Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.78K
የሰርጥ መግለጫ

"Strong minds discuss ideas, average minds discuss events, weak minds discuss people."
Rinu Ruzvelt

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-11-11 21:05:46 ስለ ደስታ
Sadhuguru

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.1K viewsedited  18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-06 22:22:45 በፍቅር መድፈር

ምንጭ ፦ ህያውነት (ኦሾ)
ትርጉም ፦ ሀብታሙ ተስፋዬ

በጥልቀት ካፈቀራችሁ ፍርሃት ድራሹ ይጠፋል፡፡ ፍርሃት እጦት፣ አሉታዊ ነገር ነው፡፡ ይህንን በጥልቀት ልትገነዘቡት ይገባል፡፡ ይህን ግንዛቤ ካልጨበጣችሁ የፍርሃትን ባህርይ ልትረዱ አትችሉም፡፡ ፍርሃት እንደጨለማ ነው:: ጨለማ የሌለ ቢሆንም ያለ ይመስላል፡፡ ጨለማ የብርሃን እጦት ነው:: ብርሃን ግን አለ፤ ብርሃኑን ካስወገዳችሁት ጨለማው ብቅ ይላል::

ጨለማ የለም፤ ጨለማን መግፈፍ አትችሉም፤ የፈለጋችሁትን ነገር ብታደርጉ ጨለማን ማስወገድ አትችሉም፣ ልታመጡት ወይም ልትወረውሩት አትችሉም፡፡ ጨለማን አንድ ነገር ማድረግ ከፈለጋችሁ ብርሃንን መጠቀም ይኖርባችኋል፣ ምክንያቱም አንድ ነገር ማድረግ የምትችሉት ህያው የሆነን ነገር ነው:: መብራቱ ስታጠፉት ጨለማ ይሆናል፤ መብራቱን ስታበሩት ጨለማ አይኖርም - በብርሃን አንድ ነገር ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ ጨለማን ግን ምንም ማድረግ አትችሉም፡፡

ፍርሃት ጨለማ ነው፣ የፍቅር እጦት ነው፡፡ ምንም ልታደርጉት አትችሉም። ልታስወግዱት ብዙ በጣራችሁ ቁጥር የበለጠ ፈሪ ትሆናላችሁ- ምክንያቱም የበለጠ የማይቻል ይሆንባችኋል፤ችግሩ ይበልጥ ውስብስብ ይሆናል፡፡ ጨለማን ከታገላችሁት ትሸነፋላችሁ፡፡ ጐራዴ ይዛችሁ ጨለማን ልትገድሉት ብትሞክሩ ትርፉ ድካም ብቻ ነው፡፡ በመጨረሻም አዕምሮ “ጨለማ ሃይለኛ ስለሆነ ነው የተሸነፍኩት” ይላል፡፡

ይሄን ጊዜ ነው ምክንያታዊ አስተሳሰብ ስህተት የሚሆነው፡፡ ሁኔታው ፍፁም ስነ-አመክኖያዊ ነው ከጨለማ ጋር ታግላችሁ ልታሸነፉ ወይም ልታጠፉት ካልቻላችሁ “ጨለማ በጣም፣ በጣም ሃይለኛ ነው፡፡ እኔ ከእሱ ጋር ስነፃፀር ደካማ ነኝ” ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አስተሳሰብ ነው፡፡ እውነታው ግን የተለየ ነው፡፡ እናንተ ሳትሆኑ ጨለማው ነው ደካማ፡፡ በእርግጥ ጨለማው እዚያ ስለሌለ ነው ልታሸንፉት ያልቻላችሁት፡፡ የሌለን ነገር እንዴት ማሸነፍ ይቻላል?

ከፍርሃት ጋር አትታገሉ፣ አለበለዚያ የበለጠ ፈሪ ትሆናላችሁ፡፡ አዲስ ፍርሃት በውስጣችሁ ይገባል፡፡ ፍርሃትን መፍራት ነው በጣም አደገኛው ነገር፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ፍርሃት እጦት ነው፡፡ ሁለተኛው ነገር ፍርሃትን ፍራቻ፣ እጦትን ማጣት ነው፡፡ ከዚያም ወደ እብደት ታመራላችሁ!

ፍርሃት ምንም ሳይሆን የፍቅር እጦት ነው፡፡ ፍርሃትን እርሱትና በፍቅር አንድ ነገር አድርጉ፡፡ በደንብ ካፈቀራችሁ ፍርሃት ይጠፋል፤ በጥልቀት ካፈቀራችሁ ፍርሃት ድራሹ ይጠፋል፡፡

ለአንዲት ቅፅበት እንኳን አንድን ሰው አፍቅራችሁ ፈርታችሁ ታውቃላችሁ? ሁለት ሰዎች ተገናኝተው በጥልቅ ፍቅር ከወደቁ - ለአንዲት ቅፅበት እንኳን ቢሆን በመሃላቸው ፍርሃት አይኖርም፡፡ መብራት በርቶ ጨለማ ሳይኖር አነድ ሚስጥራዊ ቁልፍ አለ - ፍቅር፡፡

በህያውነታችህ ውስጥ ፍርሃት እንዳለ ከተሰማችሁ የበለጠ አፍቅሩ። በፍቅር ድፈሩ፣ ደፋር ሁኑ፤ የፍቅር ጀብደኛ ሁኑ፡፡ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የበለጠ አፍቅሩ፣ የበለጠ ባፈቀራችሁ ቁጥር ፍርሃታችሁም የዚያኑ ያህል ይቀንሳል፡፡

ፍቅር ስል ከፆታ እስከ ሳማዲ ያሉትን እርከኖች ማለቴ ነው፡፡ በጥልቀት አፍቅሩ።

በፆታዊ ግንኙነት በጥልቀት ካፈቀራችሁ ከአካላችሁ ብዙ ፍርሃት ይወገዳል፡፡ ሰውነታችሁ በፍርሃት የሚንቀጠቀጥ ከሆነ የፆታ ፍርሃት አለባችሁ ማለት ነው፤ ከዚህ በፊት በጥልቅ የፆታዊ ግንኙነት ውስጥ አልነበራችሁም፡፡ አካላችሁ ሲንቀጠቀጥ ሰውነታችሁ አልተረጋጋም ማለት ነው፡: .

በጥልቀት አፍቅሩ - ወሲባዊ እርካታ ፍርሃታችሁን በሙሉ ጠራርጐ ያጠፋባችኋል፡፡ ፍርሃታችሁ ተጠራርጐ ይጠፋል ማለት ደፋር ትሆናላችሁ ማለት አይደለም፡፡ ደፋሮች የፈሪዎች ግልባጮች ናቸው:: ፍርሃት በሙሉ ተጠራርጐ ይጠፋል ስል ፍርሃትም፣ ድፍረትም አይኖሩም ማለቴ ነው፡፡

ደፋር የምትሉዋቸውን ሰዎች ተመልከቷቸው:: በውስጣቸው ጥልቅ የሆነ ፍርሃት እንዳለባቸው ትገነዘባላችሁ፣ ከውጭ ሸፋን አበጅተው ነው ደፋር የመሰሉት፤ ድፍረት ፍርሃት አልባነት አይደለም:: ድፍረት ጥሩ መከላከያ፣ ከለላ፣ ጥሩር ያለው ፍርሃት ነው፡፡ "

ፍርሃት ሲጠፋ ፍርሃት አልባ ትሆናላችሁ፡፡ ፍርሃት የሌለበት ሰው በማንም ላይ ፍርሃትን አይለቅም፤ ሌላም ሰው ፍርሃት እንዲያሳድርበት አይፈቅድም፡፡

ጥልቅ የሆነ ወሲባዊ እርካታ አካልን ያረጋጋል፡፡ ሰውነት ምሉዕነት - ስለሚሰማው በጣም፣ በጣም ጥልቅ የሆነ ጤንነት በአካላችሁ ይሰራጫል፡፡

ሁለተኛው ደረጃ ፍቅር ነው። ሰውን ያለ ገደብ አፍቅሩ በአእምሮአችሁ ውስጥ አንድ የሚገድባችሁ ነገር ካለ ማፍቀር አትችሉም። እነዚያ ሁኔታዎች እንቅፋት ይሆኑባችሗል። ፍቅር አስፈላጊያችሁ ከሆነ ስለ ሁኔታዎቹ ለምን ትጨነቃላችሁ? ያለ ገደብ በጥልቀት ማፍቀር በጣም አስፈላጊ ነው - በምላሹ ምንም አትጠይቁ ሰዎችን በመውደድ ምክንያት ብቻ ፍርሃት አልባነትን ማዳበር ከቻላችሁ ለደስታችሁ ስትሉ ብቻ ታፈቅራላችሁ?

ተራ ሰዎች ሁኔታዎቻቸው ሲሟሉሏቸው በቻ ያፈቅራሉ፡፡ “እንዲህ ከሆነክ ብቻ ነው የማፈቅርህ” ይላሉ፡፡ እናት ልጅዋን “ፀባየኛ ከሆንክ ብቻ  እወድሃለሁ” ትለዋለች፡፡ ሚስት ባሏን “እንዲህ ከሆንክ አፈቅርሃለሁ” ትለዋለች፡፡ ሁሉም ሰው ቅድመ - ሁኔታ ሲያስቀምጥ ፍቅር ይጠፋል፡፡

ፍቅር ወሰን የሌለው ሰማይ ነው! ልታጠቡት፣ ልትወስኑት አትችሉም፡፡ ቤታችሁ ውስጥ ንፁህ አየር አስገብታችሁ መስኮቶቻችሁንና በሮቻችሁን ብትቆላልፉ ብዙም ሳይቆይ የታመቀ ይሆናል፡፡ ፍቅር የሚመጣው በነፃነት ነው፡፡ ያን ንፁህ አየር ወደቤታችሁ አስገብታችሁ እንደቆለፋችሁበት ወዲያውኑ ሁሉም ነገር የታመቀ፣ ቆሻሻ ይሆናል።

ይህ የጠቅላላ ሰው ችግር ሆኖ ቆይቷል፡፡ ሰዎች በፍቅር ሲወድቁ ሁኔታዎችን ስለማይደረድሩ ሁሉም ነገር መልካም ይመስላል፡፡ የተፈቀሩት ሰዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይቀራረባሉ፡፡ ከተረጋጉ በኋላ፣ ፍቅር መሰጣጠት ከጀመሩ በኋላ፣ ቅድመ - ሁኔታዎች ይመጣሉ፡፡ ፍቅር የገበያ ዕቃ ይመስል “ይሀን ካልመሰልክ፣ እንዲህ ካልሆንሽ” ይባባላሉ፡፡

በሙሉ ልባችሁ ካላፈቀራችሁ እየተደራደራችሁ ነው:: ሌላኛውን ሰው የሆነ ነገር ካላደረግክልኝ እያላችሁ እያስገደዳችሁ ነው፡፡ ይህ ቅድመ ሁኔታችሀን ካልተሟላ ፍቅራችሁን ትከዳላችሁ፡፡ አሁን እያፈቀራችሁ ሳይሆን ፍቅራችሁን እንደ መቅጫ፣ እንደማስገደጃ እየተጠቀማችሁበት ነው:: ፍቅር ተቀባይ ወይም ፍቅር ሰጪ ብትሆኑም በሁለቱም መንገድ ፍቅር መጨረሻ አይደለም፡፡

ያገባችሁ ከሆነ ለሚስታችሁ ስጦታ ይዛችሁላት ትሄዳላችሁ - ይሄን ጊዜ ደስ ብሏት እያቀፈች ትስማችኋለች፡፡ ወደ ቤታችሁ የሆነ ነገር ይዛችሁ ካልገባችሁ ግን መራራቅ ይፈጠራል፡፡ እንኳን ልትስማችሁ አጠገባችሁ አትደርስም፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ስታደርጉ ፍቅር ለሌሎች ብቻ ሳይሆን ለእናንተም ጠቃሚ እንደሆነ ዘንግታችኋል ማለት ነው፡፡ ፍቅር የሚጠቅመው አፍቃሪዎችን ነው፤ የተፈቀሩትንም ይጠቅማል፡፡

ሰዎች ወደ እኔ ይመጡና “ጓደኛዬ አያፈቅረኝም” ይላሉ፡፡ “እኔ አላፈቅረውም ብሎ የሚመጣ የለም:: ፍቅር ማስገደጃ ሆኗል፡፡ “ጓደኛዬ አያፈቅረኝም።" ስለሌላው እርሱ! ፍቅር እጅግ ድንቅ ክስተት ነው፡፡ ስታፈቅሩ ደስተኛ ትሆናላችሁ፡፡

