Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.52K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-02-05 08:43:28 . በደወል የተጠሩ ደወሎቻችን
᳀᯼͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͟͞ ̸͞͝ ͟͞᳀͟͞ ͟͞ ̸͟͞ ͟͞ ͟͞ ͞ ͟͞ ̸ ͟͞ ͟͞᯼᳀

"ወይደምጽ ድምጸ መጥቅዕ ወኲሉ ዘሰምዓ ይደነግፅ ⇨ ደወል [ረቂቅ ነጋሪት] ይሰማል : የሰማውም ሁሉ ይደነግጣል" 【ዕዝራ ሱቱኤል ፬፥፳፫】

በትናንቱ የቅዱስ ሲኖዶስ አዋጅ ውሥጥ እንዲህ የሚል "ሲኖዲቆን" ተቀምጧል

"በሰባቱ የጸሎት ሰዓታት እየተጠበቀ በተመሳሳይ ሰዓታት ለአምስት ደቂቃ ያህል በማያቋርጥ ደወል በመደወል የማስተጋባት ሥራ እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤"

መደወሉ ከሰይጣን ማሳት እንድናመልጥ ፣ ከጠላት ወጥመድ እንድንወጣ ፣ ከገቢረ ኃጢኣት እንድንለይ ፣ ከድካም ሀኬት እንድንበረታ… እንደ ጴጥሮስ ዶሮ ልብን ለመመለስ የሚደወል ነው። እንደ ቃጭል ወይም መረዋ አነስተኛው ደወል ቃለ ዓዋዲ ተብሎ የመጠራቱ ምክንያት ይህ ነው።

በምሕላና በእግዚኦታ ጊዜ ደወል እንዲደወል ቤተክርስቲያን የምታውጀው በምሳሌነቱ ⇨ ከመስቀሉ አጠገብ ያልተለዩ የክርስቶስን መከራ አይተው ያለቀሱ የእመቤታችንና የቅዱሱን ሐዋርያ ዮሐንስ ወንጌላዊ የልቅሶ ድምፅ በማሰብ ነው። ዛሬም የጌታቸውን መንገድ ለሚከተሉ በእውነተኛ ምስክርነት ሕይወታቸው በግፍ ለሚያልፍ እንደቅጠል ለሚረግፍ ሰማዕታት መታሰቢያ እንዲሆን ይደወላል።

ደወል የራቁትን ያቀርባል የተበተኑትን ይሰበስባል ለዚህም ነው በዓላትና አጽዋማትን ሰብስቦ የሚነግረን የባሕረ ሐሳቡ ማውጫ ጥንተ መጥቅዕ የሚባለው!

የአጽዋማትና በዓላት በየዓመቱ መመላለስ መሪ የሆነ መባጃ ሐመሩንም የዓመቱን መጥቅዕ እና የመጥቅዕን ዕለተ ተውሳክ በመደመር እናገኘዋለን።

ለሐመሩ (ለመርከቡ) እና ለመጥቅዑ (ለደወሉ) መነሻ በኩፋ ፮፥፳፯ የተነገረው የኖኅ መርከብና ደወል ነው።

ኖኅ መርከቡን ከጥፋት ማምለጫ እንዲሆነው ሲያሰናዳ ቁመቱ ሦስት ክንድ፣ ስፋቱ አንድ ክንድ አድርጎ ደወል እንደሠራና በየዕለቱ በነግህ ለጸሎት፣ በቀትር ለምግብ፣ በሰርክ ለማሰናበት ሦስት ጊዜ እየደወለ ይጠቀምበት እንደነበር በመጽሐፈ ቀሌምንጦስ ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ፷፪ ጀምሮ ተዘግቦልናል።

