Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 37.92K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-12 16:41:37 ❀ ተጣሉብኝ ❀
༺♱༻
"ደቂቀ እምየ ተበአሱ በእንቲአየ ⇨ የእናቴ ልጆች ስለእኔ እርስበእርሳቸው ተጣሉብኝ" (መኃ ፩፥፮)

በዛሬው ዕለት የምናገናቸው የከበሩ የቤተክርስቲያን መብራቶች ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ ጴጥሮስ በአንድ ወቅት ስለ እናት ቤተክርስቲያን ክብር ተጣልተው እንደነበር! አንድነቷን ለመጠበቅ «ጽና ፣ አትዛል ፣ ፣ ከጥፋት ተመለስ…» ለመባባል በዛ መንድ ሳይሆን በዚህ መንገድ ጥቀማት እያሉ ተጣሉ!

ዛሬስ ለቤተክርስቲያን ሳይሆን በቤተክርስቲያን ላይ የተነሱ አንድነቷን ለማጽናት ሳይሆን ለመክፈል እንቅልፍ የሚያጡ “በዚህ መንገድ ቢሆን ነው ልክ” በሚል ቅንነት ያለው መበላለጥ ሳይሆን «ትክክል አንተ ነህ እኔ አጥፍቻለሁ» የሚል እንኳ ሲገኝ ይቅርታን በማይቀበል ጥመት ጨፍነው «ዘላቂ ጥቅም እንጂ ቋሚ ጠላት የለኝም» የሚለው ፖለቲከኛው እንኳን የሚበልጣቸው «ሃይማኖተኛ» መሳዮች!

ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው ሆኖ እየታመምን እናስታምማለን እንጂ ቁስላችን ሲያመረቅዙና ሕመማችን ሲያብሱማ ተዉ እንላለን! መንጋውን ለመጠበቅ ያልበቁ በመንጋው መጠበቅ የሚገባቸው ስማቸው እረኛ ከሚለው ወርዶ ተረኛ፣ ዘረኛ … በሚል እየተተካካ ቤተክርስቲያንን የሚያቆስሏት የሚያሳምሟት ከማያምን ይልቅ የከፉ እንዲህ ያሉ ገባርያነ እኪት ጸላዕያነ ሠናያት ለጥፋት ሲሮጡ ሔደው ሲለምኗቸው እምቢኝ ካሉ ተለይተው አለመወገዛቸው ፣ ተጠርተው አለመከልከላቸው ነገ የበለጠ ዋጋ ያስከፍለናል!

“ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው።” 【1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥8】

☞ የቀደሙቱ ጳውሎስና ጴጥሮስ ፣ አፈወርቅና ኤጲፋንዮስ ፣ ተክለሃይማኖትና ኤዎስጣቴዎስ… ስለእኔ እርስ በእርሳቸው ተጣሉብኝ ብላ የምታዝንላቸው ቤተክርስቲያን ነበረችን። ዛሬ ግን ስለእርሷ ሳይሆን በእርሷ ላይ ነውና ታዝንብናለች!

በሁሉ መንገድ ሴራው ቢበቃ፣ ሸፍጥ ቢቆም፣ «እበልጥ አልበለጥ» መባባሉ ብናስቀር ፣ መበሻሸቁን ብናርቅ … «በእነ እገሌ ምክንያት ይኽ ሆነ» ባዮች ወጣ ገባውን አይተን ለአንድነት እንቁም መለያየቱን እናስቁም፤ እድሉ ስላለን «በእኛ ምክንያት ነው ይህ ሁሉ የመጣው» ብለን የምንችለውን ብናደርግ። ባትሹት ግን ሁሉን የሚያስችለው እርሱ ሁሉን ይችላል!

ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእን ከሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ወደ አንጾክያ እንዲያስተምሩ ቢልካቸው በዚያ አሕዛብ መከራ አጸኑባቸው ኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ከቅዱስ ዮሐንስ ቢሰማ በአካሔድ መሳታቸውን ፣ ዘይቤ ማጣታቸውን አይቶ ተለያቸው … የአሕዛብን ልብስ ለብሶ ወደሸንጓቸው ገብቶ በፈሊጥ መከረና ከቅዱስ ጴጥሮስ ደርሶ በፊታቸው በጥፊ መታው ፦ ቅዱስ ጴጥሮስ " ተመይጠኑ ጳውሊ ሃበ ቀዳሚ ግብሩ" ብሎ ደነገጠ "እስኪ ሙት ካስነሳ እንመንበት?" ብሎ መክሮ ከሞተ ፫ ወር (መንፈቅ) ያለፈው የንጉሥ ልጅ እንዲያስነሳ ጠየቀላቸው! ሊቀ ሐዋርያት ሲጸልይ ቅዱስ ጳውሎስ ከውጭ፦ በእነርሱ ልብስ፣ ከውስጥ፦ በንጹሕ መንፈስ "ላንተ ብሎ እንጂ እሾም እሸለምበት ብሎ አይደለምና እባክህ ስማው አስነሳለት" እያለ በጥፊ ለመታው ወንድሙ ለመነ ያም ሙት ተነስቶ ያስነሳኝስ ያ ነው ብሎ ቅዱስ ጳውሎስን ጠቁሞላቸዋል በዚህ ነው "የእናቴ ልጆች ስለእኔ እርስበእርሳቸው ተጣሉብኝ" ያለው የተገለጠው!

የዛሬው የጠሉ የተጠሉና የተጣሉ ጥለኞች ለቤተክርስቲያን ምን እንደሚጠቅሟት እንጃ!

በእግራቸው ገስግሰው በእጃቸው ደም አፍሰው የተመለሱትን አጨብጭቦ ይቅር አልኩ ፣ ረሳሁ ፣ ታረቅሁ… ሲለን ያየነው አካል የገዛ አባቶቹን "ይቅርታቸውን አንቀበልም" ብሎ ልብንም በርንም ዘግቶ መጥፋትቱ የይቅርታን ትርጉም በምን እንደተረዳው እንጃ በራሱ መበቀል እግዚአብሔርን መጣል ነውና የበለጠ ቁጣ ይጠራል!

