩሲያ ኮሚውኒስት ፓርቲ ይህን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ለወጠው። ትዳር ዳግመኛ ድጋፍን አገኘ፡፡ ፍቺ ተፈቅዶ ግን መፋታት እጅግ ከባድ ሆነ፡፡ ምክንያቱም ቤተሰቡ እንዳለ መቆየት ይችላል የሀገሪቱን አንድነት ለማጠናከርም ይረዳል:: ያለ ሀገር ፖለቲከኞችም ሆኑ መንግሥት ሊኖር አይችልም። ትዳር የመጣው የግል ንብረት ከሚለው ሀሳብ ጋር ተያየዞ ነው የሚለውን የማርክስን ሀሳብ አላነሱም፡፡ ምክንያቱም የግል ንብረት ሲጠፋ ትዳርም አንድ ላይ ይጠፋል:: ከዚያ በኋላ አልተነጋገሩበትም፡፡

ዓለም ወደ ብዙ አካላት እንድትከፋፈል አልፈልግም። ነፃ ግለሰቦች በራሱ ጊዜ በሚቀጣጠል ፍቅር ውስጥ፣ በፀጥታና በደስታ የሚኖሩባት አንድ ዓለም እንድትፈጠር እፈልጋለሁ፡፡ ገነትን እዚሁ መፍጠር እንችላለን፡፡ ገነትን ለመፍጠር የሚያስፈልገን እምቅ ሀይል ሁሉ ቢኖረንም እየተጠቀምንበት አይደለም፡፡ በተቃራኒው ግን ብዙ እንቅፋቶችን እየፈጠርን እንገኛለን።

እኔ የፍቅር ተፃራሪ አይደለሁም፡፡ ፍቅርን እጅግ እደግፈዋለሁ፡፡ ሁለት ሰዎች ሕይወታቸውን ሙሉ አብረው ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ መለያየት አለባችሁ ማለት ሳይሆን፣ ይህን አብሮ መኖር የሚመሠረተው ፍቅር ላይ ብቻ መሆንና የሌላውን ግላዊ ሕይወትና ነፍስ በማይነካ ነፃነቱን በሚጠብቅ ሁኔታ መሆን አለበት፡፡ ይህ የሌላው ሰው ክብር ነው።

አፍቃሪ መሆን ትችላለህ፣ ፍቅር መሆን ትችላለህ:: አፍቃሪ ብቻ ከሆንክ ፍቅርን ራሱን ብቻ ከሆንክ፣ ፍቅር ወደ ጥላቻ የሚለወጥበትን ምንም ዓይነት እድል አትሰጠውም፡፡ ተስፋ የምትጥልበት ነገር ስለማይኖር ድንገተኛ ነገር ሊረብሽህ አይችልም፡፡ ስለፍቅር የምንናገረው ግን በመንፈሳዊ ክስተትነቱ እንጂ ከስነ-ተፈጥሮ አንፃር አይደለም፡፡ ስነ ፍጥረት ሴሰኝነትን እንጂ ፍቅር አይደለም፡፡ የስነ-ፍጥረት ዓላማ ዘርን መተካት ሲሆን፣ የፍቅር ሀሳብ ስነ-ተፈጥሯዊ ብቻ ነው፡፡ ሰው ተራክቦ ከፈፀመ በኋላ ቢያንስ ለሚቀጥሉት ሃያ አራት ሰዓታት ፍቅረኛው እንደማትፈልገው ይሰማዋል፡፡ ይህ ደግሞ ከእድሜ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ እድሜህ እየገፋ ሲሄድ ጊዜው አርባ ስምንት ሰአት፣ ወደ ሰባ ሁለት ሰአት... እያለ ይቀጥላል።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.5K viewsedited  05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-28 08:51:09 ከፍቅር ወደ አፍቃሪነት...........1

ምንጭ ፦ ነፃነት (ኦሾ)
ተርጓሚ ፦ ዘላለም ንጉሴ

ፍቅር  ሁለት ፍፁም የተለያዩ እንደውም ሙሉ ለሙሉ ተቃራኒ ትርጉሞች ሊኖሩት ይችላሉ፡፡ አንዱ ትርጉም ፍቅር በፍቅር ግንኙነት መልኩ ሲገለጽ እና ሌላው ደግም ፍቅር በራሱ ህልውና ይዞ ሲገኝ ነው:: ፍቅር ወደ ፍቅር ግንኙነት በሚለወጥበት ወቅት ባርነት ይሆናል:: ምክንያቱም የምንጠብቃቸውና የሚጠበቁብን ነገሮች እንዲሁም መረበሽ እና ፍርሀትን ይፈጥሩብናል፡፡ ከሁለቱም ወገንም እኔ እበልጥ ስሜት ይመጣል፡፡ የኃይል እሽቅድምድም ይሆናል:: የፍቅር ግንኙነት ትክክል አይደለም:: ፍቅር ህልውና ይዞ ሲገኝ ግን ሙሉ በሙሉ የተለየ ነገር ይሆናል፣ ስታፈቅር ከፍቅር ሌላ የፍቅር ግንኙነት እየፈጠርክ አይደለም ማለት ነው:: ፍቅርህ እንደ አበቦች ጥዑም መዓዛ ይሆናል። የፍቅር ግንኙነት አይፈጠር፣ ይህን አድርግ፣ ባህሪህ እንዲህ ይሁን አይልህም:: ከአንተ ምንም አይፈልግም። ያካፍላል። በማካፈሉም ምንም ሽልማት አይፈልግም፡፡ ማካፈሉ በራሱ ሽልማት ነው፡፡

ፍቅር ለአንተ እንደ አበቦች መዓዛ በሚሆንበት ጊዜ ታላቅ ውበት ይኖረዋል ከሰብዓዊነት በላይ የመጠቀ መለኮታዊ ነገር ይኖረዋል፡፡

ፍቅር ብቻውን ከመጣብህ ምንም ልታደርገው አትችልም፡፡ በማንኛውም ሰው ላይ አሳርን አያመጣም አንተም በማንኛውም ሰው እንድትታሰር አይፈቅድም፡፡

ግን ከልጅነት አንስቶ የፍቅር ግንኙነቶችን የመፍጠር ልምድ አለህ፡፡ ከማታውቀው ወንድ ጋር የአባትና የልጅ ግንኙነት ትፈጥራለህ:: አባትህ መሆኑን በፍፁም ርግጠኛ ልትሆን አትችልም፡፡

አንድ የሰዎችን መዳፎች በመመልከት ዕጣ ፈንታቸውን ስለሚተነብይ ሰው የሰማሁት ታሪክ አለ። በእጅ መዳፍ ንባብና በአስትሮሎጂ በመሳሰሉት እንዲሁም በእግዚአብሔርም የማያምን አንድ ወጣት ወደዚሁ ሰው ይሄድና፣ ሳይንስህ ትክክል ከሆነ እጄን አንብብና አባቴ የት እንደሚገኝ ንገረኝ አለው።»

አዋቂውም መዳፉን ተመልክቶ እንዲህ አለው «አባትህ አሳ እያጠመደ ነው፡፡» ወጣቱ ኢአማኒ ሳቀ፡፡ «እኔ የምለው ይህንኑ ነው፣ የማይረባ ሥራ ነው:: አባቴ ከሞተ ሶስት ዓመት ሆኖታል፤ ዛሬ እንዴት አሳ ለማጥመድ ይሄዳል።>>