"ኖኅም… ሦስት ክንድ ርዝማኔና አንድ ክንድ ጉድን ያለው ደወል ከሊባኖስ ዕንጨት ሠራ። መርከቡን በሚሠራበት ጊዜ ሁልጊዜ ጧት ጧት ለሥራ እንዲሠበሰቡ ደወል ይደውላል። ቀትር ሲሆን ምሳ ለመብላት እንዲሰበሰቡ ይደውላል ቀኑ አልፎ ምሽት ሲሆን ወደየቤታቸው እንዲገቡ ይደውላል። መርከቡን ለምን እንደሚሠራው ጠያቂ ቢነሳበት እግዚአብሔር የጥፋት ውሃን ይህቺን የረከሰች ምድር ለማጠብ እንደሚያዘንምና። በዚሁም ምክንያት ራሱን ሚስቱን ልጆቹንና ሚስቶቻቸውን ለማዳን መርከብን እንዲሠራ መታዘዙን ይገልፅለታል።"

የደውሉም አገልግሎት እንዲህ እያለ ከኖኅ እስከ ሙሴ ደርሷል። ሙሴም ማኅበሩን መሰብሰቢያ የብር መለከቶችን አዘጋጅቶ እንደነበር መጽሐፍ ይነግረናል
“ሁለት የብር መለከቶች አጠፍጥፈህ ለአንተ አድርግ ማኅበሩን ለመጥራት ከሰፈራቸውም ለማስጓዝ ይሁኑልህ።” 【ዘኁ ፲፥፪】

እኛም ይህን ምሳሌ ይዘን በቤተክርስቲያናችን ለመንፈሳዊ አገልግሎት እንጠቀምበታለን። በተለይ እንደኖኅ ዘመን የሥራ ደወል ከጥፋት ለማምለጥ የምንሠራውን ይህን መርከብ የሆነ ሰውነታችንን ሕንፃ ሥላሴ አካላችንን በንሰሐና በቁርባን እንድናበጃጀው ደወሉ ያለማቋረጥ ሲመታ እንሰማለን።
አገልግሎቱም ሌሊት የተኙትን በመቀስቀስ ለሰዓታትና ለማኅሌት እንዲተጉ ፲፭ ጊዜ ይደወላል፤ በነግህ በ፫ ሠዓት ለዋዜማ ቁመት ፲፪ ጊዜ ይደወላል፤ በሰርክ ለቅዳሴ መግቢያ ፫ ጊዜ ይደወላል፤ በጻዑ ንዑሰ ክርስቲያን ጊዜ ፫ ጊዜ ይደወላል፤ በእግዚኦታ ጊዜ ፯ ጊዜ ይደወላል፤ በድርገት ጊዜ ፭ ጊዜ ይደወላል።

ምሳሌውም የቀርነ መለከት ሲሆን ፲፭ ጊዜ መደወሉ የ፲፭ቱ ነቢያት ምሳሌ ነው፤ ፲፪ ጊዜ መደወሉ የ፲፪ቱ ሐዋርያት ምሳሌ ነው፤ ሌሊት መደወሉ ነቢያት በዘመነ ጽልመት መኖራቸው ምሳሌ ነው፤ በሰርክ መደወሉ ብርሃን የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመገለጹ ምሳሌ ነው።

በሥርዓተ ቅዳሴው ላይ ብቻ ለ፭ ምክንያቶች ሲደወል እንሰማለን፤ ምሳሌውን ከነምክንያቱ እንመልከት

፩】. የተጋብኦ ደወል
✦━━━━━━━
ካህናትና ምእመናን ለልዩ ልዩ አገልግሎት ወደ ቤተክርስቲያን እንዲሰበሰቡ የሚጠራ የቤተ ክርስቲያን በሮች ከመከፈታቸው በፊት የሚደወል ነው።

ምሳሌነቱ፦
የትንቢተ ነቢያት ነው:: ደውሉ ካህናትና ምእመናንን ቀስቅሶ ለአገልግሎት /ለጸሎት/ እንደሚዘጋጅ፤ ነቢያትም የሕዝቡን ልብ እየቀሰቀሱ፤ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሱ፤ ለአዲስ ኪዳን አገልግሎት እንዲዘጋጁ ያደርጉ እንደነበር ያሳያል።

፪】.የቅዳሴ መግቢያ ደወል
✦━━━━━━━━━━
ይህ ደወል ካህናት መሥዋዕቱን አክብረው ከቤተልሔም ወደ መቅደስ ሲጓዙ የሚደወል ነው፡፡

