Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.52K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-09 19:46:54
1.3K viewsDrshaye Akele, 16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 12:30:45 ኑ ለቅሶ እንድረስ
°°°°°°°°°°°°°°°
ያሳደገችኝ ደብር ተቀመጠች አሉኝ ለቅሶ
ውለታዋ ተረስቶ ክብር ማዕረጓ ተድሶ
በትእቢት ተረማመደ ቅጥር ጊቢዋን ጥሶ

ማር ይዘንባል ማር ነበር ዜማ ቅኝቷ
ስጋጃው በደም ራሰ ጥይት ዘነበ በቤቷ

ሰንደቃላማ ነበረ "የዘለለ–ዕለት" ውበቷ
ኑ እንድረሳት ለቅሶ ማቅ ለብሷል ጉልላቷ
.
.
.
ኑ እንላቀስ … ያልሰማ ይስማ መርዶ
ደብራችን አንብታለች መጋረጃዋ ተቀዶ
.
.
.

ፊደል ቀራጭ ስንዱዬ እኔን ልጅሽ ፊደል ጠፋኝ
ሀ ብለሽ ያስቆጠርሽው ሆ ብሎ ፊትሽ ደፋኝ
በጸአዳ ግምጃሽ ፈንታ ከልሽን ሳየው ከፋኝ
.
.
.
ለምጣዱ ሲባል ትለፍ ብለን ነበር አይጧ
ሰስተንላት ነገን ፈርተን ይሔ ቀን እንዳይመጣ
.
.
.
ብንጠፋ ብናጠፋ ከደጀ ሰላም ብንርቅም
የተስፋ ርስታችን ናት ‘ተዋህዶን’ አንለቅም
አንድ ፓትርይርክ (አንድ መንበር) አንድ ሲኖዶስ…
ከአንዲት ‘ቤተስኪያን’ ወዲያ አቻ ክብር አላውቅም
ልጄ በካህን እንጂ በአቶ አይጠመቅም!

ምሥራቅ ተረፈ

ተውሳክ ዘዚአየ (የእኔ ጭማሪ)

በመግደላቸው ሳያፍሩ የይቅርታ ቃል ሳይመልሱ
ጥቁር አውልቁ ይሉናል ጭራሽ ለቅሶ አትድረሱ

የሚያድግ ልጅ ከጠላ ፡ ሟች አረጋዊ ከረገመ
ያኔ ነው የሞት ጥላ ያጠላው ፡ ብርሃን ተስፋ የጨለመ
ዘውድ አንበሳው የተደፋ ፡ ዙፋን እሳቱ የከሰመ

አቢይ ማዕበል ተነስቶ ፡ የተርሴስ መርከብ ቢናወጥ
ዮናስ ከባህር ቢጣል ፡ ተላልፎ ለሞት ቢሰጥ
አየሁ … ትንቢት ሲሻር ፡ ካውሬው መንጋጋ ሲያመልጥ
እንባው መአት ሲገድብ ፡ ልቅሶው አለቱን ሲያቀልጥ
ተዋህዶ ሳትከፈል ነነዌም ሳትገለበጥ !
… አየሁ!



1.1K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 23:04:32 እግዚአብሔር ይመስገን  የውጪ ዜናዎች መዘገብ ጀምረዋል

https://vm.tiktok.com/ZMYjBMfVU/
https://vm.tiktok.com/ZMYjBMfVU/
https://vm.tiktok.com/ZMYjBMfVU/
3.0K viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 22:11:04 https://vm.tiktok.com/ZMYjkRARu/
https://vm.tiktok.com/ZMYjkRARu/
https://vm.tiktok.com/ZMYjkRARu/
229 viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, edited  19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 19:58:03 አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ 
 
ከሀይማኖት ጋር ተያይዞ ባለው ወቅታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ ላይ  ከኢሰመጉ የተሰጠ መግለጫ 
      ጥር 30/2015 ዓ.ም