አዋቂውም ሲመልስ፣ «ይህ እኔን አያገባኝም፤ እውነቱ ግን ያ የሞተው ሰው አባትህ ያለመሆኑ ነው፡፡ ትክክለኛ አባትህ አሳ እያጠመደ ነው፡፡ ወደ እናትህ ሂድና ጠይቃት፡፡ ታማኝና እውነተኛ ከሆነች የሞተው ሰው አባትህ እንዳልሆነ ትነግርሀለች። አንተ ግን አባትህ ነው ስለተባልክ ከእሱ ጋር የአባትና የልጅ ፍቅር ግንኙነት ፈጥረሀል፡፡

ሕይወታችሁ በሙሉ በብዙ ዓይነት ግንኙነቶች የተሞላ ነው:: ይህ መሰል ግንኙነቶች ደግሞ እውነትም ይሁን ሀሰተኛ፣ እጅግ ውስብስብ የሆነ ስነልቦናዊ ባርነትን ይፈጥራል። ወይ ሌላውን ባርያ ታደርጋለህ፡፡ ወይንም ራስህ ባርያ ትሆናለህ::

ሌላው መታወስ ያለበት ነጥብ ደግም ራስህን ባርያ ሳታደርግ ሌላውን ሰው ባርያ ማድረግ አትችልም፡፡ ባርነት ባለሁለት ሶስት ሰይፍ ነው፡፡ አንደኛው የበለጠ ጠንካራ፣ ሌላው የበለጠ ደካማ ሊሆን ይችላል፤ ግን በሁሉም የፍቅር ግንኙነቶች ውስጥ አንደኛው አሳሪ ሌላው ታሳሪ ይሆናል። ከእሱ አንፃር ሲመለከተው እሱ አሳሪው አንተ ደግሞ ታሳሪ ትሆናለህ። የሰው ልጅ ይህን በመሰለ ሀዘንና ሰቆቃ የመኖሩ ዋነኛ ሀቅና ምክንያት መካከል አንዱ ይኸው ነው፡፡

ጥላቻ ደግሞ ከፍቅርህ የጠነከረ ግንኙነት ይፈጥራል ምክንያቱም ፍቅርህ ከአንገት በላይ ነው:: ጥላቻህ እጅግ ጥልቅ ነው:: ጥላቻህን የወረስከው ከእነስሳዊነት ባህሪህ ነው:: ፍቅርህ ለመጪው ሕይወትህ ያለህ ብቸኛ እምቅ ኃይልህ ነው:: እውን የሆነ ክስተት ሳይሆን ወደፊት ፍሬ የሚያፈራ ዘር ነው:: ጥላቻህ ግን ሙሉ በሙሉ በተግባር ላይ የሚገኝ፣ እጅግ የጎለመሰ፣ ያለፈው የብዙ ሺህ ዓመት ታሪክህ ህያው ቅርፅ ነው፡፡ የሚያድግበት ጊዜና ቦታ የነበረው:: ለውጡ መከሰት የሚጀምረው ግን በሰው ልጆች ላይ ነው::

ግን ማንንም እኔን ከመጥላት ማገድ አልችልም ስለዚህ ማንም ሰው እንዲያፈቅረኝ ማድረግ አልችልም:: ልገልፀው የምችለው ነገር ቢኖር ጥላቻም ሆነ ፍቅር የግንኙነት መልክ በሚይዝበት ጊዜ ንፅሕናውን እንደሚያጣ ብቻ
ነው፡፡

ፍቅርህን ህልውናህ አድርገው፡፡ ፍቅር
እንዲይዝህ ሳይሆን አፍቃሪ እንድትሆን ጣር፡ ፍቅር ባሪያህ ነው። ለአንተ ፍቅር የህልውናህ ጥፁም መዓዛ ነው:: ብቻህን ብትሆን እንኳን በአፍቃሪ ኃይል ትክበባለህ፡፡ የሞተ ነገርን ለምሳሌ ግዑዝ ወንበርን ብትዳስስ እንኳን ከእጅህ ፍቅር ይፈልቃል:: ፍቅርህን የምትሰጠው ለምንም ወይንም ለማንም ሊሆን ይችላል፡፡

በፍቅር ስሜት ውስጥ መሆን የለብክም እያልኩ አይደለም፡፡ ዳሩ ግን በፍቅር ስሜት ውስጥ መኖር የምትችለው ቀድሞውን የፍቅር ግንኙነት አስተሳሰብህን በምትተውበት ጊዜ ነው:: ፍቅር በሰዎች መሀል የሚመሰረት ግንኙነት ዓይደለም።

ሁለት ሰዎች አንድ ላይ እጅግ አፍቃሪ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ አፍቃሪነታቸው በጨመረ ቁጥር በመካከላቸው የሚፈጠረው የፍቅር ግንኙነት ይጠፋል። አፍቃሪነታቸው በጨመረ መጠን፣ አንዳቸው ከሌላቸው የሚፈልጉትንና አንዳቸው በሌላቸው የሚጥሉት ተስፋ ይቀንሳል፡፡ ውስጥም ይገባሉ፡፡

በውል ሳይተዋወቁ ፍቅርን ብቻ እያሰቡ ሲወዳደሱ በመጨረሻ መወቃቀስ ይጀምራሉ፡፡ ለዚህም ነው ምንም ዓይነት ተስፋ ማድረግ እንደማያስፈልግ ልታስታውስ የምፈልገው፡፡ ፍቅር የራስህ ውስጣዊ እድገት መሆኑን አውቀህ አፍቅር። ፍቅርህ ወደላቀ ብርሀን፣ ወደላቀ እውነትና ነፃነት ከፍ ያደርግሀል፡፡ ግን የፍቅር ግንኙነት አትፍጠር፡፡

አንድ ነገር ብቻ አስታውስ፣ ፍቅር ማንኛውንም ዓይነት መጥፎ ነገር የማጥፋት አቅም አለው፣ ፍቅርን ወደ ፍቅር ግንኙነት እንዲለወጥ ከፈቀድክለት ግን፣ ፍቅር ይጠፋና የጓደኝነት ስሜት በውስጥህ ያለው ውብ ባህሪ ሲሆን ጓደኝነት ግን ወደ ትስስር ያመራል፡፡

ስለዚህ ፍቅር መልካም ነገር ነው:: እንደውም ፍቅር የሌለበት ነገር
ሁሉ ስህተት ነው:: ግን ፍቅር ከፍተኛ ዋጋ በመሆኑ ከማንኛቸውም ዓይነት በካይ መርዘኛ ነገሮች መጠበቅ አለበት፡፡ ትስስር ይበክለዋል። ዓለም በግለሰቦች የተሞላች እንድትሆን እፈልጋለሁ:: «ጥንድ» የሚለው ቃል እንኳን ይጎዳኛል፡፡ የሁለት ግለሰቦችን ህልውና አጠፋችሁ ማለት ነው፡፡ ጥንድ በራሱ ውበት የለውም፡፡

ዓለም በግለሰቦች ብቻ የተሞላች ትሁን፡፡ ፍቅር በራሱ ጊዜ ጎምርቶ ሲፈነዳ ፍቅርን ዘምሩት ፣ ጨፍሩት፣ ኑሩት፣ ግን ፍቅርን ወደ ሰንሰለት አትለውጡት፡፡ ሰውን በባርነት ለመያዝ አትሞክሩ፣ ሌላም ሰው በባርነት እንዲይዛችሁ አትፍቀዱ፡፡

