Get Mystery Box with random crypto!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

የሰርጥ አድራሻ: @zephilosophy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.78K
የሰርጥ መግለጫ

"Strong minds discuss ideas, average minds discuss events, weak minds discuss people."
Rinu Ruzvelt

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-04 17:08:49 ሞራሉ በቀላሉ የማይሰበር ሕዝብ ስነልቦናው ከፍ ያለ ነው!
(The psychology of the masses always matters)
(እ.ብ.ይ)

ሐገር በየትኛውም ጊዜ የእርስበርስ እልቂትና የጦርነት አደጋ ሊያጋጥማት ይችላል፡፡ አደጋው በራሷ ልጆች አልያም በውጪ ጠላቶቿ ሊከሰት ይችላል፡፡ ስጋት የነበረ፣ ያለና ወደፊትም የሚኖር ነው፡፡ አይደለም በሐገር ደረጃ በግለሰብ ደረጃም ትላልቅ ስጋቶች አሉ፡፡ ማንም ከደቂቃ በኋላ ስላለው ጤናው፣ ሰላሙና ደህንነቱ ማወቅ አይችልም፡፡ አንዳንድ ሁኔታዎች ከምንጠብቀውና ከምንገምተው በላይ ሆነው ከቁጥጥራችን ውጪ ሊወጡ ይችላሉ፡፡ ስጋትን መተንተን፣ ሊፈጠሩ የሚችሉ ያልታሰቡ ክስተቶችን ማሰብ ነገሮቹ ሲፈጠሩና ከተፈጠሩ በኋላ ለሚኖረው መፍትሄ ወሳኝ ነገሮች ናቸው፡፡ በጥሩም ይሁን በመጥፎ በሕይወታችን ላይ የሚፈጠሩ አዳዲስ ክስተቶች ይዘውት የሚመጡት መልካም አጋጣሚዎችና አደጋዎች መኖራቸው አያጠያይቅም፡፡ የሚሊየን ዶላሮች ሎተሪ የደረሰው ሰው የአዕምሮ ዝግጁነት ከሌለው ዕድሉ አይሆኑ የሕይወት ፈተና ውስጥ ሊሰነቅረው ይችላል፡፡ መከራ አንድም በደስታ ጊዜ፤ አንድም በሃዘን ጊዜ ሊፈጠር ይችላል፡፡ ይሄን ክስተት የሚቀበል የአዕምሮ ዕውቀትና የስሜት ብስለት ከሌለ ወድቆ መቅረትን ያመጣል፡፡ ሐገር ችግሮቿን ተሻግራ፤ መከራዎቿን አልፋ ጸንታ ልትቆም የምትችለው የሕዝቧ ስነልቦና ጠንካራ ሲሆን ነው፡፡ የህዝብ ስነልቦናው መነሻው የግለሰብ ስነልቦና ነው፡፡ በስሜት ብስለት (Emotional intelligence) ያልሰለጠነ ዜጋ ራሱንም ሆነ ሐገሩን ከሚመጣበት መከራ ሊያድን አይችልም፡፡ አስደንጋጭ ክስተት ሲፈጠር አሁናዊ አደጋውንና የሚቀጥለው መዘዙን በእንዴት ያለ መፍትሄ ማስቀረት እንደሚቻል የአዕምሮ ዝግጁነት ከሌለ ከጠፋው በላይ ሌላ ጥፋት ይከተላል፡፡

እንግሊዛውያን በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ዋዜማ ላይ ስጋት ወጥሯቸው፣ ፍርሃት ወርሯቸው ጭንቀት በጭንቀት ሆነው እንደነበር ታሪክ ይናገራል፡፡ በዚህ አስፈሪ ጊዜ አዶልፍ ሂትለር በእንግሊዛውያን ላይ የቦንብ ናዳ ለመልቀቅ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ የለንደንን ነዋሪዎች አንቅልፍ ነስቶ ነበር፡፡ ትንሹም ትልቁም ካሁን አሁን የቦንብ ናዳ ረገፈብን በሚል በፍርሃት ቆፈን ተይዞ የለንደንን ሰማይ በየደቂቃው በሰቀቀን ይመለከት ነበር፡፡ በፈረንጆቹ ጥቅምት 19 ቀን 1939 ዓ.ም. ሂትለር ለጦር ጄኔራሎቹ በለንደን ሰማይ ላይ እንዴት ጥቃት እንደሚፈጽሙ እቅዱን አብራራ፡፡ እ.ኤ.አ. መስከረም 7 ቀን 1940 ዓ.ም. ሶስት መቶ አርባ ስምንት የጀርመን ቦንብ ጣይ አይሮፕላኖች ለንደን ሰማይ ላይ ተራወጡ፡፡ ያ ቀን ለእንግሊዛውያኑ ጥቁር ቀን (Black Satureday) ነበር፡፡ በዚህ ቀን የተጀመረው ጥቃት ለተከታታይ ዘጠኝ ወራት ቀጠለ፡፡ በዚህም ከ80 ሺ በላይ የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች በጥቃቱ ሕይወታቸውን አጡ፡፡ በሚሊየን የሚቆጠሩ የለንደን ታሪካዊ ህንጻዎች ፈራረሱ፡፡ ለንደን እንዳልነበረች ሆነች፡፡

ከሁሉ የሚገርመው ይሄን አደጋ እንዴት ነበር እንግሊዛውያኑ ተቀብለው ያስተናገዱት የሚለው ነበር፡፡ እንግሊዛውያኑ ያ ሁሉ ጥቃት ሲፈፀምባቸው ትራፊኩ ስራውን ከመስራት አልታቀበም፤ ህጻናቱ በሰላሙ ጊዜ የሚጫወቱትን ጨዋታቸውን አላቋረጡም፣ ሰራተኛው ከስራው ገበታው አልተስተጓጎለም፡፡ ባለሱቆቹ ከምንጊዜውም በላይ ሱቃቸው በር ላይ ‹‹መስኮቶቻችን በጥቃቱ ቢደቅቁም መንፈሳችን ግን አልደቀቀም፡፡ ደንበኞቻችን ይግቡና የሚፈልጉትን ይሸምቱ! (Our windows are gone. But our spirits are excellent. Come in and try them)›› የሚል ማስታወቂያ ለጥፈው ደንበኞቻቸውን ይጠባበቁ ነበር፡፡ ሂትለር በጊዜው የእንግሊዝን የደህንነት መረጃና የጦር ሚስጥር ቢያውቅም የእንግሊዛውያኑን የመንፈስ ጥንካሬ ግን አያውቅም ነበር፡፡ ዊኒስተል ቸርችል በዚህ ጥቃት ከሶስት እስከ አራት ሚሊየን የሚጠጉ ዜጎቹ ጦርነቱን በመሸሽ ሐገራቸውን ለቀው ይሰደዳሉ ብሎ ቢገምትም የሆነው ግን በተቃራኒው ነበር፡፡

እንግሊዛውያኑ በጥቃቱ ዘመዶቻቸውን በማጣታቸው ሐዘን ቢሰማቸውም፤ ንብረታቸው በመውደሙ ቢበሳጩም ስሜታቸውን የሚያስጨንቅ፣ አዕምሯቸውን የሚረብሽ ምንም ዓይነት የመንፈስ ጠባሳ (Trauma) አልነበረባቸውም፡፡ እንደውም በሰላሙ ጊዜ የነበሩ ወንጀሎች በዚህ ክፉ ጊዜ ቀንሰው ነበር፡፡ የአልኮል ጠጪዎች ከሸመታ ቤት ጠፍተዋል፡፡ ደሃም ይሁን ሃብታም እርስበራሳቸው ይረዳዱ ነበር፡፡ የተጎዱ ቤተሰቦችን በመርዳትና በመጎብኘት ያፅናኑ ነበር፡፡ ፖለቲካ ከሞራላቸው አላነጣባቸውም፤ የካድሬ ጩኸት እርስበራሳቸው አልለያያቸውም፡፡ ይሄ ክፉ ጊዜ ሰው-ነታቸውን አስታወሰ እንጂ ሰብዓዊነታቸውን አልቀማቸውም፡፡ ባንክ ለመዝረፍ የሮጠ የለም፡፡ እስር ቤቶችን ሰብሬ በህግ ጥላ ስር ያሉ እስረኞችን አስለቅቃለሁ ያለ ጉልበተኛ የለም፡፡ ይሄን የቀውጢ ሰዓት ተጠቅሞ ሱቆችን ሰባብሮ እቃዎችን ለመስረቅ ያሰበ ማንም አልነበረም፡፡ በጦርነቱ ምክንያት ኢኮኖሚያቸው እንዳይጎዳ ራሳቸውን ለአደጋ አጋልጠውም ቢሆን ስራቸውን ከመስራት ያቆማቸው አንዳች ሃይል አልነበረም፡፡