በዜና አበው እንዲህ የሚል ታሪክ አለ፦

አንድ ወንድም ወደ አባ ስልዋኖስ ሄደና "በጣም ክፉ ነገር እያደረሰብኝ ያለና ሊያጣፋኝ የሚፈልገኝ ጠላት አለብኝ:: እንዲገድሉኝም ለመሰርያን(ክፉ አድራጊዋች) ነግሯቸዋልና እንዲያሳርፍልኝና እንዲገስጸው ልነግር ወደ ባለስልጣኑ መሄድ እሻለሁ" አለው ::እርሱም "እ...የመሰለህን አድርግ አለው...." :: ያም ወንድም "እንግዲያውስ ጸልይልኝ" አለውና አብረው ጸሎት ሲያደርሱ "በደላችንን ይቅር በለን እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል" ከሚለው ስፍራ ላይ ሳሉ አባ ስልዋኖስ "በደላችንን ይቅር አትበለን:: እኛም የበደሉንን ይቅር ስለማንል::" አለ:: ያም ወንድም "አባ... ተው እንጂ እንዲህማ አትበል!" ቢለው "ይበቀልልህ ዘንድ ወደ መኮንኑ የምትሄድ ከሆነ ስልዋኖስ ከዚህ ሌላ አይጸልይም" አለው:: ያም እኁ(ወንድም) ይህን ሰምቶ ወደልቡ ቢመለስ ከእግሩ ሥር ተደፍቶ የበደለውን ይቅር አለ::

❀ ሮሜ. 12:19 "ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።"

❀❀ ማቴ. 5:44-45 "እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና።"

❀❀❀ ማቴ.6:15 "ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና"

በዚህ አያያዝ ክርስትናችን ምኑ ላይ ነው? እንግዲህ እኛም እንደዚህ እያልን ልንጸልይ ነው "በደላችንን ይቅር አትበለን:: እኛም የበደሉንን ይቅር ስለማንል::"
አቤቱ ማረን ፈሪሃ ኃጢዓትን ፣
ፍቅረ መለኮትን ፣
ተዘክሮ ሞትን … ከእኛ አታርቅብን

☞ ሐምሌ አቦ ፳፻፲፭ ዓ.ም. በቴዎድሮስ በለጠ የተጻፈ።
3.8K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-12 16:41:33
3.3K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 21:21:08 ምንት አሥሐቃ ለሳራ ?
   ሣራ ለምን ሳቀች ?
    【ዘፍ. ፲፰፥፲፱】
▦▦ 〣𓆩⪩♱⪨𓆪〣 ▦▦
        የሰው ልጅ ከሌላው ፍጥረት በተለየ በፊት ገጽታው ፣ በአካላዊ ኹኔታው ፣ በቁመናው ፣ በዓይን እንቅስቃሴው ከዚያም ባሻገር በመንካትና በአካል ርሕቀት ጭምር የሚገልጣቸው ሐሳቦች አሉት፤  ታዲያ እኒህ መንገዶች አንዳንዴ ከቃል ንግግር ባልተናነሰ ሳይሆን በተሻለ መንገድ እውነተኛ ስሜትን የመግለጥ ጉልበት ይኖራቸዋል።  የነገረ ሰብእ አጥኚዎች (anthropologist)  ይኽን በአካላዊ እንቅስቃሴና በፊት ገጽታ መልእክት የማስተላለፍ መንገድ ኪኔሲክስ [Kinesics] ብለውታል።

      አንድ መረጃ  ቀጥታ በቃል ሳይነገር  በተዘዋዋሪ መንገድ የስሜት ተረፈ ምርት (emotion residue) በሆነ አካላዊና የገጽታ ኩነት ሲገለጽ  ሐሳቡ እንዴት መተርጎም እንዳለበት ልማዳዊ የጋራ ስምምነቶች ከቦታ ቦታ የሚለያዩ ቢሆንም  በዲበ ተግባቦት (Meta-communication)  ግን የጋራ ትርጉም እንዲሠጣቸው ታሶቦ «እንዲህ የሚኮነው በዚህ ምክንያት ነው» የሚል አስማሚ ትርጉም ይቀመጥላቸዋል።

      ሳቅ ከእነዚህ ውሥጥ አንዱ ነው። በሥሉስ ቅዱስ በኩል ሐይመተ አብርሃም ውሥጥ ለሳራ የቀረበ ጥያቄ አለ ፦  «ምንት አሥሐቃ ለሳራ ☞ ሣራ ለምን ሳቀች?»  በእርግጥ ጥያቄው ሳራ የሳቀችው በምን ምክንያት እንደሆነ ለማወቅ ተፈልጎ የተነገረ ሳይሆን «እንዲህ ተደንቃ የምትስቀው ፣ እጅጉን ተገርማ የምትፈገው ስለምነው? »   ለማለት እንጂ ። “እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች?”  እርሷ ግን ቅሉ ከሐሳብ አስቀድሞ ሁሉን የሚመረምረውን ፣ ከሕሊና አስቀድሞ ሁሉን የሚያውቀውን ልብአውቃ የሆነ ማእምረ ኵሉ  አምላክን ፈርታ ብትክደውም  “ሣራም ስለ ፈራች፦ አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም፦ አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት።” (ቁ፲፭)

      ከዚህ ምዕራፍ ቀድሞ በተገለጠው የዘፍጥረት ታሪክ ውሥጥ ራሱን «ኤልሻዳይ» ብሎ ለአብርሃም የገለጠ ልዑል እግዚአብሔር ለይስሐቅ ይስቃል በሚል መጠሪያ መሰየም መነሻው ከነሚስቱ ሸምግሎ በእርግና ሳለ ትወልዳለህ ሲባል የአብርሃም ተገርሞ መሳቅ እንደነበር እናያለን፦
“አብርሃምም በግምባሩ ወደቀ፥ ሳቀም፥ …  እግዚአብሔርም አለ፦ በእውነት ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅን ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ይስሐቅ ብለህ ትጠራዋለህ ”  【ዘፍ ፲፯፥፲፯(፲፱)】