ነፃ ግለሰቦችን የያዘች ዓለም በትክክል ነፃ አለም ትሆናለች።

ይቀጥላል

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.4K views05:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 19:51:24 የሚያስፈልገው ምን ያህል ነው?
Repost

ከዘመን ዘመን ሳይንስ እየተራቀቀ ተክኖሎጂ እየመጠቀ ለሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎትን የሚያቀል ፈጠራ እየተበራከተ መጥቷል። ሩጫን እና ሸክምን የሚቀንሱ እልፍ ግኝቶች በገፍ ቢቀርቡም ሩጫ አልቀለለም ሸኽም አልቀነሰም።

የየእለት ኑሯችሁን ተመልከቱ። ለቅንጦት ተብለው የሚጀመሩ ነገሮች ሳይቆዩ መሰረታዊ ፍላጎት ይሆናሉ። ለትርፍ ጊዜ ታስበው የተጀመሩቱ በመደበኛ ጊዜ የሚከወኑ ይሆናሉ። ጊዜን ይቆጥባሉ ተብለው የተጀመሩቱ ጊዜን የሚሻሙ ሆነው ይገኛሉ።

ምንድነው እየሆነ ያለው?
ፌስቡክ የቅንጦት አልነበር? አሁን መሰረታዊ ፍላጎት ወደ መሆን ራሱን አሸጋግሯል።

በፊት ሰዎች ከተረፋቸው ገንዘብ ላይ በመቀነስ የሚሸምቱት ቁስ ዛሬ ላይ መሰረታዊ ፍጆታ ከመሆን አልፎ መወዳደሪያ ሆኗል።

የሚያስፈልገን ምን ያህል ነው? በየትኛው ፍላጎትስ መዳኘት አለብን? የማይሞላ ፍላጎትን ለማስታገስ የምንሮጠው እስከየት (እስከመች) ነው?

ህይወትን ያቀላል ተብሎ የተጀመረው በሂደት ህይወትን የሚያከብድ ይሆናል። ጊዜን ለመቆጠብ የተጀመረው መንገድ ጊዜን ይበላል። ለቅንጦት ያህል እንከውነው የነበረው መሰረታዊ ፍላጎት ወደ መሆን ይሻጋገራል።

የሚያስፈልገን ጥቂት ብቻ ሆኖ አላስፈላጊ የሆነውን ለማግበስበስ ታትረን ይሆን?  ወይስ የሚያስፈልገንን ሁሉ ለማከማቸት ተጋን?

@Tfanos
@Zephilosophy
5.0K viewsedited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-19 11:14:00 ሕይወት በሚታይና በማይታይ ማዕበል የተከበበች ናት!

ሰው ሃሳቡ በግንባሩ ላይ ቢጻፍ ማን ማንን ቀና ብሎ ያያል? ደግነቱ በውስጣችን ያለውን ማንም አያውቅብንም። የምናስበውን አስበን፤ የፈለግነውን አሳውቀን የምንደብቀውን ደብቀን የመኖር ጥበቡ ለሰው ልጅ ብቻ የተሰጠ ጥበብ ነው። ልብ በሃዘን ደምቶ ፊት በፈገግታ ሲፈካ ፤ ግንባር ኮስተር ብሎ ልብ በሃሴት ሲሞላ ፤ ጉልበት ተንበርክኮ ልብ በትዕቢት ሲቆም ፤ አፍ እንደ ማር ጣፍጦ ልብ እንደ እሬት ሲመር ፤ ማን ማንን ያውቃል ያሰኛል?!

የሰው ልጅ በሚታየውና እና በማይታየው ማዕበል ውስጥ ያልፋል፤ የሚታየው ማዕበል ሌሎች የሚረዱት እና የሚያዩት ችግራችን ሲሆን፤ የማይታየው ማዕበል ደግሞ ከሌሎች ደብቀን ለብቻችን የምንጋፈጠው ችግር ነው”።

ሌሎች የማውቁት ምን አይነት ጭንቀት ይሆን እያንዳንዳችን በውስጣችን ያለው? ምን አይነት የማይታይ ማዕበል እየተጋፈጥን ይሆን?

አዎ በሰው ፊት እንስቃለን ለብቻችን ግን እንባችንን በገዛ መዳፋችን ያለማቋረጥ እናብሳለን። ከሰው መሃል ደምቀን ለብቻችን ስንሆን መግቢያ እናጣለን። ከህዝብ ፊት ከብረን በቤታችን ግን የሰው ያህል የሚቆጥረን የለም። ጠንካራ መስለን፤ ልባችንን ግን በክህደት ስብርብሩ ወጥቷል። ከላይ ሰላም የሰፈነብን እንመስላለን፤ ውስጣችን ግን በተስፋ መቁረጥ ማዕበል ይተራመሳል። ከውጪ ሲታይ ቤታችን የደመቀ ቢመስልም ውስጡ ግን እንደ ዋሻ ቀዝቅዟል። ተለቀም አነሰም ሁላችንም ለሌሎች የማይታይ ለብቻችን የምንጋፈጠው ማዕበል አለን።

እናም በየመንገዳችን ስንተላለፍ ልብ እንበል፤ ሌላው ከኛ ያነሰ ትግል የሚታገል እየመሰለን ፊት አንንሳው፤ እየረገጥን አንለፈው። የኔ ችግር እና ጭንቀት ከሌላው ይበልጣል የሚል አስተሳሰብ ሲኖረን ለሌሎች የምንዘረጋው እጅ ያጥረናል። ትኩረታችን ሁሉ የራሳችን ችግር ላይ ሲሆን ይበልጥ እናማርራለን፤ ሌሎች ለብቻቸው የሚገፈጡትን ማዕበል ስለማናይ “ምነው እኔን ብቻ” እያለን የሃዘናችንን ጉድጓድ ይበልጥ ወደታች እንቆፍረዋለን።

ከትዳር አጋራችን ጋር ክንድ ተንተርሰን እያደርን፤ እርስ በርሳችን የምንፋለመውን ትግል አናውቅም። ለዚህ ነው ጭቅጭቅ ሲነሳ መሸናነፍ እና እርቅ ማውረድ የሚከብደን፤ ማን የማንን ማዕበል ያያልና? እናም በየመንገዳችን የሚያጋጥሙን ሰዎች ሁሉ የራሳቸው የሆነ ታሪክ አላቸው፤ በጫማቸው ሳንቆም አንፍረድ። በደቂቃ ውስጥ ያየነውን ምግባራቸውን ተንተርሰን አንፍረድ።

ሌላውም እንደኔ ስሜት አለው የሚል አስተሳስብ መያዝ ስንጀምር፤ የሌላው ህመም ይሰማናል እናም ብዙ ስህተቶችን ከመፈጸም እንድናለን። ምናልባት ለብቻሽ/ ለብቻህ የምትጋፈጠው ማዕበል ካለህ በርታ… አጋዥ የለኝም ብለህ አትስጋ ፈጣሪ የማትችለውን ችግር አይሰጥህም። አንተ/አንቺ ብቻ ከሰው የተለየ መከራ አልተሰጠሽም/አልተሰጠህም እንደየአቅማችን ለሁላችንም የታደለን ነው እንጂ……ከምንም በላይ ግን እርስ በርሳችን እንተጋገዝ፤ እየተገፈታተርን መተላለፉን እናቆም ምክንያቱም ሁላችንም ለየብቻችን በምንጋፈጠው ማዕበል ደክመናልና።