ሊንድማን የተባለ የቸርችል የቅርብ ጓደኛ በጦርነቱ ሳቢያ በጣም በተጎዱ በበርሚንግሃምና ኸል (Bermingham and Hull cities) በተባሉ ሁለት ከተሞች እንግሊዛውያኑ የመንፈስ ስብራትና የአዕምሮ መረበሽ እንደደረሰባቸውና እንዳልደረሰባቸው ለማወቅ ሁለት የጥናት ቡድኖችን ወደከተሞቹ ላከ፡፡ አጥኒዎቹም ይዘዉት የመጡት የጥናት ግኝቶች (Findings) ግን ብዙዎችን ያስደነቀ ነበር፡፡ በጥናቱ ወረቀት የፊት ገፅ ላይ በትላልቅ ፊደላት የተፃፈው ፡-

‹‹There is no evidence of breakdown of morale (የሞራል ስብራት እንዳለ የሚያረጋግጥ ምንም ማስረጃ የለም)‹‹ የሚል ነበር፡፡

አዎ ሐገርን ከአደጋ በኋላ ቀና የሚያደርገው ገንዘብ ብቻ አይደለም፡፡ ሐገርን ወደፊት እንዲቀጥል የሚያደርገው የህዝቡ ፅናትና የስነልቦና ጥንካሬ ነው፡፡ እንግሊዛውያኑ የሂትለርንና የቸርችልን ፖለቲካዊ እሰጣ ግባ ችላ ብለው ለሐገራቸው የቆሙት መንፈሳቸው ጠንካራ ስለነበረ ነው፡፡ የመጣባቸውን ጥፋት ተጋፍጠው ሞራላቸውን ሳያስነኩ ሀገራቸውንም ራሳቸውንም ጠብቀው ለቀጣዩ ትውልድ አስረክበዋል፡፡ ሞቱን ተቀብለው፤ አካል ጉዳቱን ችለው ሐገራቸው ኢኮኖሚዋ እንዳይወድቅ የበኩላቸውን ሚና ተጫውተዋል፡፡ በዚህም ለሌላው የዓለም ህዝብ ምሳሌ ሆነው ሲዘከሩ ይኖራሉ፡፡

ሐገርን በፅኑ መሰረት ላይ የሚያቆመው ጠንካራ ስነልቦና ያለው ህዝብ ነው! መንፈሱ ከፍ ያለ ሕዝብ ሐገሩ ላይ የተደቀነውን ፈተና ያልፋል፤ ከፊቱ የተጋረጠውን አደጋ ይሻገራል!

አዎ! አጥፊዎች ሆይ... ‹‹ንብረቶቻችንን ልታወድሙ ትችላላችሁ፤ መንፈሳችንን ግን ማድቀቅ አትችሉም፡፡ አካላችንን ትጎዱት ይሆናል ስነልቦናችንን ለመድፈር ግን አቅም የላችሁም!››

ቸር ጊዜ!

ኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ለዘላለም ይኑሩ!

_____
እሸቱ ብሩ ይትባረክ
(እ.ብ.ይ.)

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.6K views14:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-02 21:30:39 ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(1ኛ ዮሐ.3፡15)

“ብሔርተኛ የሆነ አምባገነናዊ አገዛዝ ለጊዜው ምክንያታዊነት በጎደለው ስሜታዊና ግልብ በሆነ አስተሳሰብ ዜጋውን ወይም “ብሔር” ብሎ ከፋፍሎ ያደራጃቸውን በመንዳት የተሳካለት ይምሰለው እንጂ፣ አገዛዙን ለማስቀጠል ሲል የሚፈጽማቸውን ግፎች በሂደት ሕዝቡ እየተገነዘበው ስለሚሄድ ምንም ዓይነት ሴራ ቢጠቀም አገዛዙ ያሰበው እቅድ ዘለቄታ ሊኖረው አይችልም፡፡

በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃን ይሁን አናሳ ቁጥር ባለው “በብሔር” ማንነት
ላይ የተመሠረተ ማንኛውም አገዛዝ የሳይንሳዊ ፖለቲካዊ ስርአት ሳይሆን በአዕምሮ ቅዠት ህመም የተጠቃ፣ ፋሽስታዊ አምባገነን፣ ኢ-ሰብአዊ፣ ስርአተ አልበኛ፣ የወሮበላና የደንቆሮ ገዢ ቡድን ነው፡፡ በአጠቃላይ “የብሔርተኛ ፋሽስታዊ አገዛዝ በፖለቲካ ሳይንስ የተቃኘ ሕዝባዊ አስተዳደር ሳይሆን፣ ከአዕምሮ ቅዠት ህመም የመነጨ የድንቁርና አገዛዝ ነው::

በአሁኑ ዓለም የመልካም አስተዳደር ሳይንሳዊ ፖለቲካ ማለት፣ የአንድ ሀገርን ብዙሃን ሕዝብ አዕምሮ ከፖለቲካዊ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ነጻ በማድረግ በኑሮ ደረጃዉ እያሳደገ የማስቀጠል ብቃት ነው፡፡


በአንድ ሀገር መንግሥታዊ አገዛዝ ላይ ብዙሃኑ ሕዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ጥላቻና በቀል ከተፈጠረ ሀገሪቱ የብዙሃን ሕዝብ ድጋፍ የተቸረው የአገዛዝ ሥርዓት ባለመሆኑ ሀገሪቱ ያልተረጋጋችና ልማቷም ዘለቄታ የሌለዉ ስለመሆኑ ማሳያ ነው፡፡ ይህም ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻ እያደገ በመሄድ በዋናነት በአፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያን የመሳሰሉትን ሀገራት ሁልጊዜ ወደ እርስ በርስ ጦርነት እየከተተ ዜጋውን ወደተሻለ ኑሮ እንዳያድግ የሚገድብ ነው፡፡

ወንድሙን የሚጠላ ሁሉ ነፍሰ ገዳይ ነው...(ኛዮሐ.3፡15)፡፡ አንድ ሰው ግድያ ከመፈጸሙ በፊት የሚፈጠረው የጥላቻ አስተሳሰብ ይቀድማል፡፡ የጥላቻውም አስተሳሰብ በሂደት በግድያ ድርጊት ይፈጸማል፡፡ በአንድ ሀገር ውስጥ ብዙሃኑ ሕዝብ በፊት ስለሚገድለው ሰው በአዕምሮው ውስጥ  ቁጭት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር መንግሥት ካለ አምባገነን አገዛዝ እንጂ፣ መንግሥታዊ ስርአት አይደለም፡፡ ስርአት ማለት ማንም ሰው እንደፈለገው የማይቀያይረው፣ በሳይንሳዊ እውቀት የተደራጀ፣ ህግንና ደንብን በመከተል የታለመለትን ግብ የያዘ ተቋም  ነው፡፡