         አብርሃምና ሳራን ምን አሳቃቸው?  ደስታ ነዋ! 
⊚⃝⊚ ሰው ሲደሰት ይስቃል (ከውሥጥ ወደ ውጪ)
☞ ያዘነ ሰው ፊቱ ጠቁሮ የተደሰተ ሰው ፊቱ በርቶ መታየቱ ለዚያ ነው  «እምከመ ይቴክዝ ልብ ይዴምን ገጽ እምከመ ይትፌሣሕ ልብ ይበርህ ገጽ» እንዲል
⊚⃝⊚  በሌላ መንገድ ሰው ሲስቅም ይደሰታል (ከውጭ ወደ ውሥጥ)
☞ የተከዙ ሰዎች ወደሳቅ የሚቀርቡት ያዘኑ ሰዎች መዝናናት የሚመርጡት ለዚያ ነው   "ሳቅ የደስታ ምንጭ ነው" እንዲል

ኢያሱ ወልደ አልዓዛር (ወልደ ሲራክ) በመጽሐፉ "እስመ እምራእዩ ይትዐወቅ ሰብእ፣ ወእምገጹ ይትዐወቅ ጠቢብ ⇨ ሰው በመልኩ ይታወቃልና ፣ ጠቢብም በገጹ ይታወቃል"

የተረጋጋ፣ ተስፋ የቆረጠ፣  የታመመ፣ የደከመ ሰው ከቸኮለ(ከሚጣደፍ) ፣ ከበረታ ፣ ከሚጓጓ…  ሰው  የሚለየው በአካሐዱ ነው ፤   
           ያዘነ ከሚደሰት ፣ ወደመኝታ የሚሔድ ወደሥራ ከሚሔ ፣ ወደቤተክርስቲያን የሚሔድ ከማይሔድ…  በአለባበሱ እንደሚታወቅ። ሳቅም ከአካሔድና ከለባበስ በበለጠ የአንድን ሰው አሁናዊ ሁኔታ በተሻለ መልክ ያስረዳል፤ በ‘ኢሞጂ’ ውሥጥ የፈገግታ ገጽ / የሳቅ ፊት (smiley face) አንዱ የደስታ ስሜን ወኪል ሥዕላዊ ምልክት (ideogram)  ተቀምጧል።  

«ወእምልብሰቱ ለሰብእ ወእምሑረቱ ወእምሠሐቁ ይትዐወቅ ግዕዙ  ⇨ ካለባበሱና ካካሄዱ ከአሳሣቁም የተነሣ የሰው ጠባዩ ይታወቃል» 【ሲራ ፲፱፥፳፯(፴)】

እንዲያውም  አንዳንዴ ሳቅ ከቁጥጥር ውጪ ‘እየገነፈለ’ የደስታን ስሜት የውሥጥን ሐሴት በሌላው ፊት ያሳብቃል፤ እንደ ሳራ! ታዲያ  ፎቶ አንሺ ፣ ቪዲዮ ቀራጭ ፣ ሠዓሊ… መታወሻ  ምስልን ለማስቀረት ሲሻ "እስኪ ፈገግ በሉ" ማለቱ ቅሉ ለዚህ ነው "ፍሡሓ ገጽ" ሆኖ መታየት የደስተኝነት መገለጫ ነውና።

          አቡነ ኤርምያስንስ ምን አሳቃቸው?
አቡነ ኤርምያስን በሐዘን ፊት ፣ በተቋጠረ ገጽ ፣ በዝቶ በሚፈሰው እንባ ፣ በተከዘ ልብ የማያውቃቸው የለም! «ጦርነት» በተባለው እርስበእርስ ፍጅት ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር የመከራውን ጽዋዕ ቀምሰዋል እንደቀደመው ኤርምያስ
ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም  " ካህኑ ኤርምያስ ከሕዝበ እሥራኤል ጋር አብሮ የተሠደደው እስራኤሎችን ቃለእግዚአብሔር እንዲያስታውሳቸው ነው።" ብሏል! 

         እና ዛሬ ምን ተገኝቶ እንዲህ ይስቃሉ? 
“የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ” 【ነህ ፰፥፲】
እንደሳራ ትውልዱ ላይ ተስፋ ፈንጥቆ የበረከት ዘር ሲተካላቸው  በመካን ማሕጸን ፍሬ ቢታያቸው ገጻቸው በርቶ ፊታቸው ፈክቶ ታይቷል!  በሀገሬ ቲቪ የቀረበው የዶንኪ ቲዩብ ድንቅ ልጆች መሰናዶ በዚህ ሳምንት በደስታ የሚስቁ በሐሤት የሚፍለቀለቁ አቡነ ኤርምያስን ደጋግሞ አሳይቶናል። ዐይናቸው ውሥጥ አንድ ሕፃን ሶልያና ተፈራ ብቻ ሳትሆን  የብዙ ተተኪ አዳጊ ዜጎች ተስፋ ይታያል!  [

]

     ፈለገ አእምሮ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት በአቡነ ኤርምያስ ራእይ የታነጸው    “ታላላቅ ካቴድራሎችን ገንብተን በውስጡ አገልጋይ ከሚጠፋ አብነት ት/ቤቶችን ገንብተን እንደጥንቱ በድንኳን ብንገለገል ይሻለናል” በሚል ኃይለ ቃል እንዲህ ያለውን ፍሬ ለማየት ነበር።  ዛሬ ግን የባሰ ሌላ ችግር በሀገረ ስብከቱ ተጋርጧል፤

     ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ (ዶ/ር ) የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስና የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት የበላይ ጠባቂ በሀገራችን «በወንድማማቾች መኻል ተከስቶ በነበረው እርስ በእርስ ግጭት» የደረሰውን ውድመት ተከትሎ እሑድ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. በሚሌኒየም አደራሽ ከቀኑ 6፡oo ጀምሮ የወደቀችዋን ድንኳን ለማንሳት ፣ የተናደውን ቅጥር ለመጠገን ፣ የፈረሰውን ለማደስና እንደቀድሞው ዘመን ለመሥራት ማንም የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጥሪ እንዲህ ሲሉ ለቤተክርስቲያን ልጆች አስተላልፈዋል፦
‹‹የክርስትናው ሀዲድ ተሰብሮ የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ እንዳይቋረጥ ሃይማኖታዊ ግዴታችሁን ትወጡ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አሳስባለሁ፡፡››

«ንሕነኒ ውስተ ሐይላ ንደይ ልበነ ንዴግና ወንበላ በሐ  ወትረ ንሳለማ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ☞ እኛም በቤተክርስቲያን  ኃይል ልቡናችንን እንጨምር እንከተላት ሰላምም እንበላት» 【መጽሐፈ ቀሌምንጦስ ፲፩፥፶】

✞ ቴዎድሮስ በለጠ ✞ ሰኔ ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. ከፍራንክፈርት
7.4K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 18:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 21:19:33
4.5K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 21:01:55 እግዚአብሔር በወዴት ይገኛል ቢሉ፡-

በደዌ ደኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዘዉ በሚማቅቁ፣ አስታማሚና ጠያቂ አጥተዉ ዕለተ ሞታቸዉን በሚናፍቁ ምስኪን ህሙማን መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በባዶዉ አስፋልት ላይ ካርቶን አንጥፈዉ በሚተኙ ዝናቡ፣ ቁሩ፣ ዋዕዩ በሚፈራረቅባቸዉ፣ ቆሻሻ ገንዳ ላይ ተንጠላጥለዉ የበሰበሰ ፍራፍሬን ቀለባቸዉ ባደረጉ፣ ችጋር ጠንቶባቸዉ መማሪያ ክፍል ዉስጥ እንዳሉ በረሀብ በሚያሸልቡ የድሃ ድሃ ልጆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በግፈኞች ፍትህ ተንጋዶባቸዉ ባልዋሉበት እንደዋሉ፣ ባልሰሩት እንደሰሩ ተደርገዉ በጨለማ እስር ቤት በተወረወሩ፣ብረት በተቆለፈባቸዉ የህሊና ታሳሪዎችና የህዝብ ጠበቆች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

በእኩይ ባሎቻቸዉ አካላዊም ሆነ ስነ ልቦናዊም ጥቃት በደረሰባቸዉ፣ እጅግ የከበደዉን መከራ መቋቋም ተስኗቸዉ ቀኑ በጨለመባቸዉ እንዲሁም ቢጮሁ ቢጮሁ ሰሚ አጥተዉ ሌት ተቀን በሰቆቃ በሚባዝኑ አንስቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ለዚህች ሀገር የሚችሉትን ሁሉ አበርክተዉ አቅማቸዉ ሲደክም ጉልበታቸዉ ሲከዳ ጧሪ ቀባሪ ጧሪ ቀባሪ በማጣት ቤታቸዉ በፈረሰባቸዉ እንዲሁም ለልመና እጅ በሰጡ አዛዉንት አባቶችና አሮጊት እናቶች መካከል እግዚአብሔር ይገኛል፡፡

ታዲያ እነዚህን አካላት ሲራቡ በማብላት፣ ሲጠሙ በማጠጣት፣ ሲታሰሩ በመጠየቅ፣ ሲታረዙ በማልበስ፣ ሲያዝኑ በማጽናናት ሲታመሙ በመንከባከብ በመርዳት ከጎናቸዉ ሆነን ችግራቸዉን ከተካፈልን ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን ምክንያቱም የእርሱ ቦታዉ እዚህ ነዉና ሁሌም በፍቅሩ ይጎበኘናል እኛ አናየው ይሆናል እንጂ እርሱ ሁሌም በፍቅር ይመለከተናል መሻታችንን ሁሉ ይፈጽምልናል የሚበልጠዉንም ያደርግልናል፡፡


https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
4.6K viewsDrshaye Akele, 18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 09:27:50 ላለመጾም ምክንያት ከመፍጠር ምክንያት ፈጥሮ መጾም በእጅጉ ይጠቅማል፡፡ ደሀው ድኅነት ራሱ ጾም ነው ካለ፤ ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ መኖር ራሱጾም ነው ካለ ለመጾም ክርስቲያን መሆን ሳይሆን ሀገር ወይም ዜግነትመቀየር ሊያስፈልግ ነው ማለት ነው? ምእመናን ‹‹ይህ የሽማግሌዎች ጾም ነው›› ካሉ ስለ ጾም ማስተማርና ጾመው ማሳየት የሚጠበቅባቸው ‹‹ሰባክያን›› ደግሞ ‹‹ቃለ እግዚአብሔር ይመትር ነደ እሳት›› እያሉ ጾምን ሽሮ ለመብላት ጥቅስ ከጠቀሱ ጾምን በጽሑፍ እንጂ በሥራ ላናውቃትነው ማለት ነው፡፡

ሐዋርያት እንደታዘዙት ዓለምን ሁሉ ለማስተማር ከመሰማራታቸው በፊት መጀመሪያ ያደረጉት ጾምን ነው፡፡ ሐዋርያት አልጾሙም ማለት ከላይ የተብራራው የኢየሱስ ክርስቶስ ትንቢትና ምሳሌ ሐሰት ሆነ ማለት ነው፡፡ ሎቱ ስብሐት! ቃሉም ተፈጽሟል ሐዋርያትም ጾመዋል፡፡ እኛም ጾሙን ጾመን የምናስበውና የምንሠራው በጎ ሥራ ሁሉ ይከናወንልን ዘንድፈጣሪ በረድኤት አይለየን!