መግቢያ፡ 
ኢሰመጉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጋር ተያይዘው የሚነሱ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮችን ሲከታተል የቆየ ሲሆን ከእዚህም ጋር ተያይዞ እሁድ ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅዱስ ሲኖዶስ እውቅና ባልተሰጣቸው ሶስት ሊቃነ ጳጳሳት አማካኝነት 26 ኤጲስ ቆጶሳት የተሾሙ ሲሆን ይህንንም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ህገ-ወጥ ያለውን ድርጊት ተከትሎ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በዋናነት በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አብያተክርስቲያናት ውስጥ ከቅዱስ ሲኖዶሱ እውቅና ያልተሰጣቸው አዲስ የተሾሙ ኤጲስ ቆጶሳት ወደ አብያተክርስቲያናት በመንግስት የጸጥታ አካላት ጭምር ታጅበው በመግባታቸው እና ምዕመኑ ይህንን ባለመቀበሉ ምክንያት በተፈጠሩ ግጭቶች በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽመዋል፡፡ ለማሳያነት  በሻሸመኔ ከተማ ከመንግስት የጸጥታ አካላት በተተኮሱ ጥይቶች የሰዎች ህይወት ማለፉን፣ የአካል ጉዳት መድረሱን እንዲሁም በያቤሎ አካባቢ በቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ላይ ጭምር እስራት፣ ማዋከብ እና ድብደባ መፈጸሙን እና በተለያዩ አካባቢዎች ይህንን አካሄድ በተቃወሙ የእምነቱ ተከታዮች ላይ እና የቤተክርሲቲያኒቱ አገልጋዮች ላይ ድብደባዎች እንደተፈጸሙ፣ ቤት ሰብሮ በመግባት የህግ ስነስርዓትን ያልተከተሉ እስራቶች እንደተከናወኑ እና በርካታ ቁጥር ያለቸው ሰዎችም በብዛት እየታሰሩ መሆኑን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡

በተጨማሪም ከቅዱስ ሲኖዶሱ በተላለፈ መልእክት መሰረት ጥቁር ልብስ የለበሱ ሰዎችን በአንዳንድ አካባቢዎች እስራት፣ እንግልት እና መዋከብ እየተፈጸመባቸው እንደሆነና ይህንንም ድርጊት አንዳንድ ተቋማት እና ድርጅቶች በተመሳሳይ መልኩ እየፈጸሙት መሆኑን ኢሰመጉ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡ ስለሆነም ይህ ጉዳይ ወደየማይሆን አቅጣጫ በመሄድ ተባብሶ ከፍተኛ የሰውና የንብረት ጥፋቶችን ከማስከተሉ በፊት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና የበኩላቸውን ሀላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ ኢሰመጉ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

ኢሰመጉ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ በደረሱ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ ተጨማሪ የምርመራ ስራዎችን በመስራት ዝርዝር ዘገባ የሚያዘጋጅ መሆኑን ከወዲሁ ይገልጻል

ተያያዥ የህግ ድንጋጌዎች፡

የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 27 የሀይማኖት ነጻነት መብትን የያዘ ሲሆን በአንቀጽ 11(3) ላይ መንግስት በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ  እና ሀይማኖትም በመንግስት ጉዳይ ላይ ጣልቃ እንደማይገባ ይደነግጋል፡፡ የእዚህ ንዑስ አንቀጽ ዋነኛ አላማ ከህገ መንግስቱ ማብራሪያ መረዳት እንደሚቻለው ሀይማኖትን ከመንግስት ጣልቃ ገብነት እና ከፖለቲካ ጫና ነጻ እንዲሆን በማድረግ የዜጎችን የእምነት ነጻነት ላለመገደብ ሲሆን መንግስት በሀይማኖት ተቋማት መንፈሳዊ ስራ ላይ ጣልቃ መግባት እንደሌለበት ይገልጻል፡፡ በተጨማሪም መንግስት የማህበረሰቡን ደህንነት እና ሰላማዊ መስተጋብር የማስከበር እንዲሁም የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለበት ከህገ-መንግስቱ አንቀጽ 13 እና ከህገ መንግስቱ ማብራሪያ አገላለጽ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህም መብት በአፍሪካ ቻርተር የግለሰቦች እና ህዝቦች መብቶች አንቀጽ 8 ላይ ተደንግጎ ይገኛል፡፡

