Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.52K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-04 19:04:43 ለትዳር፣ ለጓደኝነትና አብሮ ለመስራት ፈፅሞ ልንመርጣቸው የማይገባን መርዛማ ማንነት ያላቸው ሰዎች።

መልካም ንባብ ሙሉውን ለማንበብ

https://t.me/+W9O6R7LFFZk2NmNk
1.2K viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 16:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 09:56:07 Channel photo updated
06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 09:55:47 ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና

ስለእውነት ነው የምላችሁ በደንብ አንብብ በስተመጨረሻ የምታገኙት የመንፈስ ጥንካሬ እንዲህ ነው ማለት አልችልም ብቻ እንድታነብ የእግዚአብሔር ፈቃደ በእናንተ ላይ ይሁን።

ምዕራፍ አንድ ማን ነበርኩ?

ናህድ  ማሕሙድ ሙትዋሊ እባላለሁ። ሴቶችን ብቻ የሚያስተምረው የሄልሜት ኤል ዘይቱን ትምህርት ቤት ዲን ነበርኩ...ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ

ተጻፈ በስነልቦና አማካሪ bini girmachew
@Orthodox_sibket
@Orthodox_sibket
@Orthodox_sibket
1 viewሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:48:38 ሁኔታ እንዲፈቱ እየጠየቅን ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ቤተ ክርስቲያን መብቷን ለማስከበር ወደ ቀጣይ እርምጃዎች የምትገባ መሆኑን በአክብሮት እያሳወቅን ይህንንም ድርጊት ተከታትሎ የሚያሳውቅ እና የሚያስፈጽም የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ወደሥራ እንዲገባ የሚደረግም መሆኑን ጭምር እናሳስባለን፡፡

በዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት የሊቀ ሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር በመምጣት ሕይወቱን ላጣው ልጃችን እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሃም፣ በያዕቆብና በይስሐቅ እቅፍ ያኑር፣ ለቤተሰቦቹም መጽናናትን ያድልልን እያልን ቀላልም ሆነ ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባችሁ የቤተ ክርስቲያን የጭንቅ ቀን ልጆች ደማችሁን እና መከራችሁን እንደ ሰማእታት ዋጋ ይቆጥርላችሁ ዘንድ ጸሎታችን ነው፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
1.4K viewsDrshaye Akele, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:48:38 "የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡" ብፁዕ አቡነ ሄኖክ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ላይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት የተፈጸመውን ሕገ ወጥ ድርጊት አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከሀገራችን ኢትዮጵያ ሀገረ መንግሥት ምሥረታ ጀምሮ ያለችና መንግሥትን ያጸናች፣ የራሳቸው የጽሑፍ ቋንቋ ካላቸው ጥቂት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ እንድትሆን ፊደል ቀርፃ ያስተማረች፣ መንግሥት የአረንጓዴ አሻራን መርሐ ግብር ከማስጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት የአካባቢ ጥበቃን ስትሠራ የኖረችና አሁንም በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ ገዳማትና አድባራት የአካባቢ ጥበቃ ሥራን የምትሠራ፣ ዘመናዊ ትምህርት ከመጀመሩ ከሺህ ዓመታት በፊት ሥርዓተ ትምህርት ቀርፃ ያስተማረችና የሀገር መሪዎችን፣ የስነ ህንፃ ባለሙያዎችን፣ የመድኃኒት አዋቂዎችንና ተመራማሪዎችን ያፈራች ቤተ ክርስቲያን ከመሆኗም በላይ ተቋም መሥርታ ለዘመናት የተቋምን ምንነት ያስተማረች ራሷ ሀገር የሆነች ናት፡፡

በተለይም ደግሞ መላው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ ግዛት በተያዙበት፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያንም ለመቀራመት ተስማምተው በፋሺስቱ የኢጣልያ መንግሥት አማካኝነት ሀገራችንን በወረረበት ጊዜ የንጉሱን የክተት አዋጅ ተከትሎ ሕዝቡ ለነፃነቱ እንዲዋደቅ የሀገር ፍቅር ለምእመኗ ያስተማረች በመሆኑ እና የንጉሱም ጥሪ ሀገራዊ ብቻ ሳይሆን ሃይማኖትን የመጠበቅ ጥሪም የነበረ በመሆኑ ሕዝቡ በነቂስ ወጥቶ ንጉሱን እንዲከተል ከማድረጓም በላይ ታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስን በካህናቱ አጅባ የጦር ግንባር ድረስ በመዝመት፣ ምእመኑን እና ህዝቡን በማጽናናትና ጸሎተ ፍትሀት በማድረግ በዓድዋ ጦርነት ኢትዮጵያ ሀገራችን ድል እንድትቀዳጅና ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነፃነት አርማ እንድትሆን በማድረግ ትልቁን የታሪክ ድርሻ እንደምትወስድ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡
ከዚህ የድል በዓል በኋላም ኢትዮጵያ በነፃነት በቆየችባቸው ዓመታት ሁሉ ይህን የአድዋ የድል በዓል ቤተ ክርስቲያን የሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦተ ሕግ ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ሕዝቡን በመባረክ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በታላቅ ምሥጋና እና መዝሙር በመላ ሀገሪቱ ስታከብረው የኖረች፤ ወደፊትም እየፈጸመች የምትጸናበት አኩሪ ታሪኳ ነው፡፡