ብዙ ባፈቀራችሁ መጠን ደስተኛ መሆናችሁም በዚያው ልክ ይጨምራል። ፍቅራችሁ ባነሰ ቁጥር ሌሎች እንዲያፈቅሯችሁ ትጠብቃላችሁ፤ ደስተኛነታችሁ ይቀንሳል፤ የበለጠ ውስን ትሆናላችሁ፤ የራስ ኩራታችሁ ጥገኛ ትሆናላችሁ::

@Zephilosophy
@Zephilosophy
235 views19:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-03 23:52:22 የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ማንነት

ምንጭ ፦ ደስታን የማግኘት ጥበብ
ትርጉም ፦ ዳኜ መላኩ

የሰውን ተፈጥሯዊ ማንነት በተመለከተ ከአርስቶትል እስከ ቻርልስ ዳርዊን፣ ከሲግመን ፍሪውድ እስከ ቶማስ ሆብስ የተለያዩ ሳይንቲስቶች፣ ፈላስፎችና የስነ ልቦና ልሂቃን የየራሳቸውን መላምት ትተው አልፈዋል። አንዳንዶች የሰውን ተፈጥሮ በራስ ወዳድነት ሲፈርጁት፣ አንዳንዶች ደግሞ ሰው በተፈጥሮው ምክንያታዊ ፍጡር እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡ ለአንዳንዶች ሰው በተፈጥሮው መልካም ሲሆን፣ ለአንዳንዶች ደግሞ ሰው በተፈጥሮው ፍጹም ግብዝና ጠብ አጫሪ ፍጡር ነው፡፡

በምእራባውያን እሳቤ ውስጥ ‹‹ሰው በተፈጥሮው ራስ ወዳድና ግብዝ ፍጡር ነው›› የሚለው አስተሳሰብ ለዘመናት ሳይቋረጥ የሰረጸ አስተሳሰብ ነው፡፡ በርግጥ ሰው ራስ ወዳድና ግብዝ ብቻም ሳይሆን ጥቅሙን ከማስከበር የማይመለስ ጠብ አጫሪ ፍጡር መሆኑን የሚገልጹ በርካታ ፈላስፎችና የስነ ልቦና ልሂቃን አሉ፡፡ ይህ አሉታዊና ጸለምተኛ እሳቤ በምእራቡ አለም ፍልስፍና ውስጥ ለረዥም ዘመን ሲንጸባረቅ የኖረ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ማንነት ላይ ያለንን አመለካከት በተለየ አቅጣጫ የጠመዘዘ የአስተሳሰብ ብሂል ሆኗል፡፡

በርግጥ የሰውን አውንታዊ ተፈጥሮ ለመጠቆም የሞከሩ በርካታ የምእራቡ አለም ፈላስፎችም አሉ፡፡ በ18ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ዴቪድ ሂዩም የሰው ልጅን አውንታዊ ፋይዳና ገፅታ በብዙ መልኩ ጽፏል፡፡ ከአንድ ክፍለ ዘመን በሗላም ታላቁ ቻርልስ ዳርዊን የሰው ልጅ ደመ-  ነፍሳዊ እዝነት የተላበሰ ፍጡር መሆኑን ለመጠቆም ሞክሯል፡፡

ዴቪድ ሂዩምንና ቻርልስ ዳርዊንን የመሳሰሉ በርካቶች የሰውን አውንታዊ ገጽታ በተለያየ መልኩ ለማመላከት ቢተጉም፣ ይህ ነው ተብሎ ሊገለጽ የማይችል ምክንያት የሰውን አሉታዊ ማንነት የሚጠቁሙ እሳቤዎች በአስተሳሰብ ብሂላችን ውስጥ በጉልሁ ተንሰራፍተው እንደተቀበሩ የቀሩ ይመስላሉ። በተለይም በ17ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ አካባቢ በሰብአዊ ፍጡር ላይ የማይቀለበስ ጸለምተኛ አቋም የነበራቸው ቶማስ ሆብስን የመሳሰሉ ገናና ፈላስፎች በማህበረሰቡ አስተሳሰብ የፈጠሩት ተጽእኖ ከባድና በቀላሉ የማይፋቅ ነበር፡፡ በቶማስ አመለካከት የሰው ልጅ ፈጽሞ ሊታመን የማይችል ግብዝ፣ ጠብ እጫሪና ራስ ወዳድ ፍጡር ነው።

የሰውን ደግነት የሚያመላክቱ ሀሳቦችን ሁሉ ውድቅ በማድረግ የሚታወቀው ቶማስ ሆብስ፣ በአንድ ወቅት ከመንገድ ለወደቀ ለማኝ ገንዘብ ሲመጸውት ተገኝቶ በወዳጆቹ ላይ ከፍተኛ አግራሞት አጭሮ ነበር። ሆኖም በፈላስፋው ያልተጠበቀ ድርጊት በእጅጉ የተገረሙት ወዳጆቹ ስለለጋስነቱ በጠየቁት ጊዜ ቶማስ ሆብስ የሰጠው ምላሽ «ገንዘቤን የሰጠሁት ለማኙን ለመርዳት አስቤ አይደለም፡፡ ገንዘቤን የከፈልኩት የለማኙ ድህነት ከሚፈጥርብኝ ጭንቀት ለመገላገል ነው›› የሚል ነበር፡፡

ስፔናዊው ፈላስፋ ጆርጅ ሳንታይና በበኩሉ ሰው መልካም ሆኖ ሊገኝ ቢችልም፣ መልካምነቱ `ከይስሙላ የሚመነጭ ታይቶ ጠፊ ሰብእና እንደሆነ ይጠቁማል፡፡ በመሆኑም ‹‹ከውጫዊው መልካምነቱ ትንሽ ጠለቅ ብለን ከቆፈርን በርግጥ ሰው በተፈጥሮው ከራስ ወዳድነቱ መላቀቅ የማይችል ጥቅመኛ ፍጡር መሆኑን እንረዳለን› ይላል ጆርጅ ሳንታያና፡፡

ታላቁ የስነ ልቦና ሊቅ ሲግመን ፍሪውድ ደግሞ፣ ሰው ጥቅመኛና እራስ ወዳድ ብቻ ሳይሆን በግብዝነትና በጠብ አጫሪነት ደመ- ነፍስ ህልውናውን የሚያስጠብቅ አደገኛ ፍጡር መሆኑን ይገልጻል፡፡

ተፈጥሯዊውን ደሰታ ማስመለስ

በምእራባውያኑ እሳቤ ውስጥ የተንሰራፋው ጸለምተኛ አቋም ከምስራቁ አለም እምነት በተለይም ከዳላይ ላማው የቡዲዝም ፍልስፍና ጋር ፍጹም የሚቃረን ይመስላል፡፡ ዳላይ ላማው የሰው ልጅን ተፈጥሯዊ ማንነት በተመለከተ ‹‹ሁላችን ልብ ውስጥ ፍጹም የሆነ የመልካምነት ዘር እለ። በሰውነታችን መልካም መሆን የምንችል ብቻ ሳንሆን መልካምነትን ይዘን የተፈጠርንም ነን» ይላሉ።

ዳላይ ላማው ይህን አቋማቸውን የሚያጠናክሩ እውነታዎችን የሚዘረዝሩት በከፍተኛ የእርግጠኝነት ስሜት ተሞልተው ነው

‹‹ብቡዲዝም ህይማኖታዊ ፍልስፍና ውስጥ ‹‹ቡድሀዊ ተፈጥሮን የሚባል ነገር አለ። የውስጠታችንን ጥልቅና ስረ መሰረታዊ ማንነት የሚያሳየን ይህ ቡድሀዊ ተፈጥሮ ስሜታዊ የሆነ ፍጡር ሁሉ በተፈጥሮው መልካምና ሰላማዊ እንደሆነ ይጠቁማል።

«የሰው ልጅን መልካምነት የሚያረጋግጡ በርካታ ማስረጃዎች አሉ። ከውልደት እስከ ሞት የምናደርገውን እያንዳንዱን የጉዞ ሂደት በጥልቀት ከተመለከትን በርግጥ ከጎናችን ባሉና በነበሩ ሰዎች ፍቅርና መልካምነት እየታገዝን ጉዟችንን እንደምንዘልቅ እንረዳለን፡፡ ይህ ሂደት የሚጀመረው ገና እንደተወለድን ነው። ከእናታችን ማህጸን ወጥተን አዲሲቱን ምድር እንደተቀላቀልን የምናደርገው የመጀመሪያ ነገር የእናታችንን ጡት መጥባት ነው። ወደ ምድር እንደመጣን የሚቀበለን የመጀመሪያው ነገር በሞቃት ፍቅርና ርህራሄ የተሞላው የእናት ጡት ወተት ነው፡፡ ይህ ተፈጥሯዊ ፍቅር ከእናቲቱ ዘንድ ብቻ ያለ አይደለም፡፡ አይን ካልገለጠው ህጻንም ዘንድ ይህ ተፈጥሯዊ ፍቅር አለ፡፡ በርግጥ ህጻኑ የሆነ አይነት ፍቅርና ተፈጥሯዊ የሆነ የትስስር ስሜት ባይኖረው የእናቱን ጡት ለመጥባትም ሆነ የእናቱን እቅፍ ተማምኖ በሰላም ለማሽለብ ባልፈቀደ ነበር።

«አካላዊ አፈጣጠራችንንም ካጤንን ፍቅርን እንጂ ጥላቻን ለማመንጨትም ሆነ ለማስተናገድ እንዳልተፈጠርን እንረዳለን። የጥላቻና የንዴት ስሜት በወረረን ቁጥር መላ አእምሯችን ሲታወክና አካላችን ሲነድ ይሰማናል። ከአካላዊና አእምሯዊ ደህንነታችን ጋር መስማማት የሚችለው ፍቅርና ውስጣዊ ሰላም ብቻ ነው።

‹‹በርግጥ የሰው ልጅ በተፈጥሮው መልካም ነው ስንል በዙሪያችን የምናየው ግጭት፣ ግብዝነትና ጠብ አጫሪነት ከየት መጣ? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም፡፡ በየእለቱ በዙሪያችን ሲከሰቱ የምናያቸው ግጭትና ውጥረቶች ልንሸሽጋቸው የማንችላቸው ገሀድ እውነታዎች ናቸው፡፡ ግጭት በግለሰቦች አእምሮ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በግለሰቦች፣ በማህበረሰብ ብሉም በሀገራት የእርስ በርስ ግንኙነት ውስጥ ሳይቀር በየጊዜው የሚከሰት እውነታ ነው። ይህንን እውነታ በመመልከትም ብዙዎች የሰው ልጅ በተፈጥሮው ግብዝና ጠብ አጫሪ ፍጡር ነው ከሚል ድምዳሜ ደርሰዋል።»

ዳላይ ላማው ለተወሰነ ቆይታ ሲያሰላስሉ ቆዩና ከተቀመጡበት ሰገግ ብለው ሀሳባቸውን አበክረው ማብራራት ጀመሩ። ‹‹ይህም ሆኖ በሰው ልጅ ተፈጥሯዊ መልካምነት ላይ ያለኝ እምነት ፈጽሞ የማይናጋ ነው። ምናልባት ቁጣ፣ ሁከትና ብጥብጥ በመሀላችን ሊከሰት ይችላል። ሆኖም ይህ የሰው ልጅ ተከታይ እንጂ ቀዳሚ ተፈጥሮ ሊሆን አይችልም፡፡ ይህ አይነቱ አሉታዊነት የሚከሰተው ፍቅርና መልካምነትን ለማሳየት የምናደርገው ያላሳለሰ ጥረት ከሽፎ ሲገኝ ብቻ ነው። ብዙዎች የፍቅር ውጤቱ ተስፋ አስቆራጭ መስሎ ሲታያቸው የጥላቻን መንገድ ይያያዙታል። በፍቅር የሞከርነው ሲሰናከል በጥላቻ ለማሳካት እንነሳለን። በርግጥ ክፉ ሆኖ መገኘትን የሚመርጥ ማንም የለም፡፡ ሆኖም ሰዎች መልካም ለመሆን የሚያደርጉት ጥረት የከሸፈ መስሎ ሲሰማቸው የክፋትን መንገድ ይሞክሩታል።

«በመሆኑም ክፋትና ጠብ አጫሪነት በሰው ልጅ ላይ ሊስተዋል ቢችልም ከተፈጥሯዊ ማንነቱ የሚመነጭ ሳይሆን በአስተሳሰቡ ግድፈት የሚፈጠር ነው፡፡ ክፋትና ጭካኔ አእምሯችንን በተሳሳተ መልኩ ከመጠቀም የሚመነጭ የባህሪ መዛባት ነው።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.5K viewsedited  20:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 09:31:22 ራስህን ካልሆንክ በተኮረጀ ሕይወት ዘመንንህን ትጨርሳለህ!
(እ.ብ.ይ.)

