Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የቴሌግራም ቻናል አርማ yenetube — YeneTube Y
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
Digitalliteracy
Mastercardfoundation
Educationinnovation
Shegamedia
Technologyineducation
Edtechmondaysethiopia
Edtechethiopia
Jointheconversation
Equityineducation
All tags
የቴሌግራም ቻናል አርማ yenetube — YeneTube
ርዕሶች ከሰርጥ:
Ethiopia
Digitalliteracy
Mastercardfoundation
Educationinnovation
Shegamedia
Technologyineducation
Edtechmondaysethiopia
Edtechethiopia
Jointheconversation
Equityineducation
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.12K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 489

2021-02-04 16:31:44 የኦነግ አባላት፣ የተለያዩ የድርጅቱ መዋቅሮች እና አመራሮች በፓርቲው የተፈጠረው ችግር መፍቻ ሊሆን የሚችለውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳሰበ፡፡

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የአመራሮች ክፍፍልን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተቋቋመበት አዋጅ 1133/2011 በምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች እና በስነምግባር አዋጅ 1162/2011 በተሰጠው ስልጣን መሰረት ፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ እና ቁጥጥር የሚያደርግ ተቋም ነው። በዚህም መሰረት በኦነግ ፓርቲ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት ህጋዊ እና ተደጋጋሚ ጥረቶችን ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል።

በዚህም መሰረት

1. የፓርቲው የተወሰኑ የስራ አስፈጻሚ አባላት ነሃሴ 01 ቀን 2012 ዓ.ም በተጻፈ እና በድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር በተፈረመ ደብዳቤ የድርጅቱን ሊቀመንበር መታገዳቸውን ለቦርዱ አሳውቀው እንደነበር፣ ከዚህም በተጨማሪ የድርጅቱ አመራር ላይ ተከታታይ አቤቱታዎች አስገብተው እንደነበር ይታወሳል።

በሌላ በኩል የድርጅቱ ሊቀመንበር መስከረም 02 ቀን 2013 ዓ.ም ድርጅቱ ብሔራዊ ምክር ቤት ስብሰባ አድርጎ የፓርቲውን ምክትል ሊቀመንበር፣ የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን እንዲሁም የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት እስከሚቀጥለው የድርጅቱ ጠቅላላ ጉባኤ ድረስ ከሃላፊነታቸው ታግደው እንዲቆዩ እንደወሰነ ለቦርዱ አሳውቀዋል።

2. ፖለቲካ ፓርቲ አባላት መኻከል አለመግባባት ሲከሰት እና ለቦርዱ አቤቱታ ሲቀርብለት በአዋጅ ቁጥር 1162/11 አንቀፅ 74 ንዑስ አንቀፅ 6 መሠረት ጉዳዩን ተመልክቶ የውሣኔ ሃሣብ የሚያቀርብ የባለሙያዎች ጉባኤ ለማቋቋም በተሰጠው ስልጣን መሰረት በማድረግ የሁለቱንም ቡድኖች ደብዳቤዎች እና አቤቱታዎች እንዲሁም የውስጥ ህጎች የሚያይ የባለሞያዎች ኮሚቴ ለማቋቋም ውሳኔ አሳልፎ እንደነበርም ይታወሳል፡፡

በዚህም መሰረት በእነ አቶ አራርሶ በኩል ባለሞያ ቢመድቡም ፣ በእነ አቶ ዳውድ በኩል ባለሞያ ለመመደብ ፍቃደኛ ካለመሆናቸውም በላይ የፓርቲው የውስጥ ደንብ መሰረት መጠናቀቅ ያለበት ጉዳይ ነው በማለት መልስ በመስጠታቸው የባሞያዎች ጉባኤ ማቋቋም ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

