የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
6.70K
የሰርጥ መግለጫ
የእግዚአብሄርን ፍቅር፣ ምህረትና ይቅርታ በተገለጠው የወንጌሉ ቃል መሰረት የምንማማርበት ቻናል ነው። ትምህርቶቹን በሚያመቻችሁ የሶሻል ሚድያ በኩል ለመጠቀም ከስር ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ።
Telegram ፦ @adonigospel
WhatsApp ፦ https://chat.whatsapp.com/BnTcBA0mML6E7gakQUIJ8X
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
3
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-09-01 05:55:12
ደህና አደራችሁ?
ደመና ባይኖር፣ ሰረገላ ባይኖር፣ መንኮራኩር ባይኖር .....መሳፈሪያም መጓጓዣም ሁሉ አንዳች ባይኖር በሁሉም ቦታ ፈጥኖ የሚደርስ አንድ አምላክ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ወደ ህይወታችሁ ሲመጣ አይዘገይም የሚቀድመውም የለም።
ለእግዚአብሔር ክረምት ገባ ወንዙን እንዴት ተሻግሮት ይመጣል አይባልም ወንዙን አስፓልት አድርጎ ጠቅጥቆት ይመጣል። መከራዬ በረታ እንዳይፈታው የቋጠሮው ውል ጠፍቷል አይባልም በእርሱ ፊት ትልቅ ችግር ትልቅ ፈተና የለም። ችግሬ እንኳን በሰው በአምላኬም አይፈታም አይባልም የኛ ችግር ሁሉ ከእግሩ በታች ነው። እግዚአብሔር ትልቅ ነው።
የትኛውም ቦታ መድረስ የሚችል የእግዚአብሔር እጅ ብቻ ነው። ከሲዖል የጠለቀ የለም እዛም ውስጥ ገብቶ የሚያወጣን ታዳጊ እጅ የእግዚአብሔር ነው። እጁ ያስጨነቀንን የሚያሳድድ፣ ሞትን የሚገድብ፣ ህይወትን የሚያቀርብ ረድዔታችን ነው። የደስታ ቀን ይሁንላችሁ።
አዶኒ
ነሐሴ 26/2014 ዓ.ም
@adonigospel
@adonigospel
579 views@doni, edited 02:55
2022-08-31 12:27:07
@adonigospel
@adonigospel
755 views@doni, 09:27
2022-08-31 08:48:16
በደስታ ዋሉ
አዶኒ
@adonigospel
@adonigospel
764 views@doni, edited 05:48
2022-08-31 05:38:18
አይዟችሁ!
" ሙሴም በባሕሩ ላይ እጁን ዘረጋ፣ እግዚአብሔርም ሌሊቱን ሁሉ ጽኑ የምስራቅ ነፋስ አምጥቶ ባሕሩን አስወገደው:: ባሕሩንም አደረቀው፣ ውኃውም ተከፈለ፤ የእሥራኤልም ልጆች በባሕሩ መካከል በየብስ ገቡ፣ ውኃውም በቀኛቸውና በግራቸው እንደ ግድግዳ ሆነላቸው…ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ የግብጻውያንን ሠራዊት ተመለከተ…አወከ…አሠረ…ወደ ጭንቅም አስገባቸው፣ ግብጻውያንም እግዚአብሔር በግብጻውያን ላይ ይዋጋላቸዋልና ከእሥራኤል ፊት እንሽሽ አሉ” (ዘጸ 14፣21-25)
እግዚአብሔር አሰራሩ ብዙና ልዩ ልዩ ነው ከሰው አዕምሮም በላይ ነው። በዚህ ስትጠብቁት በዚያ ይመጣል። በዚህ ክፍል ላይ እግዚአብሔር አደግድጎ የሚሰራው ፀሐይ ደምቃ በወጣች ሰዓት ሳይሆን ጨለማው የሚዳሰስ በሆነበት ጊዜ ነው።