ዘመኑ የግልቦች ነው፡፡ ቁምነገር የሌለው ትውልድ እየተመረተ ነው፡፡ ለጥበብ የሚንጋጋ ዕውቀት ቆፋሪ፣ እውነት መርማሪ እያነሰ ነው፡፡ ሩጫው ገንዘብ ወዳለበት ነው፡፡ እሽቅድምድሙ ቁሳዊ ነው፡፡ ፉክክሩ አለባበስና አበላል ላይ ነው፡፡ የዘንድሮ ቢዝነስ እውነት፣ እምነትና ሃቅ የለበትም፡፡ ሃይማኖቱም፣ ፖለቲካውም፣ ሙያውም፣ ንግዱም፣ ትምህርቱም፣ ፍቅሩም፣ ትዳሩም፣ ወዳጅነቱም፣ ዝምድናውም፣  ወዘተውም እየተሸቀበ ነው፡፡ መንጋው የሚንጋጋው ለራሱም ለሐገሩም የማይጠቅም ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ረጋ ብሎ የሚያስብ፣ ከመንጋው ተለይቶ መንጋውን የሚመልስ ጠፍቷል፡፡ መሪውም ተመሪ፤ ተመሪውም ደንባሪ ሆኗል፡፡ ሁሉም እየተምዘገዘገ ያለው ወደገደሉ ነው፡፡ “ሐሰተኛው በእምነት ስም” መፅሐፍ ገፅ 61 ላይ ‹‹ከኋላ የሚከተል መምሕር፣ ከፊት የሚቀድም ደቀመዝሙር፤ ሁኔታው ሁሉ የተምታታ ነው›› እንዳለው እርስበርሱ የተምታታ ሐገር ባለቤት ሆነናል፡፡!

የሐሽማል ደራሲ፡-

‹‹አሁን ዘመኑ የጠቢባን ሳይሆን የግልቦች ነው!›› ይለናል፡፡

እውነትነት አለው! አዎ እምነቱ ግልብ ነው፤ እውቀቱ ግልብ ነው፤ ስርዓቱ ግልብ ነው፣ አመራሩ ግልብ ነው፤ ግልብነት የዘመናችን ምልክት ሆኗል፡፡ ዛሬ ዶክተር ምህረትአብ ደበበ በ‹‹ሌላሰው›› መፅሐፉ እንደሚገልፀው ‹‹ማድረግም አለማድረግም›› ኪሳራ ሆኗል፡፡ በብዙ ነገር ረፍዶብናል፡፡ የያዘን አዚም በቀላሉ የሚለቀን አይደለም፡፡

ዓለማየሁ ገላጋይ ‹‹የተጠላው እንዳልተጠላ›› መፅሐፉ ገፅ 81 ላይ፡

‹‹የማትችለውን ዓለም በሰልፍ የምትኳኳነው፤ የምትችለውን ዓለም ባለመገንባትህ ነው፡፡›› ይላል፡፡

ልክ ነው! አዎ ዓለማችንን ተሰርቀናል፡፡ የእኛ ባልሆነ ዓለም ውስጥ ነው እየተንገላታን ያለነው፡፡ ሌሎች ባዋቀሩት የዓለም ስርዓት ውሰጥ ስለምንኖር ነው ኑሯችን የማይመች፣ ሕይወታችን መከራ ብቻ የሆነው፡፡ በልካችን የተሰፋ ርዕዮት ዓለም ስለሌለን ገልብጠን ያመጣነው ስትራተጂና ፖሊሲ ሱሪ ባንገት ሆኖብናል፡፡ ለህዝባችን የሚሆን፣ እንደሐገራችን ተጨባጭ ሁኔታ ሊያዋጣን የሚችል ስርዓት የለንም፡፡ መልካሙን የአባቶቻችንን ጥበብ ጥለነዋል፡፡ እኛነታችንን ንቀነዋል፡፡ የእኛ ባልሆነው የባዕድ ጌጣጌጥ ተማርከናል፡፡ በሰው ጥበብ ለማጌጥ እላይ ታች እንላለን፡፡ ምክንያቱም አሳቢ ሰው አጥተናል፡፡  ተመራምሮ አዲስ መንገድ የሚያሳየን ለራሱም ለወገኑም የሚተርፍ ዜጋ ተቸግረናል፡፡ ተማርኩኝ የሚለውም ለሆዱ ብቻ እንጂ ለገዛ ራሱ ነፍስ እንኳን አልተረፈም፤ እውቀቱ ከአንገት በታች ነው፡፡

ወዳጄ ሆይ.... ንጉስ ሰለሞን ‹‹ልጄ ሆይ...... ከሕዝብ ጋር አትሂድ!›› የሚልህ ከህዝብህ ተለይተህ ጥፋ ለማለት ሳይሆን ለሕዝብህ የሚሆን መፍትሄ ታበጅ ዘንድ ከመንጋው ተለይተህ አስብ እያለህ ነው፡፡ ከህዝብ ጋር ሙሉ ጊዜህን የምታጠፋ ከሆነ የምታስብበት ጊዜ አይኖርህም፡፡ ህዝብ በተፈጥሮው በወል ነው የሚያስበው፡፡ አይመረምርም፣ አይፈትንም፣ የተቀበለውን መስጠት እንጂ አዲስ የሕይወት መንገድ አይቀርፅም፡፡ ህዝብን የምትከተል ከሆነ ለራስህም፣ ለሐገርህም አትሆንም፡፡ ማሰላሰያ፣ ማገናዘቢያ፣ ራስህንም ዓለሙንም ማንበቢያ ጊዜ ከሌለህ ራስህን ዘንግተህ ያንተ ባልሆነው የሌሎች ዓለም ስደተኛ ነው የምትሆነው፡፡ መንጋው ያንጋጋሃል!

ወዳጄ ሆይ.. ወዳጅነት መልካም ነው፤ ዝምድና አይከፋም፣ አብሮአደግነት ደግ ነገር ነው፤ ባልንጀርነት ደስ ይላል፡፡ ነገር ግን የማሰቢያህን ጊዜ የሚሻማ ማንኛውም የማህበራዊ ግንኙነት ሁሉ ዘለቄታዊ ጥቅም አይሰጥህም፡፡ ሰዎች በዘልማድ ባሰመሩት የአኗኗር መስመር ብቻ መሄድ የሚያስገኘው አንዳች ነገር የለም፡፡ የብዙዎቻችን ሕይወት አሰልቺ እየሆነ የመጣው በድግግሞሽ ህይወት ውስጥ ስለምንመላለስ ነው፡፡ ኑሯችን አዙሪት የሆነው በሰጡን ርዕዮት ዓለም፣ ባቀበሉን የአኗኗር ዘይቤ ስለምንጓዝ ነው፡፡ የራሳችን መንገድ የሌለን የማሰቢያ ጊዜ ስላጣን ነው፡፡ የተወጠርንበትና የተጠመድንበት ነገር ሁሉ የሚያለማን ሳይሆን የሚያጠፋን ነው፡፡ በራሳችን መንገድ ካላሰብን የትም አንደርስም፡፡ እንዲሁ የኋሊት እንምዘገዘጋለን፡፡ ህዝብነት አያተርፍም፤ መንጋነት በራስህ እንዳትተማመን ያደርግሃል፡፡ ለህዝብ መቆም እንጂ ከህዝብ ጋር መሄድ የተለየ ውጤት አያስገኝም፡፡ ለህዝብህ ጠብ የሚል መፍትሄ አምጠህ የምትወልደው ከመንጋው ተነጥለህ ማሰብ ስትችል ብቻ ነው፡፡ መነጠልህ እስመጨረሻው የሚለይህ ሳይሆን ህዝብህን መልሶ እንዲጠቅም የሚያደርግ ነው፡፡

ወዳጄ ሆይ.... ምርጫዎችህን ለመምረጥ፣ የሕይወት መንገድህን ለመቀየስ፣ መነሻህን አሳምረህ ፍጻሜህን ለማስዋብ አንተ አንተን ሆነህ መገኘት አለብህ፡፡ ለራስህ የማታውቅ ከሆነ ሌሎች ባወቁትና በቀረፁት መንገድ ትከተላለህ እንጂ ራስህን አትመራም፡፡ ስታስብ፣ ስትመረምር፣ ስታሰላስል፣ ስታስተውል፣ አዲስ ሃሳብ ስትፈጥር ግን ችግሮችህን ትቀርፋለህ፣ መሰናክሎችህን ትሻገራለህ፣ ስልጣኔን ታመጣለህ፡፡ ራስህን ከሌሎች ባርነት ነፃ ታወጣለህ፡፡ አልያ ግን በመንጋው ተጠልፈህ በራስህ መንገድ ትመላለስ ዘንድ እንዳትችል አቅም ታጣለህ፡፡ ተከታይነት በራስህ ፀንተህ ለመቆም ሃይል እንዳይኖርህ ያደርግሃል፡፡ ተጎታች እንጂ መሪ አትሆንም፤ ጠባቂ እንጂ ሰጪ ትሆን ዘንድ አትችልም፡፡ የሰው ዓለም መፃተኛ እንጂ የራስህ ዓለም ሰሪ ለመሆን አይቻልህም፡፡ በተኮረጀ ሕይወት ዘመንንህን ትጨርሳለህ፡፡

ባለመድሐኒት ሆይ....
ራስህን አድን!
ራስህን


ል!
አንተነትህን
ቀ-ጥ-ል፣
እስትንፋስህን ቀ-ጣ-ጥ-ል፡፡

ቸር ቅጥ’ለት! ደግ ንጥ’ለት!

እሸቱ ብሩ ይትባረክ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.0K views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 22:09:20 ስቃይን መጋፈጥ

ምንጭ ፦ ደስታን የማግኘት ጥበብ
ትርጉም ፦ ዳኜ መላኩ

በቡድሀ ጊዜ ካይሳኦታሚ የተባለች አንዲት ምስኪን እናት አንድ ልጇን በሞት ተነጠቀችና ከባድ ሀዘን ወደቀባት፡፡ ይህቺ ምስኪን እናት የመጽናኛ ልጇ ሞት የምትቋቋመው አይነት አልነበረምና እጣ ፈንታዋን በጸጋ መቀበል ተሳናት፡፡ እናም ልጇን ከሄደበት አለም የሚመልስ መድሀኒት ፍለጋ አዋቂ፣ ጠቢብ ካለበት ስፍራ ሁሉ መዞር ጀመረች፡፡ ከአንዱ ጠቢብ ወደ ሌላው እየዞረች የሞትን መድሀኒት ስታጠያይቅ ሰዎች ወደ ቡድሀ ይመሯትና ቡድሀ ዘንድ ትቀርባለች፡፡

እንደ ባህሉ እጅ ነስታ ስታበቃም ቡድሀን ‹‹ልጄን ከሞት የሚመልስ መድሀኒት ልታገኝልኝ ትችላለህ?›› ስትል ትጠይቃለች።

ቡድሀም ምንም ሳያቅማማ ‹‹አዎን..... አንድ የማውቀው መድሀኒት አለ›› ይልና አክሎም ‹‹ሆኖም መድሀኒቱን ለመስራት የሚያስፈልገው ቅመማ ቅመም መገኘት አለበት›› ይላታል፡፡

እናቲቱ ልጇን ከሞት የሚመልስ መድሀኒት በመኖሩ እፎይ ትልና በተስፋ ‹‹ምንድን ነው የሚያስፈልገው? ምን ላምጣ?›› ስትል ትጠይቃለች።