ምሳሌነቱ፦
የብሥራተ ገብርኤል ነው፤ አንድም ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ እነሆ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ (ዮሐ ፩፥፪፱፡፡) በማለት የጮኸው /የተናገረው/ ድምፅ ነው።

፫】. የወንጌል ደወል
✦━━━━━━━
ይህ ደወል “ፃኡ” በሚባልበት የቅዳሴ ክፍል መካከል የሚደወል ነው።

ምሳሌነቱ፦
የስብከተ ዮሐንስ፣ የሐዋርያትና የሰብአ አርድዕት ልቅሶ ነው። (ሉቃ፫፥፫‐፯፡፡) ይህ ደወል ከተደወለ በኋላ ያለው የቅዳሴ ክፍል ፍሬ ቅዳሴ ይባላል:: ይህም መሥዋዕተ ወንጌል የሆነው የክርስቶስ ሥጋውና ደሙ የሚቀርብበት ነው:: ደወሉ ሐዋርያትና አርድእት ቅዱሳት አንስትም ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ ያዘኑትን ሐዘን፥ ያለቅሱትንም ለቅሶ፣ ያፈሰሱትንም ዕንባ የሚያስታውስ ነው።

፬】.የእግዚኦታ ደወል
✦━━━━━━━
በቅዳሴ ጊዜ መጨረሻ አካባቢ ካህናትና ምእመናን በቅብብሎሽ /በማስተዘዘል /፵፩፥ ፵፩/ ጊዜ እግዚኦታ ያደርሳሉ:: በዚህን ጊዜ ከላይ የገለጽነው ደወል ይደወላል::

ምሳሌነቱ፦
ከመስቀሉ አጠገብ ያልተለዩ የክርስቶስን መከራ አይተው ያለቀሱ የእመቤታችንና የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ የልቅሶ ድምፅ ነው:: /ዮሐ ፲፱፥፳፭‐፳፰፡፡/

፭】.የድርገት ደወል
✦━━━━━━━
ሥጋ ወደሙ ለቆራብያን ሊሰጥ (ሊታደል) ልዑካኑ ከመቅደስ ወደ ቅድስት ሲወጡ የሚደወል ነው።

ምሳሌነቱ፦
ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በገነዙት ጊዜ ያለቀሱት ልቅሶ ነው:: አንድም የሐዋርያትና የሰብአ አርድእት ትምህርት ነው:: ዮሴፍና ኒቆዲሞስ የጌታችንን ሥጋ በገነዙበት ጊዜ እያለቅሱ ነፍስ የተለየውን፣ መለኮት የተዋሐደውን የጌታችንን ሥጋ ገንዘው ባዲስ መቃብር “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር…” ብለው እንዳኖሩት፤ ካህናትም በቅዳሴ ጊዜ ነፍስ የተለየውን መለኮት ያልተለየውን (የተዋሐደውን) የክርስቶስን ሥጋና ደም እንዲያቀብሉ ደወል ይደወላል:: ሐዋርያትና ሰብአ አርድእት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀብለው ወንጌልን በመላው ዓለም አስተምረዋል፤ ሰብከዋል። ዞረው ማስተማራቸውንና በስብከታቸው የሰው ልጆች ሁሉ ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገራቸውን ለማሰብና ምእምናንም ዛሬ በደወሉ ድምፅ የዘለዓለም ሕይወት ወደሚያገኙበት፥ የክርስቶስ ሥጋና ደም እንደሚቀርቡ ለማመልከት ነው::

