Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.52K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 28

2022-08-01 18:58:08
8.8K views., 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 18:58:08
8.0K views., 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 12:19:14
እኔስ እዘምራለው ለሥላሴ እኔስ እዘምራለው ለሥላሴ
ፈጥሮኛልና በስጋ በነፍሴ እኔስ እዘምራለው ለሥላሴ



@BiniGirmachew

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ አመታዊ ክብረበአል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን የፃድቁ አባታችንን የአብርሀምን ቤት የጎበኙ ቅድስት ሥላሴ የእኛን ቤት ይጎብኙልን

@orthodox1
@orthodox1
@orthodox1
2.2K viewsBini Girmachew, edited  09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 09:21:44
የመጀመሪያው አዳሪ የአብነት ት/ቤት በአሜሪካ

መልካም ዜና ነው

"ወይኩን ቡሩከ ስሙ ለእግዚአብሔር
እምሥራቀ ጸሐይ እስከነዐረብ ይትአኰት ስሙ"

ስለ ሁሉም ነገር የእግዚአብሔር ስሙ ከጸሐይ መውጫ እስከ መጥለቂያ ድረስ የተመሰገነ ይሁን!!! እግዚአብሔር ረድቶን በአሜሪካን ሀገር የመጀመሪያውን አዳሪ የአብነት ትምህርት ቤት በፈረንጆች በጋ (Summer Camp) ጀምረናል። ሁሉም ነገር እንደ ጀማሪ ሳይሆን ልክ እንደነባር እንዲሆንልን የእግዚአብሔር ቸርነት አግዞናልና ይክበር ይመስገን!

ወላጆች በዓላማው አምነውበት ልጆቻቸውን ከስድስት እስከ ስምንት ሳምንት ድረስ ሰጥተውናል! እኛም ተረክበን የምንችለውን እያደረግን ነው። አባቶች እየመጡ እያስተማሩ ፈሪሐ እግዚአብሔር፣ ፍቅረ ቤተ ክርስቲያን ያድርባቸው ዘንድ የተቻለውን እያደረጉ ነው! ሁላችሁም በጸሎታችሁ አስቡን!!!
........................................................
ከብዙ ድካም በዋላ የመጀመሪያ መልካም ስራ እግዚአብሔር ይመስገን እንዲህ አደረኩ አይባልም እና ሌሎችም እኔን አሳብ ማስቀጠል ትችላላችሁ ሙሉ መረጃዎችን እሰጣቸዋለሁ ከፈለጋችሁ

ለክፋት ለምትፈልጉ ለቤተክርስቲያን ከሆነ ማንኛውንም በነገር በነፃ አማክራቹዋለው

ለማንኛውም የእኔን የስነልቦና የማማከር አገልግሎት የቴሌግራም ቻናል ከፈለጋችሁ

https://t.me/BiniGirmachew

እየገባችሁ ማንበብ ትችላላችሁ
8.7K viewsBini Girmachew, 06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 07:05:34 እነሆ፥ በቶሎ እመጣለሁ፥ ለእያንዳንዱም እንደ

ሥራው መጠን እከፍል ዘንድ ዋጋዬ ከእኔ ጋር

አለ" ራእ. 22:11-12
7.2K viewsBini Girmachew, 04:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:19:53 መቼም ዛሬ ልሹምባችሁ የሚለንን እንጂ ተሹምልን የምንለውን ማግኘት ያዳግታል! እንዲያም የሚሉት ተገኝቶ ተሹምልን ቢሉት እንኳ እምቢኝ የሚል ይገኛል ለማለት ይከብዳል!
ወይራውን እዩትማ "ለእግዚአብሔር መብራት ለሰው ቅባት መሆኔን ልተውን?" ይላል
በለስስ "ርዝመቴንና የከበረ ፍሬዬን ልተውን?" ይላል
ወይንን ደግሞ ስሙት "ለእግዚአብሔር መስዋእት ለሰው ትፍስሕት መሆኔን ልተውን?" ይላል

መንገሥ መሠልጠን (ባዕለ ሥልጣን መሆን) ነው ሀብተ ክህነትን ሥልጣን ይለዋልና "ወወሃቦሙ ሥልጣነ ዘከማሁ ከመ ይፍትኁ ዘኢይትፈታኅ " እንዳለ ቅዱስ ኅርያቆስ:: ሢመተ ጵጵስና በላቀ ማዕረግ መንጋውን የሚመሩበት አብያተ ክርስቲያናትን የሚያስተዳድሩበት ሢመት (ሹመት) ነው! የበለጠ ክብርን ለመቀበል ብቻ ሳይሆን በበለጠ ተጠያቂነትም የበለጠ ፍርድ ያመጣልና ቅዱስ ያዕቆብ " ተአምሩ ከመ እንተ ተአቢ ደይነ ንነሥእ ~~~> የባሰውን ፍርድ እንድንቀበል ታውቃላችሁና።" (ያዕ 3:1) ዓይናችን አንዳይራብ ጆሯችን እንዳይጠማ በዘመናችን በቅለው አይገባንም ያሉትን ትህትናን እንደኩታ ለብሰው ፍቅርን እንደ ሸማ የደረቡትን ያሳየን አምላከ አበው የተመሰገነ ይሁን!