                       ሚስጢረ አደራው

            ውብ አሁን

@zephilosophy
4.6K viewsedited  08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 22:19:24 «የድሀ ፊት የአምባገናኖች ግፍ በየእለቱ የሚጻፍበት የማስታወሻ ደብተር ነው፡፡ እናም ድሃ ምን ፊት አለው? አምባገነንት የክፋቱን ገድል በየቀኑ በግፍ ቀለማት የሚስልበት የስቃይ ሰሌዳ ነው፡፡ ተስፋውን በቁም ሲገድሉበት ተመልሶ ላይወዛ የገረጣ ቆዳ፣ ቤቱን በጠራራ ጸሀይ ሲያፈርሱበት አሮ የከሰለ ፊት፣ ሲያስሩትና ሲገርፉት በሰንበር ሞዛይክ የተሳለ ገላ፣ ልጆቹን ሲያስሩበትና ሲገድሉበት ባነባው እንባ የታረሰ ፊትና ደም የለበሰ አይን የተሳለበት ሰሌዳ ነው፤ የድሃ ፊት፡፡ እናም ድሀ የኔ የሚለው ፊት የለውም፡፡ የሌለውን ፊት ደሞ ሊሸፍን አይጥርም፡፡››

ምንዳርአለው ዘውዴ
አፍን ዘግቶ ፉጨት

@Zephilosophy
4.5K views19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 17:08:49 ሞራሉ በቀላሉ የማይሰበር ሕዝብ ስነልቦናው ከፍ ያለ ነው!
(The psychology of the masses always matters)
(እ.ብ.ይ)

ሐገር በየትኛውም ጊዜ የእርስበርስ እልቂትና የጦርነት አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል፡፡ አደጋው በራሷ ልጆች አልያም በውጪ ጠላቶቿ ሊከሰት ይችላል፡፡ ስጋት የነበረ፣ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው፡፡ አይደለም በሐገር ደረጃ በግለሰብ ደረጃም ትላልቅ ስጋቶች አሉ፡፡ ማንም ከደቂቃ በኋላ ስላለው ጤናው፣ ሰላሙና ደህንነቱ ማወቅ አይችልም፡፡ አንዳንድ ሁኔታዎች ከምንጠብቀውና ከምንገምተው በላይ ሆነው ከቁጥጥራችን ውጪ ሊወጡ ይችላሉ፡፡ ስጋትን መተንተን፣ ሊፈጠሩ የሚችሉ ያልታሰቡ ክስተቶችን ማሰብ ነገሮቹ ሲፈጠሩና ከተፈጠሩ በኋላ ለሚኖረው መፍትሄ ወሳኝ ነገሮች ናቸው፡፡ በጥሩም ይሁን በመጥፎ በሕይወታችን ላይ የሚፈጠሩ አዳዲስ ክስተቶች ይዘውት የሚመጡት መልካም አጋጣሚዎችና አደጋዎች መኖራቸው አያጠያይቅም፡፡ የሚሊየን ዶላሮች ሎተሪ የደረሰው ሰው የአዕምሮ ዝግጁነት ከሌለው ዕድሉ አይሆኑ የሕይወት ፈተና ውስጥ ሊሰነቅረው ይችላል፡፡ መከራ አንድም በደስታ ጊዜ፤ አንድም በሃዘን ጊዜ ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይሄን ክስተት የሚቀበል የአዕምሮ ዕውቀትና የስሜት ብስለት ከሌለ ወድቆ መቅረትን ያመጣል፡፡ ሐገር ችግሮቿን ተሻግራ፤ መከራዎቿን አልፋ ጸንታ ልትቆም የምትችለው የሕዝቧ ስነልቦና ጠንካራ ሲሆን ነው፡፡ የህዝብ ስነልቦናው መነሻው የግለሰብ ስነልቦና ነው፡፡ በስሜት ብስለት (Emotional intelligence) ያልሰለጠነ ዜጋ ራሱንም ሆነ ሐገሩን ከሚመጣበት መከራ ሊያድን አይችልም፡፡ አስደንጋጭ ክስተት ሲፈጠር አሁናዊ አደጋውንና የሚቀጥለው መዘዙን በእንዴት ያለ መፍትሄ ማስቀረት እንደሚቻል የአዕምሮ ዝግጁነት ከሌለ ከጠፋው በላይ ሌላ ጥፋት ይከተላል፡፡

እንግሊዛውያን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ዋዜማ ላይ ስጋት ወጥሯቸው፣ ፍርሃት ወርሯቸው ጭንቀት በጭንቀት ሆነው እንደነበር ታሪክ ይናገራል፡፡ በዚህ አስፈሪ ጊዜ አዶልፍ ሂትለር በእንግሊዛውያን ላይ የቦንብ ናዳ ለመልቀቅ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ የለንደንን ነዋሪዎች አንቅልፍ ነስቶ ነበር፡፡ ትንሹም ትልቁም ካሁን አሁን የቦንብ ናዳ ረገፈብን በሚል በፍርሃት ቆፈን ተይዞ የለንደንን ሰማይ በየደቂቃው በሰቀቀን ይመለከት ነበር፡፡ በፈረንጆቹ ጥቅምት 19 ቀን 1939 ዓ.ም. ሂትለር ለጦር ጄኔራሎቹ በለንደን ሰማይ ላይ እንዴት ጥቃት እንደሚፈጽሙ እቅዱን አብራራ፡፡ እ.ኤ.አ. መስከረም 7 ቀን 1940 ዓ.ም. ሶስት መቶ አርባ ስምንት የጀርመን ቦንብ ጣይ አይሮፕላኖች ለንደን ሰማይ ላይ ተራወጡ፡፡ ያ ቀን ለእንግሊዛውያኑ ጥቁር ቀን (Black Satureday) ነበር፡፡ በዚህ ቀን የተጀመረው ጥቃት ለተከታታይ ዘጠኝ ወራት ቀጠለ፡፡ በዚህም ከ80 ሺ በላይ የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች በጥቃቱ ሕይወታቸውን አጡ፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ የለንደን ታሪካዊ ህንጻዎች ፈራረሱ፡፡ ለንደን እንዳልነበረች ሆነች፡፡

ከሁሉ የሚገርመው ይሄን አደጋ እንዴት ነበር እንግሊዛውያኑ ተቀብለው ያስተናገዱት የሚለው ነበር፡፡ እንግሊዛውያኑ ያ ሁሉ ጥቃት ሲፈፀምባቸው ትራፊኩ ስራውን ከመስራት አልታቀበም፤ ህጻናቱ በሰላሙ ጊዜ የሚጫወቱትን ጨዋታቸውን አላቋረጡም፣ ሰራተኛው ከስራው ገበታው አልተስተጓጎለም፡፡ ባለሱቆቹ ከምንጊዜውም በላይ ሱቃቸው በር ላይ ‹‹መስኮቶቻችን በጥቃቱ ቢደቅቁም መንፈሳችን ግን አልደቀቀም፡፡ ደንበኞቻችን ይግቡና የሚፈልጉትን ይሸምቱ! (Our windows are gone. But our spirits are excellent. Come in and try them)›› የሚል ማስታወቂያ ለጥፈው ደንበኞቻቸውን ይጠባበቁ ነበር፡፡ ሂትለር በጊዜው የእንግሊዝን የደህንነት መረጃና የጦር ሚስጥር ቢያውቅም የእንግሊዛውያኑን የመንፈስ ጥንካሬ ግን አያውቅም ነበር፡፡ ዊኒስተል ቸርችል በዚህ ጥቃት ከሶስት እስከ አራት ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎቹ ጦርነቱን በመሸሽ ሐገራቸውን ለቀው ይሰደዳሉ ብሎ ቢገምትም የሆነው ግን በተቃራኒው ነበር፡፡