ደወሉ ትናንት ሁከት በነገሡባቸው ቦታዎች ምእመናንን ለክብር ወደ ምድራዊቷ ቤተመቅደስ ብቻ ሳይሆን ወደሰማይ ማደርያ ወደ ዘልዓለማዊው መኖርያ ጠርቷል። ጉባኤ ጳጳሳቱም "ተገቢውን ሲኖዶሳዊ እና ሃይማኖታዊ ጸሎት በማድረግ በሁሉም አጥቢያ ሥርዓተ ፍትሐት እንዲፈጸምላቸው" ትዕዛዝ አስተላልፏል።
3.9K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 08:43:25
3.6K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 21:24:33 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ
ጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
4.3K viewsDrshaye Akele, 18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 21:24:33 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ከኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ አዋጅ
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረው አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ በኢትዮጵያ የኦሮሚያ እና የብሔር ብሔረሰቦች ቅዱስ ሲኖዶስ በሚል በሕገ ወጥነት በቀድሞ ስማቸው አባ ሳዊሮስ የተባሉ ግለሰብ መሪነት ይህ መግለጫ እስከተሰጠበት ቀን ድረስ በተለያዩ ክልሎች እና የፌዴራል መንግሥት በሚመራቸው ቦታዎች ውስጥ በሚገኙ የቤተ ክርስቲያኗ አህጉረ ስብከት የሆኑትን ሥርዓተ አምልኮዋን የምትፈጽምባቸው በየመዋቅሩ የሚገኙ አስተዳደር ቢሮዎችን ከሕግ አግባብ ውጭ የቤተ ክርስቲያኗ እምነት ተከታይ ያልሆኑ ግለሰቦችን በማካተት በመንግሥት ልዩ ኃይል ድጋፍ በመውረር እና በመስበር የሕግ አግባብነት በሌላቸው እንዲሁም መብት እና ጥቅም ሳይኖራቸው በማሸግ ቤተ ክርስቲያን ላይ ወረራ እየተፈጸመባት የሚገኝ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ለመረዳት ችሏል፡፡
መንግሥትም ሰላም እና ደህንነትን ከማስጠበቅ ባለፈ የሕይወት እና የአካል ደህንነት መብትን እንዲሁም የመንቀሳቀስ መብትን በመገደብ ያለአግባብ ታግተው መቆየታቸውን ከሊቃነ ጳጳሳት ውስጥ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስን ከዚህ ቀደም መግለጻችን የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ድርጊታቸውም ሳይታቀቡ በጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 3፡30 አካባቢ የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑትን ብጹዕ አቡነ ያሬድን በሕገ ወጥ መልኩ የዜግነት መብታቸው ተጥሶ በደረቅ ሌሊት በማሰር እና በማዋከብ ከሀገረ ስብከታቸው ለቀው እንዲወጡ የተደረጉ ሲሆን እንዲሁም የተለያዩ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትን ወደየ አህጉረ ስብከታቸው እንዳይሄዱ ማስፈራሪያ በመላክ የቤተ ክርስቲያችንን ክብር እና ልዕልና እጅጉን የሚጎዳ እና አሳዛኝ ድርጊት እየተፈጸመባት ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የየሀገረ ስብከት ሥራ አኪያጆችንና ሠራተኞችን፤ አገልጋይ ካህናትንና ምእመናን በሕገ ወጥ መልኩ በማሰር እንደ መንግሥት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ባለመወጣቱ ቤተ ክርስቲያናችን እጅጉን አዝናለች፡፡
ከዚህም አልፎ መንግሥትም በቤተ ክርስቲያችን በኩል በተደጋጋሚ የተሰጠውን ማሳሰቢያ ችላ በማለቱ ምክንያት በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ከተማ ሕገ ወጦቹ መንግሥትን ተገን በማድረግ የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሕገ ወጥ መልኩ ወረራ ለመፈጸም ባደረጉት እንቅስቃሴ ቤተ ክርስቲያንችንን ለመጠበቅ በወጡ ምእመናን ላይ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የአደባባይ የግድያ ወንጀል ተፈጽሟል፡፡ ሌሎች በቁጥር ያልታወቁ ምእመናንም ላይ ከፍተኛ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ይህንንም ሕገ ወጥ ተግባር በተመለከተ ተገቢውን ሕጋዊ የሰላም እና የደህንነት ከለላ እንዲያደርጉ ለሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግሥታት በተደጋጋሚ ማሳሰቢያ ቤተ ክርስቲያናችን ብትሰጥም ይህንን ማሳሰቢያ ወደጎን በመተው መንግሥት ሕገ ወጡን ቡድን በመደገፍ እና በማስፈጸም ከላይ የተገለጹትን አሳዛኝ ድርጊቶች በይፋ በአደባባይ ፈጽሟል፡፡
ስለሆነም የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጠራው አስቸኳይ ጉባዔ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል፡፡
1. በብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት እና የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፤ የክፍል ኃላፊዎች፤ ካህናት፤ አገልጋዮች እና ምእመናን ላይ የተፈጸመውንና እና እየተፈጸመ ያለውን ሕገ ወጥ እስር እና ወከባ ቅዱስ ሲኖዶስ በፅኑ አውግዟል፤