ይቆየን! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

☞ t.me/An_Apocalypse
3.9K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 09:27:50 በምሳሌው መሠረት በጣፊ ወይም በልብስ ሰፊ የተመሰለው ኢየሱስክርስቶስ ነው፡፡ በአዲስ እራፊ ጨርቅ ምሳሌነት የተወከለው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ በአዲስ ኪዳን እንድንጾመው የሠራልን ጾም ነው፡፡ የተቀደደውና መጣፊያ የሚያስፈልገው ልብስ ደግሞ የሐዋርያት ሕይወት ምሳሌ ነው፡፡
እንደ ምሳሌው ሁሉ ሰዎች የክርስቶስ ልብሶች ይባላሉ፡፡

‹‹አልባሲሁሰ ለክርስቶስ መሃይምናን እሙንቱ›› እንዲል፡፡ ይህም ‹‹የክርስቶስ ልብሶቹ ምእመናን ናቸው፡፡›› ማለት ነው፡፡ክርስቶስም ለሰዎች ልብሳቸው ነው፡፡ሐዋርያው ‹‹እናንተ የተጠመቃችሁ ክርስቶስን ለብሳችኋል›› ብሏልና፡፡(ገላ3.27) ምእመናን የክርስቶስ ልብሶች ናቸው ማለት የክብሩ መገለጫዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ልብስ የክብር መገለጫ ይሆናልና፡፡ እርሱ ደግሞ ለምእመናን ልብስ ነው ማለት ጌጣቸው፣ ነውራቸውንየሚሸፍንላቸውና ክብራቸውም እርሱ ነው ማለት ነው፡፡

ጾም ‹‹እራፊ›› መባሏ ምሥጢር አለው፡፡ ይኸውም እራፊ የተለያየውን እንደሚያቀራርብና አንድ እንደሚያደርግ ጾምም የተለያዩ ፈቃዳት ያሏቸውን ነፍስና ሥጋ አንድ ታደርጋለች፡፡ ከዚህም በላይ ከእግዚአብሔር የተለየውን ሰውም አስታርቃ አንድታደርገዋለች፤ ከመንጋውም እንዲቀላቀል ትረዳዋለች፡፡

‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ማለት አንድ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ እራፊ እንደማይጥፍ ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስም የሐዋርያት ሰውነት በኃጢአት ያረጀ ሆኖ ሳለ በመንፈስ ቅዱስ ሳያድስላቸው አዲስ የሠራውን የአዲስ ኪዳን ጾም ጹሙ ብሎ ሐዋርያትን አያዛቸውም ማለት ነው፡፡

ሰውነታቸው ሲታደስ ያን ጊዜ ግን ይጾማሉ፡፡
ይህ አገላለጥ እግዚአብሔር መንጋዎቹን ያለ አቅማቸው እንዲሸከሙ የማያደርግ አዛኝ ጌታ መሆኑን ያሳያል፡፡
እንዴት ቢባል ሐዋርያትን ሊፈጽሙት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እያሉ እንዲጾሙ አላዘዛቸውምና፡፡ ፈጣሪ ለሕዝቡ መቼ ሕግ መስጠት እንዳለበት በሚገባ ያውቃል፡፡ ለእስራኤላውያን በባርነት ሳሉ ዐሥርቱ ትእዛዛትን ያልሰጣቸው ስለዚህነው፡፡ ቢሰጣቸውም ሊጠብቁት አይችሉም ነበርና፡፡ በባርነት ያለ ሰው የራሱ ነጻነት እስከሌለው ድረስ የፈቀደውን ማድረግአይችልም፡፡

በታላላቅ ተአምራት ከባርነት ካወጣቸው በኋላ ግን ሕጉን ሰጣቸው፡፡ ስለዚህ ከክርስቲያን ወገን ማንም ቢሆን ከአቅሙ በላይ የሆነ ነገርፈጣሪ እንዳዘዘው አያስብ፡፡ የታዘዝነው ሁሉ በዐቅማችን ልክ እንደሆነ እንመን፡፡

③ኛ... ‹‹በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግንአቁማዳው ይፈነዳል: የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡›› ይህ ስለ ጾመ ሐዋርያት የተመሰለው ሦስተኛውና የመጨረሻው ምሳሌ ነው፡፡
በአረጀ አቁማዳ የተመሰለው ሐዋርያት በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ሳይታደሱ በፊት የነበራቸው ሕይወት ሲሆን፤ በአዲስ ወይን የተመሰለው ደግሞ ጌታችን በወንጌል የመሠረተልን ጾም ነው፡፡ የጾም ሕግን የሰጠን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ደግሞ በጠጅ ጣዩ (በጠማቂው) ተመስሎ ቀርቧል፡፡ አዲስ ጠጅ ባረጀ አቁማዳ እንደማይጣል አምላካችንም ባልታደሰ ሕይወታቸው ሐዋርያትን እንዲጾሙ አላዘዛቸውም፡፡

ቀደም ሲል ጾም ሥጋን ለጊዜው ደስ ባለማሰኘቱ በኀዘን እንደሚመሰል ተመልክተን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በዚህ ምሳሌ ጾም ነፍስን ደስ የሚያሰኝ በመሆኑ በወይንተመስሎ አገኘነው፡፡ ‹‹ወይን የሰውን ልብ ደስ ያሰኛል›› እንዲል፡፡ (መዝ103.15) ጠጅ ጣዮች ሲጥሉ (ሲጠምቁ) ተመልክታችሁ ታውቃላችሁ? አስቀድመው ቦታ ያዘጋጁለታል፡፡ እግር እንዳይበዛበትም ጥላ እንዳይወድቅበትም ይጠነቀቃሉ፡፡ እንዳይነፍስበትም ቀን ከሌሊት ይተጉለታል፡፡ በመጨረሻ ሥራው አልቆ ሳለ ጠጁ ከደረቀ (ከጠነከረ) ይላላ ብለውማር ያልሱታል (ይበርዙታል)፡፡ ከላላ ደግሞ ይድረቅ ብለው ጊዜ ይሰጡታል፡፡