3. በኦነግ አመራር መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የተደረገው የመጀመሪያው የቦርዱ ጥረት ባለመሳካቱ ጉዳዩን ከባለሞያዎች ጉባኤ ይልቅ በራሱ ሊያየው ተገድዷል። በዚህም መሰረት ከሁለቱም ወገን የገቡትን እገዳዎች በማየት እና የገቡ ሰነዶችን በመመርመር እንዲሁም ከሁለቱም ቡድን አመራሮች ጋር እንዲሁም ከስነስርአት እና ቁጥጥር ኮሚቴ አመራር አባላት ጋር ሰፊ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱም ወቅት ፓርቲው አመራር ቀውስ ውስጥ እንደገባ፣ ለአባላቱ አመራር መስጠት የሚችልበት ሁኔታ ላይ እንዳልሆነ፣ በተለይም ደግሞ ሁለቱም ቡድኖች ያቀረቧቸው እገዳዎች ህጋዊ እንዳልሆኑ ቦርዱ ወስኗል። በዚህም መሰረት የሁለቱም ወገን እገዳ የቀረበባቸው አባላት በነበራችው ህጋዊ ሃላፊነት ላይ እንደሚቆዩ ወሰነ።

በተጨማሪም ሁለቱም አካላት ህጋዊ ሂደቱ የተሟላ ሰነድ ባለማቅረባቸው፣ ፓርቲው ያለበት የአመራር ቀውስ ለመፍታት አለመቻላቸውን በመረዳት ቦርዱ የአመራር መከፋፈሉን ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወን የፓርቲው አባላት መሪዎቻቸውን እንዲመርጡ ታህሳስ 08 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ከመወሰኑም በተጨማሪ የጠቅላላ ጉባኤውን ለማመቻቸት ሃላፊነቱንም እንደሚወስድ አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል።

4. ከላይ በተጠቀሰው ውሳኔ መሰረት ለሁለቱም አመራር ቡድኖች ቦርዱ ውሳኔ በደብዳቤ ደርሷቸው የመጀመሪያውን ውይይት በቦርዱ አመቻችነት በጋራ ለማከናወን የመጀመሪያውን የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አባላት ጥሪ ቢደረግላቸውም በድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር አቶ አራርሶ የሚመራው የስራ አስፈጻሚ ቡድን ቦርዱ በጠራው ስብሰባ ላይ ሲገኝ በአቶ ዳውድ የሚመራው ቡድን ግን “ቦርዱ ይህንን የማመቻቸት ህጋዊ ሚና የለውም” በማለት በውይይቱ ላይ አልገኝም በማለታቸው በቦርዱ የተደረገው ጥረት አሁንም ሊሳካ አልቻለም።
5. ይህ ሂደት በዚህ ላይ እንዳለ ሁለቱም ወገኖች የተለያዩ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ማመልከቻዎችን ለቦርዱ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል።

6. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 19 ቀን 2013 ዓ.ም ባደረገው የቦርድ አመራር አባላት ስብሰባ በኦነግ ስራ አስፈጻሚ መከፈልን አስመልክቶ እስከአሁን የተደረጉ ጥረቶችን እና ለመፍታት የወሰዳቸውን እርምጃዎች በዝርዝር መርምሯል። በዚህም መሰረት ቦርዱ እጁ ላይ ባሉት የህግ እና የአስተዳደር መሳሪያዎች በመጠቀም ሊያግዝ የሚችልበት ተጨማሪ አሰራር አለመኖሩን ተረድቷል።

7. በዚህም መሰረት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አባላት፣ የተለያዩ የድርጅቱ መዋቅሮች እና አመራሮች ለችግሩ መፍቻ ሊሆን የሚችለውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ቦርዱ ማሳሰብ እንደሚገባው ወስኗል። በመሆኑም ፓርቲው በመሃከሉ ያለውን አለመግባባት በስራ አስፈጻሚ አመራሮቹ ሊፈታ ባለመቻሉ የተለያዩ የድርጅቱ መዋቅሮች እና አባላት አውቀው ጠቅላላ ጉባኤ እነዲከናወን የሚያደርጉባቸውን ማንኛውንም መንገዶች እንዲጠቀሙ ቦርዱ በጥብቅ ያሳስባል።

Via:- FBC
@Yenetube @Fikerassefa
12.3K viewsedited  13:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 16:18:07 ኮሮና ቫይረስ ወንዶች በተፍጥሮ የመውለድ አቀማቸውን ሊቀነስው እንደሚችል ሳይንቲስቶች አስታወቁ።