እንግሊዛውያኑ በጥቃቱ ዘመዶቻቸውን በማጣታቸው ሐዘን ቢሰማቸውም፤ ንብረታቸው በመውደሙ ቢበሳጩም ስሜታቸውን የሚያስጨንቅ፣ አዕምሯቸውን የሚረብሽ ምንም ዓይነት የመንፈስ ጠባሳ (Trauma) አልነበረባቸውም፡፡ እንደውም በሰላሙ ጊዜ የነበሩ ወንጀሎች በዚህ ክፉ ጊዜ ቀንሰው ነበር፡፡ የአልኮል ጠጪዎች ከሸመታ ቤት ጠፍተዋል፡፡ ደሃም ይሁን ሃብታም እርስበራሳቸው ይረዳዱ ነበር፡፡ የተጎዱ ቤተሰቦችን በመርዳትና በመጎብኘት ያፅናኑ ነበር፡፡ ፖለቲካ ከሞራላቸው አላነጣባቸውም፤ የካድሬ ጩኸት እርስበራሳቸው አልለያያቸውም፡፡ ይሄ ክፉ ጊዜ ሰው-ነታቸውን አስታወሰ እንጂ ሰብዓዊነታቸውን አልቀማቸውም፡፡ ባንክ ለመዝረፍ የሮጠ የለም፡፡ እስር ቤቶችን ሰብሬ በህግ ጥላ ስር ያሉ እስረኞችን አስለቅቃለሁ ያለ ጉልበተኛ የለም፡፡ ይሄን የቀውጢ ሰዓት ተጠቅሞ ሱቆችን ሰባብሮ እቃዎችን ለመስረቅ ያሰበ ማንም አልነበረም፡፡ በጦርነቱ ምክንያት ኢኮኖሚያቸው እንዳይጎዳ ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠውም ቢሆን ስራቸውን ከመስራት ያቆማቸው አንዳች ሃይል አልነበረም፡፡

ሊንድማን የተባለ የቸርችል የቅርብ ጓደኛ በጦርነቱ ሳቢያ በጣም በተጎዱ በበርሚንግሃምና ኸል (Bermingham and Hull cities) በተባሉ ሁለት ከተሞች እንግሊዛውያኑ የመንፈስ ስብራትና የአዕምሮ መረበሽ እንደደረሰባቸውና እንዳልደረሰባቸው ለማወቅ ሁለት የጥናት ቡድኖችን ወደከተሞቹ ላከ፡፡ አጥኒዎቹም ይዘዉት የመጡት የጥናት ግኝቶች (Findings) ግን ብዙዎችን ያስደነቀ ነበር፡፡ በጥናቱ ወረቀት የፊት ገፅ ላይ በትላልቅ ፊደላት የተፃፈው ፡-

‹‹There is no evidence of breakdown of morale (የሞራል ስብራት እንዳለ የሚያረጋግጥ ምንም ማስረጃ የለም)‹‹ የሚል ነበር፡፡

አዎ ሐገርን ከአደጋ በኋላ ቀና የሚያደርገው ገንዘብ ብቻ አይደለም፡፡ ሐገርን ወደፊት እንዲቀጥል የሚያደርገው የህዝቡ ፅናትና የስነልቦና ጥንካሬ ነው፡፡ እንግሊዛውያኑ የሂትለርንና የቸርችልን ፖለቲካዊ እሰጣ ግባ ችላ ብለው ለሐገራቸው የቆሙት መንፈሳቸው ጠንካራ ስለነበረ ነው፡፡ የመጣባቸውን ጥፋት ተጋፍጠው ሞራላቸውን ሳያስነኩ ሀገራቸውንም ራሳቸውንም ጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ አስረክበዋል፡፡ ሞቱን ተቀብለው፤ አካል ጉዳቱን ችለው ሐገራቸው ኢኮኖሚዋ እንዳይወድቅ የበኩላቸውን ሚና ተጫውተዋል፡፡ በዚህም ለሌላው የዓለም ህዝብ ምሳሌ ሆነው ሲዘከሩ ይኖራሉ፡፡

ሐገርን በፅኑ መሰረት ላይ የሚያቆመው ጠንካራ ስነልቦና ያለው ህዝብ ነው! መንፈሱ ከፍ ያለ ሕዝብ ሐገሩ ላይ የተደቀነውን ፈተና ያልፋል፤ ከፊቱ የተጋረጠውን አደጋ ይሻገራል!

አዎ! አጥፊዎች ሆይ... ‹‹ንብረቶቻችንን ልታወድሙ ትችላላችሁ፤ መንፈሳችንን ግን ማድቀቅ አትችሉም፡፡ አካላችንን ትጎዱት ይሆናል ስነልቦናችንን ለመድፈር ግን አቅም የላችሁም!››

ቸር ጊዜ!

ኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ለዘላለም ይኑሩ!

_____
እሸቱ ብሩ ይትባረክ
(እ.ብ.ይ.)

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.6K views14:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 21:30:39 ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(1ኛ ዮሐ.3፡15)

“ብሔርተኛ የሆነ አምባገነናዊ አገዛዝ ለጊዜው ምክንያታዊነት በጎደለው ስሜታዊና ግልብ በሆነ አስተሳሰብ ዜጋውን ወይም “ብሔር” ብሎ ከፋፍሎ ያደራጃቸውን በመንዳት የተሳካለት ይምሰለው እንጂ፣ አገዛዙን ለማስቀጠል ሲል የሚፈጽማቸውን ግፎች በሂደት ሕዝቡ እየተገነዘበው ስለሚሄድ ምንም ዓይነት ሴራ ቢጠቀም አገዛዙ ያሰበው እቅድ ዘለቄታ ሊኖረው አይችልም፡፡

በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃን ይሁን አናሳ ቁጥር ባለው “በብሔር” ማንነት
ላይ የተመሠረተ ማንኛውም አገዛዝ የሳይንሳዊ ፖለቲካዊ ስርአት ሳይሆን በአዕምሮ ቅዠት ህመም የተጠቃ፣ ፋሽስታዊ አምባገነን፣ ኢ-ሰብአዊ፣ ስርአተ አልበኛ፣ የወሮበላና የደንቆሮ ገዢ ቡድን ነው፡፡ በአጠቃላይ “የብሔርተኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ በፖለቲካ ሳይንስ የተቃኘ ሕዝባዊ አስተዳደር ሳይሆን፣ ከአዕምሮ ቅዠት ህመም የመነጨ የድንቁርና አገዛዝ ነው::

በአሁኑ ዓለም የመልካም አስተዳደር ሳይንሳዊ ፖለቲካ ማለት፣ የአንድ ሀገርን ብዙሃን ሕዝብ አዕምሮ ከፖለቲካዊ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ነጻ በማድረግ በኑሮ ደረጃዉ እያሳደገ የማስቀጠል ብቃት ነው፡፡