“የብሔርተኛ” አምባገነናዊ አገዛዝ ሳይንሳዊ የፖለቲካ ስርአት ሳይሆን፣ በባህሪው በቀሪው ዜጋ አዕምሮ ውስጥ ሁልጊዜ ቁጭት፣ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ ንዴትና ጥላቻን የሚፈጥር የስርአተ አልበኛና የአሸባሪነት አገዛዝ ነው፡፡ የብዙሃኑ ህዘብ አዕምሮ ለቁጨት፣ ለንዴትና ለጥላቻ የሚዳርግ አገዛዝ ይዋል ይደር እንጂ፣ አንድ ቀን በብዙሃኑ ህዝብ አመጽ በውርደት መወገዱ እንደማይቀር የአሁኑ ዓለም ታሪካዊ ሃቅ ነው፡፡ በአሁኑ ዓለም “በብሔር” ማንነት ላይ የተመሠረተ ፋሽስታዊ አገዛዝ በማህበራዊ፣ በፖለቲካዊና በኢኮኖሚዊ እንዲሁም በኃይማኖታዊ ጉዳዮች ላይ እንኳ ሳይቀር የበላይነቱን በማረጋገጥ ሰውን ከሰው የሚለይ፣ የሚያገልና አድልኦን የሚፈጽም ሳይንሳዊ ያልሆነ አገዛዝ ነው፡፡ ስለሆነም በብዙሃኑ ሕዝብ ዘንድ ምንጊዜም ቢሆን ተቀባይነት ስለሌለው ሁልጊዜ ሰላምና መረጋጋትን በማሳጣት ለአብዮት የሚዳርግ ነው፡፡

በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ በተቃኘ ፋሺስታዊ አገዛዝ ውስጥ ሁሉም ባይቀበለውም ነገር ግን እጅግ አብዛኛው ዜጋ በ”ብሔር” ማንንነት አዕምሮ ቅዠት ህመም ይለከፋል፡፡ የ”ብሔርተኛ” ፋሽስታዊ አገዛዝ የስልጣኑን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሲል የሚያራምዳቸው መሠረታዊ ሴራዎች አሉት፡፡ እነዚህ ሴራዎችም በህዝብ አዕምሮ ውስጥ ቁጭት፣ ንዴትንና ጥላቻን በአገዛዙ ላይ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመሩ ይሄዳሉ፡፡ በመሆኑም ይህ ቁጭት፣ ጥላቻ ይዋል ይደር እንጂ “በብሔር” ማንነት ተከፋፍሎ የነበረውን ሕዝብ ወደ መተባበበር ይገፋፋውና አገዛዙን ለማስወገድ የሞት ሽረት ትግል ውስጥ ሳይወድ በግዱ ይገባል፡፡

ሰብስቤ አለምነህ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
7.3K viewsedited  18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-30 09:12:14
4.1K views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 17:36:42 ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም
ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትም

....የቀጠለ

ሽማግሌው የግራ ጆሯቸውን፤ ከፊቶች አንዱን እያከኩ ተነሡ።

“እንግዲህ ሰማንህ ዕድሉ። ለሰሚ የቸገረ ነገር ነውና የሸንጎውን ሐሳብ አድምጠን ፍርዱን ለዋናው ዳኛ እንሰጣለን። ፈጣሪና መጥረቢያ አጥፍተዋል። ፍርድ ይገባቸዋል? የምትል እጅህን አውጣ ተብለሃል!”

ማንም ሰው እጁን አላወጣም። ዕድሉ ይባስ ከፋው። ከዚህ ሁሉ በደሉ ጀርባ ዓለም ያሴረ መሰለው።

“ተው አንተ ሸንጎ አንተም እንደምሳር በወደቀ ላይ አትዝመት፣ ተው ንጉሥም ሲያጠፋ አጥፍተሃል ይባል፣ ተው መፈራራት ይቅር፤ ተው ለበዳዮችህ አታቀርቅር፣ ተው ፍርዴን አታጣምም፤ ተው ተፈጥሮን አታሳምም። ተው እውነት እየመረረችህም ጠጣት። ተው የምታሽርህን ጋታት!”

“ፈጣሪና መጥረቢያን ነጻ ናቸው የምትል። ፈጣሪ አይከሰስም! የምትል እጅህን አውጣ ተብለሃል” ሁሉም እጁን አወጣ። ማውጣት ብቻ ሳይሆን ፈጣሪ በደንብ እንዲያየው ወደ ሰማይ እየተንጠራራ።
ሽማግሌው ወደ ዋናው ዳኛ ዞረው “እንግዲህ ፍርዱን ለእርስዎ ሰጥተናል!” አሉ።
“እንግዲህ ፍረድ ካላችሁኝ ይኸው ፍርዴ። በእውነት ይሄ ሰው ቀላል እፍዳ አላሳለፈም። ፈጣሪም መጥረቢያም በድለውታል። ኧረ እንደውም እስከ ዛሬ እንደዚህ የተበደለ ሰው ገጥሞኝም : አያውቅም። ስለዚህ መጥረቢያው በእጃችን ነው። እንጨቱ ተፈልጦ ማገዶ ይሁን። ብረቱ ሲቃጠል ይኖር ዘንድ፤ ያበላሸውን ይክስ ዘንድ ተቀጥቅጦና ቀልጦ የተበሳ ሰታቴ ወይ ላመፈጅ ይጠገንበት። ፈጣሪም ካለበት ተይዞ “ዕድሜ ይፍታሕ” እንዲታሰር ፈርጃለሁ። ይዞ ላመጣውም ያሻውን ያህል የምትታለብ ጥገት፤ ሮጦ የደረሰበትን ያህል ጋሻ መሬት፤ ልቡ የፈቀደውን ያህል ሚስትና እቁባት ይሸለም ዘንድ ፈርጄያለሁ። ይግባኝ አለኝ! የሚል ተከሳሽ ከተያዘ በኋላ ማሰማት ይችላል። ጨርሼያለሁ!”

ዕድሉ ቀና በአዛውንቱ ቅንነት እየተደነቀ አመስግኖ ወረደ። ሕዝቡም ገጸበረከቱ እያጓጓው፤ ፈጣሪን በየመቅደሱ በርብሮ ሊያገኝ ተመመ። “ፈጣሪ” ያልነው ማንን ነው? ዳኛውም ማንንም ሳያስከፋ ሸንጎውን መበተኑን ለሚቀጥሉት ብዙ ዓመታት በኩራት ሊያወራ ከግንባሩ ግራ እስከ አገጩ ከተዘረጋው፤ በከንፈሩና በዓይኑ ከሚቋረጥ ጠባሳው ጋር አንከስ አንከስ እያለ ወደ ቤቱ አዘገመ። ተከሳሽ በሌለበት ከሳሽ ሙግቱን ቢረታ ማነው ያሸነፈው?

ድሕረ “ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትም”

የዕድሉ መጥረቢያ እጀታ ተፈልጦ በጋመ እሳት ውስጥ ገባ። እንደ ትዝታ በትናንሽ ዓይኑ የሚያፈጥ እንጀራ ለመጋገር ከሌሎች እንጨቶች ጋር አበረ። ሚስቱ ሰው ጠርቷት በወጣችበት ኩሽናው በእሳት ተያያዘ። በቀላል ሊያጠፉት አልቻሉም። እሳቱ እንደሰደድ ተዛምቶ የአዝማሪው ሐዋዝንና ሌሎች ሦስት ቤቶችን አወደመ። ሚስቱ ስትጠየቅ “እንዲህ በፍጥነት የሚዛመት እሳት አይቼ አላውቅም! ይኸማ የፈጣሪ ቁጣ ነው!” ትላለች። በደዌ ዳኛ፣ በአልጋ ቁራኛ ተይዘው የተኙት እትዬ ተዋቡ በእሳቱ ተቃጥለው ሕይወታቸው አለፈ። ዕድሉ ሞታም ሰው መፍጀት ያልተወችውን መጥረቢያው ውስጥ ዕጣ ፈንታው እያወካ የሚስቅበት መሰለው። ከሰማይ፣ ከምድሩም እንደተጣላ ጠረጠረ። “እንጀራ እበላበታለሁ” ባለበት አንድ መጥረቢያ ጦስ ሕይወቱ ምስቅልቅል ሲል መታገስ አልቻለም። ሞቱን አልፈራም። እየተበደሉ ይቅር አለማለት ዞሮ ራሱን ተገተገው። “ተበድለህም ይቅርታ መጠየቅ ምን ማለት ነው?” ...ልጆቹን ሳያሳድግ መሞቱ እያንገበገበው አጣጣረ። ከሰውም፣ ከአማልክትም መታረቅ የማይችል ቂም ቋጥሮ ሳይበረክት በተወለደበት አልጋ ላይ ሞት ተገናኘው።