ሌሊት እንቅስቃሴ ሁሉ የሚቆምበት፣ ብዙ ነገሮች ዝግ የሚሆኑበት ነው። ለእስራኤል በሌሊት የሚታያቸው የሚከተላቸው የፈርዖን ጦርና ወታደር ነው። ጠላት ቢገሰግስ ቢመጣ እግዚአብሔር ሳይቸኩልና ሳይጣደፍ ስራውን ይሰራ ነበር። ለእስራኤል ጨለማ ቢሆንም ለእግዚአብሔር ግን የስራ ሰዔት ነበር።
ለሊቱን ሁሉ ይላል፦ አዎ ለሊት ሁሉ ሲተኛ፣ ድምፅ ሁሉ ሲጠፋ፣ የኛ ነገር ያበቃ ያከተመ በሚመስልበት ሰዓት፣ ተስፋ ያደረግነው ነገር የሞተ በሚመስልበት፣ ምንም የሚታይ ነገር በጠፋበት ወቅት፣ ብንጠራው የሚደርስልን ብንሸሽ የሚከፍትልን ወዳጅ በሌለ ሰዓት እግዚአብሔር ለእኛ እየሰራልን ነው። የእግዚአብሔር የስራ ውጤት ብልሽት የለውም ውብ ያደርገዋል።
እንደ እስራኤል ሄዳችሁ ብዙ ተጉዛችሁ አላሳልፍ ባለ ችግር ቆማችሁ ይሆናል፤ ብዙ ነገር ጨልሞባችሁ ይሆናል፤ ከፊትም ከኋላም ሞት እየሸተታችሁ፣ በሁሉ ነገር አበቃ ብላችሁ ደምድማችሁ ይሆናል። ነገር ግን የሚወዳችሁ እግዚአብሔር እንዳይረዳችሁ ችግራችሁ አይከለክለውም፣ ጨለማችሁ አያግደውም ያስጨነቃችሁን ያስጨንቀዋል፣ ባህሩን ያደርቀዋል፣ ውሀውን እንደ ግንብ ያቆመዋል፣ ያሳደዳችሁን ጠላት በደመናና በእሳት አምድ ይመክተዋል። ያን ጊዜ በደስታ ትሻገራላችሁ። ለሊት ብቻ ሆኖ አይቀርምና ተሻግራችሁ በንጋት እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም ብላችሁ ትቀኛላችኩ። አይዟችሁ እግዚአብሔር ድንቅን ሊያደርግላችሁ በስራ ላይ ነው።
አዶኒ
በድጋሚ የተለጠፈ August 25/2019 የተፃፈ
Join @adonigospel
@adonigospel
801 views@doni, 02:38
2022-08-30 17:35:27
የህብረት ዝማሬ
@adonigospel
829 views@doni, edited 14:35
2022-08-30 05:47:56
ያልፋል
የዛሬው መራብህ ያልፋል፤ የዛሬው መቸገርህ ያልፋል፤ የዛሬ ለቅሶህ ያልፋል፤የዛሬው ተስፋ የመቁረጥ ስሜትህ ያልፋል፤ የዛሬ መድከምህ ዝለህ መሰልቸትህ ያልፋል፤ ጤናህ ተናግቶ መሰቃየትህ ያልፋል፤ በወዳጅ መከዳትህ ያልፋል፤ ጓደኛ ማጣት ያልፋል፤ ግራ ያጋባህ የሀገርህ ሁኔታ ያልፋል፤ ታስረህም ቢሆን ይሄም ያልፋል።
ይሄም ያልፋል
ዛሬ ሞልቶህ ቢሆን መልካም ነው ግን ያልፋል፤ የጣመ እየበላህ ያማረ እየጎረስክ ይሆናል ይህም መልካም ነው ግን ያልፋል፤ ካዝና ሙሉ ሀብት ቢተረፈረፍልህ ሳትቸገር የፈለከውን ታደርግ ይሆናል ይህም ግን ያልፋል።
ወዳጆቼ በዚህ ዓለም ላይ አለኝ ብላችሁ የሚያኮራ አንድም ነገር የለም፤ አጣሁም ብላችሁ ሕይወትን ከንቱ የሚያደርግባችሁም ምንም ነገር የለም። ማጣትም ማግኘትም ያልፋል አሳላፊው እግዚአብሔር በዙፋኑ ስላለ ያልፋል። አንተ ቤት ገንብተህ እፎይ ብለህ፣ ህንፃ አቁመህ እፎይ ብለህ ይሆናል። ህንፃውም ምድሪቱም በታላቅ ትኩሳት እንደወረቀት ተጠቅልለው ያልፋሉ። የማያልፈው ልዑል አምላክህ እግዚአብሔር ነው። ከሞትም በኃላ ላለው ሕይወትህ ሊያልፍህ የማይገባው ይህ ጌታ ብቻ ነው።
እዚህ ምድር ላይ ላያልፍ የመጣ ምንም ነገር የለም!