2. በጥር 27 ቀን 2015 ዓ.ም በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በሻሸመኔ ከተማ በደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን፤ ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ የወጡት ምዕመናን ላይ ጭካኔ በተሞላ ሁኔታ የተፈጸመው ሕገ ወጥ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የተፈጸመው አሰቃቂ የሞት ድርጊትን ፍጹም ታወግዛለች፤ ተገቢውን ሲኖዶሳዊ እና ሃይማኖታዊ ጸሎት በማድረግ በሁሉም አጥቢያ ሥርዓተ ፍትሐት እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
3. ቅዱስ ሲኖዶስ በጥር 26 ቀን 2015 ዓ.ም ባስተላለፈው ውሳኔ እና በሰጠው መግለጫ መላው የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታዮች ጾመ ነነዌን ሙሉ የሱባዔ ጊዜ በማድረግ ጥቁር ልብስ ያለውን ትርጓሜ በመግለጥ እንድንሰነብት መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
3.1. ለዚህም ዝርዝር አፈጻጸም መመሪያ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ከጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 3 ቀናት በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የምትገኙ ማናቸውም ካህናት እና ምዕመናን ሙሉ ጥቁር ልብስ በመልበስ በየአብያተ ክርስቲያናት እና በገዳማት ያለውን ሥርዓተ ጸሎት እንድትመሩ እና እንድትከታተሉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
3.2. በየትኛውም እንቅስቃሴ ይህንን ጥቁር ልብስ በመልበስ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ንቁ በመሆን እንድትፈጽሙ፤ ሆኖም ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ይህንን ዓለም አቀፍ የጸሎትና የምህላ መርሐ ግብር ካወጀበት ቀን በኃላ በተለያዩ ከተሞች የጥቁር ልብስን ሆነ ተብሎ ከገበያ እንዲወጣ እየተደረገ መሆኑን በመረዳታችን ምዕመናን ያላችሁን ተመሳሳይ አልባሳት በመጠቀም የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን በእንቅስቃሴያችሁ ሁሉ እንድትፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
3.3. በነዚህ ቀናት ውስጥ አገልግሎቱ በድምጽ ማጉያ እንዲከናወን እና የሙሉ ጊዜ ሆኖ በሰባቱ የጸሎት ሰዓታት እየተጠበቀ በተመሳሳይ ሰዓታት ለአምስት ደቂቃ ያህል በማያቋርጥ ደወል በመደወል የማስተጋባት ሥራ እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤
3.4. ይህንንም የየአህጉረ ስብከት፤ የወረዳ ቤተ ክህነት እና የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሰበካ ጉባኤያት በመከታተል እንድታስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
3.5. የአኃት አብያተ ክርስቲያናት፤ የኦርቶዶክስ ዓለም፤ እውነቱን የምታውቁና የምትደግፉ ማናቸውም ኃይማኖታዊም ሆነ ማህበራዊ ተቋማት እና ግለሰቦች የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ጥሪ በመደገፍ በአንድነት ትቆሙ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላፋለን፡፡
4. በነዚህ የጸሎትና የምሕላ ጊዜያት የደነደኑ ልቦች ወደ ልቦናቸው ተመልሰው የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥሪ ሰምተው የማይፈጽሙ እንደሆነ
4.1. በየካቲት 5 ቀን 2015 ዓ.ም በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካህናት እና ምእመናን ከጠዋቱ 11፡00 ጀምሮ በየአጥብያቸው በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እስከ ጠዋቱ 1፡30 ድረስ ሥርዓተ ቅዳሴው ከተፈጸመ በኃላ ከጠዋቱ 2፡00 ላይ ሁሉም ገዳማት፣ አድባራት እና አብያተ ክርስቲያናት በተመሳሳይ ሰዓት ደወል በመደወል ምእመናን በሙሉ እስከ ጠዋቱ 2፡30 ድረስ እንዲሰባሰቡ በማድረግ ከየአጥቢያው በመነሳት የጥምቀተ ባህር ወይም የመስቀል አደባባይ ላይ ታቦተ ሕጉን በማክበር፤ በማጀብ በዝማሬ እና በምህላ በአንድ ቦታ በመሰባሰብ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡
4.2. የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ዝርዝር አፈጻጸም መመሪያን በተመለከተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የምናሳውቃችሁ መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡
5. ማንኛውም የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ቤተ ክርስቲያን ያዘዘችውን ሰላማዊ ጥያቄ በሚከወንበት ማንኛውም የአገልግሎት ጊዜ ተግባራቱ ሰላማዊ መሆናቸውን በመገንዘብ ተገቢውን ጥበቃ የማድረግ ግዴታ እንዳለበት አውቆ እንዲያስፈጽም ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳስባል፤
4.2K viewsDrshaye Akele, 18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 21:24:22
3.7K viewsDrshaye Akele, 18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 11:37:44
1.9K views08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-04 11:33:47 በሻሸመኔ ቤተክርስቲያን የድረሱልኝ ደውል አሰምታለች እስካሁን በኦሮምያ ፖሊስ አንድ ወጣት ህይወት ጠፍቷል::