ልክ ነፍሱ ስትወጣ

አንዳንዶች “መጣሁልህ! ምን ልታደርገኝ እንደሆን አይሃለሁ?!” ብሏል
ይላሉ።

አንዳንዶች “ይቅር በለኝ?! እኔም ይቅር ብዬሃለሁ!” ብሏል ይላሉ።

ሚስቱ ግን ዛሬም ድረስ ዕድሉን ሲያነሡባት ልጆቿን ታቅፋ አምርራ ታለቅሳለች።

“እንግዲህ አይዞሽ! ፈጣሪ የወደደውን ነው
የሚጠራው!”
አሉ ሰባኪው ሾላ።

ጤናው እብዱ ከነግሣንግሡ እያለፈ ሳቀ። ረዥም ሳቅ ሳቅ ...ሁሌ እንደሚስቀው የልግጫ ሳቅ ሳቀ። “ታዲያ ፈጣሪ ሲጠራ፤ እንዳንከራተተ ነው እንዴ? ሳይክስ? ሳይዳስስ?”

@Zephilosophy
@Zephilosophy
6.2K viewsedited  14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 17:34:52 “መቼም አልሰማ ብለህ ክሴን እቀጥላለሁ” ካልክ የሆንከውን አብራርተህ ተናገር! አታደናግር!” ሽማግሌው ጮኸ።

“ነገሩ እንዲህ ነው። የሆነ ቀን አለልማዴ ዓለሜን አስከትዬ ዛፍ ቆረጣ ሄድሁ። በእኔ ቤት ዛፍ ቆርጬ ገንዘብ ላገኝ ነው እንግዲህ። አዬ! ...ምነው በቀረብኝ። ዓለሜን አርቄ አስቀምጬ መጥረቢያዬን ይዤ ዛፉ ላይ ወጣሁና መተግተግ ጀመርሁ። ምን የተረገመው ቀን እንደሆነ እንጃ ከዛፉ ላይ አንዲት ሰላላ ቅርንጫፍ ብላት ብሠራት አልቆረጥ አለችኝ። ዛሬ ደግሞ የምን ተአምር ነው የገጠመኝ? እያልሁ ደጋግሜ ብመታት ጭራሽ እንደድንጋይ መጥረቢያዬን አንጥራ ትመልሳለች እንጂ ፍንክችም አትልም። ሠላሳ ዓመት ዛፍ ስቆርጥ እንዲህ ዓይነት ነገር ገጥሞኝም አያውቅም። የዚህ ሀገር እንጨት እንደምታውቁት ገራም ነው፤ እንኳን ቅርንጫፍ ግንዱም ዐሥሬ ደኅና ካገኙት ይበቃዋል። ተንጋልሎ ያርፋል። የትንግርቴን ተፋጥጬ ሳነሣ ስለው፣ ሳነሣ –ስለው ...እልህ ይዞኝ እንጂ እጄ ዝሎ ኖሮ መጥረቢያው አምልጦኝ ቁልቁል ተምዘገዘገ። በዓይኔ ስከተለው...

” ዕድሉ ቀና ሳግ አንቆ አላናግር ስላለው አቀርቅሮ ጊዜ ወሰደ።

“ለቅሶህን ተውና ቀጥል ተብለሃል!”

“በዓይኔ ስከተለው እንደ ኪሩብዔል ሰይፍ ሲገለባበጥ ወርዶ ከየት መጣች ያላልኳት የልጄ አናት ላይ ሰመጠ። ይታያችሁ! ለእንጨት የሰነፈ መጥረቢያ ለልጄ ሲሆን በረታ። ለካ ዓለሜን አርቄ ባስቀምጣትም አሳዝኛት ሥሬ መጥታ ሽቅብ ስታየኝ ነበር። እኔ አፈር ልብላላት ...ሞት ሲጠራት እኮ ነው! ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ሠላሳ ዓመት ሙሉ ገጥሞኝ የማያውቀውን የእዚያ ቀን መጥረቢያ ያመለጠኝ? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል አድርጌ የማላውቀውን መጥረቢያ የሚያመልጠኝ ቀን ልጄን ይዤ የመጣሁት? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ከዓመት እስከ ዓመት የሚያሰቃያት ንዳድ ያንን ቀን ጋብ ያለላት? ታዲያ ፈጣሪ ቢለው አይደል ለእጅ የምትሰንፍ ቅርንጫፍ በስል መጥረቢያ የለገመቸው? ለምን “እንቢ! ስትለኝ አልተውኋትም? ምነው መጥረቢያውስ ካልጠፋ አውላላ መዳፍ የማታህል የልጄን አናት የመረጠው? ፈጣሪ ቢለው አይደል?”

አዝማሪው ሐዋዝ ተነሣ
“መቼም እንደሰው ልጅ ጉድ የትም የለም። ጠማማ ዕድሉንም፣ ስንፍናውንም በፈጣሪ ማሳበብ ይወዳል። አንተ የአርባ ዓመት ጎልማሳ ስትሆን ምነው ልጅህን መጠበቅ አላወቅህበት? እጅህ እስኪዝል አንድ ቅርንጫፍ ቀጥቅጥ ያለህ ፈጣሪ ነው? ከእጅህ አሽቀንጥረህ ስትጥለውም ወደወረወርክበት ይሄዳል እንጂ መጥረቢያ እግር የለው፤ ዓይን የለው፤ ምን አድርግ ነው የምትለው? ይህን ድፍረት ለተናገርህበት ራሱ ቅጣት ይገባሃል። ኧረ ምነው! ስንት ነገር ጥለን ነው የመጣነው፤ ጊዜያችንን ባንፈጅ...?”

ዕድሉ ቀና ክሱን ሰምቶ የሚደግፈው አለማግኘቱ አንገበገበው። ኀዘኑ እጥፍ ድርብ ሆነ። መናገሩ እንደማይጠቅም ሲሰማው ልቡ አመነታ። ቢሆንም የተበደለው አላለቀም። ቢያንስ “ተናግሬ ይውጣልኝ!” ብሎ ተቀበለ።

“አይ ሐዋዝ! አንተ ጎረቤቴ ሆነህ የደረሰብኝን ሁሉ ስታውቅ እንዲህ ማለትህ አሳዝኖኛል። ጊዜ የተፈጀብህ ለምኑ ነው? አናውቅም የት ውለህ የት እንደምታነጋ? ሌላ ምንም አልልህም አንተም ሴት ልጅ አለችህ። በልጅ የመጣ እንዴት እንደሚያንሰፈስፍ ደርሶብህ እየው።” ንግግሬ እንዳልጠቀመ አይቼያለሁ። ቢሆንም ልናገረውና የመጣው ይምጣ...”