በአንድ ሀገር መንግሥታዊ አገዛዝ ላይ ብዙሃኑ ሕዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ከተፈጠረ ሀገሪቱ የብዙሃን ሕዝብ ድጋፍ የተቸረው የአገዛዝ ሥርዓት ባለመሆኑ ሀገሪቱ ያልተረጋጋችና ልማቷም ዘለቄታ የሌለዉ ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ይህም ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻ እያደገ በመሄድ በዋናነት በአፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያን የመሳሰሉትን ሀገራት ሁልጊዜ ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየከተተ ዜጋውን ወደተሻለ ኑሮ እንዳያድግ የሚገድብ ነው፡፡

ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(ኛዮሐ.3፡15)፡፡ አንድ ሰው ግድያ ከመፈጸሙ በፊት የሚፈጠረው የጥላቻ አስተሳሰብ ይቀድማል፡፡ የጥላቻውም አስተሳሰብ በሂደት በግድያ ድርጊት ይፈጸማል፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃኑ ሕዝብ በፊት ስለሚገድለው ሰው በአዕምሮው ውስጥ  ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር መንግሥት ካለ አምባገነን አገዛዝ እንጂ፣ መንግሥታዊ ስርአት አይደለም፡፡ ስርአት ማለት ማንም ሰው እንደፈለገው የማይቀያይረው፣ በሳይንሳዊ እውቀት የተደራጀ፣ ህግንና ደንብን በመከተል የታለመለትን ግብ የያዘ ተቋም  ነው፡፡

“የብሔርተኛ” አምባገነናዊ አገዛዝ ሳይንሳዊ የፖለቲካ ስርአት ሳይሆን፣ በባህሪው በቀሪው ዜጋ አዕምሮ ውስጥ ሁልጊዜ ቁጭት፣ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር የስርአተ አልበኛና የአሸባሪነት አገዛዝ ነው፡፡ የብዙሃኑ ህዘብ አዕምሮ ለቁጨት፣ ለንዴትና ለጥላቻ የሚዳርግ አገዛዝ ይዋል ይደር እንጂ፣ አንድ ቀን በብዙሃኑ ህዝብ አመጽ በውርደት መወገዱ እንደማይቀር የአሁኑ ዓለም ታሪካዊ ሃቅ ነው፡፡ በአሁኑ ዓለም “በብሔር” ማንነት ላይ የተመሠረተ ፋሽስታዊ አገዛዝ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚዊ እንዲሁም በኃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ እንኳ ሳይቀር የበላይነቱን በማረጋገጥ ሰውን ከሰው የሚለይ፣ የሚያገልና አድልኦን የሚፈጽም ሳይንሳዊ ያልሆነ አገዛዝ ነው፡፡ ስለሆነም በብዙሃኑ ሕዝብ ዘንድ ምንጊዜም ቢሆን ተቀባይነት ስለሌለው ሁልጊዜ ሰላምና መረጋጋትን በማሳጣት ለአብዮት የሚዳርግ ነው፡፡

በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ በተቃኘ ፋሺስታዊ አገዛዝ ውስጥ ሁሉም ባይቀበለውም ነገር ግን እጅግ አብዛኛው ዜጋ በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ ቅዠት ህመም ይለከፋል፡፡ የ”ብሔርተኛ” ፋሽስታዊ አገዛዝ የስልጣኑን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሲል የሚያራምዳቸው መሠረታዊ ሴራዎች አሉት፡፡ እነዚህ ሴራዎችም በህዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ንዴትንና ጥላቻን በአገዛዙ ላይ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ በመሆኑም ይህ ቁጭት፣ ጥላቻ ይዋል ይደር እንጂ “በብሔር” ማንነት ተከፋፍሎ የነበረውን ሕዝብ ወደ መተባበበር ይገፋፋውና አገዛዙን ለማስወገድ የሞት ሽረት ትግል ውስጥ ሳይወድ በግዱ ይገባል፡፡

ሰብስቤ አለምነህ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
7.3K viewsedited  18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-30 09:12:14
4.1K views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 17:36:42 ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም
ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትም

....የቀጠለ

ሽማግሌው የግራ ጆሯቸውን፤ ከፊቶች አንዱን እያከኩ ተነሡ።

“እንግዲህ ሰማንህ ዕድሉ። ለሰሚ የቸገረ ነገር ነውና የሸንጎውን ሐሳብ አድምጠን ፍርዱን ለዋናው ዳኛ እንሰጣለን። ፈጣሪና መጥረቢያ አጥፍተዋል። ፍርድ ይገባቸዋል? የምትል እጅህን አውጣ ተብለሃል!”

ማንም ሰው እጁን አላወጣም። ዕድሉ ይባስ ከፋው። ከዚህ ሁሉ በደሉ ጀርባ ዓለም ያሴረ መሰለው።

“ተው አንተ ሸንጎ አንተም እንደምሳር በወደቀ ላይ አትዝመት፣ ተው ንጉሥም ሲያጠፋ አጥፍተሃል ይባል፣ ተው መፈራራት ይቅር፤ ተው ለበዳዮችህ አታቀርቅር፣ ተው ፍርዴን አታጣምም፤ ተው ተፈጥሮን አታሳምም። ተው እውነት እየመረረችህም ጠጣት። ተው የምታሽርህን ጋታት!”

“ፈጣሪና መጥረቢያን ነጻ ናቸው የምትል። ፈጣሪ አይከሰስም! የምትል እጅህን አውጣ ተብለሃል” ሁሉም እጁን አወጣ። ማውጣት ብቻ ሳይሆን ፈጣሪ በደንብ እንዲያየው ወደ ሰማይ እየተንጠራራ።
ሽማግሌው ወደ ዋናው ዳኛ ዞረው “እንግዲህ ፍርዱን ለእርስዎ ሰጥተናል!” አሉ።
“እንግዲህ ፍረድ ካላችሁኝ ይኸው ፍርዴ። በእውነት ይሄ ሰው ቀላል እፍዳ አላሳለፈም። ፈጣሪም መጥረቢያም በድለውታል። ኧረ እንደውም እስከ ዛሬ እንደዚህ የተበደለ ሰው ገጥሞኝም : አያውቅም። ስለዚህ መጥረቢያው በእጃችን ነው። እንጨቱ ተፈልጦ ማገዶ ይሁን። ብረቱ ሲቃጠል ይኖር ዘንድ፤ ያበላሸውን ይክስ ዘንድ ተቀጥቅጦና ቀልጦ የተበሳ ሰታቴ ወይ ላመፈጅ ይጠገንበት። ፈጣሪም ካለበት ተይዞ “ዕድሜ ይፍታሕ” እንዲታሰር ፈርጃለሁ። ይዞ ላመጣውም ያሻውን ያህል የምትታለብ ጥገት፤ ሮጦ የደረሰበትን ያህል ጋሻ መሬት፤ ልቡ የፈቀደውን ያህል ሚስትና እቁባት ይሸለም ዘንድ ፈርጄያለሁ። ይግባኝ አለኝ! የሚል ተከሳሽ ከተያዘ በኋላ ማሰማት ይችላል። ጨርሼያለሁ!”