የሰብዓዊ መብቶች ዓለም አቀፍ መግለጫ እና የሲቪልና የፖለቲካ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃልኪዳን አንቀጽ 18 ላይ ማንኛውም ሰው የሀሳብ፣ የህሊናና የሀይማኖት ነጻነት እንዳለው ይደነግጋሉ፡፡

የኢሰመጉ ጥሪ፡ 
 ሀይማኖት የማህበራዊ መስተጋብር አንዱ ክፍልና መብት በመሆኑ መንግስት የማህበረሰቡን ሰላማዊ እንቅስቃሴ የማስጠበቅ ኃላፊነት እንዳለበት  በመረዳት የፌደራል እና የክልል መንግስታት የዜጎችን ደህንነት እንዲያስከብር፣

 የፌደራል መንግስት እንዲሁም የክልል መንግስታት እና በዋናነት ችግሮች እየተፈጠሩበት ያለው  የኦሮሚያ ክልል መንግስት የጸጥታ አካላት  በቤተክርስቲያን እውቅና ያልተሰጣቸውን ኤጲስ ቆጶሳት በተለያዩ አብያተክርስቲያናት መመደብ አግባብ አይደለም በማለት የተቃወሙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ላይ የሚፈጽሙትን ከህግ አግባብ ውጪ የሆነ ግድያ፣ አካል ማቁሰል፣ ድብደባ እና እስር እንዲያቆሙ እንዲሁም ከቅዱስ ሲኖዶስ በተላለፈው መልእክት መሰረት ጥቁር ልብስ የለበሱ ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ እስሮች እና ድብደባዎችን እንዲያስቆም፣ ከህግ  አግባብ ውጪ ግድያ፣ እስራት፣ ደብደባ እና ሌሎችም የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የፈጸሙ የጸጥታ አካላትን መንግስት በህግ ተጠያቂ  እንዲያደርግና ይህንንም ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ እንዲሁም ጉዳዩ መፍትሄ እንዳያገኝና ወደ ግጭት እንዲቀየር ለማድረግ ነገሮችን ወደ ሌላ አቅጣጫ የሚስቡ አካላት ሁሉ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኢሰመጉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
3.2K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), edited  16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 19:58:03 ከሀይማኖት ጋር ተያይዞ ባለው ወቅታዊ የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ከኢሰመጉ የተሰጠ መግለጫ

የኢሰመጉ አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ-ጥር 30/2015 ዓ.ም
2.8K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 10:40:30 እግዚአብሔር መልካም ነው በመከራ ቀን መሸሸጊያ ነው



4.1K viewsDrshaye Akele, edited  07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 08:16:15 «እኔን ብትጥሉኝ ሀገሩ ሰላም ይሆናል!»
°°°°°°°━✦•✧༒✧•✦━°°°°°°°
በደወሉ ተቀስቅሰን ነቅተን ይሆን?

ዮናስ ሆይ "ምንት ያነውመከ?"
↳ “ ምነው ተኝተሃል? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ” እንጂ (ቁ. ፮)

ያ… ከእግዚአብሔር ርቆ እግዚአብሔርም ርቆት ምሕረት እያባረረ መዓት የሚጠራ ዮናስማ እኛ ነን።

ዛሬ ላይ የደረሰብንና የደረስንበትን ጥፋት በማጤን ብናየው ሌሎቹ ስተውና አሳስተው የመጣ ሳይሆን እኛው ባለማዕተቦቹ አጥፍተንና ጠፍተን ያመጣነው ለመሆኑ እንደ ነቢዩ ዮናስ በላያችን የወጣብን ዕጣ ያሳብቃል፤