በጠጅ ለተመሰለ ለጾምም በዓይነቱ ተመሳሳይ ከጥቅሙ አኳያ ደግሞ የበለጠ ጥንቃቄ ሊደረግለት ያስፈልጋል፡፡ ለጠጅ ቦታ እንደሚዘጋጅለት ለጾምም ሰውነትን ማዘጋጀትና ጊዜና ዕለት ወስኖ መመደብ በአጠቃላይ ጾምን ማወጅ ይገባል፡፡ ስንዱ እመቤት ቤተክርስቲያናችን የአጽዋማት ዐዋጅ ስላላት እኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የዚህ ችግር የለብንም፡፡ ለጠጅ እግር እንዳይበዛበትና ጥላ እንዳይድቅበት እንደሚጠነቀቁለት ጾማችንም በከንቱ ውዳሴ አጋንንት እንዳይገቡበትና ያለ መልካም ሥራ በጾም ብቻ ቀርተን ዋጋው እንዳያንስብን እየተጠነቀቅን መጾም ይገባናል፡፡ ጠጅ ደረቀ ይላላ፤ ላላ ይድረቅ እንደሚባል ጾማችን በሕግ ከተሠራልን በላይ ሠዓቱ እንዳይበዛና ከዓቅማችን በላይ አልፎ ሰውነታችን እንዳይጎዳ፤ እንደዚሁም የአጽዋማትን ሰዓት ሳንጠብቅ ቀርተንም መንፈሳዊ ሕይወታችን እንዳይላላ ማዕከላዊውን ስፍራ ይዘን በሕገ ቤተክርስቲያን መሠረት በጥንቃቄ መጾም እንደሚገባን ይህ ሦስተኛው ምሳሌ ያስረዳናል፡፡

ይህን ትምህርት ጌታችን መድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ የሚቋጨው ‹‹አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› በሚለው ኃይለ ቃል ነው፡፡ ዐረፍተ ነገሩ አዲስ የወይን ጠጅ መጣል ያለበት በአዲስ አቁማዳ መሆኑን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት ሕይወታቸው በጸጋ መንፈስ ቅዱስ ከታደሰ በኋላ በአዲሱ አቁማዳቸው አዲሱን ወይን ጣሉ፡፡ ማለትም በአዲስ ሕይወት የአዲስ ኪዳንን ጾም (ጾመ ሐዋርያትን) መጾም ጀመሩ፡፡

አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቁማዳ ሲጣል ያፈነዳዋል፡፡ በአዲስ አቁማዳ ሲጣል ግን ያለፋዋል እንጂ ሊያፈነዳው አይችልም፡፡ ስለዚህ ወይኑም አቁማዳውም አዲስ የሆኑ እንደሆነ አቁማዳው ወይኑን ያፈላዋል፡፡ ወይኑ ደግሞ አቁማዳውን ያለፋዋል፡፡ በዚህ ጊዜ‹‹ሁለቱም ይጠባበቃሉ›› የሚለው ቃል ይፈጸማል፡፡ ጾምና ሰውነት እንደ ወይንና አቁማዳ ናቸው፡፡ ወይንና አቁማዳ እንደሚጠባበቁ (እንደሚጠቃቀሙ) ጾምና ሰውነትም እንዲሁ ናቸው፡፡ ሰው የጾም ሕግን ቢጠብቅ ሕግም እርሱን ትጠብቀዋለች፡፡ ‹‹ይጠባበቃሉ›› የተባለው ለዚህ ነው፡፡ ይህን የሚያስረዳ ‹‹አኮ ንሕነ ዘነዓቅቦሙ ለሕገጋት አላ እማንቱ ሕገጋት የዓቅቡነ ለዓቂብ ወለተፀውኖ›› የሚል ቃል ይገኛል፡፡ ይህም ‹‹ሕጎችን እኛ አንጠብቃቸውም፡፡ እነርሱ መጠበቅን ይጠብቁናል፤ መጠጊያም ይሆኑናል እንጂ፡፡›› እንደማለት ነው፡፡
ወይኑ ቆዳውን ማልፋቱ መልካም ነገር ነው፡፡ የለፋ ቆዳ ብዙ አገልግሎት ስላለው ይፈለጋልና፡፡ ለቀበቶ፣ ለቦርሳ፣ ለጫማና ለልብስ የሚሆነው የለፋ ቆዳ ነው፡፡ የጾምም ጥቅም እዚህ ላይ ነው፡፡ ለልዩ ልዩ አገልግሎትና ጥቅም የሚውል መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን ከፈለግን በጾም የለፋ (የደከመ) ሰውነት ያስፈልገናል፡፡ ቆዳን ማልፋት ማዘጋጀት እንጂ ከጥቅም ውጭ ማድረግ አይደለም፡፡ ሰውነትን በጾም ማድከምም ለመንፈሳዊ ሥራ ማዘጋጀት እንጂእንዳይሠራ ማድረግ እንዳልሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ የታረሰ መሬት ለዘር እንደሚመች በጾም የደከመ ሰውነትም ለመንፈሳዊጉዞ ይመቻል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ‹‹ጉልበቶቼ በጾም ደከሙ›› ያለው ለዚህ ነው፡፡ (መዝ108.24)

ይህን የመሰለ ምሥጢር ያለውን ጾም ‹‹የሽማግሌዎች ጾም፣ ከጥንት ያልነበረ›› እያሉ በመጽሐፍ እና በቀኖና የሌላ ስም በመስጠት ምእመናን እንዳይጾሙት ማድረግ የዲያብሎስ ትጥቅ የማስፈታት ዘዴ እንጂ ሌላምን ሊሆን ይችላል?
3.1K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 09:27:50 መምህራችን ክቡር ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ (Hibret Yeshitila Hibret) ከዛሬ 10 ዓመት በፊት ያጋሩን ጽሑፍ ነው! በየዓመቱ እንደ አዲስ የሚነበብና ባለብዙኅ ምሥጢር ትምህርት በመሆኑ ተደጋግሞ እንዲነበብ አጋርቻለሁ!
በጎ ጾም መልካም ንባብ ያድርግልን!