በቻይና ሃውዞንግ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚገኙ ተማራማሪዎች አገኘን ባሉት ውጤት ከሆነ የኮሮና ቫይረስ ከሚያስከትላቸው የረዥም ጊዚያት የጎንዮሽ ጉዳቶች መካከል አንዱ የወንዶችን የመውለድ አቅም የሚያዳክም መሆኑ ነው ያስታወቁት፡፡

እንደ ሳይንቲስቶ ከሆነ (called Angiotensin-converting enzyme 2) የተባለው ኢንዛይም በከፍፈተኛ ቁጥር በሳንባ፤ በአንጀቶች፤ በልብ፤ በኩላሊቶችና በወንዴ የዘር ማምረቻ አካላት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ይሄውም በወንዶች የዘር ምርት እንዲመረት ይረዳል ብለዋል፡፡

ስለሆነም ቫይረሱ የዚህን ኢንዛይም ቁጥሩን እንደሚቀንሰው ደርሰንበታል ብለዋል እነዝ፡፡

ይሄውም በውንዶች የዘር ፍሬ ምርት ላይ ቀጥተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው ብለዋል ሳይንቲስቶቹ፡፡

ተመራማሪዎቹ በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ምርምር የተደረገላቸው ወንዶች በመራቢያ አካላቸው ውስጥ የዘር ፍሬ ምርታቸው በቁጥር ሳይያዙ ከነበረው የቀነሰና እየቀነሰ እንደሚሄድም አመላክተዋል፡፡

ቁጥሩ ከመቀነሱም በተጨማሪ ያሉት የዘር ፍሬዎችም ቢሆኑ እንቅስቃሲያቸው የዘገየና በሴቶች ማህጸን ውስጥ ጽንስ ለመፍጠር የሚስችለውን እንቁላል የመስበር ጉልበቱ የተዳከመ ነው ሲሉ ጠቁመዋል፡፡

ሳይንቲስቶቹ በተለይይ በኮሮና ቫይርስ ተይዘው ላገገሙ ወንዶች፤ ልዩ ክትትልና ምርመራ ሊደረግላቸው ይገባል በማለት ያስጠነቀቁ ሲሆን፤ አሁን የተገኘው አመላክች ነገር ደግሞ በጉዳዩ ላይ እጅግ እንገብጋቢ የሆነ ጥናትና ምርምር እንዲደረግበት በር ከፋች መሆኑን ጥሪ አቅበዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

Via:- Ethio FM
@Yenetube @Fikerassefa
15.1K views13:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 16:16:59 የጥር ወር ዋጋ ግሽበት ጭማሪ አሳየ፡፡

የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበትመረጃ ሁኔታ በጥር ወር 2013 ዓ/ም የተመዘገበው አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር በ19.2 በመቶ ከፍ ብሎ ታይቷል፡፡

አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ወር ጋር ሲነፃፀር በ1.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

የምግብ ዋጋ ግሽበት የጥር ወር 2013 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነፃፀር በ23.1 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

በያዝነው ወር በአብዛኛው የእህል አይነቶቸ፣ አትክልትና አንዳንድ የጥራጥሬ ዓይነቶች የዋጋ ጭማሪ አስመዝግበዋል።

በሌላ በኩል ስኳር፣ የምግብ ዘይት፣ ቅመማ ቅመም፣ ድንች እና ቡና ዋጋ ጭማሪ በዚህም ወር በመቀጠላቸው ለዋጋ ግሽበት ምጣኔ መጨመር አስተዋጽኦ አድርገዋል ሲል የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አውርቷል።

ያለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ዋጋ ከአሁኑ ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር በንጽጽር ዝቅተኛ ስለነበር የዋጋ ግሽበቱ በያዝነው ወርም ከፍ ብሎ ታይቷል፡፡

በሌላ በኩል ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት የጥር ወር 2013 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ጋር ሲነፃፀር የ14.5 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

ከምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከፍ እንዲል ካደረጉት ዋና ምክንያቶች ውስጥ በተለይም በአልኮልና ትምባሆ፣ አነቃቂዎች (ጫት)፣ የቤት እንክብካቤና ኢነርጅ (ማገዶና ከሰል) ፣ የቤት መስሪያ እቃዎች፣ ህክምና፣ ትራንስፖርት (ነዳጅ) እና ጌጣጌጥ (ወርቅ) ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ ነው ተብሏል፡፡