እሾህ የተሾመ ዕለት ግን! የበላይና የበታች የማይለይበት ዘመን ይመጣልና ያን ጊዜ " አሌ ላ ለዛቲ ቤተ ክርስቲያን ~~~> ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ወየውላት ወዮታ አለባት" ከማለት ርቀን ለእኛ ለራሳችን ወየውልን ወዮታ አለብን እንላለን! " ሠራዒና መጋቢ የማይታወቅበት ዘመን ይመጣልና ያን ጊዜ " አሌ ለነ " ካህንና ሕዝብ የማይከባበሩበት ዘመን ይመጣልና ያን ጊዜ" አሌ ለነ" መንጋውና እረኛው የማይግባቡበት ዘመን ይመጣልና ያን ጊዜ " አሌ ለነ" ብቻ ማር ይመራል ወተት ይጠቁራል ዓይነት ጭንቅ ያኔ ነው! ባለቤቱ በነቢዩ ላይ አድሮ እንደተናገረ እንዲህ ስላሉት መንጋውን ረስተው ራሳቸውን ለሚያሰማሩ ራሳቸው ዋጋ ላያገኙ ሌላውንም ዋጋ ለሚያሳጡት "ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ በእረኞች ላይ ነኝ፥ በጎቼንም ከእጃቸው እፈልጋለሁ፥ በጎቼንም ከማሰማራት አስተዋቸዋለሁ። ከዚያም ወዲያ እረኞች ራሳቸውን አያሰማሩም በጎቼንም ከአፋቸው አድናለሁ፥ መብልም አይሆኑላቸውም።" ( ሕዝ. 34:10) መልሶም " የማሰማርያዬን በጎች ለሚያጠፉና ለሚበትኑ እረኞች ወዮላቸው! ይላል እግዚአብሔር፦ስለዚህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሕዝቤን ስለሚጠብቁ እረኞች እንዲህ ይላል። በጎቼን በትናችኋል አባርራችኋቸውማል አልጐበኛችኋቸውምም እነሆ፥ የሥራችሁን ክፋት እጐበኝባችኋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር " (ኤር 23:1-2) ይላል::

ፍትህ መንፈሳዊ ግን መንጋውን በመጠበቅ ራሳቸውን በማረቅ የተሰጣቸውን የክርስቶስ እንደራሴነት በሚገባ እንዲፈጽሙ ይህንን ያዛል " ወይደሉ ለክሙ ኦ ኤጲስ ቆጶሳት ከመ ትኩኑ ሰብአ ዓይን ለህዝብ እስመ አዕይንቲሁ አንትሙ ለክርስቶስ… እናንት ኤጲስ ቆጶሳት ሆይ ለህዝቡ ጉበኞች ልትሆኑ ይገባችኋል የክርስቶስ ዓይኖች እናንተ ናችሁና" አስቀድሞም በነቢዩ ሕዝቅኤል ላይ አድሮ ይህን ተናግሯልና "የሰው ልጅ ሆይ፥ ለእስራኤል ቤት ጠባቂ አድርጌሃለሁ፤ ስለዚህ የአፌን ቃል ስማ ከእኔም ዘንድ አስጠንቅቃቸው። እኔ ኃጢአተኛውን። በእርግጥ ትሞታለህ ባልሁት ጊዜ፥ አንተም ባታስጠነቅቀው ነፍሱም እንድትድን ከክፉ መንገዱ ይመለስ ዘንድ ለኃጢአተኛው አስጠንቅቀህ ባትነግረው፥ ያ ኃጢአተኛ በኃጢአት ይሞታል፤ ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ። ነገር ግን አንተ ኃጢአተኛውን ብታስጠነቅቅ እርሱም ከኃጢአቱና ከክፉ መንገዱ ባይመለስ፥ በኃጢአቱ ይሞታል፥ አንተ ግን ነፍስህን አድነሃል። ደግሞ ጻድቁ ከጽድቁ ተመልሶ ኃጢአት በሠራ ጊዜ እኔ በፊቱም ዕንቅፋትን ሳደርግ፥ እርሱ ይሞታል፤ አንተም አላስጠነቀቅኸውምና በኃጢአቱ ይሞታል ያደረጋትም ጽድቅ ነገር አትታሰብለትም፤ ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ። ነገር ግን ኃጢአት እንዳይሠራ ጻድቁን ብታስጠነቅቅ እርሱም ኃጢአት ባይሠራ፥ ተጠንቅቆአልና በእርግጥ በሕይወት ይኖራል፤ አንተም ነፍስህን አድነሃል።" (ሕዝ. 3:17-21)

በዚህ ግብረ ኖላዊነት ለተሾሙ የነፍስ ጠባቂዎች መንጋ የምንሆን ምዕመናንንም እየተገዛን ልንታዘዝላቸው እያከበርን ልንወዳቸው ይገባል፤ ምክንያቱምሊቀ ጳጳሳቱ በማየ ገቦው ከወለደን ፈጣሪያችን በታች በንሰሀ የሚያድስ "አባታችን" ወደ ሕይወት መንገድ የሚመራ "እረኛችን" በምድር ሳለን የምንገዛለት "አምላካች" ነውና፤ መጽሐፍ እንደሚል "ኤጲስ ቆጶስ ውእቱ አቡክሙ እምታሕተ እግዚአብሔር ዘወለደክሙ እማይ ወእመንፈስ ቅዱስ ዝንቱ ውእቱ አምላክክሙ በዲበ ምድር እምታህተ እግዚአብሔር አምላክ ዘበአማን…ከውሀና ከመንፈስ ቅዱስ ከወለዳቸው ከእግዚአብሔር በታች ኤጲስ ቆጶሱ አባታችሁ ነው በእውነት ገዢ ከሆነው ከእግዚአብሔር በታች በዚህ ዓለም ገዣችሁ ነው "

እንደወይን እንደበለስ እንደወይራ ሆነው ሲኖሩ አይገባንም እያሉ በትሑት ሰብእና በቅን ልቡና ያገለግሉና ያስገለግሉ ዘንድ ቤተክርስቲያን ግድ ያለቻቸውን "እስመ እሙንቱ ቀዋምያኒሃ ለቤተ ክርስቲያን" ብለን ለምዕመናን ሕይወት የሚሟገቱ: መናፍቃንን ተከራክረው የሚረቱ: ከገቢረ ኃጢአት የሚያላቅቁ: በጸሎታቸው የሚጠብቁ: በትሩፋታቸው የሚያጸድቁ መሆን ይቻላቸው ዘንድ ረጅም ዘመናት ሰፊ ወራት እንዲሰጣቸው "በእንቲአሆሙ ናስተበቁዕ" ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን እንለምናለን እንማልዳለን::