ከሁሉ በተለየ እግዚአብሔርን አውቃለሁ በእግዚአብሔርም እታወቃለሁ የምንል ግን በሁከቱ መኃል ከጾምና ከጸሎት ርቀን ተኝተንና ነፋስ በሚጠራ ወጀቡን በሚያጠነክር ዘመቻ ተጠምዶ ወደ ውሥጠኛው የጎጥ ⇨ የዘር ⇨ የነገድ ⇨ የዜግነት ክፍል ወርደን ከባድ እንቅልፍ ጥሎናል!

በአንቂ ስብከትና በአነቃቂ ንግግር (motivational speech & Inspirational sermon) ከተኛንበት ነቅተናል የምንል ዮናሶች ሆይ ከእንቅልፋችን ስንላቀቅ ምን ብለን ምን አድርገን ይሆን?

◆ ዮናስን ቀስቅሰው ፭ ጥያቄ ጠይቀውታል “ ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እባክህ ንገረን፤ ሥራህ ምንድር ነው? ከወዴትስ መጣህ? አገርህስ ወዴት ነው? ወይስ ከማን ወገን ነህ? አሉት።” 【 ዮና ፲፥፰】

ከ፭ቱ ለ፬ቱ ምላሽ ሠጠ አንዱን ግን አልፎታል ፦ ሊቃውንቱ “አይቴ ብሔርከ ላሉት ግን አይመልስም” ይላሉ።

ያኛው ዮናስ ዮናስ "ባህርና የብሱን የፈጠረ የሰማይን አምላክ እግዚአብሔርን አመልካለሁ …" ይላል እንጂ እንደዚህኛው ዮናስ ጠቅላይ ቤተክህነቱን በጎጥ እሳት ፣ ቅዱስ ሲኖዶሱንም በዘር ምድጃ ላይ ጥዶ «የዚህን ሀገር፣ የዛኛውን ሰፈር የዚህን መንደር እግዚአብሔር ነው የማመልከው» አላለም። (ቁ ፱)

◆ ያኛው ዮናስ ስለችችሩ ምንጭ "አነ አእመርኩ ከመ በእንቲአየ መጽአክሙ ዝንቱ ማዕበል ዐቢይ ⇨ ይህ ታላቅ ማዕበል በእኔ ምክንያት እንዳገኛችሁ አውቃለሁ … " አለ እንጂ እንደዚህኛው ዮናስ «ይህማ የመጣብን በነእንትና ስውር አጀንዳ ፣ በእነ እገሌ ሤራ ፣ በነ እገሊት ሸፍጥ… ነው» አላለም (ቁ ፲፪)

◆ ያኛው ዮናስ ስለመፍትኼው "ንስኡኒ ወወርዉኒ ውስተ ባህር ወየኀድገክሙ ⇨ (እኔኑ) አንሥታችሁ ወደ ባሕር ጣሉኝ፥ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል" አለ እንጂ እንደዚህኛው ዮናስ «በሌሎች ድካምና ስንፍና በእናንተ በደልና ኃጢዓት ይህ ሁሉ በመምጣቱ እነርሱ ቢወገዱ እናንተ ብትጠፉ ችግሩ ተወግዶ መከራው ጠፍቶ መረጋጋት ይሰፍናል» አላለም (ቁ ፲፪)

ብቻ ከዚያኛው ዮናስ ይልቅ ይኼኛው ዮናሶች እጅግ እናሳዝናለን! በጎጥሸ እሳት በዘር ምድጃ ላይ እንደተኛን ነው የምንሰበከው ፣ ዛሬም የሸዋና የጎጃም ሲኖዶስ እያልን ነው የምንጾመው

ሰው ከዚህ አደንዛዥ የዘረኝነት እንቅልፍ ሳይነቃ ፣ ከዚህ ከፋፋይ የጎጥ ቅዠት ሳይባንን ቢጾምና ቢጸልይ ፣ ቢሰበክና ቢማር ፣ ቢሰብክና ቢያስተምር … ጥቅሙ ምንድነው? የተነገረውን አድምጦ እንዴት በልቡ ሊያኖረው ይቻለዋል?