Via:- Sheger
@Yenetube @Fikerassefa
11.4K views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 12:39:34
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በጎንደር ከተማ ያቋቋመውን የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከል ሥራ አስጀመረ።

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ 347 አባላትና ከ140 በላይ አባል ያልሆኑ ተገበያዮች እንዲሁም የኤሌክትሮኒክ የግብይት ማዕከላት በአዲስ አበባ፣ በሃዋሳ፣ በሑመራና በነቀምት ከ22 ሺህ በላይ ደንበኞች አሉት።

ዛሬ ደግሞ በጎንደር ከተማ ዘመናዊ የኤሌክትሮኒክ ግብይት ማዕከልን ወደ ሥራ አስገብቷል። ማዕከሉ ከ90 በላይ ተገበያዮችን በአንድ የግብይት መርሐ ግብር ማስተናገድ የሚችል ነው።

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የኢፌዴሪ ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበልና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድማገኝ ነገራን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው ወደ ሥራ መግባቱ የተበሰረው።

የአካባቢው ተገበያዮች ወደ አዲስ አበባ መሔድ ሳይጠበቅባቸው በቀጥታ የግብይት ውድድሩ አካል እንዲሆኑ የሚያስችላቸው ዘመናዊ አሰራር ነው። ይህም ከፍተኛ ወጭንና እንግልትን የሚቀንስ አሰራር ነው ተብሏል።

ምርት ገበያው የጥራጥሬና ቅባት እህሎችንና ቡና አቅራቢዎች ከሸማቾች ጋር በኤሌክትሮኒክ ሥርዓት በመደራደር የሚገበያዩበት ዘመናዊና ቀልጣፋ አሠራር መሆኑን በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የንግድ ኦፕሬሽን ከፍተኛ ስፔሻሊስት አቶ ቸርነት ታመነ ለአብመድ ገልጸዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
12.3K views09:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 11:26:51 አልማ በዚህ አመት መጨረሻ 6 ሺህ የመማሪያ ክፍሎችን ሰርቼ አስረክባለው አለ።

የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) ከተመሰረተ ጀምሮ የአባላቱን ቁጥር እየጨመረ የተለያዩ ስራዎችን እንደሰራ ይገለጻል።

በተለይም በትምህርት በጤና እና ስራ ፈጠራ ዘርፎች የሰራው ስራ ተጠቃሽ ነው።

የአማራ ልማት ማህበር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ሞገስ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት በክልሉ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች 84 በመቶዎቹ ከደረጃ በታች ናቸው ብለዋል።

ይህንን ችግር ለመቅረፍና ደረጃቸውን ጥሩ ለማድረግ በዘንድሮው አመት ብቻ 6 ሺህ የመማሪያ ክፍሎችን ሰርተን እናስረክባለን ሲሉ ተናግረዋል።

ትምህርት ቤቶቹ የሚሰሩትም በአማራ ክልል በሁሉም ዞኖች ሲሆን መማሪያ ክፍሎቹም ከመጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች እስከ መሰናዶ ላሉት አገልግሎት ይሰጣል ስለመባሉ ተሰምቷል።

የአማራ ልማት ማህበር በአሁኑ ሰአት 4.7 ሚሊየን አባላት እንዳሉት ገልጿል።

የአባላቱ ቁጥር ሲጨምርና የሀብት መጠኑ ሲያድግ በማህበራዊ ሀላፊነቶችም የእንቦጭ አረምን ለማስወገድ በተሰራው ስራና በጎርፍ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል።

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
12.3K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 10:05:48 የአውስትራሊያ መንግስት በኮቪድ የተያያዘ አንድ ግለሰብ ማግኘቱን ተከትሎ ከ2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ከቤታቸው እንዳይወጡ እገዳ መጣሉ ተሰምቷል ።

ባለፈው ሰኞ በምዕራባዊው አውስትራሊያ ፔርዝ ከተማ ሪፖርቱ ይፋ የተደረገ ሲሆን መንግስት ለ5 ቀን የሚቆይ ጥብቅ እገዳ ማስተላለፉን ሮይተርስ ዘግቧል ።