ዋናው ዳኛ አንካሳ እግራቸውን በእጆቻቸው እያመቻቹ የሚሆነውን በዝምታ ይሰማሉ።

“ይቅር ብዬ አልፌው እንጂ የተበደልሁትስ ይህ ብቻ አልነበረም። ከሆነ አይቀር ግን ይኸው ስሙት። ታላቁ ልጄ እንደምታውቁት የቀኝ እጁ አራት ጣቶች ቆራጣ ናቸው። የእርሱ ታናሽ ደግሞ እጁም እግሩም ላይ ስድስት ስድስት ጣት አለው። ይህ እንዴት ሆነ? ሲቀለድብኝ መሆኑ ነዋ! .....አንድ ቀን ጠዋት የጀመርሁ ሥራ ፍለጋ ስንከራተት ውዬ ሰውነቴ ዝሎ አመሻሽ ላይ ቤት ደረስኩ። ምንም ምንም ሳልል፤ እህልም ሳልቀምስ፤ ልብሴንም ሳላወልቅ መጥረቢያዬን ቆጥ ላይ ሳልሰቅል ተኛሁ። ብዙም አልቆየ ታላቅ ልጄና ነፍሰጡር ሚስቴ በጩኸት ቤቱን ሲያናጉት ብትት ብዬ ተነሣሁ። ሳይ ከልጄ መዳፍ ላይ ደም እንደወራጅ ውኃ ይንዠቀዠቃል። ዘልዬ አፈፍ ሳደርገው አራት ጣቶቹ ተራ በተራ ጠብ፣ ጠብ ብለው እንደጉድፍ መሬት ላይ ወደቁ። ያ መጥረቢያ ከንፈሩ ደም ጠግቦ ተጋድሟል። የሆነው ወዲያው ገባኝ። ታዲያ ምን ዋጋ አለው? ከረፈደ ዕውቀት የቀደመ ጠርጣራነት እንደሚበልጥ ማን አስተምሮኝ ያኔ? ደንቆሮ፣ የደንቆሮ ዘር አይደለሁ። አንድ ቀን መጥረቢያዬን ማራቅ ብረሳ... ። ዛሬም ድረስ አውራ ጣቱ በመዳፉ ላይ ብቻዋን ፍርፍር ስትል ሳያት እንባዬ ይመጣል። ጠማማ ዕድሌን መግራት ተስኖኝ እንዳጎደልሁት ይሰማኛል!”

"ይበቃል ተብለሀል።"

...
“አይበቃኝም ገና መች ጀመርኩትና?! ኋላ ስንቀዠቀዠ ቤቱ ሄድኳ። ምነው ፈጣሪ ምነው ሳምንህ ጉድ ሠራኸኝ? ስል አለቀስሁ። ስለትህን አጉድዬ አውቃለሁ? የምበላው ባጣ እንኳ አሥራትና መባህን ነክቼ አውቃለሁ? ውለታ አታውቅም? አምላክ አይደለህም ተንደርድረህ ከሰው ልታንስ ነው? ምነው እኔን እንዳሻህ ብታደርገኝ? ምነው ልጆቼን ብትተውልኝ?” አልኩት። ሞኝ፣ የሞኝ ዘር አይደለሁ? ...የሰማኝ መሰለኝ። “አይዞህ
ያለኝ መሰለኝ። “ይቅርታህን! የዛሬን ብቻ እለፈኝ ትቼሃለሁ” ያለኝ መሰለኝ። “ታርቀናል” ብዬ እንባዬን ጠርጌ ተነሣሁ። ቤት ስደርስ ያቺ ወረግቡ ሚስቴ ስታምጥ ደረስኩ። ቀበቶዬን አላልቼ የምትሰጥም አንተ፤ የምትነሣም አንተ ተመስገን!” አልሁት። ክፋቱን ረሳሁለት። ሚስቴ ምዉ ሳይጠና ተገላገለች። ቆንጅዬ ወንድ ልጅ በጨርቅ ጠቅልለው አሳቀፉኝ። ሳይደግስ አይጣላም!” ይሉ የለ የእኛ ሀገር ሰዎች? ...ደጋጎቹ። “መከራዬን አይተሃልና ኀዘኔን በሳቅ፣ ለቅሶዬን በደስታ ቀይረሃልና” ስል ስሙን ካሣ አልኩት። የካሠኝ መስሎኝ! አይ ደንቆሮ፣ የደንቆሮ ዘር ...ቶሎ አይነቃም እኮ።

ያዋለደችው ሴት በደስታ የምሆነውን ሲያሳጣኝ ፊቷን ጨምታ ስታየኝ ጠረጠርኩና ጨርቁን ገለጥሁት። በእጆቹም በጣቶቹም ላይ ስድስት ስድስት ጣቶች አሉ። ስድስተኛ ሆነው የበቀሉት እንደሌሎቹ ጠንካራ ስላልሆኑ ወዲያና ወዲህ ተንከርፍፈዋል። ደነገጥሁ። ከማዘን ማበድ ቀረበኝ። ጣቱ ስድስት መሆኑ አይደለም፤ ነገረ-ሥራው ገርሞኝ እንጂ። የታላቁን አራት ጣት ነሳኸኝ ብዬ “ምነው?” ስላልኩት ካሣ ላይ መመለሱ ነው? ይሄ ቀልድ እንጂ ሌላ ምን ይሆናል? ድርቅ በጎርፍ ይካሣል? ሥርጉዳት በእባጭ ይሣሳል? ኧረ እንዲህም አድርጎ ቀልድ የትም የለ!”
4.6K views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 16:30:22 ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም
ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትም

ደራሲ-ሄኖክ በቀለ
መፅሀፍ- ሀገር ያጣ ሞት

እዚህ ሀገር ውስጥ መቃብራቸው ሊማስ አንድ ሐሙስ የቀራቸው፤ ሕይወትን በዓይናቸው ቂጥ ገላምጠው የጨረሱ፤ “ፍርድና ርትዕ ዘልቋቸዋል” የተባሉ አዛውንት የሚፈርዱበት በሰንበት አንዴ የሚቆም ሸንጎ አለ። በዳይና ተበዳይ ተጠፍረው ይቀርቡና ይካሰሳሉ። በዳይም፣ ተበዳይም የመጡበትን ተናግረው የተሰጠውን ፍርድ ተቀብለው አመስግነው ይሄዳሉ።

ዕድሉ ቀና “ሰማይ አይታረስ ንጉሥ አይከሰስ!” በሚል ማኅበረሰብ መሃል እየኖረ —ሰማይ ሊያርስ ንጉሥ ሊከስ እንባውን እያዘራ ደረሰ። ነታባ ጋቢ የለበሱ ዳኞች በሸንጎው መሃል ተሰይመዋል። ተከሳሽና ከሳሽ፤ ወሬ ሊያጦለጡል የመጣ የሀገር ሰው፤ ከወደቀው ዋርካ ጀርባ ተንቋጠው አሰፍስፈው ገቢር የሚቀላውጡ ሕፃናት ቦታውን ሞልተውታል።

ሸንጎውን የሚመሩት ሽማግሌ ከተቀመጡበት ብድግ ብለው ሁሉም ዝም እንዲል እጃቸውን እያወዛወዙ ምልክት ሰጡ። ሽማግሌው ፊታቸው በሽብሽባት የተፈሰፈሰ አሮጌ ቦርሳ የመሰለ፤ ድክም ፍዝዝ ብለው ዓይኖቻቸው ብቻ የነቁ፤ ጭብጥ የምታህል አናታቸው ላይ ግራና ቀኝ ትላልቅ ጆሮዎቻቸው ተሰፍተው ሦስት ፊት እንዳላቸው ነገር የሚያስቱ፤ ከወገባቸው ጎበጥ ያሉ ሰው ናቸው።

“ክስ ያለህ ቅረብ ተብለሃል!” አሉ ባለች በሌለች አቅማቸው ጅንን ብለው። ከልባቸው አበጥ ስላሉ ይሆን ከወገባቸው ጎበጥ ያሉት?

ዕድሉ ተንደርድሮ ከሳሽ የሚቆምበት ጉብታ ላይ ተሰየመ። “ይህ ሁሉ ነሆለል የተሰበሰበው “ሚስቴን ወሸሙብኝ”፤ “በሬዬን ነዱብኝ”፤ “አጥሬን ደፈሩብኝ” ሊል አይደል? እንደእኔ የተበደለ በድፍን ሀገሩ ቢታሰስ አንድ ይገኛል? ...ኧረ እንዲያውም!”