እኒህም ላዩ እንዳይፈስ ታቹ እንዳይተነፍስ መካከሉ እንዳይደፈርስ ድርሻቸውን ለመወጣት የሚሾሙ ኤጲስ ቆጶሳትናቸውና ሐዋርያትን በስም የሚመስሉ በግብር የሚከተሉ ባለፉት አባቶች መንበር ተተክተው መንጋውን የሚመሩ ሀገረ ስብከት የሚያስተዳድሩ ይሆኑ ዘንድ ረጅም ዘመናት ሰፊ ወራት የሰጣቸው ዘንድ "በእንቲአሆሙ ናስተበቁዕ" ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን እንለምናለን እንማልዳለን::

ባለፉትና ባረፉት ኄራን አበው እግር የሚተኩ ናቸውና በአበው ሥርዓት "ኦ እግዚኦ አንብር ለነ ዲበ መንበሩ ህየንቴሁ ኖላዌ ኄረ ኢንኩን ከመ መርዔት ዘአልቦ ኖላዊ ወከመ ኢይምስጠነ ተኩላ መሳጢ" በሚለው ጸሎታቸው አክዮስ አክዮስ (ይደልዎ ይደልዎ) እያልን በብሔረ አግዓዚ የሚሰብኩ በከሥቴ ብርሃን መንበር የሚተኩ አበውን በዘመናችን እንቀበላልን! እንደ አባ ኅርያቆስም በሐዋርያቱ ሥርዓት እንዲህ እንላለን " ኦ አበዊነ ንቡራነ እድ ሥዩማን መትልወ ሐዋርያት እስመ ነሳእናክሙ አስተብቋ ዕያነ ለሃበ እግዚአብሔር .... የሐዋርያት ተከታዮች የሆናችሁ በአንብሮ እድ የተሾማችሁ አባቶች ሆይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእኛ የምታማልዱ እናንተን ተቀብለናችኋል እኮን !"

(ያስፈጽማቸው በጸሎታቸውም ይጠብቀን አሜን!)

ከቴዎድሮስ በለጠ ሰኔ ፳፰ ቀን ፳፻፱ ዓ·ም የተጻፈ
7.0K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:19:53 እርሱም ተፈወሰ።" (2ኛ ነገ. 20:7) " ከበለሱም ጥፍጥፍ ቁራጭና ሁለት የወይን ዘለላ ሰጡት፤ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንጀራ አልበላም ውኃም አልጠጣም ነበርና በበላ ጊዜ ነፍሱ ወደ እርሱ ተመለሰች።" (1ኛ ሳሙ. 30:12) እና መጽ. ባሮክ

* በሕገ ወንጌል መድኅነ ዓለም ክርስቶስ የ"ሆሳዕና"ው ማግሥት በመንገድ ሲያልፍ ሊበላ ፍሬ ፈልጎ የተጠጋው ወደዚህችው የበለስ ተክል ነበር "በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና። ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት። በለሲቱም ያንጊዜውን ደረቀች።" (ማቴ. 21:19)

በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ

"በለስ ዘይቤ ቤተ እስራኤል እሙንቱ" ባለው የምዕመንን ሰውነት በለስ ይለዋል ምግባር አልባ እንዳትሆን! በአንጻረ በለስ ኃጢዓት የተቆረጠላት ለገቢረ ጽድቅ ጉልበት እንዲኖራት ያደረጋት በለስ የሕይወታችን ምሳሌ ናት

የዘመናት መለወጥ የወቅቶች መፈራረቅ አስረጂ ምልክት ሰጪ ነው ! በዚህም ባህረ ሀሳቡን ቀምረው የአጽዋማቱን መውጫና መግቢያ ለይተው በማስተማር ለድኅነተ ነፍስ የሚያበቃ ምግባር አሠርተው ተዘክሮተ ሞት ከምዕመናን እንዳይታጣ የሚመክሩ አበው መምህራንን ይመስላል:: "ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤" (ማቴ. 24:32) "በለሱ ጐመራ፥ ወይኖችም አበቡ መዓዛቸውንም ሰጡ ወዳጄ ሆይ፥ ተነሺ ውበቴ ሆይ፥ ነዪ።" (መኃ. 2:13)

ታግሠው ቢጠብቁት በሚገኝ በከበረ ፍሬው ምግብና ፈውስ ነው! ምግበ ነፍስ ቃለ እግዚአብሔርን ፈውሰ ነፍስ ንሰሐን ከምዕመናን ሕይወት የሚያደርሱ አበው ካህናቱን መምህራነ ነፍስ ሊቃውንቱን ይመስላል "በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።" (ምሳ. 27:18)

#ዕፀ_ወይን

"ወይቤልዎ ኩሎ ዕፀው ለወይን ንአ ንግሥ ለነ። ወይቤልዎ ወይን እኅድግኑ ወይንየ ወትፍሥሕትየ ዘበኀበ እግዚአብሔር ወዘኀበ እጓለ እመሕያው ወእሑር እንግሥ ለዕፀው … እንጨቶች ሁሉ ወይንን ና ንገሥልን አሉት፤ ወይንም ለእንጨቶች እነግሥ ዘንድ ለእግዚአብሔር መስዋእት ለሰው ትፍስሕት መሆኔን ልተውን አላቸው። "

ወይንም ዕለተ ፍጥረቱ ሠሉስ ነው! ቅባት የሚሰጥ ለመብልነት ለመብራትም የሚውል የወይራ ወገን ቢሆንም ከዕጸው ሁሉ እጅግ የተመረጠና የተወደደ ነው ! "አቤቱ ጌታዬ በዚህ ዓለም ካሉ ከታላላቁ ከታናናሾቹም እንጨቶች አንድ የወይን ሐረግን መረጥህ" (ዕዝ ሱቱ 3:23)

* በሕገ ልቡና:- ኖኅ ከጥፋት ውኃ በኋላ በሥራው ገበሬ ሆኖ የተከለው ወይን ነበር " ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይንም ተከለ። " (ዘፍ. 9:20) የልዑል እግዚአብሔር ካህን የክርስቶስ ምሳሌ መልከጼዴቅ ያስታኩት የነበረው በወይን ነው "የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅም እንጀራንና የወይን ጠጅን አወጣ እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ካህን ነበረ።" (ዘፍ. 14:18)