በቫይረሱ ከተያዘው ግለሰብ ጋር ቀረቤታ ነባራቸው የተባሉ 13 ሰዎችም በለይቶ ማቆያ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።
አውስትራሊያ ኮቪድ 19 በመከላከል ውጤታማ ስራዎችን የሠራች አገር ስትሆን እስካሁን 29 ሺህ ዜጎቿ በቫይረሱ ሲያዙ 909 ሰዎች ደግሞ ህይዎታቸውን አጥተዋል ።

የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ሁሉም ዜጎች ክትባት እንዲያገኙ እየሠራን ነው ብለዋል።

አሁን ላይ አውስትራሊያ 4.4 ቢሊዮን ዶላር በመመደብ 26 ሚሊየን ዜጎቿን ለመከተብ እየሠራች ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግን ተጨማሪ 1.9 ቢሊዬን ዶላር ያስፈልገናል እያሉ ይገኛሉ።

Via:- Ethio FM
@Yenetube @Fikerassefa
11.8K views07:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 09:26:54 የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ለ53 ቢሊየን ብር ኪሣራ ተዳርጓል!

የአዲስ አበባ ቤቶች ኮርፖሬሽን ሕገወጥ ተግባራትና በአመራር ዝርክርክነት ለ53 ቢሊየን ብር ኪሣራ መዳረጉ ተገለፀ። ኮርፖሬሽኑ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መገንባት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ኦዲት አለመደረጉም ተጠቆመ።በኮተቤ ሜትሮ ፖሊታን ዩኒቨርሲቲ የከተማ ልማት መምህርና በከተማ አስተዳደሩ አማካኝነት በጋራ መኖሪያ ቤቶች ዙሪያ ጥናት ያደረገው ቡድን አስተባባሪ ዶክተር ቱሉ ቶላ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት፤ የአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት ሲካሄድ ቆይቷል።በዚህ ጊዜ ውስጥም ኦዲት ተደርጎ አያውቅም።

ግንባታው ከፍተኛ የሀገሪቱ ሀብት የፈሰሰበት ቢሆንም በሕግና በሥራት የሚመራ አልነበረም የሚሉት ዶክተር ቶላ፤ በዚህ የተነሳ ለከፍተኛ የአሠራር ብልሹነትና የገንዘብ ዕዳ መዳረጉን አመልክተዋል።ቡድኑ ባደረገው የማጣራት ሂደት ለግለሰቦች የተላለፈበት መንገድ ያልታወቀ፣ መረጃ ያላቀረቡ፣ ዝግ የሆኑ፣ ባዶ ቤቶችና መሰል ችግሮች መለየታቸውን ጠቁመው፣ በከተማዋ ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት እጥረት እያለ ለ11 ዓመታት ዝግ ሆነው የቆዩ ቤቶች እንደነበሩም ጠቁመዋል። ከዚህም ባሻገር 21 ሺህ የሚሆኑ ቤቶች በማን እንደተያዙ ምን አይነት መረጃ ያልቀረበባቸው እንደነበሩም አስታውቀዋል።ቤቶቹ በዚህ መልኩ እንዲባክኑና ለሙስና እንዲዳረጉ የተደረገው ሆን ተብሎ ነው የሚሉት ዶክተር ቱሉ፣ ለዚህም ቤቶቹ መረጃ እንዳይኖራቸው ማድረግ አንዱ የሌብነት ስልት እንደነበረ ጠቁመዋል።

በዚህም መሰረት 85 ከመቶ የሚሆኑ ቤቶች ምንም አይነት የቤት መግለጫ የሌላቸው እንደሆኑ አመልክተዋል።በአዲስ አበባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ላይ ከህብረተሰቡ የሚሰሙ ሮሮዎች የቆዩ መሆናቸውን የሚናገሩት ዶክተር ቱሉ፣ ሆኖም በዚህ ደረጃ ችግሩ ሥር የሰደደ ስለመሆኑ ግንዛቤ አልነበረንም።ጥናት በምናደርግበት ወቅትም ሀገሪቷ በምን አይነት ውስብስብ ችግር ውስጥ እንደነበረች ማየት ችለናል ብለዋል።

[EPA]
@YeneTube @FikerAssefa
15.0K views06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 09:00:24 ወደ መቀሌ ተልኮ መደረሻው ሳይታወቅ የቆየው 1.3 ቢሊየን አዲሱ ብር ተገኘ!