ዕድሉ ቀና በአዛውንቱ ቅንነት እየተደነቀ አመስግኖ ወረደ። ሕዝቡም ገጸበረከቱ እያጓጓው፤ ፈጣሪን በየመቅደሱ በርብሮ ሊያገኝ ተመመ። “ፈጣሪ” ያልነው ማንን ነው? ዳኛውም ማንንም ሳያስከፋ ሸንጎውን መበተኑን ለሚቀጥሉት ብዙ ዓመታት በኩራት ሊያወራ ከግንባሩ ግራ እስከ አገጩ ከተዘረጋው፤ በከንፈሩና በዓይኑ ከሚቋረጥ ጠባሳው ጋር አንከስ አንከስ እያለ ወደ ቤቱ አዘገመ። ተከሳሽ በሌለበት ከሳሽ ሙግቱን ቢረታ ማነው ያሸነፈው?

ድሕረ “ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትም”

የዕድሉ መጥረቢያ እጀታ ተፈልጦ በጋመ እሳት ውስጥ ገባ። እንደ ትዝታ በትናንሽ ዓይኑ የሚያፈጥ እንጀራ ለመጋገር ከሌሎች እንጨቶች ጋር አበረ። ሚስቱ ሰው ጠርቷት በወጣችበት ኩሽናው በእሳት ተያያዘ። በቀላል ሊያጠፉት አልቻሉም። እሳቱ እንደሰደድ ተዛምቶ የአዝማሪው ሐዋዝንና ሌሎች ሦስት ቤቶችን አወደመ። ሚስቱ ስትጠየቅ “እንዲህ በፍጥነት የሚዛመት እሳት አይቼ አላውቅም! ይኸማ የፈጣሪ ቁጣ ነው!” ትላለች። በደዌ ዳኛ፣ በአልጋ ቁራኛ ተይዘው የተኙት እትዬ ተዋቡ በእሳቱ ተቃጥለው ሕይወታቸው አለፈ። ዕድሉ ሞታም ሰው መፍጀት ያልተወችውን መጥረቢያው ውስጥ ዕጣ ፈንታው እያወካ የሚስቅበት መሰለው። ከሰማይ፣ ከምድሩም እንደተጣላ ጠረጠረ። “እንጀራ እበላበታለሁ” ባለበት አንድ መጥረቢያ ጦስ ሕይወቱ ምስቅልቅል ሲል መታገስ አልቻለም። ሞቱን አልፈራም። እየተበደሉ ይቅር አለማለት ዞሮ ራሱን ተገተገው። “ተበድለህም ይቅርታ መጠየቅ ምን ማለት ነው?” ...ልጆቹን ሳያሳድግ መሞቱ እያንገበገበው አጣጣረ። ከሰውም፣ ከአማልክትም መታረቅ የማይችል ቂም ቋጥሮ ሳይበረክት በተወለደበት አልጋ ላይ ሞት ተገናኘው።

ልክ ነፍሱ ስትወጣ

አንዳንዶች “መጣሁልህ! ምን ልታደርገኝ እንደሆን አይሃለሁ?!” ብሏል
ይላሉ።

አንዳንዶች “ይቅር በለኝ?! እኔም ይቅር ብዬሃለሁ!” ብሏል ይላሉ።

ሚስቱ ግን ዛሬም ድረስ ዕድሉን ሲያነሡባት ልጆቿን ታቅፋ አምርራ ታለቅሳለች።

“እንግዲህ አይዞሽ! ፈጣሪ የወደደውን ነው
የሚጠራው!”
አሉ ሰባኪው ሾላ።

ጤናው እብዱ ከነግሣንግሡ እያለፈ ሳቀ። ረዥም ሳቅ ሳቅ ...ሁሌ እንደሚስቀው የልግጫ ሳቅ ሳቀ። “ታዲያ ፈጣሪ ሲጠራ፤ እንዳንከራተተ ነው እንዴ? ሳይክስ? ሳይዳስስ?”

@Zephilosophy
@Zephilosophy
6.2K viewsedited  14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 17:34:52 “መቼም አልሰማ ብለህ ክሴን እቀጥላለሁ” ካልክ የሆንከውን አብራርተህ ተናገር! አታደናግር!” ሽማግሌው ጮኸ።

“ነገሩ እንዲህ ነው። የሆነ ቀን አለልማዴ ዓለሜን አስከትዬ ዛፍ ቆረጣ ሄድሁ። በእኔ ቤት ዛፍ ቆርጬ ገንዘብ ላገኝ ነው እንግዲህ። አዬ! ...ምነው በቀረብኝ። ዓለሜን አርቄ አስቀምጬ መጥረቢያዬን ይዤ ዛፉ ላይ ወጣሁና መተግተግ ጀመርሁ። ምን የተረገመው ቀን እንደሆነ እንጃ ከዛፉ ላይ አንዲት ሰላላ ቅርንጫፍ ብላት ብሠራት አልቆረጥ አለችኝ። ዛሬ ደግሞ የምን ተአምር ነው የገጠመኝ? እያልሁ ደጋግሜ ብመታት ጭራሽ እንደድንጋይ መጥረቢያዬን አንጥራ ትመልሳለች እንጂ ፍንክችም አትልም። ሠላሳ ዓመት ዛፍ ስቆርጥ እንዲህ ዓይነት ነገር ገጥሞኝም አያውቅም። የዚህ ሀገር እንጨት እንደምታውቁት ገራም ነው፤ እንኳን ቅርንጫፍ ግንዱም ዐሥሬ ደኅና ካገኙት ይበቃዋል። ተንጋልሎ ያርፋል። የትንግርቴን ተፋጥጬ ሳነሣ ስለው፣ ሳነሣ –ስለው ...እልህ ይዞኝ እንጂ እጄ ዝሎ ኖሮ መጥረቢያው አምልጦኝ ቁልቁል ተምዘገዘገ። በዓይኔ ስከተለው...

” ዕድሉ ቀና ሳግ አንቆ አላናግር ስላለው አቀርቅሮ ጊዜ ወሰደ።

“ለቅሶህን ተውና ቀጥል ተብለሃል!”

“በዓይኔ ስከተለው እንደ ኪሩብዔል ሰይፍ ሲገለባበጥ ወርዶ ከየት መጣች ያላልኳት የልጄ አናት ላይ ሰመጠ። ይታያችሁ! ለእንጨት የሰነፈ መጥረቢያ ለልጄ ሲሆን በረታ። ለካ ዓለሜን አርቄ ባስቀምጣትም አሳዝኛት ሥሬ መጥታ ሽቅብ ስታየኝ ነበር። እኔ አፈር ልብላላት ...ሞት ሲጠራት እኮ ነው! ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ሠላሳ ዓመት ሙሉ ገጥሞኝ የማያውቀውን የእዚያ ቀን መጥረቢያ ያመለጠኝ? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል አድርጌ የማላውቀውን መጥረቢያ የሚያመልጠኝ ቀን ልጄን ይዤ የመጣሁት? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ከዓመት እስከ ዓመት የሚያሰቃያት ንዳድ ያንን ቀን ጋብ ያለላት? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ለእጅ የምትሰንፍ ቅርንጫፍ በስል መጥረቢያ የለገመቸው? ለምን “እንቢ! ስትለኝ አልተውኋትም? ምነው መጥረቢያውስ ካልጠፋ አውላላ መዳፍ የማታህል የልጄን አናት የመረጠው? ፈጣሪ ቢለው አይደል?”