* በሕገ ኦሪቱ እንደ ወይራ ሁሉ ከምድረ ርስት ከነአን ገጸ በረከት አንዱ ወይን ነው! "ስንዴ ገብስም ወይንም በለስም ሮማንም ወይራም ማርም ወደ ሞሉባት ምድር፥..." (ዘዳ. 8:8)

* በሕገ ወንጌል ክርስቶስ በከብካበ ቃና ዘገሊላ የለወጠው ውኃ ጠጅነቱ የወይን ነበር "ኢየሱስም ውኃውን የወይን ጠጅ ወዳደረገባት ወደ ገሊላ ቃና ዳግመኛ መጣ።" (ዮሐ. 4:46) ራሱንም መስሎ ያስተማረበት ነው (ዮሐ. 15:1-5)

በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ

የምዕመናን ሕይወት በዐጽቀ ወይን አስገኚ ጌታቸውም በሐረገ ወይን እየተመሰለ ይነገራል "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ. 15:5) "አብ ጉንደ ወይን ወልድ ጉንደ ወይን መንፈስ ቅዱስ ጉንደወይን" እንዲል ቅዳሴ ማርያም

ጌታችን ሥጋውን በኅብስት እነደሰጠ ለማጠየቅ ሲሻ ራሱን በኅጠተ ሥርናይ (በስንዴ ቅንጣት) ይመስላል እንዲሁም ደሙን በወይን እንደሰጠ ሲያመላክተን ራሱን በሐረገ ወይን የመስልል! በእርሱ አምነው ሥራ የሚሰሩ በትምህርቱ አምነው ጸንተው የሚኖሩ በልተውት ጠጥተውት የሚከብሩ ምዕመናንም በዚሁ ተመስለዋል "ወይናችን አብቦአልና የወይናችንን ቦታ የሚያጠፉትን ቀበሮች፥ ጥቃቅኑን ቀበሮች አጥምዳችሁ ያዙልን።" (መኃ.2:15)

#ዕፀ_ራምኖን (አስታ ወይም ዶግ ወይም እሾህ )
"ወይቤልዋ ዕጸው ለራምኖን ንዒ አንቲ ንግሢ ለነ ወትቤሎሙ ዕጸ ራምኖን ለዕጸው እመ በአማን ታነግሡኒ ...በጽድቅ ላዕሌክሙ ንዑ ታጽለሉ ታሕተ ጽላሎትየ እመ ኢወጽአት እሳት እምራምኖን ወትበልዖ ለአርዘ ሊባኖስ ... ዛፎችም ሁሉ እሾህን፦ መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት።እሾሁም ዛፎችን፦ በእውነት እኔን በእናንተ ላይ ታነግሡኝ እንደ ሆነ ኑ ከጥላዬ በታች ተጠጉ። እንዲሁም ባይሆን እሳት ከእሾህ ይውጣ፥ የሊባኖስንም ዝግባ ያቃጥል አላቸው።"

ፍሬ አልባ ቅጠሉም የማያጠላ ሌላውም እንዳያፈራ አንቆ የሚይዝ ካፈራውም ተጠግቶ ወግቶ የሚያደማ ክፉ ተክል እሾህ ነው! የአዳም የበደሉ ርግማን መገለጫ መሆኑ ተገልጿል "እሾህንና አሜከላን ታበቅልብሃለች የምድርንም ቡቃያ ትበላለህ።" (ዘፍ. 3: 18) በዚህ ምርገም ጥላ ሥር ያሉትን ልጆቹን ሁሉ እሾህ ይላቸዋል ከንጽሕት እመ አምላክ ድንግል ማርያም በቀር እርሷን "በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ" ይላታል (መኃ. 2:2) የታካቾች ፍኖት መገለጫ ሆኖም ተነግሯል "የታካች መንገድ እንደ እሾህ አጥር ናት የጻድቃን መንገድ ግን የተደላደለች ናት።" (ምሳ. 15:19)

የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል የያዛቸው በእሾሆች የታነቁ ይባላሉ ለነዚህም እሾሁ ብዕል ሰፋጢት (አታላይ ባልጠግነት) ሐልዮ መንበርት (ቦታን ማሰብ ሥልጣንን መናፈቅ) ትካዘ ዓለም (ሥለ ሥጋ ማሰብ) ፍቅረ ብእሲትና ፍቅረ ውሉድ እያታለላቸው በመንፈሳዊ ሕይወት እንዳይጎለብቱ ማነቆ ይሆንባቸዋል! ትሩፋት አፍአዊን ሠርቶ ትሩፋት ውሳጣዊ የቀረችበት እሾኻማ ይባላል!

"ሁሉም ለገንዘብ ይገዛል።" እንደተባለ (መክ. 10:19) እመጸውተዋለሁ እያሉ ገንዘብ የሚሰበስቡ አሉ እኒህን መጽሐፍ "ኢትኩን መፍቀሬ ነዋይ በእንተ ፍቅረ ነዳያን" ይልባቸዋል::
ፍሬ ከሌላቸው ፍሬ አልባ ከሚያደርጉ እሾሆች መራቅ ደግሞ እጅጉን ይገባል:: ገንዘብ እየሰጡ እጅ መንሻ እያመጡ ሹሙን ሸልሙን ከሚሉ እሾሆች መሸሽ ይገባል "እሾህና ወጥመድ በጠማማ ሰው መንገድ ናቸው ነፍሱን ግን የሚጠብቅ ከእነርሱ ይርቃል።" እንዳለን የጥበብ ወዳጇ (ምሳ 22:5) "ሥልጣንን በመውደድ አስኬማቸውን ቀንድ" አድርገው መልሰው ቤተክርስቲያንን ከሚወጉ የምሕረት አምላክ ይጠብቀን::