‹‹አንድ ጭብጥ የሰናፍጭ ፍሬ ማምጣት ይኖርብሻል›› ይላታል ቡድሀ፡፡

እናትየው የሰናፍጭ ፍሬውን ካለበት ፈላልጋ እንደምታመጣ ቃል ገብታ ትነሳለች። ሆኖም ቡድሀን ተሰናብታ ልትወጣ ስትል አንድ ማስጠንቀቂያ አክሎ ይነግራታል። ‹‹ሰናፍጩን ማምጣት ያለብሽ ሞት ገብቶ ከማያውቅበት ቤት ነው፡፡ ልጁን፣ ሚስቱን፣ ወላጆቹን ወይም አገልጋዮቹን በሞት ካልተነጠቀ ሰው ቤት ነው ሰናፍጩ መምጣት ያለበት» ሲል ያስጠነቅቃታል፡፡

እናትየው በዚሁ ትስማማና የሰናፍጭ ፍሬውን ማፈላለግ ትጀምራለች። ከቤት ቤት እየዞረች ታጠያይቃለች፡፡ በየገባችበት ቤት የጠየቀቻቸውን ሰናፍጭ ለመስጠት ቢስማሙም በቤታቸው ውስጥ ሰው ሞቶባቸው እንደሆን ስትጠይቅ ሁሉም በሞት የተነጠቁትን ይነግሯታል፡፡ አንዳንዶቹ ልጃቸውን፣ አንዳንዶቹ ወላጆቻቸውን በሞት አጥተዋል፡፡ አንዳንድ ቤት ውስጥ ባል ወይም ሚስት ስትሞት ቤቶች ውስጥ ደግሞ ሰራተኛና የሴት አገልጋዮች በህይወት የሉም፡፡ እናቲቱ በየቤቱ እየገባች ብትጠይቅም ሞት ቀድሟት ያልገባበት ቤት ልታገኝ አልቻለችም፡፡

ካይሳኦቶሚ ሞት ያልደረሰበት ቤት እንደሌለ ስትረዳ፣ በርግጥ ሞት በርሷ ላይ ብቻ የወደቀ ሀዘን እንዳልሆነ ተገነዘበች፡ ሁሉም ሰው የሚወደውን አጥቷል። ሞት በሁሉም ላይ የሚደርስ የህይወት እጣ ፈንታ ነው፡፡ ይህን በማየት ካይሳኦቶሚ የልጇን ህይወት አልባ አካል ይሁን ብላ ተቀብላ ወደ ቡድሀ ተመለሰች፡፡ ቡድሀም በታላቅ ርህራሄ እንዲህ ሲል አጽናናት

‹‹ልጅሽን በሞት ያጣሽው አንቺ ብቻ አይደለሽም፡፡ የሞት ህግጋት በምድራዊ ፍጡራን ላይ ሁሉ የተጣለ ነውና ከቶውኑ ቋሚ የሆነ የለም።"

«የእናቲቱ ጉዞ በርግጥ ከምድራዊው ሀዘንና ስቃይ ነጻ የሆነ ሰብአዊ ፍጡር እንደሌለ የሚያመላክት ንግርት ነው፡፡ ይህን እውነታ መገንዘብ ውስጣዊ መረጋጋትን የሚያሰርጽ ታላቅ ሀይል አለው። ስቃይ የሁሉም ሰው እጣ ፈንታ መሆኑን ማወቅ ብቻውን ሀዘንና ህመማችንን ባያስወግደውም ይህንን ተፈጥራዊ እውነታ መቀበል ችግርና ህመምን በመታገል የምናተርፈውን ተጨማሪ ስቃይ ይቀንሳል።

"ህመምና ስቃይ በሁሉም ላይ የሚደርስ የህይወት ገጽታ ቢሆንም ምንም ጉዳት እንዳልደረሰብን ሁሉ በቀላሉ ልንቀበለው እንችላለን ማለት አይደለም። አሳዛኝ የህይወት ዱብዳዎችን ማስተናገድ በእጅጉ ከባድ ነው። ይህ በመሆኑም ሰዎች ስቃያቸውን ለማምለጥ የሚረዱ የተለያዩ ዘዴዎችን ፈብርከዋል። አንዳንድ ጊዜ ስሜትና አስተሳሰባችንን የሚያደነዝዙ መድህኒቶችን በመጠቀም ከስቃያችን እፎይ ለማለት እንሞክራለን። አንዳንዴም የህይወት እውነታዎቻችንን የሚያስረሱ አልኮልና አደንዛዥ እጾችን በመጠቀም ከችግራችንም ከራሳችንም ለማምለጥ እንማስናለን። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ከስሜታዊ ስብራቶቻችን ለመሸሽ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ውስጣዊ የሆነውን ስነ ልቦናዊ ትግል እናካሂዳለን፡፡ አንዳንዴም ችግራችንን በመካድ ስቃዩን ላለመጋፈጥ ስሜታችንን በውስጣችን እናዳፍናለን፡፡ ወይንም ችግሩ መኖሩንን እናምንና ህመሙን ላለማሰብ አእምሯችንን ጎጂና ትርጉም አልባ በሆኑ ጉዳዮች እንጠምዳለን፡፡ ብዙዎቻችን ደግሞ ችግራችንን ላለመቀበል ጥፋታችንን በሌሎች ላይ አላከን ሰዎችን እንወቅሳለን፡፡››

‹‹ስቃይ ተፈጥሯዊ እውነታ ነው፡፡ ለጊዜው ልናስታግሰው ብንችልም ለዘላለሙ ልናስወግደው አንችልም፡፡ ፈውስ እንዳላገኘ ቁስል ውስጥ ለውስጥ እየመረቀዘ በየጊዜው እዥ ያነባል፡፡ በየጊዜው የሚሰጠው መድሀኒት ውጪውን ቢያደርቀውም ውስጡ መግል እንደቋጠረ ይቀራል።

«ምናልባት ስቃይን በአልኮልና በአደንዛዥ እጽ ለጊዜው መሸሽ ይቻል ይሆናል፡፡ ሆኖም በዚህ የማያቋርጥ የሽሽት ሂደት የሚፈጠረው ግላዊና ማህበራዊ ጉዳት ወደ አልኮል ከመራን ስቃይ የባሰ ህመምና ችግር ይፈጥራል፡፡ ስቃያችንን ላለመቀበልና ለማዳፈን በውስጣችን የምናካሂደው ስነ ልቦናዊ ትግል ህመማችንን በጥቂቱ ሊያስረሳን ቢችልም ችግሩ ሳይፈታ ተቀምጦ ይቀራል፡፡

ስቃይ ከሰው ልጅ ህልውና ሊወገድ የማይችል ተፈጥሯዊ ገጽታ መሆኑን በመግለጽ ቢጀምሩም፣ አቀራረባቸው ከዚህ ስቃይ ነጻ መውጣት የምንችልበት መንገድ እንዳለ የሚጠቁም ነበር፡፡ ሆኖም በዳላይ ላማው እምነት ሁሉም ነገር እውነታውን ተቀብሎ ከመጋፈጥ ይጀምራል፡፡

‹‹በእለት ተእለት ህይወታችን ውስጥ ችግሮች መከሰታቸው የማይቀር ነው፡፡ በማንኛውም ሰው ህይወት ውስጥ ከሚከሰቱ ሊወገዱ የማይችሉ ችግሮች ውስጥ በዋነኝነት የሚጠቀሱት እርጅና፣ ህመምና ሞት ናቸው ስለነዚህ ችግሮች አለማሰብ ችግሮቹን በማስረሳት ጊዜያዊ እፎይታ ሊሰጠን ቢችልም ችግሮቹን ከመሸሽና ከመራቅ ይልቅ ፊት ለፊት መጋፈጡ የችግሮቹን ጥልቀትና የሚያስከትሉብንን ጉዳት በትክክል ለመገንዘብ ያስችላል፡፡

‹‹በጦርነት ውስጥ ስለ ጠላትህ ትጥቅና የውጊያ ስልት ትኩረት ላለመስጠት ብትሞክር ተገቢውን ዝግጁነት ከማጣትም ባሻገር በፍርሀት ትታሰራለህ፡፡ ሆኖም የጠላትህን አቋም፣ ትጥቅና የውጊያ ብቃት ጠለቅ ብለህ ብትመረምር በተሻለ ዝግጅትና ቁርጠኝነት ውጊያውን ትጀምራለህ፡፡ ስለ ጦርነት በቂ እውቀት የሌለው፣ ሽጎጥና ቦምብ አይቶ የማያውቅ ወታደር እራሱን በበቂ ሁኔታ ሳያዘጋጅ ለጦርነት ቢሰለፍ ምናልባት ገና ሳይመታ በድንጋጤ እራሱን ሊስት ይችላል፡፡ ሆኖም የሚገጥመውን ሁኔታ አስቀድሞ ሲያስብበት ከሁኔታው ጋር አብሮ ለመሄድ ይቀለዋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ችግሮችህን ከመርሳት ይልቅ ፊት ለፊት ለመመልከት ብትሞክር ችግርህን በተሻለ መልኩ የመፍታትና የማስተናገድ እድል ይኖርሀል፡፡››

@Zephilosophy
@Zephilosophy
14.6K views19:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-23 17:49:11 ኤግዚስቴንሻሊዝም እና ኒሂሊዝም

ምንጭ ፦ የፍልስፍና መግቢያ
ደራሲ ፦ ደሳለኝ ስዩም

ኤግዚስቴንሻሊዝም በፍልስፍና ውስጥ ብዙ ከተሠራባቻው ፍልስፍናዊ ንድፈ-ሐሳቦች አንዱ ነው፤ በአንዳንድ ምልከታዎቹ ከኒሂሊዝም ጋር የሚጋራቸው ነጥቦች ስለሚኖሩ ሁለቱን ንድፈ-ሐሳቦች ቁልጭ አድርጎ ማሳየት ባይቻል እንኳ ተዛምዶና ተባዕዷቸውን ለማሳየት መሞከር ተገቢ ነው። ኤግዚስቴንሻሊዝም “አሁን” እና “እዚህ” በሚሉ ነጥቦች ያምናል። “ኒሂሊዝም” ግን በምንም አያምንም፤ ካመነም በምንም ነው።

ኒሂሊዝም የትኛውንም ዓይነት ዓለማዊ ሀቅ አይቀበልም፤ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በሩስያ ሥነ-ጽሑፎች ውስጥ እንዳበበ ወይም እንደተመሠረተ ይታሰባል። በዚያም በሩስያ በነበሩ ተቋማዋዊ መዋቅሮች አመጽ ከመነሳት አልፎ የትኛውም መንግስታዊ፣ ሃይማኖታዊ እና ማኅበራዊ መዋቅርንም መቃወም ችሏል።

“ኤግዚስቴንሻሊዝም” በየትኛውም የሕይወት ትርጓሜ የማይስማማ ነገር ግን እያንዳንዱ ግለሰብ የራሱን ዓለም መሥራት እንደሚችል የሚያስረዳ ወይም በእዚህ እውነት የሚያምን ነው። በጠቅላላው ሁለቱም እሳቤዎች ናቸው። መነጽራቸው የሚለያየው ግባቸው ላይ ነው።

ኒሂሊዝም በምንም ከማመን ይልቅ ምንምን የሚያመልክ ነው። በምንምነት ማመን በክብ ውስጥ ላለ ነገር ሁሉ ዕውቅና መስጠት ነው። “ኤፕሲቲሞሎጅካል” ፍልስፍናቸውም “ራሽናሊዝም” እና “ማቴሪያሊዝም” ነው፡ የግለሰብ ነጻነት ደግሞ የመጨረሻ ግባቸው። አይዲያሊዝም ወይም እምነታዊነት ለእነርሱ ዋጋ የለውም።

ኒሂሊስት ሰዎች “እግዚአብሔር የለም” ብለው የሚያምኑ ሰዎች አይደሉም፤ ይልቁንም የእግዚአብሔርን መኖር ማረጋገጥ እስካልተቻለ ድረስ በእግዚአብሔር መኖር እርግጠኞች አይደሉም። በሌላ ምሳሌ ደግሞ ለማየት አንዲት ሚስት በባሏ ላይ ብትቀላውጥ “ባል ግድ የለም አይጎዳኝም” ብሎ ያልፋል ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ጉዳዩ የሚሆነው ሚስት በሕይወት ውስጥ ትቀላውጥ እንደሆነ ማስረጃዎች በመኖራቸውና ባለመኖራቸው ላይ ነው። ይህም ሆኖ ሚስት መቀላወጧ በማስረጃ የተረጋገጠም ቢሆን ባል የሆነ ጊዜ በእርሷ ላይ ስላለመቀላጡ ማስረጃው ምንድን ነው? ስለዚህም እርግጠኛ የምንሆንበት ሕይወት የለንምና ሚስት ቀላውጣ ብትገኝ የሚደንቅ ሊሆን አይችልም ይላሉ።