ዕድሉ ቀና ለወትሮው ክስና ክርክር ባለበት የማይደርስ፤ ከምድርም ከሰማይም የተስማማ፤ ቢበድሉት ውጦ ቢወጉት ደምቶ ዝም የሚል ጭምት ነበር። ዛሬ የከሳሽ ጉብታ ላይ ቆሞ ሲታይ የሸንጎው ታዳሚ ጸጥ እረጭ ብሎ አፈጠጠ። ሸንጎውን የሚመሩት ሽማግሌ ብቻ ደስ አላላቸውም ። ዕድሉ በዕድሜ የሚበልጡትን ከሰሾች ገፈታትሮ መቅደሙ አበሳጭቷቸው ይሁን፤ ወይ የስልጣናቸውን  አቅም የሚያሳዩበት ምቹ ጊዜ ጠብቀው ስላገኙ ይሁን..

“ተከሳሾችህን ወደ ፊት ጥራ ተብለሃል!”

ዕድሉ ቀና ከከሳሽ መደቡ ላይ ፈንጠር ብሎ ወረደ።
ለተከሳሽ የተዘጋጀው ክብታ ላይ ደርሶ በእጁ የያዛትን መጥረቢያ አስቀመጣት። የተሰበሰበው የሀገር ሕዝብ ሁኔታውን በግራ መጋባት ይከታተላል።

“ተከሳሾቼ ሁለት ናቸው። አንዱ ይኸው! ይሄ መጥረቢያ ነው። ሁለተኛውን እንኳ የት እንዳለ አላውቅም። ብጠራው አይመጣም። ብቆጣው አይፈራም። በሰው ሕግ አይመራም። “ተወኝ! ስለው ይስቅብኛል። ምን እንደበደልሁት እንጃ ብቻ ሰባት ሰማያዊ ጋቢ ለብሶ እያደፈጠ ያጠቃኛል። ባለክንፍ አሽከሮች፣ የገዘፉ አዝማቾች፣ እልፍ ነጫጭ ሎሌዎች አሉት...”

“ማሸሞሩን ትተህ ምናል ብትናገር?” ሽማግሌው ትዕግስት አጥተው ይቅበዘበዛሉ።

“እንደውም ሁለተኛው ተከሳሽ ፈጣሪ ነው።”

ዙሪያውን ከቦ የተዘለለው የሀገር ሰው ቦታውን በቱማታ አተረማመሰው። እዚያም እዚህም የተቆጡ ሰዎች በዕድሉ ድፍረት ተለኩሰው መንቦግቦግ ጀመሩ። አንዳንዱ ፈጣሪ ለእዚህ የንቀት ንግግር እዚያው በመብረቅ እንዳያደባያቸው ይለምናል። እስከነተረቱስ “ለኃጥአን የመጣ ለጻድቃን ይተርፋል!” ይሉ የለ? አንዳንዱ “ዕድሉ መወገሩ አይቀርም!” በሚል ተስፋ ሹል ባልጩት ፍለጋ በዓይኑ ይማትራል። አንዳንዱ ዓይናቸው ሥር ላበደው ዛፍ ቆራጭ ከንፈር ይመጥጣል። ከዋርካው ጀርባ ያደፈጡ አመዳም ሕፃናት ምን እንደተከሰተ ለመቅለብ ጆሮዎቻቸውን ዘርግተው ይቀላጠፋሉ።

ዕድሉ ድምፁ በጩኸት ማዕበል ተውጦ ምን እንደሚል አልተሰማም እንጂ፤ የሀገር ሰው ቁጣ ምንም ሳይመስለው ኃይለቃል እያወራ ይውረገረጋል።

ሽማግሌው ሕዝቡን እንደምንም ዝም አሰኝተው ወደ ዋናው ዳኛ ዞሩ። ፊታቸው ላይ ወፍራም ቁጣና ቀጭን ደስታ እኩል ተሸርቧል። በሰው ፊት ያዋረዳቸው ይህ ሰው አፍታ ሳይቆይ የሞቱን መግነዝ በራሱ እጅ ስለፈተለ ከንፈራቸው ላይ የታፈነ ፈገግታ ያጣጥራል።

“ምን ይላሉ እርስዎ?”

ዋናው ዳኛ ፊታቸው ላይ የተጋደመውን ጠባሳ ቆርጣ የምትስለመለም ዓይናቸውን አጨንቁረው “እስቲ እንስማው?! መቼም አይገድለን...” አሉ። ቁጣ ያደበላለቀው ሸንጎ ከዕድሉ ድፍረት በላይ በዳኛው ውሳኔ ተደናገጠ። ፊቶች ወዛቸው ተመጦ ተቁለጨለጩ። እንኳን ፈጣሪን ያህል ነገር ተከሶ ወትሮም ግራና ቀኝ ማገናዘብ አልተለመደም። ዋናው ዳኛ ከእዚህ በፊት ሸንጎ ረግጠው የማያውቁ ለሄላ-ገነት በቀረበው ሀገር በኩል የሚኖሩ ሽማግሌ ናቸው። በሰው በሰው ጠቢብነታቸው የሀገር ሸንጎ ጠሪዎች ጋር ደርሶ ተፈልገው የተገኙ ስለነበሩ ሕዝቡ እያጉረመረመም ቢሆን ትዕዛዛቸውን ተቀበለ።

ሽማግሌው እየቀፈፋቸው ወደ ዕድሉ ዞረው “ቀጥል ተብለሃል!” አሉ። የጎበጠ ጀርባቸው ተቃና። ያበጠች ልባቸው ፈርጣ ይሆን?
ዕድሉ ጉሮሮውን ጠራርጎ፤ ለፍልሚያ እንደሚዘጋጅ ሰው ሰውነቱን አፍታቶ ቀጠለ።

“እንግዲህ ክሴን ስሙት። ይህቺ መጥረቢያና ፈጣሪ በደካማ ጉልበቴ ገብተው በድለውኛል። በማይመጣ መጥተውብኛል። ካደፈጠ አውሬ፤ ከተሰበቀ ጦር፣ በክፉ ከሚያይ ጎረቤት ሸሽጌ ለወግ ትብቃ ያልኳት ልጄን ገድለውብኛል። እውነት እዚህ ሀገር ፍትሕ ካለ በእዚህ እንዲጠየቁልኝ ነው የምሻው።”
አንዱ ቁጣው ያልበረደ ወጣት ብድግ ብሎ...

“ምነው? ምነው ዕድሉ ምነው? ሰብሉ ሰምሮ፤ አዝመራው አሽቶ፤ ጠላት ደሞ በደጅ ቆሞ እያጓራ እያየህ ሲሆን ሲሆን ማመስገን ሳይሆን በንስሓና በጸሎት መትጋት ሲገባህ፤ ደረትህን ገልብጠህ ከአምላክ ጋር እኩል ቤት ትገጥማለህ? ምናል መቅሰፍት ባትጠራብን?!!”

ዕድሉ ቀና የወጣቱ መልስ እንደ አንዳች እያደረገው ከአፉ ላይ ነጥቆ ቀጠለ።

“ዝምበል!
“ያልተነካ ግልግል ያውቃል! ማለት እንደአንተ ዓይነቱን ነው። የራስህ ጉዳይ! የልጄን ደም ጠጥቶ የበቀለ አዝዕርት ምን ይረባኛል? ለምን ያሸተውን ጠራርጎ ነቀዝ አያነቅዘውም። ለምን አንበጣና ተምች አያደብነውም?! ሆድ ቢሞላ የልጄን ክብልል ዓይን ይሆነኛል? ጠግቤ ባገሳ የአንገቷን ሽታ የአንገቷን ሽታ ይለኛል? ምነው ደኅና ሰው ነህ ስልህ እንዲህ ቀለልህ?!”

ይቀጥላል...