እንደ ማጠቃለያ

ሁሉን እንዳሰቡት እንደሚጠብቁትም አለማግኘት ደስታን የሚያጓድል ኃዘንን የሚያመጣ ይመስላል:: ይሁንና ግን እግዚአብሔር እንደወደደ ነገር ሁሉ መደረጉን ለምናምን "የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ" (ነህ 8:10)እንዳለው በነገር ሁሉ እያመሰገንን በተለይ ባለንባት ዘመን እንዲህ እያልን ልንኖር የገባል “ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ ... እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል" (ዕን. 3:17)
4.3K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:19:52 #ገሪዛን !
በሰማሪያ ያለች የኖራ ደንጊያ ተራራ ናት! ከሜዲትራንያን ወደ 3ሺህ ያህል (2855) ጫማ ከፍታ ያላትና በሳምራውያን ትውፊት አብርሃም ይስሕቅን "የሰዋባት" መለከጼዴቅን ያገኘባት ያዕቆብ ለአምላኩ ምስዋዕ ያቆመባት (ደብረ ሞርያም) ገሪዛን ናት:: ዛሬ መርገመ ጌባል ያልወደቀባት በረከት ነፍስ የሚታደልባት የደብረ ገሪዛን ራስ የተባለች የቤተ ክርስቲያናችን የምሕረት አውድ ናት:: ሊቀ ነቢያት ሙሴ እንዲህ እንዳለ "አምላክህም እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ አንተን ወደምትሄድባት ምድር ባገባህ ጊዜ፥ በረከቱን በገሪዛን ተራራ መርገሙንም በጌባል ተራራ ታኖራለህ።" (ዘዳ. 11:29)

ኢዮአታምና ርዕሰ ደብረ ገሪዛን (አውደ ምሕረቱና መምህሩ) የተገናኙት ሰው ሰው ያደረገውን ፈጣሪውን በረሳበት ለእግዚአብሔር መገዛትን እምቢኝ ብሎ ልክ እንደዛሬው ሰዎች ይግዙን የሚል "ግለሰብን ማጠን" በሠለጠነበት ዘመን ነበር! "ወኢተዘከርዎ ለእግዚአብሔር አምላኮሙ ዘአድኀኖሙ እምእደ ኩሉ ፀሮሙ እም እለ አውዶሙ… በዙርያቸው ካሉ ጠላቶቻቸው ከጠላቶቻቸው እጅ ያዳናቸው እግዚአብሔርን አላሰቡም " (መሳ· 8:25) እንዳለው:: እንዲህ ነው እንጂ "በቦታው ላይ ባለ ቦታው ሲገኝ" ኢዮአታም ምንኛ የታደለ ሰው ነው! መፍቀሬ ጥበብ "ጊዜና እድል ግን ሁሉን ይገናኛቸዋ" እንዳለ (መክ. 9:11)

እንዲህ ሲል ሰባኪው እያለቀሰ ነገሩን ይጅምራል "ስምዑኒ ሰብአ ሰቂማ ወይስማዕክሙ እግዚአብሔር ~~~> የሴኬም ሰዎች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲሰማችሁ ስሙኝ።" የዚህች አገር የሲቂማ ወይም የሴኬም ህዝቦች እግዚአብሔር ይስማችሁና እስኪ ስሙኝ! አዎ ሰው ቃለ መምህራንን ቢሰማ እግዚአብሔር ይሰማዋልና ከመልካሙ መልካም ያገኛልና መጽሐፍ "እግዚአብሔርን ብትፈሩ ብታመልኩትም፥ ቃሉንም ብትሰሙ፥ በእግዚአብሔርም ትእዛዝ ላይ ባታምፁ፥ እናንተና በእናንተ ላይ የነገሠው ንጉሥ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ብትከተሉ፥ መልካም ይሆንላችኋል።"(1ኛ ሳሙ.12:14)እንዳለ!

ለዛሬውም የአገሬው ነዋሪ ሰባኪው አትሮንሱን ተደግፎ "ስምዑኒ ሰብአ 'ኢትዮጵያ' ወይስማዕክሙ እግዚአብሔር" ብሎ ጀምሯል:: ያኔ ልባሙ መጋቤ ምሥጢር በደኃሪት ልደት ከዕፀ ሕይወት ድንግል የተገኘ ፈጣሪው ፍሬ ሕይወት ክርስቶስ የተቀኘውን ቅኔ መነሻ ያደርጋል (ምስጢሩን ዕፅ ካገናኛቸው ብሎ)
ሠናየ ዕፅ ይፈሪ ፍሬ ሠናየ
ወእኩይሰ ዕፅ ይፈሪ ፍሬ እኩየ (ማቴ 7:17)


#ዕፀ_ዘይት (የወይራ ዛፍ)

ኢዮአታም "ነገሩን" የጀመረው እንዲህ ብሎ ነው:-
ወሆሩ ዕፀው ያንግሡ ሎሙ ንጉሠ ወይብልዋ ለዕፀ ዘይት ንዒ ንግሢ ለነ… ወትቤሎሙ ዕፀ ዘይት እኅድግኑ ቅብዕየ ዘሰብሐ እግዚአብሔር በላዕሌየ ወእጓለ እመሕያው ወእሑር እንግሥ ላዕለ ዕፀው… እንጨቶች ንጉሥን ያነግሥ ዘንድ ተሰብስበው ዕፀ ዘይትን (ወይራን) ነይ ንገሽልን አሏት እፀ ዘይትም ሂጄ ለእንጨቶች እነግሥ ዘንድ ለእግዚአብሔር መብራት ለሰው ቅባት መሆኔን ልተውን አለቻቸው " ይላል!
ከዕለተ ሠሉስ ዕፀው መካከል ዕፀ ዘይት (የወይራ ዛፍ) አንዱ ነው! ቅባት የሚሰጥ ለመብልነት ለመብራትም የሚውል የወይራ ወገን ነው::