ይሄንን ነገራቸውን ሊገለጥ የሚችል ሁለት ገላጭ ምሳሌዎቻቸውን ማየት እንችላለን። “What he wished to believe, that is what each man believes” “ሊያምን የሚመኘው ማንም የሚያምነውን ነው” እና “The life of mortals is so mean a thing as to be virtually un-life” “የሟች መኖር ማለት አለመኖር ነው” ወይም “ሟች ሕይወቱ አለመኖር ነው”። (ሁለቱም አባባሎች በሃይዲገር የተጠቀሱ ናቸው)

ኒሂሊስቶች ለእዚህ እሳቤአቸው አስረጂ የሚያደርጉት የሰው ልጅ ምኞትን እና ቅዠትን ከሕይወቱ ካስወጣ ምንም መሆኑን ይገነዘባል” የሚል ነው። ለመሆኑ የኒሂሊስቶች መጨረሻ ምን ሊሆን ይችላል? እነርሱስ በምን ሊገለጡ ይችላሉ? ሕይወት ትርጉም የላትም፣ ይች ዓለምም ምንም ናት ብለው ያመኑ ኒሂሊስቶች ከእነዚህ በአንደኛው ጥላ ላይ ያርፋሉ።

ፍልስፍናዊ ሞት ፡

እጅ ይሰጣሉ፤ “ሕይወት ትርጉም አልባ ናት ስለዚህም መፈላሰፌ ዋጋ የለውም” ከሚል መነሻ ራሳቸውን በሃይማኖት ጥላ ሥር ይደብቃሉ፤ ወይም በአንድም በሌላ መንፈሳዊ ዋሻ ውስጥ ራሳቸውን ያስቀምጣሉ።

አካላዊ ሞት :

ትርጉም አልባ በሆነ ዓለም ውስጥ በሕይወት መኖር አሰልቺና የስቃይ ምንጭ ስለሚሆንባቸው ራሳቸውን ያጠፋሉ።

መቀበል :

ሕይወት እውነተኛ እና የመጨረሻ ትርጉም እንደሌላት እያወቁ መኖር።

ለመደምደም ሦስት ተመሳሳይ የሚመስሉ ነገር ግን የተለያዩ ፅንሰ ሐሳቦችን እንይ

ኤግዚስቴንሻሊዝም

"በግለሰባዊ ግንዛቤ፣ ግለሰባዊ መልካም ፈቃድና ግለሰባዊ ኃላፊነት ውህድ ኑረት አንድ ሰው በዓለም ውስጥ የራሱን የሕይወት ትርጓሜ መስጠት ይችላል ወይም ይገባዋል” ብሎ የሚያምን ነው።

ኒሂሊዝም

“ዓለም ትርጉም አልባ ነው ብሎ ማመን ብቻ ሳይሆን ለዚህ ዓለም እና ሕይወት ትርጉም ለመስጠት መሞከር በራሱ ምንምነት ነው” ብሎ የሚያምን ነው።

አብዘርዲዝም :

ደግሞ ለሕይወት ትርጉም ለማግኘት የሚደረገው ትግል ሁሉ ከተፈጥሮ የተነሣ ሁሌም ከትርጉም አልባነት ጋር የሚደረግ ግብ ግብ ነው፣ ነገር ግን ሕይወት ማለት ሁሌም ቢሆን ይህንን ተቀብሎ ሕይወት ልትሰጥ የምትችለውን አዎንታዊነት ሁሉ ለማግኘት መፍጨርጨር ነው።

በስተመጨረሻ ሥራ ላይ ያለውን የፍልስፍና ትርጓሜ ማየቱ መልካም ይሆናል። እስካሁን ያየናቸው የፍልስፍና ትርጓሜዎች በቅን ልቦና ያየ ሰው ፍልስፍናን እንዲህ ሊበይነው ይችላል። ወይም ይገባል።

“ፍልስፍና ማለት ጥብቅ በሆነ ምክንያታዊነት ላይ በመመሥረት በጣም ጠቃሚ የሆኑ ጥያቄዎችን ለመመለስ መሞከር ማለት ነው”

በዚህ ብያኔ ውስጥ ያለው መሠረታዊ ጭብጥ “ጥብቅ እና ምክንያታዊ" የሚለው ነው። ነገር ግን “ስለምን?” –እዚህ ጋ ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ። በማውጠንጠን፣ በመተንተን ወይም በኀልዮአዊነት መንገዶችም ቢሆን እያንዳንዳቸው በሚያተኩሩባቸው ጉዳዮች ላይ በቂ አስረጂ ያለውን ጥብቅ ምክንያታዊነት ማቅረብ ነው። እንዳየነውም በተለያየ መደብ ያሉት ፈላስፎች በራሳቸው ጠቃሚ ያሏቸውን ጥያቄዎች ለመመለስ ይሠራሉ። እነዚያም ጥያቄዎች ለእነርሱ መሠረታዊ ናቸው።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.7K views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 22:18:08 .... ካለፈው የቀጠለ

የፆታ ፍልስፍና ......3

ይሄንን አተያይ ለመቀንጠስ ይላሉ እነዚህ አሳቢያን <ለሴቶችም ልክ እንደ ወንዶች ሁሉ ዕድልን መስጠት ያስፈልጋል። ሴቶቹ አይችሉም ብሎ ከመከልከል ይልቅ ወንዶች በሚሰለፉበት ፖለቲካዊና ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ ተቋም ውስጥ ሴቶችም ተመሳሳይ ዕድል እንዲያገኙ ማድረግ ችግሩን ይፈታዋል። ይህን ማድረግ ከተቻለ እንደ ፕሌቶና አርስቶትል
ያሉት ፈላስፎች ያስቀመጧቸው <<ሁሉም ሴቶች የማይለወጥ የማይናወጥ የዝቅተኝነት እጣ ፈንታ አለባቸው›› የሚለውን ደምሳሽ ዕይታ መቀየር
ይቻላል ይላሉ።

የሃይማኖት፣ የማኅበረሰብ እና የፖለቲካ ተቋማትን በማደስ (Reform) ትውልዱ በአመለካከቱ የተሻለ ግራ ቀኙን ማገናዘብ የሚችል ሴትን ከወንድ እኩል መመልከት የሚችል ማድረግ ይቻላል የሚለው የአሳቢያኑ ዕይታ ነው። “ስቱዋርት ሚል” እና “ዊልስቶን ክራፍት” ይሄንን ለማለት ያስቻላቸው “ሴቶች የበታች ናቸው።” የሚለው አመለካከት “ተፈጥሯዊ ያልሆነ ሰው ሠራሽና በመፈጠር የመጣ ሳይሆን በመፍጠር የመጣ ነው” ከሚል መነሻ ነው። በእነዚህ ሰዎች ዕይታ ነባሩን ማኅበረ-ፖለቲካዊ መዋቅር እንደገና ማደራጀት በራሱ ለሴት ጨቋኝ የሆነውን እሳቤ ከሥር ለመመንገል ያስችላል።

“Vindication of the rights for women” በሚለው ዝነኛ መጽሐፏ ዊልስቶን ክራፍት እንዲህ ትላለች፤ “ሴቶች በተፈጥሯቸው ሆደ ቡቡ ደካማ፣ አልቃሻ፣ ስሜታዊ እና እኑስ ሆነው አልተፈጠሩም። ይልቁንም በማኅበረሰቡ እንዲህ እንዲሆኑ ተደርገው ይሠራሉ እንጂ.. ሴቶች በተፈጥሮ ከተፈጠሩት በላይ ማኅበረሰቡ እንዲሆኑ ወደ ሚመኝላቸው ደካማነት እንዲጓዙ የሚደረግባቸው ጫና ይበዛል።”
በዊልስቶን ክራፍት እሳቤ ሴቶችን ልፍስፍስ፣ አልቃሻና ጥገኛ አድርጎ የሠራቸው መፈጠር (Nature) ሳይሆን ማኅበረሰቡ (Nurture) ነው። የእዚህ ሁሉ መሠረት ደግሞ አሁን ያለው የትምህርት ሥርዓት ነው” ትላለች። በየሀገሪቱ ያለውን የተንሸዋረረ የትምህርት ሥርዓት ስትተችም እንዲህ ትላለች። .... “Like the flowers which are planted in too rich a soil, strength and usefulness are sacrificed to beauty –(1792:7)

እንዲህም ትላለች ክራፍት ... “በዚህ የተነሣ ሴቶች አመክንዮ የመጠቀም ብልሃታቸውን ለማዳበር እንዳይችሉ ተደርገዋል። ትምህርቱም የሰውን ልጅ ወደ ፍጽምና የሚወስድ መሆኑ ቀርቶ ሰዎች ኑሯቸውን ብቻ እንዲኖሩ የሚያስተምር ሆነ።”

ሰዎች የሚኖሩት ኑሮ ደግሞ የሴት እና የወንድን ዕጣ ፈንታ ቀድሞ የበየነ ነው። እየተሰጠ ያለው ትምህርት ሴቶች እንዴት ሰጥ ቀጥ ለጥ ብለው መኖር እንዳለባቸው (አንገትን ደፍቶ መኖርን) ሲያስተምር ወንዶች ደግሞ እንዴት አለቃ፣ አዛዥና ጉልበተኛ መሆን እንዳለባቸው የሚያስተምር ሆኗል።

ወንዶች ከሴቶች ይልቅ በአካል ጠንካራ እና ሁሉን ቻይ ተደርገው ስለተሠሩ ሴቶችን እንደ ጥቅም የለሽ ወይም እንደ መገልገያ ቁስ ለመጠቀም ምክንያት መሆን የለበትም።

በሌላ በኩል “ስቱዋርት ሚል” ተፈጥሮ (Nature) የሚለውን እሳቤ አምርሮ ይቃወማል። “the subjection of women” በሚለው ሥራው ውስጥ «በሚኖረን የዕለት ከዕለት ግብብነትና ቅርርብ እየተገነዘብናት እንሄዳለን እንጂ፣ የትኛዋንም ሴት ቢሆን ስለተፈጥሮዋና አንደኛዋ ፤ ስለአንደኛዋ ስላላት ልዩነት ልናውቅ አንችልም። በመሆኑም በተለምዶ ወይም ቀድሞ ባለው ፍልስፍና ውስጥ የሴቶች ተፈጥሮ እየተባለ የሚወራው ነገር ውኃ የማይቋጥር ተልካሻ ሙግት ነው” ይላል። ይሄ ተልካሻ ሙግት የወንዶችን የበላይነት ለማስረጽ ከማሰብ የዘለለም አይደለም ይላል ስቱዋርት ሚል

አባታዊ የሆነው የእዚህ ዓለም አተያይ “ወንዶች በተፈጥሮ አገኙት። የሚባለውን ነገር ሴቶች እንዳላገኙት (እንደማያገኙት) ያስመስላል። ይሄ አባዊ (Androcentric) ሥርዓት በሴቶቹ ላይ የራሱን ፍላጎት እና መላምት ከጫነ በኋላ ይሄ የሴቶች ተፈጥሮ ነው ብሉ ይደመድማል።

በመሆኑም ከዚህ ዓይነቱ የቅጥፈት አተያይ ለመውጣት ወንዶችና ሴቶች ማንነታቸውን የሚያጎለብቱባቸው መንገዶች ለሁሉም የሰው ልጅ (ለሁሉም ፆታ) በእኩል ሊሰጡ ይገባል። ወንዶች ብቻ የሚችሉት እየተባለ ሴቶች ሊከለከሉ የሚችሉበት መንገድ መዘጋት አለበት።

አሁን አክራሪ የሆነውን ምላሽ እንመልከት። ከላይ የተመለከትናቸው ሁለትቶ ፈላስፋዎች ዕይታቸው ለዘብተኛ ነው፤ “ተቋማዊ አሠራርን በማስተካከል ዓለም ስለ ሴቶች ያለውን የተንሸዋረረ ዕይታ ማስታረቅ ይችላል» የሚል ሐሳብ ያላቸው ናቸው። ፈረንሳያዊቷ ኢግዚስቴንሻሊስት "ሲሞን ዲቦቨር” ደግሞ የቀደመውን ፍልስፍና ከመሠረቱ ትንደዋለች።