@Zephilosophy
@Zephilosophy
3.9K views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-14 08:03:01 ፖለቲከኛ የሚኖረው በመታገል ነው። በማደናቀፍ እና በማደናቀፍ ነው የሚኖረው። እነዚህ የእርሱ ምግቦች ናቸው.ሂትለር በህይወት ታሪኩ እንዲህ ሲል ጽፏል፡- ጠላቶች እስካልሆኑ ድረስ ታላቅ መሪ መሆን አይችሉም። ጠላት ባይኖርህም ስለ ጠላት እያወራህ አገርህ አደጋ ላይ እንዳለች አስብ። ምክንያቱም ሰዎች ሲፈሩ ለባርነት ይዘጋጃሉ። ሰዎች ሲፈሩ ፖለቲከኞችን ለመከተል ዝግጁ ናቸው።

እብድ ሰው ቢሆንም አንዳንድ ጊዜ በጣም ጠቃሚ የሆኑ አረፍተ ነገሮችን ይናገር ነበር። ታላላቅ ሰብዓዊ መሪዎች የተወለዱት በጦርነት ጊዜ እንደሆነ ተናግሯል። ስለዚህ ትልቅ ጦርነት እስካልተፈጠረ ድረስ ታላቅ መሪ መሆን አይችሉም። ይህን ታላቅ መሪ የመሆን ህልምን እውን ለማድረግ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን መግደል አለብህ፤ እሱም ትክክል ነው። በሰላም ጊዜ ሰዎች መከተል አያስፈልጋቸውም፤ ቃሉ ሕግ ይሆን ዘንድ ሰዎች መሪያቸውን አምላክ አያደርጉም።

osho
1.9K views05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:43:38 ያለ ፍቅር የሚደረግ ወሲብና ያለ እዉነት የሚደረግ አምልኮ አንድ ናቸዉ።
ሁለቱም ከመንፈስ አጉድሎ ስጋን የሚያሞኙበት የመስገብገብ ስሜት ነዉ።"

ኦሾ/ osho

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.5K views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:37:02 ኦሾ እንዲህ ይላል:-

ፖለቲከኛ የስነልቦናና የመንፈስ ታማሚ ነው። በአብዛኛው ፖለቲከኞች ጤናማ ተክለ ቁመና ይኖራቸዋል። አካላቸው እንከን አልባ ሲሆን ዋናው ሸክም የሚያርፍበት አእምሮአቸው ግን ህመምተኛ ነው። አእምሮአዊ ህመማቸው ሲበዛ ደሞ የመንፈስ ታማሚ ይሆናሉ። የህመሙ አይነት የዝቅተኝነት ( የበታችነት) ስሜት ወይም Inferiority complex የሚባለው አይነት ነው።

የስልጣን ጥማት ያለበት ማንም ሰው የበታችበት ስሜት ተጠቂ ነው። በውስጡ የሚሰማው ዋጋ ቢስነትና ከሌሎች ማነስ ብቻ ይሆናል። በተለያዩ መንገዶች ከሌሎች እናንሳለን። ይህ ማለት ግን የበታችነት ስሜት ሊሰማን የግድ ነው ማለት አይደለም። ፖለቲካኛ ግን የበታችነት ደዌ ተጠቂ ነው። ራሱን ምጡቅ ከሆኑ የሰው ልጆች ጋር ሊያነጻጽር መሞከሩ የበታችነት እንዲሰማው ያደርገዋል። ራሳችሁን ከአንስታይንና ሲግመንድ ፍሩድ ጋር የምታፎካክሩ ከሆነ ዋጋ ቢስነትና ትንሽነት ሊሰማችሁ ይችላል።
ይህ የዋጋቢስነት ስሜት በሁለት መንገዶች ይወገዳል። አንዱ ሀይማኖት ሲሆን ሌላው ደግሞ ፖለቲካ ነው።
ፔለቲካ ይህን ደዌ ይደብቀዋል እንጂ አያጠፋውም። የህመሙ ተጠቂ በዚህ የበታችነት ስሜት የሚሰቃየው ሰው ፕሬዚዳንት ሊሆን ይችላል። የመሪነትን ወንበር መያዝ በውስጣዊ ማንነታችሁ ላይ ምን ለውጥ ያመጣል?
ከሞራርጂ ዴሳይ ጋር ያጋጨኝ ይኸው ጉዳይ ነበር።በህንድ ከሚከበረው አመታዊ የሀይማኖቶች የጋራ ጉባኤ አስቀድሞ የጃይና መነኩሴው አቻርያ ቱልሲ ከጋበዛቸው ሀያ እንግዶች መካከል እኔና ዴሳይ ነበርንበት። ወቅቱ 1960 ነበር ። ተጋባዦች በቀጣይ የሚሳተፉትን ሀምሳ ሺ የሀይማኖት ተከታዮች በተመለከተ ለመወያየት ነበር ለቅድመ ትውውቅ የተጋበዝነው። ሆኖም ግን ከመጀመርያው ነበር ችግር የተፈጠረው።
የችግሩ መነሻ ደግሞ ጋባዣችን የሆነው ቱልሲ ከፍ ካለው መቀመጫ ላይ ሲቀመጥ ሀያችን ደግሞ መሬት ላይ ተቀመጥን። አቀማመጡን የተቃወመው ብቸኛ ሰው ሞራርጂ ዴሳይ ነበር። ከሀያዎቻችን መካከል ዴሳይ ብቸኛው ፖለቲከኛ ሲሆን ሌሎቻችን ከተለያዩ መስኮች ነበር የመጣነው።
አጠገቤ የተቀመጠው ዴሳይ ተቃውሞውን እንዲህ ሲል ለጋባዣችን አቻርያ ቱልሲ አሰማ።
"...እኛ እንግዶቹ መሬት ላይ ተቀምጠን አንተ ከፍ ያለውን ወንበር መያዝህ ተገቢ አይደለም። ስብሰባ እየመራህ ቢሆን ችግር የለውም። ነገር ግን ከሀያችን ከፍ ብለህ መቀመጥህ ምን አይነት ስነ ስርአት ነው?"

መነኩሴው ተደናገጡ። ከወንበራቸው ባይወርዱም በሀፍረት ተሸማቀዋል። ፖለቲከኛው ሞራርጂ ዴሳይ ላነሳው ጥያቄ ምላሽ የሰጠው የአቻርያ ቱልሲ ምክትል ነበር። የመነኩሴው አቀማመጥ ለውይይቱ አመቺነት ተብሎ መሆኑን በመጥቀስ ማንንም ዝቅ አድርጎ ለማየት አለመደረጉን ተናገረ።
ሞራርጂ ግን በቀላሉ የሚያቆም አልሆነም። "እዚህ ለተገኘነው በሙሉ አለቃችን አንተ አይደለህም። ለምን ከኛ ከፍ ብለህ ተቀመጥክ? ድርጊትህ ስርአት አልባ አይሆንም? በማለት ሲጠይቅ መነኩሴው ብቻ ሳይሆኑ ሁላችንም ተረበሽን።

" ከይቅርታ ጋር- እኔ ልመልስልህ?" በማለት ዴሳይን ጠየኩት።
"መልሱን ማወቅ እፈልጋለው- መልስልኝ" በማለት ሲፈቅድልኝ መናገር ጀመርኩ።

"በመጀመርያ እዚህ ብቻህን አይደለም የመጣኸው። ከአንተ ውጪ 19 እንግዶች ተገኝተናል። አንተን ብቸኛው ጠያቂ ያደረገህ ማነው?" በማለት ጠየኩትና ወደሌሎቹ ተጋባዦች ዞሬ "የመነኩሴው አቀማመጥ ላይ ተቃውሞ ያለው ሌላ ሰው ካለ እስኪ እጃችሁን አሳዩኝ" ስል ጠየኳቸው። አንዳቸውም አላሳዩኝም።