* በሕገ ልቡና በሰብአ ትካት ለጥፋት ውኃ መወገድ በሰላም አብሣሪዋ ርግብ የመጣ ምልክት ይኼ ወይራ ነው! "ርግብም በማታ ጊዜ ወደ እርሱ ተመለሰች በአፍዋም እነሆ የለመለመ የወይራ ቅጠል ይዛ ነበር። ኖኅም ከምድር ላይ ውኃ እንደ ቀለለ አወቀ።" (ዘፍ.8:11)

* በሕገ ኦሪት ከምድረ ርስት ከነአን ገጸ በረከት አንዱ ይኼ ወይራ ነው! "ስንዴ ገብስም ወይንም በለስም ሮማንም ወይራም ማርም ወደ ሞሉባት ምድር፥..." (ዘዳ. 8:8 ) በቤተ መቅደሱ ያሉ ሁለቱ ኪሩቤል የተቀረጸው : የመቅደሱ መግቢያ መቃን እና የቅድስተ ቅዱሳኑ ደጃፍ አምድ የተሰራው ከዚሁ ከወይራ ነው! (1 ነገሥ. 6:23-34)

* በሕገ ወንጌል በመዋዕለ ሥጋዌው ሌሊት ሌሊቱን ጌታችን የመረጣት የጸሎት ሥፍራ ምጽአቱን ያስተማረባትና ዕርገቱን የፈጸመባት ደብር የወይራ ዛፍ የበዛባትን ሥፍራ "ደብረ ዘይትን" ነው! ሉቃ. 21:37 ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።

በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ

የወይራ ዛፍ የቤተ እግዚአብሔር መብራት ምንጭ ነው! የፈጣሪን ገጸ ምህረት ተወካፌ ጸሎትነት ያሳያል "አንተም መብራቱን ሁል ጊዜ ያበሩት ዘንድ ለመብራት ተወቅጦ የተጠለለ ጥሩ የወይራ ዘይት እንዲያመጡልህ የእስራኤልን ልጆች እዘዛቸው።" (ዘጸ· 27:20)

የወይራ ዛፍ ክር የሚነድበት ዘይት መገኛ ነው! ለእግራችን መብራት ለመንገዳችን ብርሃን የሆነ ህጉን ለሚያስተምሩ ምግባር ለሚያሰሩ አበው ምሳሌ ነው! "ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።" (መዝ. 118:105)
የወይራ ዛፍ በቤተ እግዚአብሔር ያማረ የተወደደ እንደሆነ እንዲሁ በሥላሴ ፊት ባለሟልነት በምዕመናን ዘንድ መወደድ በአጋንንት ዘንድ መፈራት ያላቸውን አበውን የመስላል! "ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ... ውበቱም እንደ ወይራ ይሆናል" (ሆሴ 14:6)

የወይራ ዛፍ ብዙ ፍሬ እንዲያፈራ ባለ ብዙ ጸጋና ክብር የሆኑትን አበውን ይመስላል! " ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው።" (መዝ. 127:3)

የወይራ ዛፍ ቀን ከአእዋፍ ሌሊት ከአራዊት በአጥር በቅጥር ተጠብቆ እንዲኖር በረድኤቱ በቤቱ ጥላ ተጠብቀው የሚኖሩ አበውን ይመስላል! "እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ፤" (መዝ· 51:8)

#ዕፀ_በለስ

"ወይብልዋ ለበለስ ንኢ ንግሢ ለነ ወትቤሎሙ በለስ እኅድግኑ ምጥቀትየ ወፍሬየ ቡሩክ ወእሑር እንግሥ ለዕፀው … በለስን ነዪ ንገሽልን አሏት በለስም ሂጄ በእንጨትም እነግሥ ዘንድ ርዝመቴንና የከበረ ፍሬዬን ልተውን አለቻቸው። "
ዕፀ በለስም እንደ ዕፀ ዘይት በማክሰኞ (ማግሥቱ ለሰኞ) የተፈጠረ በቁመቱና በከበረ ፍሬው የሚታወቅ ክወይራ ጋር የሚተከል የሾላ ወገን ወተታም ተክል ነው!

* በሕገ ልቡና አዳምና ሴቲቱ በጎውንና ክፉውን ከምታሳውቀው ዛፍ (ባይብሏት በጎ ዕፀሕይወትና በጎ ምንግሥተ ሰማያትን ቢበሏት ደግሞ ክፉ ሞትንንና ክፉ ገሃነመ እሳትን ይምታሳውቅ ናትና) ቆርጠው በመብላታቸው ከጸጋው ሲራቆቱ ያገለደሙት ቅጠል በገነት ከነበሩት ዕፀው ቆጽለ በለስ ነበር "የሁለቱም ዓይኖች ተከፈቱ፥ እነርሱም ዕራቁታቸውን እንደ ሆኑ አወቁ የበለስንም ቅጠሎች ሰፍተው ለእነርሱ ለራሳቸው ግልድም አደረጉ።" ( ዘፍ. 3:7) ኩፋሌውም "ወከደነት ኀፍረታ በቆጽለ በለስ" ይለዋል

* በሕገ ኦሪት ፍሬ በለስ ወይም በኩረ በለስ በአገልግሎቱ በለሰ ማእረር እንዲሁም ዐጽቀ በለስ እየተባለ ተገልጿል! ልዑለ ቃል ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ አሥራ አምስት ዓመት የተጨመረለትን የንጉሡ የሕዝቅያስን ቁስል የፈወሰለት በዐጽቀ በለስ ነው: ነቢየ እግዚአብሔር ኤርምያስ አቤሜሌክን መድኃኒት እንዲያመጣ ቢልከው በሙዳየ በለስ ይዞት ስድሳ ስድስት ዓመት የተኛውና ኋላ በንሥር ከነጦማሩ የላከው ይህንኑ በለስ ነው! ዳዊት የአማሌቃዊውን ባሪያ የግብጹን ብላቴና ከሦስት ቀን በኋላ ያዳነው በዚሁ በለስ ነበር "ኢሳይስም፥ የበለስ ጥፍጥፍ አምጡልኝ አለ፤ አምጥተውም በእባጩ ላይ አደርጉለት፥
3.6K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:19:52 "ስምዑኒ ሰብአ 'ኢትዮጵያ' ወይስማዕክሙ እግዚአብሔር … የ"ኢትዮጵያ" ሰዎች ሆይ ስሙኝ እግዚአብሔር ይስማችሁ"
(መሳ 9:7:- ከታናሹ ኢዮአታም)