እግዚአብሔር ከፊታችሁ እንደ ጋሬጣ የተገተረባችሁን ነገር ሁሉ ያሳልፍላችሁ። ቤታችሁ የገባ ሀዘን ቢኖር ይለፍላችሁ። በመለኮታዊ ክንዱ ይለፍ የምትሉትን ነገር ሁሉ ያሳልፍላችሁ።
አዶኒ
በድጋሚ የተለጠፈ ሚያዝያ 22/2014 ዓ.ም
Join
@adonigospel
@adonigospel
2.5K views@doni, 02:47
2022-08-29 08:30:48
በሰላምና በደስታ መዋልን ያድላችሁ
@adonigospel
@adonigospel
986 views@doni, edited 05:30
2022-08-28 13:20:10
የልቤ ልብ አንተ ነህ
ነፍሷ እኮ ነህ የነፍሴ
መኖሬ ህልም ነበር
ባትሆነኝ እስትንፋሴ
ዘማሪት ዘርፌ
እጅግ የምወደው ነፍሴ የምትፈስበት ዝማሬ ነው በድጋሚ ተባረኩበት
@adonigospel
1.1K views@doni, edited 10:20
2022-08-28 08:00:08
ተወዶጆች፦ ለክፉ ሁሉ የበለጠ ጠንካራ ጥሩ ነገር አለ፤ ለእያንዳንዱ ጨለማ ሰፊ ብርሃን አለ። ለእያንዳንዱ ሀዘን ወሰን የሌለው ደስታ አለ። ለማንኛውም እንቆቅልሽ የተብራራ ፍቺ አለ። ለብዙ ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ አለ። ባዶ ለሆነ ነገር ሁሉ ሙሉ የሚያደርግ ነገር አለ። ከሁሉም በላይ መድኃኒዓለም ከኛ ጋር አለ። ደስ ብሏችሁ ዋሉ!
አዶኒ
Join @adonigospel
@adonigospel
1.1K views@doni, 05:00
2022-08-27 20:19:05
ብዙዎች ዛሬን ማየት ናፍቀው ሳይመለከቷት አሸልበዋል፤ አንዳንዶችም ራዕያቸውን ሳያሳኩ ወደዛኛው ዓለም ሔደዋል። እኛም ነገን ማየት እንናፍቃለን ነገ ላይ ከመድረሳችን በፊት ዛሬን በሚገባ ልንኖራት ይገባል። እኛ ዛሬ የሚጎበኘን ሰው አለ የሚጠይቃቸው ደጃቸው የሰው ኮቴ ከሰማ የሰንበቱ ምስኪኖች አሉ። በበዓል ቀን ሁሉም ሰው በቤቱ ከቤተሰቡ ጋር ሲሰባሰብ በብቸኝነትና በብዙ ናፍቆት ብቻቸውን የሚያሳልፉ አዛውንቶች አሉ። እነርሱን በማሰብ ካለን በመቁረስ አዲሱን አመት እንድንቀበል በፍቅር እጠይቃችኋለሁ።
በፍፁም ማንንም ሰው ለማሳቀቅ ታስቦ የተጠቀሰ የገንዘብ መጠን አይደለም። ይህንን ማድረግ የማይችል ሰው የአቅሙን ማድረግ ቢችል አጠራቅመን አስቤዛውን በመግዛት ለምስኪኖቹ ማድረስ እንችላለን። እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይባርካችሁ!
@adonigospel
659 views@doni, 17:19