✮༒✮ #ጾመ_ሐዋርያት ✮༒✮

(በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ)

በየዓመቱ በዕለተ ሰኑይ ብቻ (ሰኞ ቀን ብቻ) የሚጀምሩ ሦስት አጽዋማት አሉ፡፡ እነርሱም ዓቢይ ጾም፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ሐዋርያት ናቸው፡፡
እነዚህ አጽዋማት ምን ጊዜም ቅበላቸውእሁድ ሲሆን የሚገቡት ደግሞሰኞ ቀን ነው፡፡

በየትኛውም ዓመት ይህን ዕለት አይለቁም፡፡ ስለዚህ የ2004 ጾም ሐዋርያት ግንቦት 27 ሰኞ ዛሬ ተጅምሯል ፡፡ (ጽሑፉ የተለጠፈበትን ዓመት ያመለክታል ለዘንድሮው ሰኔ 1 ዛሬ ሰኞ) ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በየግላችንም ያጋጠሙንን መንፈሳዊና ሥጋዊ ውጊያዎች በማሰብ ድል የምናደርግበትን ኃይል ፈጣሪያችን ይሰጠን ጾሙን ከወትሮው በበለጠ ጥንቃቄ ልንጾመው ይገባናል፡፡

የጾሙን ታላቅነት ተረድተን እንድንጾመው የትመጣውን፣ ትንቢቱን፣ ምሳሌውንና ምሥጢሩን መረዳት አጋዥ ስለሚሆነን አስቀድመን ስለጾሙ እንማር ዘንድ በአጭሩ አቅርቤዋለሁ! የምችለውን ያህል እጽፍ ዘንድብርታቱንና ጥበቡን የሰጠኝ አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ክብር ምስጋና ይድረሰው! አሜን!

ጾመ ሐዋርያት በራሳቸው በሐዋርያት የተጀመረ ጾም እንደመሆኑ መጠን በአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከዛሬ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዓመታት በፊት ጀምሮ ሲጾም የኖረ ጾም ነው፡፡ ለዚህም የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የአዋልድ መጻሕፍትና የታሪክ በርካታ ምስክሮች አሉ ስለዚህ ጾሙን እንደ እንግዳ ነገር መቁጠርና ዘመን አመጣሽ አድርጎ ማየት የራስን አላዋቂነት ያሳያል፡፡ ይህን ማለት ያስፈለገው ጥቂቶች ጾሙን ድሮ ያልነበረና ዘመን አመጣሽአድርገው ስለሚናገሩ ነው፡፡
ጾመ ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ዕድሜያቸው ለጾም የደረሱ ምእመናን በሙሉ እንዲጾሙአቸው ካወጀቻቸው ሰባት የአዋጅ አጽዋማት መካከል አንዱ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጌታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ አንደበት ቀን የተቀጠረለት፣ ትንቢት የተነገረለትና ምሳሌ የተመሰለለት ጾም መሆኑ ከአጽዋማት ሁሉ ለየት ያደርገዋል፡፡

ጌታችን ስለዚህ ጾም ትንቢተ በመናገር፣ ምሳሌ በመመሰል ሰፊትምህርት የሰጠው ፈሪሳውያን ወደ እርሱ ቀርበው ‹‹ደቀ መዛሙርትህ የማይጦሙት ስለ ምንድር ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ነው፡፡ እርሱም ሲመልስ እንዲህ አላቸው፡- ‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን? ነገር ግንሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡ በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡ በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አቁማዳው ይፈነዳል፤ የወይን ጠጁም ይፈሳል፡፡ አቁማዳውም ይጠፋል፡፡ ነገር ግን አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ያኖረዋል ሁለቱም ይጠባበቃሉ፡፡›› (ማቴ9.14-17)

በመቀጠል እስከ መጨረሻ የምንመለከተው ከላይ የሰፈረውን የማቴዎስ ወንጌል አጭር ገጸ ንባብ ሐሳብ በመሆኑ መለስ እያሉ
ታሪኩን ማንበብ ወይም በልብ ከመዘገቡ በኋላ ቀጣዩን ክፍል ማንበብ ምሥጢሩን ለመረዳት ያግዛል፡፡
በዚህ የጌታችን መልስ ውስጥ ‹‹ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጦማሉ፡፡›› የሚል ስለጾመ ሐዋርያት የተነገረ የትንቢት ቃል እናገኛለን፡፡ ይህ አምላካዊ ቃል ጾሙ ስለሚጀመርበት ወራት ቀጠሮ ይሰጣል፡፡ ያም ጊዜ ሙሽራው ከእነርሱ ከተወሰደ በኋላ ያለው ጊዜ ነው፡፡ ‹‹ሙሽራው ከተወሰደ›› በኋላ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ካረገ በኋላ ማለት ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ የሚጀምረው በዚህ ቃል ምክንያት ነው፡፡ ይህም ቤተ ክርስቲያን ምን ያህል መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ያላት መሆኗን ያሳያል፡፡
ጾመ ሐዋርያት ከዕርገት በኋላ ለዐሥር ቀናት ያህል ዘግይቶ እንጂወዲያው አይጀምርም ምክንያቱም የሐዋርያት ሰውነት በአዲስ ሁኔታ ጌታችን ላዘጋጀው የአዲስ ኪዳን ጾም ተመቻችቶ ያልተገኘ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በመጀመሪያ የሐዋርያት ሰውነት ለጾሙ መዘጋጀት ነበረበት፡፡ ከዚያ በኋላ ሐዋርያት መጾም ጀምረዋል ይህም በጌታችንን የመልስ ቃል ውስጥ የተካተተ እንጂ የፈጠራ ድርሰት አይደለም፡፡ ‹‹በአረጀ ልብስ ላይ››እና ‹‹በአረጀ አቁማዳ›› የሚሉት ሁለት ተከታታይ ምሳሌያዊ ማብራሪያዎች ሐዋርያት ሰውነታቸው በመንፈስ ቅዱስ ከመታደሱ በፊት ጾም መጾም እንደማይጀምሩ ወይም እንደሌለባቸው የሚያስረዱ ምሳሌዎች ነበሩ፡፡ ስለዚህ ሐዋርያት የተዘጋጀላቸውን ጾም መጾም የጀመሩት ከኢየሱስክርስቶስ ዕርገት በኋላ በዐሥረኛው ቀን በወረደ ጸጋ መንፈስቅዱስ የሕይወት ሕድሳት አግኝተው ነው፡፡