አሁን በምርጫ ቦርድ ተዘርዞ ህልውናው እንዲከስም የተደረገው ቀድሞ የትግራይ ክልልን ሲያስተዳድር የነበረው ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እና በማዕከላዊው መንግስት መካከል ጦርነት የተቀሰቀሰ ዕለት ጥቅምት 24 ቀን 2013 አ.ም ምሽት ወደ ትግራይ መቀሌ በአሮጌው ብር እንዲቀየር በብሄራዊ ባንክ በአውሮፕላን የተላከው አዲሱ 1.3 ቢሊየን ብር መዳረሻው መታወቁን ዋዜማ ራዲዮ ሰምታለች።

ከምንጫችን እንደሰማነው በአሮጌው ብር እንዲቀየር የተላከው 1.3 ቢሊየን ብር መቀሌ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ አንድ ክፍል ውስጥ ታሽጎ ነው የተገኘው።

ህወሀት የሀገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት ፈፅሟል በተባለበትና ግጭቱ ወደለየለት ጦርነት በተሸጋገረበት በዚያ ዕለት አሮጌውን የብር ኖት እንዲተካ የተላከው ብር መዳረሻ አልታወቀም ነበር።

በወቅቱም መንግስት ገንዘቡን በትግራይ ክልል ላሉ የተለያዩ ባንኮች አከፋፍያለሁ ብሎ በብሄራዊው የቴሌቭዥን ጣብያ ማስነገሩ ይታወሳል። ማይጨው ፣ አደዋ ፣ሽሬ እንዳስላሴ እና አዲግራት ላሉ የተለያዩ ንግድ ባንኮች ብሩ ተከፋፍሏል ተብሎም ነበር። ሆኖም በወቅቱ በክልሉ ከነበረው ሁኔታ አንጻርና እንደተባለውም ብሩ በክልሉ ላሉ የባንክ ቅርንጫፎች እንዳልተከፋፈለ ዋዜማ ራዲዮ ከታማኝ ምንጮቿ አረጋግጣ መዘገቧ ይታወሳል።

የ1.3 ቢሊየን አዲሱን ብር እጣ ፈንታም የፌዴራል መንግስት የመቀሌ ከተማን ከተቆጣጠረም በሁዋላ በመቀሌ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደ አዲስ ስራ እንኪጀምር አላወቀም ነበር ብለውናል ምንጫችን። ሆኖም ከሳምንታት ወዲህ በመቀሌ ያለው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫ እንደገና ስራ ሲጀምር ነው የቅርንጫፉ ሰራተኞች ብሩን በአንድ ክፍል ታሽጎ ያገኙት። ገንዘቡ ሲገኝም የመጠን ቅናሽ እንዳልነበረው ከምንጫችን መረዳት ችለናል።የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በክልሎች ብርን ለማሰራጨት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎችን በማእከልነት እንደሚጠቀም ይታወቃል።

[ዋዜማ ራዲዮ]
@YeneTube @Fikerassefa
14.5K viewsedited  06:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 08:59:59
ለጓደኛ፣ ለወዳጅ ዘመድ፣ ለሙሽሮች እና ለተመራቂዎች ለየት ያለ ስጦታ መስጠት ይፈልጋሉ?
#join

@giftsoflovee
@giftsoflovee

+251914839754
+251936871620
#ኣድራሻችን፡ 4 ኪሎ: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ
4.1K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-02-04 08:59:59
የዋሪት የውሀ ማጣሪያ ከ15% ልዩ ቅናሽ ጋር

ሰብስቤ www.sebsibie.com በመግባት መገበየት ይችላሉ።

ሰብስቤ ሁሉንም ሰብስቦ በአንድ ላይ የያዘ የግብይት ድረገፅ

ከ3,200 በላይ ዕቃዎች

@SebsibieEthiopia
www.sebsibie.com

0953707070

Dedicated online shopping platform
5.9K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