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን "ከዘመኑ ጋር የማትሄድ ዘመኑንም የማትከተል" ናት!
ለምን?
እምቅድመ ዘመናት ዘመናዊ የሆነውን የክብር ባለቤት ልዑል እግዚአብሔርን በማምለክ ዓመታትን ዋጅታ በወቅቶች ላይ ሠልጥና በመኖር ዘመን የምታስከትልጊዜያትን ቀምራ የምትገልጥ ቀዳሚ ፍኖት በመሆኗ ነው! በዚህም "ክርስትና ቀዳሚነት ኦርቶዶክሳዊነትም ብልጫ ነው" እንላለን::

የዚህ መገለጫ ማሳያ እንድትሆን የሀዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቶስ በደሙ የመሠረታት ጌታችን በሦስቱ መገለጫነት ሕንፃ ቤተ መቅደስ፣ የምእመን ሰውነትና የክርስቲያኖች ጉባኤ አድርጎ አጽንቷታል:: በዚህም ላይ በሃይማኖት ለሚገኝ ክብር ማረፊያና ማሳረፊያ አድርጓት ቅን ሥዩማንን እየሰጣት ቀድሞ ሐዋርያትን ኋላም አርድዕትን ሾሞ ጠብቆ ሲያስጠብቃት እናያለን (ሉቃ. 6:13, 10:1, ሐዋ. 20:28) ኋላም በ "መትልወ ሐዋርያት" (Apostolic Succession ) ተጠብቃ እነርሱም "እስከዓለም ፍጻሜ ከእናንተ ጋር ነኝ" (ማቴ 28:19)ያላቸውን ቃል ኪዳን ይዘው ተከታዮቻቸውን አበው በአንብሮተ እድ እየሾሙ በ"ትልወተ ወልድ" ሥር "ተለውተ አሠሮሙ ለሐዋርያት" እንዲባሉ ለትውልድ እስከ ኅልፈተ ዓለም ሊያስተላልፏት ግብረ ኖላዊነታቸውን በሚገባ እየተወጡና ፈጣሪያችንን እያማጸኑ ለአምላካቸው አደራ እየሰጡ ካለንበት ዘመን ደርሰናል:: "ወሴሙ ቀሲሳነ ላዕለ ቤተ ክርስቲያን ወጸለዩ ወጾሙ ወአማኅጸነዎሙ ለእግዚአብሔር ዘኪያሁ ተአመኑ... ለቤተክርስቲያንም ቀሳውስትን ሾሙ የሚታመኑትን እግዚአብሔርንም አማጸኑት" እንዲል (ሐዋ. 14:23)

ይህ ሐዋርያዊ የማዕረገ ክህነተ ኖላውያን ሠንሠለት "እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት" የተባለችውን ቤተ ክርስቲያን ሲያስጠብቅ ዘመንን እያስከተለ ከዛሬ ደርሷል! ሰሞኑን በሢመተ ጵጵስና ይህንኑ መገለጫ ለማስጠበቅ ቅዱስ ሲኖዶሳችን "የቤት ሥራው" ሲተገብር መሰንበቱ ይታወቃል:: በሰማይ ጸንታ ያለች ዘልዓለማዊትና መነፈሳዊት ሥርዓት በምድር መገለጫዋ እንዲጸና ፈቃደ እግዚአብሔርን ያስቀደመ መንፈሳዊ ተግባር በቤተ ክርስቲያን ሊፈጸም የሚገባው የምድራውያን ሕግ የሚያኖራት ሳይሆን በመለኮታዊ ሥልጣን የምትተዳደር ስለሆነ ጉባኤ መንፈስ ቅዱስ (ቅዱስ ሲኖዶስ) የዚህ ብቸኛው ባለድርሻ ነው! በዚህ ጽሐፍም ጭብጥ ይህን ሳንዘነጋ ከቅዱሳት መጻሕፍት ቃል አውስተን በጉዳዩ ዙርያ ስላሉ ጠቃሚ ፍሬ ነገሮች የቅዱሳን አምላክ እንደፈቀደልን እንማማራለን! " ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ።"(ኤፌ. 4:29) መቼም አንዳንድ ሰው ከተወለደ ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞቱ ሲያወጣና ሲያወርድ ይኖራል እንጂ የመጨረሻውን ቁርጥ ያለ ነገር የሚናገረው በጊዜ ሞቱ ነው ይባላል "ይትወላወል ሰብእ እምጊዜ ልደቱ እስከ ዕለተ ሞቱ" እንዲል! በሃይማኖት መኖር ግን ሁል ጊዜ ከእውነትና ከእውነቱ ጋር ብቻ "እንበለ ተወላውሎ" መተባበር ለማንጽ የሚጠቅምና በጎ የሆነውን ቃል በሥራና በእውነት ሲገልጡ መኖር ነው! በቅድሚያ ጭብጡ እጅግ እንዳይሰፋ ጉዳዩን አጠቃሎ የሚያስቀምጥልንን ምሳሌ ከቅዱስ መጽሐፋችን እናንሳ "ናስተሕምምኬ ከመ ንርከብ ምሳሌ እስመ ምሳሌ ከሣቴ ገጸ ነገር ውእቱ ~~~> እስቲ ምሳሌ እንደናገኝ እናስብ ምሳሌ የነገርን ፊት ገላጭ ነውና" እንዲል መዝገበ ሃይማኖት!