በሌላ በኩል ደሞ

"ቤተክርስቲያን ግቢ ተዘግቶ ፀሎት እያደረግን ነው:: መከላከያ ወደእካባቢው እየገባ ነው:: በዚህ ሰአት ተኩስ ድምፅ አይሰማም:: ህዝቡ እያለቀሰ ፀሎት እያደረገ ነው:::" ከሻሸመኔ ዘሐበሻ ያነጋገራቸው ምዕመናን::
2.1K views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 14:57:35 የቅዱስ ሲኖዶስ መልእክት

በሙሽራው በክርስቶስ የደረሰውን መከራ ዐይታ ፀሐይ ለ፫ ሠዓት በምድር ላይ እንደጨለመች የሙሽሪቷን የቤተክርስቲያንን መከራ ያዩ ምእመናን በምድራቸው ላይ ለሦስት ቀን ይጨልማሉ!

【https://www.youtube.com/live/hv_59sOTrmg?feature=share】

"ሰብአ ነነዌ ጸዊሞሙ ተማኅሊሎሙ ድኅኑ እሞቶሙ…
አድኅነነ እግዚኦ አምላክነ ዘአድኃንካ ለነነዌ ሀገር በትንብልና ሣህልከ"

ጾመ ነነዌንና በወቅቱ የደረሰብንን ታላቅ መከራ ምክንያት በማድረግ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ለ፫ ቀናት ( ፳፻፲፭ ዓ.ም.) በዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያን ምእመናን ሁሉ ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ ጾም ጸሎትና ምኅላ በመያዝ በዐውደ ምሕረት ተገኝተን ሁሉን ማድረግ ወደሚችል አምላክ ወደ እግዚአብሔር እንድናለቅስ ጥሪ ተላልፏል።

☞ ጥቁር የመከራ ምልክት ነው !
መከራ የወደቀባቸው ሰዎች ሐዘን ደርሶብናል ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም በደረሰብን መከራ በማዘናችን አምላካችን ከልባችን ሐዘን አርቆ ከፊታችንሸእንባ አድርቆ ወደእኛ የምሕረት ፊቱን እንዲመልስልን በንሰሐ ወደእርሱ ጥቁር ለብሰን እንማጸናለን።