ከላይ በተጠቀሰው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ውስጥ ስለጾመ ሐዋርያት የቀረቡ ሦስት ዓይነት ምሳሌዎችን እናገኛለን፡፡ ምሳሌዎቹ በምሥጢር የተሞሉ በርካታ መንፈሳዊ መልእክቶችን ያዘሉ ናቸውና ተራ በተራ እንመለከታቸዋለን፡፡

①ኛ...‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› የሚለው ዐረፍተ ነገር በገጸ ንባቡ ውስጥ ስለ ሐዋርያት ጾም የተመሰለው የመጀመሪያው ምሳሌ ነው፡፡ ሚዜዎች የተባሉት እንደ መጥምቁ ዮሐንስ መንገድ የሚጠርጉ፣ የሚያስተምሩና ምእመናንን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚያቀረቡ ሁሉ ናቸው፡፡ ሙሽሪትን ወደ ሙሽራው መውሰድ የሚዜዎች ሥራ መሆኑ በአይሁድና በኢትዮጵያውያን ባህል ሲሠራበት የኖረ ነው፡፡ ስለዚህ ዋነኞቹ ሚዜዎች ሐዋርያት ናቸው ማለት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሽራ ሲሆን ቤተክርስቲያን (ምእመናን) ደግሞመርዓት (ሴት ሙሽራ) ትባላለች፡፡ (2ቆሮ11.2፤ዮሐ3.29)
‹‹ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉን?›› ሲልሚዜዎች ሙሽራውን ለማስደሰት ሲሉ ምንም የሚያሳዝን ነገር ቢያጋጥማቸውም እንኳን ጨክነው በመቻል ያሳልፉታል እንጂ በሙሽራው ፊት እንደማያዝኑ፤ እንደዚሁም መጾም ተገቢ ነገር ቢሆንም ሐዋርያትኢየሱስ ክርስቶስ ከእነርሱ ጋር ሳለ መጾም እንደማይገባቸው ነገር ግን ከእነርሱ ተለይቶ ሲያርግ መጾም እንደሚጀምሩ ያስረዳል፡፡

በዚህ ምሳሌያዊ ንባብ ውስጥ ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ መጾም ተድላነቱ ለነፍስ እንጂ ለሥጋ አይደለምና፡፡ ሥጋ ጾምን እስኪለምድ ድረስ ቅጣት ይሆንበታል፡፡ ስለዚህ በጾም ነፍስ ስትደሰት ሥጋ ግን ያዝናል፡፡ በዚህ ምክንያት ጾም በኀዘን ተመስሏል፡፡ በዚህም ምክንያት ጾም በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ከኀዘን፣ ከዕንባ፣ከጸጸትና ከንስሐ ጋር ተያይዞ ቀርቧል፡፡ (ኢዩ2.12)

②ኛ...‹‹በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚያኖር የለም፤ መጣፊያው ልብሱን ይቦጭቀዋልና፤ መቀደዱም የባሰ ይሆናል፡፡›› ይህ ዐረፍተ ነገር ደግሞ ሁለተኛው ምሳሌ ነው፡፡ እራፊ ማለት ቅዳጅ ወይም መጣፊያ ጨርቅ ማለት ነው፡፡ የስፌት ባለሙያ ባረጀ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ አይጥፍም (አይሰፋም) ወይም አይለጥፍም፡፡ ይህም አንደኛ ግንጥል ጌጥ እንዳይሆን፤ ሁለተኛ ላሮጌ ልብስ ሲባል አዲሱን ማበላሸት እንዳይመጣና አዲሱ ካሮጌው ስለሚበረታ የባሰ እንዳይቦጭቀው በማሰብ ነው፡፡
3.2K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 09:27:41
2.7K views𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Θεόδωρος (תאודור )(تواضروس) Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 16:07:42 ☞ አንተ ግን ፍሬ በሌለው ተክል ፣ ቅጠል በሌለውም ዛፍ ፣ ፈሳሽ በሌለው ወንዝ ፣ ውኃ በሌለው ጉድጓድ ፣ የመንግሥት ዘውድ በሌለው ንጉሥ ፣ የጦር መሣሪያ በሌለው ወታደር ፣ ዝናም በሌለው ደመና ፣ ፍሬ በሌለው እሸት ፣ ለምግብ የሚሆን ሀብት በሌለው አባት ፣ ጡቶች በሌላት እናት ፣ ጣሪያ በሌለው ሕንፃ፡ መዝጊያ በሌለው ደጃፍ፡ አክሊል ባልደፋ ሙሽራ ፣ ጌጥ በሌላት ሙሽሪት፣ ልብሰ ተክህኖ በሌለው ካህን ፣ ቁርባን በሌለው መሠዊያ ፣ የመርከብ ሥርዓት በማያውቅ ዋናተኛ ፣ ገንዘብ በሌለው ገበያተኛ ፣ የብረት ጥሩር በሌለው ባለሠረገላ፣ ጦሮች በሌሉት ፈረሰኛ ትመሰላለህ ! በክርስትና ማኅተም ያልከበርህ ለጵጵስና እንዴት ተመረጥህ? በመታመን ያልተሸለምህ ሆይ እንደ ምን ለክህነት አገልግሎት ተመረጥህ?

Let us look from the beginning at that very tradition, teaching, and faith of the «Orthodox Church» which the Lord gave (εδωκεν), the apostles preached (εκηρυςαν) and the Fathers preserved (εφυλαςαν). Upon this the Church is founded. 【Athanasius of Alexandria (First Letter to Serapion, 28)】

በቃን ማለት አልቻልንበትምና ሥሉስ ቅዱስ ራሱ በቃችሁ ይበለን!

ከቴዎድሮስ በለጠ ☞ ግንቦት ፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ከሀረር መካነ ሥላሴ ካቴድራል
1.1K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 13:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