አዝማሪው ሐዋዝ ተነሣ
“መቼም እንደሰው ልጅ ጉድ የትም የለም። ጠማማ ዕድሉንም፣ ስንፍናውንም በፈጣሪ ማሳበብ ይወዳል። አንተ የአርባ ዓመት ጎልማሳ ስትሆን ምነው ልጅህን መጠበቅ አላወቅህበት? እጅህ እስኪዝል አንድ ቅርንጫፍ ቀጥቅጥ ያለህ ፈጣሪ ነው? ከእጅህ አሽቀንጥረህ ስትጥለውም ወደወረወርክበት ይሄዳል እንጂ መጥረቢያ እግር የለው፤ ዓይን የለው፤ ምን አድርግ ነው የምትለው? ይህን ድፍረት ለተናገርህበት ራሱ ቅጣት ይገባሃል። ኧረ ምነው! ስንት ነገር ጥለን ነው የመጣነው፤ ጊዜያችንን ባንፈጅ...?”

ዕድሉ ቀና ክሱን ሰምቶ የሚደግፈው አለማግኘቱ አንገበገበው። ኀዘኑ እጥፍ ድርብ ሆነ። መናገሩ እንደማይጠቅም ሲሰማው ልቡ አመነታ። ቢሆንም የተበደለው አላለቀም። ቢያንስ “ተናግሬ ይውጣልኝ!” ብሎ ተቀበለ።

“አይ ሐዋዝ! አንተ ጎረቤቴ ሆነህ የደረሰብኝን ሁሉ ስታውቅ እንዲህ ማለትህ አሳዝኖኛል። ጊዜ የተፈጀብህ ለምኑ ነው? አናውቅም የት ውለህ የት እንደምታነጋ? ሌላ ምንም አልልህም አንተም ሴት ልጅ አለችህ። በልጅ የመጣ እንዴት እንደሚያንሰፈስፍ ደርሶብህ እየው።” ንግግሬ እንዳልጠቀመ አይቼያለሁ። ቢሆንም ልናገረውና የመጣው ይምጣ...”

ዋናው ዳኛ አንካሳ እግራቸውን በእጆቻቸው እያመቻቹ የሚሆነውን በዝምታ ይሰማሉ።

“ይቅር ብዬ አልፌው እንጂ የተበደልሁትስ ይህ ብቻ አልነበረም። ከሆነ አይቀር ግን ይኸው ስሙት። ታላቁ ልጄ እንደምታውቁት የቀኝ እጁ አራት ጣቶች ቆራጣ ናቸው። የእርሱ ታናሽ ደግሞ እጁም እግሩም ላይ ስድስት ስድስት ጣት አለው። ይህ እንዴት ሆነ? ሲቀለድብኝ መሆኑ ነዋ! .....አንድ ቀን ጠዋት የጀመርሁ ሥራ ፍለጋ ስንከራተት ውዬ ሰውነቴ ዝሎ አመሻሽ ላይ ቤት ደረስኩ። ምንም ምንም ሳልል፤ እህልም ሳልቀምስ፤ ልብሴንም ሳላወልቅ መጥረቢያዬን ቆጥ ላይ ሳልሰቅል ተኛሁ። ብዙም አልቆየ ታላቅ ልጄና ነፍሰጡር ሚስቴ በጩኸት ቤቱን ሲያናጉት ብትት ብዬ ተነሣሁ። ሳይ ከልጄ መዳፍ ላይ ደም እንደወራጅ ውኃ ይንዠቀዠቃል። ዘልዬ አፈፍ ሳደርገው አራት ጣቶቹ ተራ በተራ ጠብ፣ ጠብ ብለው እንደጉድፍ መሬት ላይ ወደቁ። ያ መጥረቢያ ከንፈሩ ደም ጠግቦ ተጋድሟል። የሆነው ወዲያው ገባኝ። ታዲያ ምን ዋጋ አለው? ከረፈደ ዕውቀት የቀደመ ጠርጣራነት እንደሚበልጥ ማን አስተምሮኝ ያኔ? ደንቆሮ፣ የደንቆሮ ዘር አይደለሁ። አንድ ቀን መጥረቢያዬን ማራቅ ብረሳ... ። ዛሬም ድረስ አውራ ጣቱ በመዳፉ ላይ ብቻዋን ፍርፍር ስትል ሳያት እንባዬ ይመጣል። ጠማማ ዕድሌን መግራት ተስኖኝ እንዳጎደልሁት ይሰማኛል!”

"ይበቃል ተብለሀል።"

...
“አይበቃኝም ገና መች ጀመርኩትና?! ኋላ ስንቀዠቀዠ ቤቱ ሄድኳ። ምነው ፈጣሪ ምነው ሳምንህ ጉድ ሠራኸኝ? ስል አለቀስሁ። ስለትህን አጉድዬ አውቃለሁ? የምበላው ባጣ እንኳ አሥራትና መባህን ነክቼ አውቃለሁ? ውለታ አታውቅም? አምላክ አይደለህም ተንደርድረህ ከሰው ልታንስ ነው? ምነው እኔን እንዳሻህ ብታደርገኝ? ምነው ልጆቼን ብትተውልኝ?” አልኩት። ሞኝ፣ የሞኝ ዘር አይደለሁ? ...የሰማኝ መሰለኝ። “አይዞህ
ያለኝ መሰለኝ። “ይቅርታህን! የዛሬን ብቻ እለፈኝ ትቼሃለሁ” ያለኝ መሰለኝ። “ታርቀናል” ብዬ እንባዬን ጠርጌ ተነሣሁ። ቤት ስደርስ ያቺ ወረግቡ ሚስቴ ስታምጥ ደረስኩ። ቀበቶዬን አላልቼ የምትሰጥም አንተ፤ የምትነሣም አንተ ተመስገን!” አልሁት። ክፋቱን ረሳሁለት። ሚስቴ ምዉ ሳይጠና ተገላገለች። ቆንጅዬ ወንድ ልጅ በጨርቅ ጠቅልለው አሳቀፉኝ። ሳይደግስ አይጣላም!” ይሉ የለ የእኛ ሀገር ሰዎች? ...ደጋጎቹ። “መከራዬን አይተሃልና ኀዘኔን በሳቅ፣ ለቅሶዬን በደስታ ቀይረሃልና” ስል ስሙን ካሣ አልኩት። የካሠኝ መስሎኝ! አይ ደንቆሮ፣ የደንቆሮ ዘር ...ቶሎ አይነቃም እኮ።

ያዋለደችው ሴት በደስታ የምሆነውን ሲያሳጣኝ ፊቷን ጨምታ ስታየኝ ጠረጠርኩና ጨርቁን ገለጥሁት። በእጆቹም በጣቶቹም ላይ ስድስት ስድስት ጣቶች አሉ። ስድስተኛ ሆነው የበቀሉት እንደሌሎቹ ጠንካራ ስላልሆኑ ወዲያና ወዲህ ተንከርፍፈዋል። ደነገጥሁ። ከማዘን ማበድ ቀረበኝ። ጣቱ ስድስት መሆኑ አይደለም፤ ነገረ-ሥራው ገርሞኝ እንጂ። የታላቁን አራት ጣት ነሳኸኝ ብዬ “ምነው?” ስላልኩት ካሣ ላይ መመለሱ ነው? ይሄ ቀልድ እንጂ ሌላ ምን ይሆናል? ድርቅ በጎርፍ ይካሣል? ሥርጉዳት በእባጭ ይሣሳል? ኧረ እንዲህም አድርጎ ቀልድ የትም የለ!”
4.6K views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