ፕሌቶ እና አርስቶትል “ነገሮችን ነገር የሚያደርግ የራሳቸው የሆነ የማይለወጥ የማይናወጥ ማንነት (Essence) ሥሪት ናቸው።” በማለት የሞገቱበትን ፍልስፍና ውድቅ ታደርጋለች - “ኢሰንስ” የሚባል ነገር “ኢሴንሻሊዝም” የሚባል ፍልስፍና አይረባም ስትል።

የዲቦቨር መከራከሪያ የነገሩ መገለጫ ከሆነው “ኢሰንስ” ይልቅ የነገሩ ኅልውና (Existence) ይቀድማል። የአንድ ነገር ዕጣ ፈንታውን ለመወሰን መገለጫው ምንነቱ ላይ ሳይሆን መኖር አለመኖር (ጎልዮው) ላይ ነው ማነጣጠር ያለብን” ትላለች። የዲቦቮር ፍልስፍና (Existentialism) በእዚህ የተነሣ ዕጣ ፈንታ ላይ ሳይሆን ነጻነት ላይ ያተኩራል።

“ስለሆነም መገለጫዎችን እያነሡ የሴቶች ዕጣፈንታ ከማለት ይልቅ ሴቶች በራሳቸው ኅልዮአዊ መሆናቸውን ተቀብሎ ፈቃድ እንዳላቸው ማመኑ ነው ትክክለኛ መንገድ” -ትላለች ዲቦቮር።

The second sex”” በተሰኘው ዝነኛ መጽሐፏ “የትኛው አካላዊ፣ ሥነ-ልቡናዊ ወይም ኢኮኖሚያዊ እውነታ ሴቶች በተፈጥሮ ያላቸውን ምንነት ሊወስን አይችልም” ትላለች። “one is not born, but rather, become a woman” (1976፡267) “ሴታዊነት” ወይም «የሴት” ተብለው የተለዩ ሁሉ ለሴቶች እየተሰጡ ያሉ መገለጫዎች
ናቸው።

ይሄ “የሴት” እየተባለ የሚሰጥ መገለጫ ደግሞ ሴቶችን “ሌሎች” እንዲሰኙ አድርጓቸዋል። በመሆኑም ወንድነት እንደ አንደኛ ደረጃ ፆታ ሴትነት እንደ ሁለተኛ ደረጃ ፆታ ተቆጠረ።

ወንዶች ሴቶች “እነርሱ” ሲሉ ዝቅ የሚያደርጓቸውን ያህል ሴቶችም ወንዶችን “እነርሱ” እያሉ ሌላ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያሉ አድርገው እንዲቀበሉ ተገደዱ።

ወንዶች “እኔ” ሲሉ ሴቶችንም “እርሷ” ሲሉ ራሳቸውን ባለቤት አዛዥ የበላይ ሴቶች ደግሞ የበታች መገልገያ ቁስ ያደርጓቸዋል። ከልጅነት ጀምሮ ወንዱ ወንድነት ሴት ሴትነት እየተላበሱ እንዲያድጉ ይደረጋል።

ለወንዱ ጎረድራዳነት፣ ድምቡጭነት፣ ውፍረት ወይም ክሳት መሥፈርት አይሆንም። የወንድ መልክ ለውድድር አይቀርብምና። ወንድ አያለቅስም፤ ወንድ ደረቱን ነፋ ማድረግ አለበት። በአንጻሩ ሴት መኳኳል አለባት፤ ኣካሏን ካልጠበቀች የሚነካት (የሚመኛት) እንደሌለ ይነገራታል። ረጅም ሰዓቷን መስታወት ፊት እንድትቆም ትደርጋለች።

ለዲቦቮር የትኩረት ነጥቧ የሴት ገላ ሳይሆን “ሴት” ራሱ ፆታው ነው። ወንድ ሲነሣ ስለ አካላዊነቱ አይነገርም ይልቁንም ሰለ ወንድነቱ ይነሣል። እንዲያ ከሆነ ሴት ደግሞ ራሱን ችሎ ማንነት ነው፤ “ኅልዮነቱ የተረጋገጠ” ትላለች። በሴት ላይ ያሉ ፈተናዎችም እነዚህ ናቸው ትላለች። በራስ ውበት ፍቅር መውደቅ (ውበት አምላኪነት)፣ ፍቅር (ጥገኝነት) እና ሃይማኖት (ተገዥነት)።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
5.1K views19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 19:32:14 .... ካለፈው የቀጠለ

የጾታ ፍልስፍና........2

ምንጭ ፦ የፍልስፍና መግቢያ
ፀሀፊ ፦ ደሳለኝ ስዩም

ስለዚህም ይላል አርስቶትል- ስለዚህም በተፈጥሮው የተነሣ ወንድ በሴት ላይ ጌታም በሎሌ ላይ የበላይ መሆን አለበት። ለእዚህ ምክንያቱ ደግሞ ወንዶች ከሴቶች ይልቅ አዛዥነት ይዋጣላቸዋል። “ሴቶች ከወንዶች እኩል ስልጣን ቢያገኙስ?" ለሚለው ጥያቄ የአርስቶትል ምላሽ ከፕሌቶ ጋር የሚመሳሰል ነው “ምንም ቢሆን ሴቶች ደካሞች ናቸው” ይላል።

የ20ኛው ክፍለ ዘመን ፈላስፋ “ፍሮይድ” ደግሞ ስለ ወንዶች ልጆችና ሴቶች ልጆች እድገት (ጉልምስና) ያስቀመጠው ንድፈ ሐሳብ በሥርዓተ ጾታ አቀንቃኞች ዘንድ ትልቁ የመከራከሪያ ነጥብ ሆኖ ቆይቷል። እንደ ፍሮይድ ገለጻ ሴቶች ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩ በዝቅተኝነት መንፈስ እየተሰቃዩ ዕድሜአቸውን የሚገፉ ፍጡራን ናቸው። ለእዚህ ሰበቡ ይላል ፍሮይድ- ሴቶች የወንዶች ዓይነት ብልት (የወሲብ አካል) ስለሌላቸው ትንሽነት ይሰማቸዋል፤ የቅናት መንፈስ ያቃጥላቸዋል፤ ራሳቸውን ከወንዶች ጋር እያነጻጸሩም አካላቸውን ይጠላሉ፤ ሁልጊዜም በዚህ የተነሣ ይብከነከናሉ። አፋራም፣ ተሸማቃቂና ተጨናቂ ይሆናሉ። (ፍሮይድ፤1911፤29-33)

የወንድ ዓይነት ብልት ስለሌላቸውም የተሸናፊነት ስሜትን ያዳብራሉ፤ ከወንዶች በታች እንደሆኑ እያደረጉ ራሳቸውን ይስላሉ። “ጎዶሎ ሰዎች ነን” እያሉም ለልባቸው ይነግራሉ። ይሄ የፍሮይድ ዕይታ ከሥነ ልቦናዊ ትንታኔ ባለፈ ሥነ-ሕይወታዊ ይዘት እንዳለው መመልከት ይቻላል፤ ይኸውም በፍሮይድ ዕይታ በጾታ ላይ ሥነ-ሕይወታዊ ውስንነት (BIO -logical determinism) አለ ማለት ነው።

ይሄን የሥነ ሕይወታዊ ዕጣ ፈንታ ውስንነት እንዳለ የሚቀበለው ፍይሮድ «ሴቶች እንደ ወንዶች ሁሉ ጠንካራ ባለመሆናቸው ወንዶች የሚችሉትን መቻል አይሆንላቸውም” ይላል። በምድር ላይ ሁለተኛ ደረጃ ፍጡሮች ሲሆኑ ቀለል ያሉ የሕይወት ተልዕኮዎችን በወንዶች ሥር ሆነው መፈጸም ተፈጥሯዊ ግዴታቸው ነው ይላል። በዚህ የተነሣ ሴት ማለት የተኮላሸ ወንድ ወይም እንደ ወንድ መከወን የማይቻላት ወይም ወንዱ በሚከውነው ነገር እየቀናች (ወንዱ የሚከውነውን እየተመለከተች ሕይወትማ “እንደዚያ ነው” እያለች በቅናት እያረረች) የምትኖር ፍጥረት ናት። የእዚህ ሁሉ ሰበቡ እንደ ወንድ ያለ ብልት ያላት አለመሆኑ የሚፈጥርባት የዝቅተኝነት መንፈስ ነው።

ከፍ ሲል ያየነውን ደመ-ነፍሳዊ (ጅምላ ጨራሽ) ብያኔ አብዛኛው ማኅበረሰብ የሚጠቀምበት ያልተፈተሸ የጋራ አቋም ነበር ለማለት ይቻላል። የጠቀስናቸው ፈላስፋዎችና የሳይንስ ሰዎች ምኞት (ግምት) (Assertion) ከማስቀመጥ ባለፈ አመክኗዊ (Regress) የሆነ ምልከታን አላጋሩንም።

ቀጥለን የምንመለከታቸው በዘመናዊው ፍልስፍና ውስጥ ስማቸው የሚጠራ ፈላስፋዎችም “ሴቶች የበታች ናቸው” የሚል አቋማቸውን ለማስረዳት ሞክረዋል። ከእነዚህ መካከል “ኢማኑኤል ካንት”ና “አርተር ሾፐን ሀወር” ይገኙበታል።

ካንት “Anthropology form a pragmatic point of view” በሚል ድርሳኑ ሴቶችን ከተፈጥሯዊ እና አካላዊ ፍላጎቶቻቸው አንጻር ይተነትናቸዋል። ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩ ይላል ካንት ሴቶች ከወንዶች ይልቅ ስሜት ያጠቃቸዋል። እንደ ሰው ሊያገናዝብ የሚገባው “አመክንዮአዊነት” በስሜታቸው የበላይነት የተጨቆነ ነው። . . .

ይሄ ስሜታዊነታቸውም ሴቶች በሚታዩባቸው የመንበቅበቅ (የመፍራት) እና በራስ ያለመተማመን ችግር ቁልጭ ብሎ ይታያል።

በዚህም የተነሣ ሳይወዱ በግድ የወንድ ጥገኛ ይሆናሉ። ወንድ እንዲጠብቃቸውና “አለሁ” እንዲላቸው ይመኛሉ። ከአመክንዮ ይልቅ ስሜትን ስለሚጠቀሙ ለዕውቀት ለመርህ እና ለምክንያታዊነት ያላቸው አቅም ውስን ይሆናል። “ይሁን እንጂ...” ይላል ካንት –“ይሁን እንጂ የሰው ልጅ እንደ ሰው እንዲቀጥል ሴቶች ለስሜት ያደሩ፣ ፈሪዎችና የወንድ ጥገኛ መሆናቸው አዎንታዊ አስተዋፅኦ አለው።”

ከዚህ ሐሳብ ጋር በሚስማማ ነገር ግን ቆንጠጥ ባለ አገላለጽ የገለጸው ደግሞ የጀርመኑ የሾፐን ሀወር ፍልስፍና ነው። “On women” በሚል መጣጥፉ “ሴቶች አስመሳዮች እና አታላዮች ናቸው” ይላል። “ሴቶች ከተፈጥሯቸው መበደል (መጓደል) የተነሣ ምክንያታዊነትን የማያውቁ በእያዳንዱን ነገር (አጋጣሚ) ውስጥ ራሳቸው ተብለጭልጨው ለመታየት የሚፈልጉ ራስ ወዳዶች፣ ዋሾዎችና አስመሳይ ፍጥረቶች ናቸው” ይላል።

ሾፐን ሀወር እንደሚለው ሴቶች በሰው ልጅ ተፈጥሮ ውስጥ የሚኖራቸው ፍላጎት ትኩረት የመሳብ ነው። በምድር ላይ የሚኖሩትም አንዳች ፈጠራ ለመፍጠር ወይም ልዩ ነገር ለማድረግ ሳይሆን ሁሉም በእነርሱ ላይ ትኩረት ሊያደርግበት የሚችልበትን መንገድ ለመፈለግ ነው። በየአጋጣሚው ለመታየት፤ በብዙኃን ዓይን ውስጥ ለመግባት ይመኛሉ።

የአመክንዮ አቅመ-ቢስነታቸውን ለመሸፈንም ቅን፣ የዋህ፣ ጥሩ ሆነው ይታያሉ። ቀልባቸው የሩቅ ነገርን ይነግራቸዋል፤ አዛኞችና ሆደ-ቡቡዎች ሆነው ይታያሉ። ሴቶች አሁን እየሆነ ባለው ነገር ላይ ወይም ፊት ለፊታቸው ለሚገጥማቸው ነገር ትኩረትን ያደርጋሉ። ይሄም የስሜታዊነታቸው መታያ ነው። ወንዶች ግን ምክንያትን መጠቀም ይችላሉና ያለፈው እና የወደፊቱ ላይ ያውጠነጥናሉ ። ስለዚህም መርሕን፣ ደንብን፣ ዕውቀትንና ምክንያትን በመጠቀም ረገድ የሴቶች ደካማነት ቁልጭ ብሎ ይታያል።