እስኪ መጀመሪያ የተኛ ይንቃ ⇨የነቃ ደግሞ ይማር ⇨ ከዚያ የተማረ ደግሞ ይሰበክ ።

ጠቢቡም ቀዳሚ ሊሆን ስለሚገባው ተግባር እንዲህ ይላል

" አንቅሆ እምዐቢይ ንዋም ለዘይነውም !"
【የተኛ ሰውን ከጽኑ እንቅልፍ ቀስቅሰው】ከዚያ አስተምረህ ከስንፍና ለየው ስንፍናውን በእውቀት ሲረታው ከስሜት ርቆ ይሰበክልሃል። ያለዚያስ?

… ያለዚያማ

"ዘይነግሮ ለአብድ ከመ ዘይነግሮ ለድቁስ ፤ ወሶበ አኅለቀ ነጊሮቶ ይብለከ ምንተ ትቤ ? ⇨ ለሰነፍ ሰው የሚነግር (የሚሰብክ) ሰው ለተኛ ሰው እንደሚነግር ሰው ነው ነግረኸው ከጨረስህ በኋላ ምን ተናገርህ? (ምን ነበር ያልከው?) ይልሃል።" 【ሲራ· ፳፪ ፥፰】

አያሌ «የማኅበረሰብእ አንቂዎች» እየተፈራረቁ በአግባቡ እንዳንተኛ እያባነኑንና በአግባቡ እንዳንነቃ እያቃዡን ከእምነት አጣልተው ወይ ኑሯችንን ሳናልም ወይ ደግሞ ሕልማችንን ሳንኖር እንድንዳክር ጋርደውናል።

አዝማሪው
«የተኛን ቀስቅሶ በማርዳት የለፋ
መች ቀብር ይሄዳል ጡሩምባ ሚነፋ?» ብሏል

"ጥሩምባ ነፊ ቀብር አይሔድም" እያሉ ቀስቃሾቹ ተኝተው፣ አንቂዎቹም ፈዘው ቢገኙ ተያይዞ ማለቅ ነው። ብቻ የነቃ ቀስቃሽ ከደብሩ ፡ ያረዳ አልቃሽ ከቀብሩ ብናይ ሸጋ ነበር።

ከመአቱ እንዲመለስ መቅሰፍቱንም እንዲያስወግድልን የምንችል ነነዌን ከጥፋት መንገድ እናውጣት ካልቻልን ራሳችን ከነነዌ እንውጣ፤ የሆነለት ሌላውን ከጥፋት ለይቶ ለማዳን ይድከም ያልሆነለት ስለራሱ ነፍስ ከመጥፋት ተለይቶ ከነነዌ ይውጣ።

"ነብዩ ዮናስ የተናገረው ነገር ያለውድ በግድ ይደረጋልና ልጄ አሁንም ከነነዌ ውጣ።" 【ጦቢ ፲፬፥፰】

ቴዎድሮስ በለጠ ጥር ፳፱ ነነዌ ፳፻፲፭ ዓ.ም.
6.7K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-06 08:16:11
4.9K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-05 08:43:28 ደወል የጠራቸው ደውሎቻችንን በዚህ የሰማይ አክሊል ዋጋ መንገድ እንድንከተላቸው የበቃን ሁላችንን ያድርገን !

【 በቴዎድሮስ በለጠ ጥር አማኑኤል ፳፻፲፭ ዓ.ም. 】

☞ የቤተክርስቲያንን ድል አድራጊነት የሰማዕቱን ክብር የሚገልጥ ይህን ሥዕል ለላከልኝ ሠዓሊ ኃይለማርያም ሽመልስ ምስጋናዬ ላቅ ያለ ነው!
3.9K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