☞ ጥቁር የእውቀት ምልክት ነው !
ከእውቀት ማዕድ የተሳተፉ ምሩቃን ‘አዋቆች’ ነን ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም የእውቀት ባለቤት እግዚአብሔርን የምንከተል መንፈሳውያን ሁላችን ሁሉን የምንመረምር በማንም የማንመረመር ነን ስንል ጥቁር ለብሰን የክርስትናውን ክብር እንገልጣለን።

☞ ጥቁር የእውነት ምልክት !
ዳኞች ፍትሕ አድራጊዎች ነን በእውነት እንፈርዳለን ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም በምድራውያኑ ዳኞች ሚዛን ሲዛባ ፍርድ ሲጎድል ደካማው ሲበደል እኛን ግን የሚመራን እውነተኛው ዳኛ እንዳለ በማመን እግዚአብሔር በሚመራን የእውነት መንገድ የምንኖር እውነተኞች ነን ስንል ጥቁር ለብሰን የእውነት ምስክሮች ለመሆን የምንተጋ መሆናችንን እናሳያለን።

"Those are called the likes of angels who, clothed in the black pallium, have cast away the world and all worldly things, live in celibacy and seek to be like Christ."【Blessed Jerome of Stridon】

↳ እነዚያ ጥቁር ሞጣሕት ለብሰው ዓለምንና በዓለም ያለውን ሁሉ ንቀው የጣሉ ክርስቶስን ለመምሰል የሚጋደሉ በመላእክት ሕይወት የተገለጡ ምድራውያን መላእክት ናቸው ! 【የተመሰገነ ይሩማሲስ】

የገዳማውያን ኅብረት በላኩልን መልእክት ደግሞ ይህ ሁሉ የመጣው በእኛው ጾም ጸሎትና ቅድስናን ችላ በማለታችን ስለሆነ እስከ ዓርብ (ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፫) ድረስ
በየዕለቱ ፵፩ ስግደት እንድንሰግድ
እስከ ፱ ሠዓት እንድንጾም
ዓርብን በአክፍሎት እንድናሳልፍ
ጠዋት ለኪዳን ቀን ለቅዳሴ ሠርክ ለምሕላ ቤተክርስቲያን እንድንገኝ
በ3:00 ፣በ6:00 ፣ በ9:00 ባለንበት ፩ ሰላም ለኪ እና አቡነ ዘበሰማያት በማድረስ አምላካችንን እንድንማጸነው ጥሪ ተላልፏል።

"ድንግል ሆይ ከዓይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት ወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ" 【ቅዳሴ ማርያም】
2.0K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 14:56:28
የቅዱስ ሲኖዶስ መልእክት

በሙሽራው በክርስቶስ የደረሰውን መከራ ዐይታ ፀሐይ ለ፫ ሠዓት በምድር ላይ እንደጨለመች የሙሽሪቷን የቤተክርስቲያንን መከራ ያዩ ምእመናን በምድራቸው ላይ ለሦስት ቀን ይጨልማሉ!

"ሰብአ ነነዌ ጸዊሞሙ ተማኅሊሎሙ ድኅኑ እሞቶሙ…
አድኅነነ እግዚኦ አምላክነ ዘአድኃንካ ለነነዌ ሀገር በትንብልና ሣህልከ"

ጾመ ነነዌንና በወቅቱ የደረሰብንን ታላቅ መከራ ምክንያት በማድረግ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ለ፫ ቀናት ( ፳፻፲፭ ዓ.ም.) በዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያን ምእመናን ሁሉ ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ ጾም ጸሎትና ምኅላ በመያዝ በዐውደ ምሕረት ተገኝተን ሁሉን ማድረግ ወደሚችል አምላክ ወደ እግዚአብሔር እንድናለቅስ ጥሪ ተላልፏል።

☞ ጥቁር የመከራ ምልክት ነው !
መከራ የወደቀባቸው ሰዎች ሐዘን ደርሶብናል ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም በደረሰብን መከራ በማዘናችን አምላካችን ከልባችን ሐዘን አርቆ ከፊታችንሸእንባ አድርቆ ወደእኛ የምሕረት ፊቱን እንዲመልስልን በንሰሐ ወደእርሱ ጥቁር ለብሰን እንማጸናለን።