“ራሳቸውን ለመጠበቅ አንበሶች ጥፍርና ጥርስ፤ ዝሆኖች ኩምቢና ጥርስ፣ ኮርማዎች ቀንድ፣ አሳዎች መደበቂያ ቀለም የታደሉትን ያህል ተፈጥሮ ለሴቶች ቅጥፈትን ሰጥታቸዋለች። ሁሉም ብቃት ለወንድ በአካላዊ ጥንካሬና በምክንያታዊነት የተሰጠውን ያህል ሴቶች ይሄንን ለመቋቋም ቅጥፈትን (ውሸትን) ታድለዋል።”

በእርግጥ ሾፐን ሀወር ያስቀመጠው የሴቶች ደካማነት “ደካማነት” ተብሎ ብቻ የሚገለጽ አይደለም። ይላልም ሾፐን ሀወር “ሴቶች ራሳቸውን የሚከላከሉበትና የኅልውናቸው መንገድም ነው። ወንዶች ኅልውናቸውን ለማስቀጠል ጥንካሬን እና ምክንያታዊነትን ሲጠቀሙ ሴቶቹ ደግሞ ስሜትን እና ደካማነትን ይጠቀማሉ።”

ሾፐን ሀወር ሀሳቡን ሲያጠቃልል “ሴቶች ከመውለድ ያለፈ አላማ የላቸውም» ይላል። ሌላ ዓላማ ወይም ፍላጎቶች ቢኖራቸው በራሳቸው አቅም ከመምራትና ከመጋፈጥ ይልቅ የወንዶች ጥገኛ ሆነው ፍላጐቶቻቸው በተዘዋዋሪ መንገድ ያሟላሉ።

እስካሁን ለማየት እንደሞከርነው የሃይማኖት፣ የፍልስፍናም ይሁኑ የሳይንስ ሰዎች ወንዶችና ሴቶች እኩል አይደሉም፤ ወንድ የበላይ ሴት የበታች ናት የሚል አቋም ሲያራምዱ ነበር። ይህ በመላው ዓለም ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ የመሰለ የወል ዘልማድ በጊዜ ሒደት በሴቶችና እና ለሴቶች በሚያስቡ ወንዶች እየተሞገተ ሊመጣ ችሏል። አስቀድሞ ከላይ ላየነው ሴትን ጨቋኝ አመለካከት የምላሽ (Defense) ሥራ ነው የተጀመረው። አመጣጣቸውም ሁለት ወገን ነው - ለዘብተኝነትና አክራሪነት። ከለዘብተኞቹ እንጀምር።

ለዘብተኛ የተሀድሶ ዕይታን ከሚመርጡ ፈላስፎች ጆን ስቱዋርት ሚል እና ሜሪ ዊልስቶን ክራፍት ይገኛሉ። እነዚህ ፈላስፎች በቀደመው እና በሴት ጨቋኙ ፍልስፍና ውስጥ ከሚነሡ ሐሳቦች ሴት በተፈጥሮ ደካማ - ናት የሚል አተያይን ይሞግታሉ።

    ይቀጥላል

@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.9K viewsedited  16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-13 22:16:28 የጾታ - ፍልስፍና......1

ምንጭ ፦ የፍልስፍና መግቢያ
ፀሀፊ ፦ ደሳለኝ ስዩም

የነገሩ ጅማሮ ጥንታዊ ነው። ወንዱ “መጨቆኑን” ሴቷ “መጨቆኗን”፤ አውቀው ወይም ሳያውቁ ዘመናት በሰው ልጆች ታሪክ ላይ ተፈራርቀዋል። ስለዚህም የሴቶች “መብትን መጠየቅ” በአንዴ የፈነዳ ነገር ሊሆን አይችልም። አንዳንድ ምሑራን እንደ ምሳሌም፡- ዳንኤል ጠንክር (2018) ሊሉ እንደሚሞክሩት <<የኢንዱስትሪ አብዮትን ተከትሎ የመጣ እንደ ጎርፍ ደራሽ አይደለም። በተበጣጠሰ መልኩ ይሁን እንጂ ፌሚኒዝም ታሪኩን ወደኋላ መቁጠር የሚችል እምቢተኝነትን ያካተተ የመብት ጠያቂዎች አመጻ እና ተማጽኖ ነው።” (ሰላማዊት 2002)

በዓለም የተነሡ ታላላቅ የሳይንስ፣ የሃይማኖት ወይም የፍልስፍና ሰዎች ሴቶችን የሚስሉበትን መንገድ በአጭሩ መመልከት ከእዚህ በላይ የተንደረደርንበትን ሐሳብ ያጠነክርልናል። በተጨማሪም ሴቶች እና የሴቶችን ጥያቄ ማስተጋባት የቻሉ ወንዶች እንዴት ጥያቄዎችን በውስጣቸው ማንቆርቆር እንደጀመሩ መመልከቱ የ“ፌሚኒዝም"ን መጠንሰስ እና ቅርጽ እየያዘ መምጣት በጥልቀት ለመረዳት ነጥበ-መብራቴ (Spot light) እንደሚሆን አምናለሁ። በክርስትና አማኞች ዘንድ ደጋግሞ ስሙ የሚጠራው ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን ጻፈ...

“ሚስቶች ሆይ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ። ክርስቶስ ደግሞ የቤተክርስቲያን ራስ እንደሆነ እርሱም አካሉን የሚያድን እንደሆነ ባል የሚስት ራስ ነውና። ዳሩ ግን ቤተክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ይገዙ!” -- (ኤፌሶን 5፥21-24)

ጳውሎስ ብዙ ቦታ ስደትና ግርፋት እንደደረሰበት በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኩ ተዘግቧል። ወደ አንድ ሥፍራ ሲሄድ ብቻ ሊሰብክ ያለውን “ቅዱስ ቃል” ሊሰሙት ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎች ተሰባሰቡ፤ ዕውቀቱንም ሰምተው ሞገቱት -በዕውቀት ያምኑ ነበርና አሸነፋቸው። “ያ” ሥፍራ ግሪክ ነው። ግሪኮች ደግሞ አስቀድሞ የዕውቀት ባሕል ነበራቸው። ከላይ የተቀመጠው የጳውሎስ መልዕክት ከግሪካዊያኑ ፈላስፎች (ጳውሎስ ከመነሣቱ ሦስት መቶ ዓመታት ቀድመው የነበሩ) ጋር የሠመረ ነው። -እንየው።

የዓለምን የፍልስፍና ጎዳና ከጠረጉት፣ ሥማቸው በሳይንሱም በጥበቡም ውስጥ ከሚነሣላቸው ፈላስፎች አንዱ ፕሌቶ ነው። ፕሌቶ “Republic" በተባለ ድርሳኑ ተጻራሪ የሚመስሉ ሁለት ሐሳቦችን ስለ ሴቶት አፈጣጠር ያራምዳል። የመጀመሪያው ሐሳብ “ሴት እና ወንድ በተፈጥሯቸው በአንድ ሥራ ላይ ለመሠማራት ወይም ተመሳሳይ ትምህርትን ለመማር ይችላሉ” የሚል ነው።

ሴት ወይም ወንድ እንደ ሕጻን አንድ ዓይነት ትምህርትን ተምረው በአቅማቸው መጠን ከሦስቱ የፕሌቶ የሰው ልጅ መደቦች ውስጥ በአንደኛው መደብ የሚያርፉ ይሆናል። ፕሌቶ “ወንድ እና ሴት አንድ ዓይነት ትምህርት መማርም ሆነ አንድ ዓይነት ሥራ መሥራት ይችላሉ” ይበል እንጂ “በሴት እና በወንድ መሃል ልዩነት የለም” ማለቱ አይደለም። ይልቁንም ያላቸው ልዩነት ሴት ወይም ወንድ ቢሆኑ ማኅበረሰባቸው ውስጥ ለሚወጡት ሚና ያን ያህልም ተጽዕኖ የለውም የሚል ነው።

ሁለተኛው የፕሌቶ ነጥብ ከላይኛው የሚቀጥል ነው። ወንዶች እና ሴቶች በአንድ መሥራት ወይም አንድ ዓይነት ትምህርት መማር ቢችሉም እንኳን ሁሌም ቢሆን ሴቶች ከወንዶች ያነሰ አፈጻጸም ወይም ብቃት ይኖራቸዋል። ወንዶች እና ሴቶች በጦር ሜዳ ወይም በፈረስ ግልቢያ ቢሠማሩ ሴቷ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ደከም ያለች ትሆናለች እንደ ማለት ነው።

በፕሌቶ ዓለም ውስጥ በሚኖሩ ሦስት የማኅበረሰብ ክፍሎች (መሪዎች፣ ጦረኞች፣ አምራቾች) ላይ ልክ እንደ ወንዶች ሁሉ ሴቶችም የመገኘት አቅም ይኖራቸዋል። ይሁን እንጂ በተመደቡበት መደብ ላይ ሁሉ አፈጻጸማቸው ከወንዶች ያነሰ ነው። ፕሌቶ ከእርሱ አስቀድሞ የነበሩ ፈላስፋዎች ያራምዱት የነበረውን “በማናቸውም መንገድ ሴት ደካማ ናት፤ የወንድ የበታች ናት” የሚለውን ጅምላ ጨራሽ መከራከርያ ያለማመንታት የተቀበለው ይመስላል።

በሌላ በኩል አርስቶትል ስለሴቶች ከፖለቲካ ፍልስፍናው በተጨማሪ በባዮሎጂ ምልከታው ላይም ጊዜ ሰጥቶ ያብራራል። “On the generation of animals” በሚል ጽሑፉ ውስጥ ስለ ሁሉም ፍጥረታት በሚባል ደረጃ ያብራራል።

በዚህ ማብራሪያ “በሁሉም እንስሳት ውስጥ ሴቶች ከወንዶች ሲነጻጸሩ ገና ያላለቁ ፍጡሮች ናቸው” –የሚል መደምደሚያ ይሰጣል። እንዲህም ይላል “ሴቶች ማለት የተጨናገፉ ወንዶች ናቸው።” ይህንንም የሚለው “የሴቶች አካላት እንደ ወንዶች የሰው አካል እንዲሁም ነፍስ ለመሆን ሒደታቸውን ያልጨረሱ ናቸው” በማለት ነው።

በአርስቶትል አባባል ዋነኛው ሴቶች ያጡት መሠረታዊ ነገር ነፍስ (soul) ነው። እንደ አርስቶትል ገለጻ ልጅ በመውለድ ሒደትም ላይ ሴቶች አካልን ብቻ ሲያዋጡ ወንዶች ደግሞ ለጽንሱ ነፍስን ያዋጣሉ።

“While the body is from the female, it is the soul that is from the male, for the soul is the reality of particular body” --(Arstotle - 322 :2069)

አርስቶትል አንድ ጽንስ ወንድ ወይንም ሴት እንዴት ሊሆን እንደሚችል ትንታኔ ይሰጣል። ጽንስ ወንድ ወይም ሴት እንዲሆን አስተዋጽኦ ናቸው የሚላቸውን ነገሮች ሲገልጽ እንዲህ ይላል።

"....more female are produced by the young and by those verging on old age than by those on prime of life; in the former the vital heat is not yet perfect, in the latter it is failing. And those of a moister and more feminine state of body are more wont to beget females... (Ibid: 2145);

«ብዙ ሴቶች የሚጸነሱት (የሚወለዱት) በለጋዎች ወይም በአዛውንቶች ነው። ለጋዎች ውስጥ ያለው ወሳኝ ሙቀት ወይም ተነሣስቶት ገና ያልዳበረ ወይም ያልበሰለ ሲሆን በዕድሜ የገፉ ሰዎች የሚጸንሷቸው ውስጥ ደግሞ ይህ እሳት ወይም ተነሣስቶት ያለፈና የጠፋ ነው። ሴታሴት የሆኑና ኮስማና ሰውነት ያላቸው ወንዶች ደግሞ ብዙ ጊዜ ሴት እንድትወለድ ምክንያት ይሆናሉ።”

