Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የቴሌግራም ቻናል አርማ yenetube — YeneTube Y
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
Digitalliteracy
Mastercardfoundation
Educationinnovation
Shegamedia
Technologyineducation
Edtechmondaysethiopia
Edtechethiopia
Jointheconversation
Equityineducation
All tags
የቴሌግራም ቻናል አርማ yenetube — YeneTube
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
Digitalliteracy
Mastercardfoundation
Educationinnovation
Shegamedia
Technologyineducation
Edtechmondaysethiopia
Edtechethiopia
Jointheconversation
Equityineducation
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.12K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 488

2021-02-05 13:13:23
ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join

@giftsoflovee
@giftsoflovee

+251914839754
+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
5.8K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-05 13:13:23
የዋሪት የውሀ ማጣሪያ ከ15% ልዩ ቅናሽ ጋር

ሰብስቤ www.sebsibie.com በመግባት መገበየት ይችላሉ።

ሰብስቤ ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

ከ3,200 በላይ ዕቃዎች

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070

Dedicated online shopping platform
6.5K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 22:58:53
14.0K viewsedited  19:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 21:12:07
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 749 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተያዙ፡፡

ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ 6,002 የላብራቶሪ ምርመራ 749 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

ባለፋት 24 ሰዓታት የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርን 2,126 አድርሶታል።

በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 254 ሰዎች ማገገማቸው የተነገረ ሲሆን ይህም ከበሽታው ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር 124,242 አድርሶታል፡፡

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 140,157 ደርሷል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
18.0K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 20:30:17 የሱዳን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በምዕራብ አርማጭሆ ሰላም በር ከተባለ አካባቢ የተፈናቀሉ ሰዎች እስካሁን ተገቢ መጠለያ አላገኘንም ሲሉ አማረሩ።

እንደተፈናቃዮቹ ከወራት በፊት በተፈጠረው ወቅታዊ ሁኔታ መኖሪያ አካባቢቸውን ቢለቁም ተገቢ የመጠለያ ድጋፍ አልተደረገላቸውም፡፡የከተማ አስተዳደሩ ከዚህ በፊት መጠለያ ሰትጫቸዋለሁ ቢልም ተፈናቃዮች ግን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው ነበር፡፡ የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ኮሚሽነር ዘለዓለም ልጅለም በበኩላቸው 1ሺህ 800 ያህል ተፈናቃዮች መኖራቸውን የሚያመለክት መረጃ እንደደረሳቸው አመልክተው አጠቃላይ ጉዳዩን የሚያጠና ቡድን ነገ ወደ ቦታው እንደሚሄድም ተናግረዋል፡፡

[DW]
@YeneTube @FikerAssefa
16.8K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 19:54:36
ብሄራዊ የመረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአቪዬሽን ደህንነት ሙያ ያሠለጠናቸውን 200 ኦፊሰሮች አሰመረቀ!

በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ስር የሚገኘው ብሄራዊ የመረጃ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በአቪዬሽን ደህንነት ሙያ ያሠለጠናቸውን 200 ኦፊሰሮች አስመረቀ። የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመሰገን ጥሩነህ  ተመራቂዎቹ የሀገር ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሚያደርገውን  የተሳካ ጉዞ ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ እገዛ እንደሚኖራቸው ገልፀዋል።

[FBC]
@YeneTube @FikerAssefa
12.8K views16:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 19:51:52
ዕቃ ለማውረድና ለመጫን የተጋነነ ዋጋን የሚጠይቁ ጫኝና አውራጆችን የማጣራት ሥራ በማድረግ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን አስታወቀ።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ኮማንደር ፋሲካ ፋንታ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፣ ለዕቃ ማውረድና መጫን የሚከፈለው ገንዘብ በዕቃ ባለቤትና በአውራጁ መካከል በሚደረገው ስምምነት እንጂ አውራጁ በተመነው ዋጋ ብቻ እዳልሆነ አስታውቀዋል።የዕቃው ባለቤት ከፈለገ እቃውን በራሱ የማውረድና የመጫን ሙሉ መብት እንዳለ ያመለከቱት ሃላፊው ፣ ባለቤቱን የመጫንና የማውረድ መብት የሚከለክሉ እንዲሁም ለመሥራትም የተጋነነ ዋጋ የሚጠይቁ ጫኝና አውራጆች ተጣርተው ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስታውቀዋል።
ከዚህ በፊት በተለይ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 9፣ ወረዳ 10 እና ወረዳ 12 በጎሮ፣ በቡልቡላና በሰሚት አካባቢ እንዲሁም በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በኮዬ ፈጬና የጋራ መኖሪያ ቤቶችና በመናኸሪያ አካባቢ፣ በጫኝና በአውራጅ ሥራ የተደራጁ 170 የሚሆኑ ሰዎች ለራሳቸው ከቤት ሆነው ሌሎች ሰዎችን በመቅጠር በህብረተሰቡ ላይ የተለያዩ ወንጀሎችን ሲያስፈጽሙ ተደርሶባቸው ህጋዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ጠቁመዋል።