በእስራኤል ከተነሱት መሳፍንት ህዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር የመለሰ: የበአልን መሰዊያ ያፈረሰ: ሦስት እልፍ ከሁለት ሺህ ይዞ ወጥቶ እንዳይመኩ በሦስት መቶ ሠራዊት ብቻ ጠላቶቻቸውን ምድያማውያንን ያሳፈረ: የሰላም መሰዊያን አቁሞ ፈጣሪውን ያከበረ: "ምድርን አርባ ዘመን ያሳረፈ" የዮአስ ልጅ ሮብአም የተባለው ጽኑዕ ኃያል ጌድዮን ነው!

"ወይቤልዎ ሰብአ እስራኤል ለጌድዮን ተመልአክ ለነ አንተ ወደቂቅከ እስመ አድኀንከነ እም እዴሆሙ ለምድያም" ~~~> የእስራኤልም ሰዎች ጌዴዎንን፦ ከምድያም እጅ አድነኸናልና አንተ ልጅህም የልጅ ልጅህም ደግሞ ግዙን አሉት።" ይለናል!
ጌድዮን ግን እንዲህ አላቸው " ኢይትመለአክ አንሰ ለክሙ ወወልድየኒ ኢይትመለአክ ለክሙ እግዚአብሔር ይትመለአክ ለክሙ" ~~~> እኔ አልገዛችሁም፥ ልጄም አይገዛችሁም እግዚአብሔር ይገዛችኋል!

ይኽ ሰው ብዙ ሚስቶች ነበሩት ከበኩር ልጁ ዮቶር እስከ ታናሹ ኢዮአታም ድረስ ካብራኩ የተከፈሉም ሰባ ልጆች ነበሩት! ከእነዚህም አቤሜሌክ ሰቂማ (ሴኬም) ከምትገኝ ዕቀብቱ (ዕቁባቱ) የተወለደለት ወንድ ልጅ ነው! ጌድዮን ሲያርፍ በአባቱ እና በወንድሙ መካነ መቃብር ኤፍራታ አሳረፉት::

እንግዲህ አባት እግዚአብሔር እንጂ እኔም ልጆቼም አንገዛችሁም ያለውን ትቶ እኔ "የአጥንታችሁ ፍላጭ የሥጋችሁ ቍራጭ" ካልገዛሁ ያለ አቤሜሌክ ሰባውን ወንድሞቹን በአንድ ደንጊያ ላይ ገድሎ በሰቂማ (ሴኬም) የወይራ እንጨት አጠገብ ነገሠ! ከሰባው ግን ሸሽቶ ያመለጠና ተሰውሮ የተረፈው ታናሹ ኢዮአታም ወደ ገሪዛን ተራራ ወጥቶ ቆመ! ጮኾም እያለቀሰ መሳሌውን በዕፀው እየመሰለ ተናገራቸው::

እንዲህ ሲል ይጀምራል "ስምዑኒ ሰብአ ሰቂማ ወይስማዕክሙ እግዚአብሔር" ~~~> የሰቂማ (የሴኬም) ሰዎች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲሰማችሁ ስሙኝ።
አንድ ጊዜ ዛፎች በላያቸው ንጉሥ ሊያነግሡ ሄዱ
1. ወይራውንም። በእኛ ላይ ንገሥ አሉት። ወይራው ግን፦ እግዚአብሔርና ሰዎች በእኔ የሚከበሩበትን ቅባቴን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው።
2. ዛፎችም በለሱን፦ መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት። በለሱ ግን፦ ጣፋጭነቴንና መልካሙን ፍሬዬን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው።
3. ዛፎችም ውይኑን፦ መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት። ወይኑም። እግዚአብሔርንና ሰውን ደስ የሚያሰኘውን የወይን ጠጄን ትቼ በዛፎች ላይ እንድሰፍፍ ልሂድ? አላቸው።
4. ዛፎችም ሁሉ እሾህን፦ መጥተህ በላያችን ንገሥ አሉት።እሾሁም ዛፎችን፦ በእውነት እኔን በእናንተ ላይ ታነግሡኝ እንደ ሆነ ኑ ከጥላዬ በታች ተጠጉ። እንዲሁም ባይሆን እሳት ከእሾህ ይውጣ፥ የሊባኖስንም ዝግባ ያቃጥል አላቸው።

የጊዜውን ምሳሌና ፍካሬ ከዚህ እናቆየው
የታሪኩ ፍጻሜ ግን ለሦስት ዓመት የኢዮአታም ርግማን ደርሶባቸው እሾኹን በራሳቸው ላይ አንግሠው ቆዩ! ኋላ የገዛቸው አቤሜሌክን ግን አንዲት ሴት በወፍጮ ስባሪ ናላውን እስኪበጠበጥ ራሱን ቀጥቅጣው "ሴት የገደለው እንዳልባል ሰይፍህን መዘህ ግደለኝ" ብሎ በጋሻ ጃግሬው እጅ ተወግቶ ሞቷል::
ወደ ሃተታው ግን እንመለስ፤

#ኢዮአታም !
የስሙ ፍካሬአዊ ፍቺ "እግዚአብሔር ፍጹም ነው አምላክ ትክክል ነው" ማለት ነው! በእማሬያዊ ፍቺው ባልቅኔና እንደዘመናችን መምህር ሰባኪ ነው! አዎ በእውነት ምሳሌ መስሎ ነገር አራቆ ግኡዛን ፍጥረታትን ግዕዛን እንዳላቸው እንደ ተናጋሪና ሰሚ አድርጎ ጥልቅ በሆነ አካሄድ በአውደ ምሕረት የሚቆም አሰምቶ የሚናገር እያዘነ እያለቀሰ የሚሰብክ እውነትና ሕይወት የሆነውን ማኅየዊ ቃል የሚያስተምር "መጋቤ ምሥጢር" ነው ኢዮአታም፤
4.1K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 22:19:24
"ስምዑኒ ሰብአ 'ኢትዮጵያ' ወይስማዕክሙ እግዚአብሔር … የ"ኢትዮጵያ" ሰዎች ሆይ ስሙኝ እግዚአብሔር ይስማችሁ"
(መሳ 9:7:- ከታናሹ ኢዮአታም)
4.0K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