በፖለቲክስ ውስጥ ደግሞ አርስቶትል ሴቶች በማኅበረሰብ ውስጥ ስለሚኖራቸው (ሊኖራቸው ስለሚገባው) ሚና ይገልጻል። ኅብረተሰባዊነትን ከሚሰብከው ፕሌቶ በተቃራኒ አርስቶትል ቤተ-ሰባዊነትን ይሰብካል። ለአርስቶትል ጠቅላላ ሰዎች እንደ ፕሌቶ እሳቤ በሦስት መደብ ተከፍለው ማኅበረሰብን ሊመሠርቱ አይገባም። ይልቁንም ቤተሰባዊ መዋቅር ቅድሚያ መምጣት አለበት። በቤተሰብ ውስጥ የባልና ሚስት፣ የጌታና ሎሌ፣ የወላጅና ልጅ የኃይል አሰላለፎች አንድን ማኅበረሰብ ለመመሥት ወሳኝ ቁም ነገሮች ይሆናሉ።

አርስቶትል እንደሚያምነው ማኅበረሰብ መመሥረት የሚኖርበት ቤተሰብ ከተሰኘው ማኅበር በመነሣት ነው። የባልና የሚስት የኃላፊነት ክፍፍልም ለትልቁ ማኅበረሰባዊ የሥልጣን ክፍፍል መነሻው ነው።

    ይቀጥላል

@Zephilosophy
@Zephilosophy
4.2K viewsedited  19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 22:47:05 ..... ካለፈው የቀጠለ

አራቱ የጠባይ እርከኖች.....2

አእምሮ (ዕውቀት)፣ ልቡና(መድሎት)፣ እና ኅሊና (መንፈስ) ያለው ሰው ብቻ ነው፡፡ አእምሮን ለማወቅ፣ ለመረዳትና ለማሰብ፤ ልቡናውን ባወቀና በተገነዘበው ላይ ተመሥርቶ ለማገናዘብ፣ ለለማስተያየትና ለማነጻጸር፣ ለመመዘንና ለመወሰን፤ ኅሊናውን ለማብሰልሰል፣ ለማሰላሰል፣ ወደ ኋላ ለማሰብ፤ ወደ ፊት ለመተንበይ፣ ወደ ላይ ለመንጠቅ፣ወደ እመቃት ለመጥለቅ ከቻለ ለው አንደ ሰው «ሙሉ ሰው» ሆኗል የሚባለው::

ሰውነት ምንም እንኳን ከፍተኛው የሰብእና አካል ቢሆንም ጉድለቶች ግን አሉት፡፡ እንደ ዶከተር እጓለ አገላለጥ ለ<<ጽርየት>> ትኩረት አይሰጥም፡፡ <<ጽርየት» ማለት በግርድፉ ንጽሕና ነው፡፡ በዋናነት ግን የአእምሮ፣ የኅሊናና የልቡና ንጽሕናን ይመለከታል፡፡

ሰውነት በአንድ በኩል ሳይገራ ይዟቸው ከታችኞቹ ጠባያት ያመጣቸዉ እንከኖች፣ በሌላ በኩል ደግሞ የሐሳብ፣ የእምነት፣ የፍልስፍና፣ የዘር፣ የባህልና የሥልጣኔ ልዩነቶችን ለመፍታት በሚወስዳቸው መፍትሔዎች ምክንያት «ዕድፈት» ያጋጥመዋል፡፡

«ዕድፈት» ማለት ጥበብን፣ ዕውቀትን፣ ሥልጣንን፣ ገንዘብንና ዝናን ለግላዊ ፍላጎት ለማዋል የሚሠራ ሰብአዊ ሤራ ነው፡፡ በተለይም ይኼ ሤራ ሳይገራና ሳይገዛ ከመጣ የአውሬነትና የእንስሳነት «ተረፈ ጠባይ» ጋር ከተቀላቀለ አደገኛ ነው፡፡ ለአውሬነትና እንስሳነት ጠባያት የዕውቀት፣ የጥበብ፣ የሃይማኖት፣ የፖለቲካና የፍልስፍና ስያሜ እየሰጡ _ የሰውን ልጅ የሚያስቸግሩ ሰዎች የሚከሠቱት በዚህ ዕድፈት ምክንያት
ነው፡፡

ጽርየትን ለማግኘት ወደ አራተኛው የሰብእና ደረጃ መግባት ያስፈልጋል፡፡ ጽርየት የሚገኘው ከመልአክነት ነው፡፡ መልአክነት ዋናዎቹ መገለጫዎቹ ሁለት ናቸው፡፡ «ለሌሎች በሚደረግ መሥዋዕትነት በመርካት» እና «ምስጉን ህላዌ» ናቸው፡፡ ለሌሎች በሚደረግ መሥዋዕትነት መርካት ማለት ለሀገር፣ ለወገን፣ ለዓለም ሕዝብ፣ ከዚያም አልፎ ለእንስሳት ለእፅዋት፣ ለወንዞችና ለሀይቆች፣ ለአእዋፍና ለዓሦች፣ ለሰማዩና ለምድሩ በሚከፈል መሥዋዕትነት መርካት ማለት ነው። <<የራስ ደስታ የሌሎችም ደስታ ነው» ብሎ ማሰብ ሰውነት ሲሆን «የኔ ደስታ ከሌሎች ደስታ ይመነጫል›› ብሎ ማሰብ ግን መልአክነት ነው፡፡ መልአክነት በምግብና መጠጥ፣ በልብስና ጫማ፣ በክብርና ዝና፣
በሥልጣንና ገንዘብ፣ በውበትና ቁንጅና ሳይሆን ይህቺን ዓለም መልካም የሰው ልጆች መኖሪያ ለማድረግ፣ ነጻነትንና ፍትሕን፣ እኩልነትንና ርትዕን፣ ሰላምንና መልካም አነዋወርን ለማስፈን በሚከፈል መሥዋዕትነት መርካት ነው፡፡

ሰው በሚያገኘው ሳይሆን በሚሰጠው መደሰት፣ በሚዋልለት ሳይሆን በሚውለው፣ በሚደረግለት ሳይሆን በሚያደርገው፣ በሚከብረው ሳይሆን በሚያከብረው ነገር ይበልጥ መደሰት ሲጀምር ነው ጽርየት የሚገኘው፡፡

«ምስጉን ህላዌ» ማለት «እያመሰገኑና እየተመሰገኑ መኖር» ነው፡፡ መላእክት እያመሰገኑና እየተመሰገኑ እንደሚኖሩት ሁሉ ሰውም ጽርየት ሲኖረው የሰዎችን መልካም ሥራ ለማየት፣ ከአድናቆት ለመጀመር፣ በስሕተታቸው ከመበሳጨት ይልቅ ከበጎ ሥራቸው ተነሥቶ ስሕተታቸውን ለማረም፣ በጉድለታቸው ከመናደድ ይልቅ ጉድለታቸውን ለመሙላት፣ ከጠማማው ግራር ታቦት ለመቅረጽ፣ ከእሾሃማው እንጨት ዕጣን ለመልቀም የሚተጋ ማለት ነው፡፡ እንዲህ ያለው ሰው የሚያጋጥመው ፈተና፣ የሚጋረጥበት ተግዳሮት፣ የሚደርስበት ችግር የለም ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን በእነዚህ ደስታውን አይነጠቅም። መሥዋዕትነቱ የሚያመጣውን በጎ ውጤት እንጂ የደረሰበትን አያስበውምና፡፡

በእርሱ ድካም የሚበረቱትን፣ በእርሱ ቁስል የሚፈወሱትን፣ በእርሱ እሥራት የሚፈቱትን፣ በእርሱ ሕማም የሚድኑትን፣ በእርሱ ሥራ የሚጠቀሙትን፣ በእርሱ ሞት የሚወለዱትን ያስባልና ደስተኛ ነው:: ለዚህ ነው አመስጋኝ የሚሆነው፡፡ ተመስጋኝ ህላዌም ይኖረዋል፡፡ የሚሠራው ሥራ የሚጠፋ አይደለም፡፡ ለትውልደ ትውልድ የሚኖር ነው፡፡

ምናልባት በአንድ ዘመን የተሸሸገ ቢመስል እንኳን መሬት ውስጥ እንደተቀበረ እሳተ ገሞራ አንድ ቀን ራሱን መግለጡ አይቀርም፡፡ ታሪኩን የሚጽፍለት፣ ገድሉን የሚዘክርለት ባያገኝ እንኳን እውነት ራሷ አፍ አውጥታ ምስክር ትሆነዋለች፡፡

ስለዚህ የእርሱ ኑባሬ በሞት አይገታም፡፡ ሞት ቅርጹን ይቀይረዋል እንጂ ክብሩንና ህላዌውን አይቀይረውም፡፡ እንዲያውም በቆየ ቁጥር ጣዕሙ እንደሚጨምር ወይን ዘመናት ባለፉ ቁጥር የሚያስታውሱትንና የሚያመሰግኑት እየበዙ ይሄዳሉ፡፡ የሚፈልጉትና የሚጠቀሙበት ይጨምራሉ፡፡ ለዚህ ነው <<ምስጉን ህላዌ>> አለው ያልነው። ሲመሰገን የሚኖር ህላዌ ማለት ነው፡፡

ጽርየትን ገንዘቡ ያደረገ ሰው ከወንጀል፣ ከጥመት፣ ከኃጢአት፣ ከጠቅመኛነት፣ ከአምባገነንነት፣ ከጥፋትና ከክፋት ጋር አይገጥምም፡፡ ይጸየፈዋል፡፡ እንዲህ ያሉትን ታግሦ፣ አቻችሎ፣ ተሸክሞ፣ እንዳላየ አልፎ፣ የራሱ ጉዳይ ብሎ፣ እኔን አይመለከተኝም ብሎ አያልፈውም፡፡ ድንግዝግዝ ሰብእና እንጂ ጽርየት እነዚህን አይታገሥምና፡፡

ዓለም የጣፈጠቺውና የምትጣፍጠው፣ በአጭሩ ዕድሜያችን ብዙ ነገር እንድናይ ያደረጉን፣ የሰው ልጅ ድካም ቀልሎ፣ የሰው ልጅ ሕማም ድኖ፣ የሰው ልጅ ጉድለት ሞልቶ፣ የሰው ልጅ ሥልጣኔ መጥቆ፣ የሰው ልጅ ሥርዓት ሠምሮ የምናየው በእነዚህ መልአካውያን አስተዋጽዖ የተነሣ ነው፡፡ ክፋቱ ቁጥራቸው ጥቂት ነው፡፡ ሥራቸው ግን ከተባረከ ይበቃል አንዱ» እንደተባለው ነው፡፡

እነዚህ መልአካውያን በአውሬነት፣ በእንስሳነትና በሰውነት ውስጥ ያሉ ከፉ ዐመሎችን ሁሉ ገርተው፣ ቀጥተውና ገዝተው ልዕልናን ያገኙ ናቸው፡፡ በአእምሮ ሳይሆን በልዕለ አእምሮ የሚሠሩ ናቸው፡፡ ማንም እንደ ባዶ ኮምፒውተር የፈለገውን ፕሮግራም አይጭናቸውም፤ አይቀይዳቸውም፣ በሳጥን አስገብቶ አይወስናቸውም፡፡

እነርሱ በሐሳብ ልዕልና፣ በመንፈስ ንጽሕና ይራመዳሉ፡፡ ድንበሮችና አጥሮች፣ ቋንቋዎችና እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች፣ ጎሳዎችና ጎጦች ሊገድቧቸው አይቻላቸውም፤ «መልዕልተ ኩሉ ሥጋውያን>> ናቸው:: እነርሱን በጥቅምና በገንዘብ፣ በክብርና በዝና፣ በሥልጣንና በርስት መደለል አይቻልም፡፡ እነዚህን ሁሉ ዐውቀው፣ ንቀው፣ ልቀው፣ መጥቀው፣ ከፍ ባለው የሰው ልጅ ክብር «መልአክነት>> ላይ ደርሰዋል፡፡ እነዚህን ለሌሎች በመለገስ ይደሰታሉ እንጂ ለእነርሱ በማግኘት አይደሰቱም፡፡

ዓለም በዚህ ዘመን የተቸገረቺው እነዚህን መልአካውያን እያጣች አውሬዎቹን እያበዛች፣ እንስሳቱን እያበረታታች፣ ሰብአውያኑንም ከጽርየት እየገታች በመሄዷ ነው፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
296 views19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