[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
11.9K viewsedited  16:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 19:49:54 በትራፊክ አደጋ የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ።

ዛሬ ከቀኑ 9፡00 ሰዓት በምስራቅ ጎጃም አስተዳደር ዞን በሞጣ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሦስት ሰዎች ህይወት ማለፉን የሞጣ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

መነሻውን ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ንብረትነቱ የቻይና መንገድ ስራዎች ከሆነ ፒካፕ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው የተፈጠረው።

በህዝብ መኪና ውስጥ ያሉ አራት ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

የግጭቱ መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑን ከሞጣ ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@YeneTube @FikerAssefa
14.5K views16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 19:36:53 የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በትግራይ ክልል የነበሩ የኤርትራ ስደተኞች በህወሃት ታጣቂዎች ጉዳት እንዳይደርስባቸው ሲከላከል እንደነበር ከስደተኞች መስማቱን የስደትና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጄንሲ አስታወቀ፡፡

የኤጄንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ በትግራይ ክልል በሚገኙ የስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ስደተኞች ከጥቃት እንዲጠበቁ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ሚና መጫወቱን አስታውቀዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ ራሳቸው ከ15 በላይ ስደተኞችን ማነጋገራቸውን የገለጹ ሲሆን ለህይወታቸው በመፍራት ከሽመልባና ከጻጽ መጠለያ ጣቢያዎች መውጣታቸውንና መከላከያ ሰራዊት ጥቃት እንዳይደርስባቸው እንደተከላከለላቸው እንደገለጹላቸው ተናግረዋል፡፡

አቶ ተስፋሁን የኢትዮጵያ መንግስት “የሕግ ማስከበር ዘመቻ” ከመጀመሩ በፊት በሽመልባ 8ሺ፤ በህጻጽ ደግሞ 11 ሺ 500 ስደተኞች ይኖሩ እንደነበር ገልጸው አሁን ግን በነዚህ መጠለያ ጣቢዎች ውስጥ ምንም ስደተኛ እንደሌለ ተናግረዋል፡፡

በትግራይ በሚገኙ አራት የሥደተኛ መጠለያ ጣቢዎች 92ሺ ስደተኞች ይገኙ እንደነበር የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ ከነዚህ ውስጥ በሁለቱ ጣቢያዎች ውስጥ የነበሩ ስደተኞች አሁን ላይ በአማራ ክልል፣ በአዲስ አበባና በዛው በትግራይ ክልል እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በሽመልባና በህጻጽ የስደተኛ መጠለያ ጣቢያዎች ይኖሩ ከነበሩት መካከል አራት ሺ የሚሆኑ ስደተኞች አሁን ላይ ወደ ማይ አይኒ እና አድሀሩሽ መጠለያ ጣቢያዎች መግባታቸውን አቶ ተስፋሁን ተናግረዋል፡፡ በስደተኞቹ ላይ ከፍተኛ ችግር መድረሱን፤መጎዳታቸውንና ሌሎችንም በተመለከተ ወደፊት የማጣራት ስራ እንደሚሰራ አቶ ተስፋሁን ተናግረዋል፡፡
በሱዳን የሚገኙ የኢትዮጵያ ስደተኞችን በተመለከተ መቸ ወደ ሀገር ቤት ይመለሳሉ የሚለውን በትክክል ማስቀመጥ እንደሚያስቸግር ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

ቁጥራቸው ወደ 60 ሺ እንደሚጠጋ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን መግለጹን ያነሱት አቶ ተስፋሁን ሁሉም ዜጎቻችን ወደሀገራቸው እንዲመለሱ እንፈልጋለን ብለዋል፡፡

ሱዳን ያሉት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲመጡ እንፈልጋለን ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ 

Via:- Alian
@Yenetube @Fikerassefa
11.2K viewsedited  16:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 16:34:56
መልካም ገና ይሁንላችሁ - ዴሊቨሪ ሀዋሳ
ከተማችን ላይ ከሚገኙ ሁሉም ሬስቶራንቶች ጋር አብረን እንሰራለን በቤቶ ሆነው የሚያስፈልጎትን ይዙዙን።

ስልክ :- 0952626262 / 0462126282

#deliveryhawassa #Hawassa
4.1K views13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