☞ ጥቁር የእውቀት ምልክት ነው !
ከእውቀት ማዕድ የተሳተፉ ምሩቃን ‘አዋቆች’ ነን ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም የእውቀት ባለቤት እግዚአብሔርን የምንከተል መንፈሳውያን ሁላችን ሁሉን የምንመረምር በማንም የማንመረመር ነን ስንል ጥቁር ለብሰን የክርስትናውን ክብር እንገልጣለን።

☞ ጥቁር የእውነት ምልክት !
ዳኞች ፍትሕ አድራጊዎች ነን በእውነት እንፈርዳለን ሲሉ ጥቁር ይለብሳሉ።

እኛም በምድራውያኑ ዳኞች ሚዛን ሲዛባ ፍርድ ሲጎድል ደካማው ሲበደል እኛን ግን የሚመራን እውነተኛው ዳኛ እንዳለ በማመን እግዚአብሔር በሚመራን የእውነት መንገድ የምንኖር እውነተኞች ነን ስንል ጥቁር ለብሰን የእውነት ምስክሮች ለመሆን የምንተጋ መሆናችንን እናሳያለን።
1.7K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), edited  11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-03 12:57:32 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን! ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የጾምና የምሕላ አዋጅ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

"የነነዌም ሰዎች እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ!
ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።"
ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ 3 ቁጥር 5

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በተከሰተው ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮቿን በመጣስ መፈንቅለ ሲኖዶስ በማድረግ በሕገወጥ መንገድ ኤጲስ ቆጶስነት ሢመት በሰጡትና በተሾመ ግለሰቦች ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥር 18 ቀን 2015ዓ.ም. ቃለ ውግዘት ማስተላለፉ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ እነዚህ ሕገወጥ ቡድኖች ከድርጊታቸው ሊታቀቡ ካለመቻላቸውም በላይ በመንግሥት ኃይሎች በመታገዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምታስተዳድራቸውን መንበረ ጵጵስናዎችንና ቢሮዎችን በኃይል በመውረርና በመስበር ከፍተኛ ጥፋት እያደረጉ ከመሆኑም በላይ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችን ሠራተኞች ካህናትና ምእመናን በማሰርና በማንገላታት ላይ ይገኛል፡፡ መንግሥትም ሕግ ከማስከበር ይልቅ ለሕገ ወጥ ቡድኖች ድጋፍ በመስጠት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና መብት ሊያስከብር ስላልቻለ ሁሉን ማድረግ ወደሚቻለው አምላካችን በመማፀን ጸሎትና ምሕላ ማድረጉ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተረድቷል።

በመሆነም ጾመ ነነዌን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም የሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን ጥቁር ልብስ ብቻ በመልበስ በጾምና በጸሎት ምሕላ በመያዝ በቤተ ክርስቲያን ዓውደ ምሕረት በመገኘት ወደ እግዚአብሔር ጾም፤ ጸሎትና ምሕላ እንድታቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

ጥቁር ልብስ የምንለብሰው በመከራ መጽናት ለመግለጽ ነው፡፡
እንደሚታወቀው ጥቁር የእውቀት ምልክት ነው ተማሪዎች አውቀናል ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛ ከእውቀት በላይ የሆነውን አምላካችንን በመማፀን ከዚህም ማንም ሊያናውጽን እንደማይችል የምናረጋግጥበት፤ ጥቁር የእውነት ምልከት ነው ዳኞች እውነት እንፈርዳለን ሲሉ ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ፡፡ እኛም መከራው የሚያሰቅቀን ሳይሆን ይበልጥ ልንጸናና ልንበረታ የሚገባ መሆኑን ለዓለም ሕዝብ የምናሳይበት በመሆኑ ከጥር 29 እስከ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ለሦስት ቀናት በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነን ወደ ፈጣሪያችንን እንድንጮህ አደራ እንላለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ጥር 26 ቀን 2015ዓ.ም. አዲስ አበባ
2.0K viewsDrshaye Akele, 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