ከዛ ወደ ዴሳይ ዞሬ "በመነኩሴው አቀማመጥ ስሜቱ የተነካው ብቸኛ ሰው አንተ ነህ። በአስቸጋሪ የበታችነት ስሜት አረንቋ ውስጥ መሆንህን ያሳብቅብሀል።እንደ ዶ/ር ካታሪ ያሉ ምሁራን ፈጽሞ ቁብ ያልሰጡት ነገር አንተን ብቻ ነው ያስቀየመህ።
ከአቻርያ ቱልሲ በላይ ኮርኒሱ ላይ ምትኖረው ሸረሪት ትታይሀለች? ለመሆኑ ከፍ ያለ ስፍራ ላይ መሆን የበላይ የሚያደርግ ይመስልሀል? እንግዲህ ስሜትህን የነካው ይሄ ነው። የህንድ የፋይናንስ ሚኒስቴር መሆን ያልፈወሰው ደዌ ውስጥህ አለ። አንድ ቀን የሀገራችን ጠ/ሚንስትር ለመሆን መፈለግህ አይቀርም" አልኩት።

በንግግሬ ተናደደ።"እብድ ነህ እያልከኝ ነው?" ሲል በቁጣ ጠየቀኝ

"አዎ" ስል መለስኩለት። "እነዚህ 18 ተሰብሳቢዎች ቅድም እጃቸውን አለማውጣታቸው ይህንኑ ያረጋግጥልሀል። የመነኩሴው ከፍ ብሎ መቀመጥ የረበሸው አንተን ብቻ ነው" ስል መለስኩለት።
"ለመሆኑመነኩሴው ቀድሞ ወንበሩ ላይ አስቀምጦህ ቢሆን ኖሮ መሬት ላይ ለተቀመጥነው ሌሎቻችን ክብር ስትል ተመሳሳይ ጥያቄ ታነሳ ነበር?" በማለት ጠየኩት።

"ፈጽሞ አስቤው አላውቅም ነበር። በርካታ ስብሰባዎች ስመራ ከፍ ያለ መድረክ ላይ ነው ምቀመጠው። ማንም ተሰብሳቢ ጥያቄውን አንስቶ አያውቅም።" በማለት መለሰልኝ።

"ጥያቄህ ለምን አቻርያ ቱልሲ ከፍ ያለ ቦታ ተቀመጠ የሚል አደለም። ያንተ ጥያቄ ለምን ከቱልሲ በታች ተቀመጥኩ የሚል ነው። የራስህን ህመም ወደ ሌላ ሰው አታጋባ።
" ምናልባት አንተ ብቻ ሳትሆን አቻርያ ቱልሲም የህመሙ ተጠቂ ይመስለኛል። በመነኩሴው ቦታ ብሆን ኖሮ መጀመርያ መድረኩ ላይ አልቀመጥም ነበር። ብቀመጥም ደግሞ ጥያቄ ስታነሳ ይቅርታ ጠይቄ እወርድ ነበር። ሆኖም ግን እንደምታየው አሁንም ከቦታው አልወረደም። ለጥያቄህ መልስ መስጠት ያቃተው ይመስላል። ከመነኩሴው ይልቅ እኔን ያሳሰበኝ የአንተ ሁኔታ ነው። በስልጣን ሚዛን እንዲሁም በበላይነትና በበታችነት የተሞላ ጭንቅላት ያላቸው ፖለቲከኞች ናቸው ።" በማለት ምላሽ ሰጠሁት።
በወቅቱ ዴሳይ ተናደደ። ላለፉት ሀያ አምስት አመታትም ቂም ያዘብኝ።


@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.6K views17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 05:43:22 .... ካለፈው የቀጠለ

በቆሻሻ መጣያ ውስጥ ያለን ነገር ወስደህ ለራስህ ማዳበሪያ መጠቀም ግን ትችላለህ፡፡ ወይም ደግሞ በቆሻሻ መጣያው ውስጥ በትግል መኖር ትችላለህ፡፡ ያለህ ምርጫ ይህ ነው፡፡ በስሜት ህዋሳትህ የተገነዘብከው ሁሉ ወደ ውስጥህ ስለሚገባ የምትቀበለውን ነገር በተመለከተ መምረጥ ባትችልም፣ የትኛውን እንደምትጠቀምና የትኛውን እንደማትጠቀም የማስተዋል ኃይል ግን አለህ፡፡ ራስህን በመመልከት ሕይወትህ ምን ያህሉ አስገዳጅ፣ ምን ያህሉ ደግሞ በማወቅ ላይ የተመሰረተ እንደሆነ ተመልከት፡፡ አብዛኛው ክፍል አስገዳጅ እንደሆነ ታያለህ፡፡ በአስገዳጅነት የተከሰትክ ከሆነ፣ ራስህ እንድትሆን በፈለግከው መንገድ አይደለህም ማለት ነው፡፡ በሕይወትህ ያለብህ አንድ ችግር፣ ሕይወት ሊሆን ይገባዋል ብለህ በምታስበው መንገድ የሚሆን አለመሆኑ ነው፡፡ በፈጣሪ የምታምን ከሆነ፣ አንድ ነገር በአንተ መንገድ ካልሄደ፣ በእርሱ መንገድ ሄዷል ማለት ነው። በፈጣሪ መንገድ የሄደ በመሆኑ ደስ ሊልህ ይገባል፡፡ ያ ግን እውነታ አይደለም፡፡ ችግሩ ዓለም በአንተ መንገድ አለመሄዱ ሳይሆን አንተ በራስህ መንገድ አለመሄድህ ነው።

በዓለም ላይ ማንም በአንተ መንገድ አይከሰትም፡፡ በዙሪያህ ያለ ማንኛውም ሰው መቶ በመቶ በአንተ መንገድ አይመጣም፡፡ አንተ ግን በራስህ መንገድ መሆን አለብህ፡፡ በራስህ መንገድ የማትሆን ከሆነ ግን አሳዛኝ ትሆናለህ፡፡ ሰው የመሆን አሳዛኝ ነገር ይህ ነው፡፡ ዓለም በአንተ መንገድ አለመሆኗ ችግር አይደለም፣ ችግሩ አንተ በራስህ መንገድ አለመሆንህ ነው፡፡ ውስጣዊ ነገሮችህን ካላስተካከልክ፣ በአጋጣሚ ለመኖር እየሞከርክ ነው ማለት ነው፡፡ ከአንድ ነገር ነፃ መሆንና አንድን ነገር አለማወቅ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ የዓለምን መንገዶች ካላወቅክ፣ ዛሬ ወይም ነገ ልትጋጭ ትችላለህ፡፡ የዓለምን ተንኮለኛ  መንገዶች የምታውቅ ከሆነ ግን ወደዚህ ውስጥ አትገባም፡፡ ስለዚህ ስቃይ በማወቅ የሚመጣ አይደለም፡፡ ማንም ሰው አውቆ ራሱ ላይ ስቃይ አይፈጥርም፡፡ በሆነ መንገድ እየተሰቃየህ ከሆነ፣ ያ እየተሰቃየህበት ያለው ክፍል አያውቅም ማለት ነው፡፡ የተለያዩ ደረጃዎች ያሉት ስቃይ እየተከሰተ ከሆነ፣ በውስጥህ የተለያየ ደረጃ ያለው አለማወቅ አለ ማለት ነው፡፡

በውስጥህ ንቁ የሆነው የትኛውንም ነገር በምትፈልገው መንገድ ትጠብቀዋለህ፡፡ የማይታወቀውን የትኛውንም ነገር ደግሞ በምትፈልገው መንገድ ልትጠብቀው አትችልም፡፡ ስለዚህ በሕይወትህ ልታደርገው የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር ራስህን በበለጠ ሁኔታ ንቁ ማድረግ ነው፡፡ ሁሉም ነገር ሙሉ በሙሉ ንቁ እንዲሆን ጥረት የምታደርግ ከሆነ፣ አንተነትህ መቶ በመቶ በምትፈልገው መንገድ ይሆናል፡፡ ይህ አንድ ሽራፊ ሕይወት ልክ አንተ በምትፈልገው መንገድ ይሆናል፡፡ ያ በሚሆንበት ጊዜ ያለጥርጥር ራስህን እጅግ ደስተኛ ሰው እንደምታደርግ ጥያቄ የለውም፡፡

ምንጭ ፦ የህይወት ኬሚስትሪ (ሳድጉሩ)
ትርጉም ፦ ሀኒም ኤልያስ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.2K views02:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