ይሁን እንጂ ይህ በዓል ላለፉት ጥቂት ዓመታት የድል በዓል መሆኑ ቀርቶ የጠብ እና የጥላቻ በዓል እየሆነ መምጣቱ ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ ያሳዘነ ተግባር ሆኗል፡፡ በተለይም ትላንት የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተከበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል በቤተ ክርስቲያን ላይ የአድዋ የድል በዓልን አስታኮ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው እጅግ አሳዛኝ ድርጊትን ግን ቤተ ክርስቲያን ሰምታና አይታ በዝምታና በሐዘን ብቻ የምታልፈው ጉዳይ አልሆነም፡፡

በየካቲት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓል ለማክበር ህዝቡ ከየቤቱ ተሰባስቦ ከጠዋቱ ፫፡፲፭ ላይ ታቦተ ሕጉ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከመንበረ ክብሩ ወጥቶ ዑደት ካደረገና ሕዝቡን ባርኮ በዐውደ ምህረቱ ላይ ከቆመ በኋላ ሊቃውንቱ ያሬዳዊ ወረብ በማቅረብ ላይ እንዳሉ ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ልዕልናን ተላልፈው በሰሜን በኩል ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ፪ ጊዜ በተኮሱት አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የንግሥ በዓሉ በመረበሹ በዓሉ ተቋርጦ ከጠዋቱ ፬ ሰዓት ላይ ታቦተ ሕጉ ወደ መንበሩ ተመልሷል፡፡ በዚህም ምክንያት እስከአሁን በደረሰን መረጃ መሠረት በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ከፍተኛ ረብሻ በመፈጠሩ ምክንያት ፩ ምእመን በተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ ታፍነው ሕይወታቸውን ማጣታቸውን፣ አገልጋይ ካህናት አባቶች፣ ምእመናን እና ምእመናት ከፍተኛ የሆነ አካላዊ እና ሥነ ልቡናዊ ጉዳት ደርሶባቸዋል፤ ከ፲፭ ያላነሱ የሰንበት ትምህርት ቤት አገልጋይ ተማሪዎች በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡

ይህ ድርጊት ከተፈፀመ በኋላም መንግሥት የቤተ ክርስቲያኒቱን ክብርና ልዕልና በመዳፈር በቤተ ክርስቲያን ላይ ይህን በደል የፈፀሙ የጸጥታ መዋቅር አካላትን ለሕግ ያቀርባል፣ እንደ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወጣል ብለን ብንጠብቅም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ በዓሉን አስመልክቶ በዕለቱ ባወጣው መግለጫ ችግሩን የፈጠሩት አካላት ‹‹የአደባባይ በዓሉን ለመረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል፡፡ የጸጥታ መዋቅሩ ችግሩን ለመቆጣጠር በወሰደው እርምጃ ጉዳቱን ለመቀነስ ችሏል›› ሲል የችግሩን ሁኔታ ገልጧል፡፡

በዚህ መግለጫውም ላይ አሁንም ችግሩ የሌሎች ቡድኖች እንደሆነና የቤተ ክርስቲያኒቱን በዓል የረበሸው የእነዚህ አካላት እንቅስቃሴ ነው በማለት የሰጠው መግለጫ በቦታው ላይ ከነበረው እውነታ በእጅጉ የራቀ እና ድርጊቱ የተወሰኑ ግለሰቦች ሳይሆን የመንግሥት እውቅና ያለው መሆኑን እንዲሁም መንግሥት ችግሩን ለማረም እና መፍታት ፍላጎት የሌለው መሆኑን እንድንረዳ አድርጎናል፡፡ የቤተ ክርስቲያን በዓል እንዲረበሽ እና ምእመናን ሕይወታቸውን እንዲያጡ እንዲሁም እንዲጎዱ ያደረገው ከመንግሥት የጸጥታ መዋቅር የተተኮሰው አስለቃሽ ጭስ እና ጥይት መሆኑ ለሁሉም የታወቀ ሆኖ እያለ ጉዳዩን ወደ ሌላ አካል ለማላከክ የተሄደበትን ርቀት ቤተ ክርስቲያን በፍፁም የምትቀበለው አይሆንም፡፡

የመንግሥት የጸጥታ አካል በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ምእመናን ላይ ጉዳት ሲያደርስ እና የቤተ ክርስቲያንን ክብር ሲያጎድፍ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ በጥር ፩ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም በቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰቡ ምእመናን ላይ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ ውስጥ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ብዙ ምእመናን እንዲጎዱ የተደረገ ሲሆን በጊዜው መንግሥት ይህን ድርጊት በፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ ከመውሰድ ይልቅ ልክ እንደአሁኑ ችግሩ የሕገ ወጦች ነው በማለት ለድርጊቱ እውቅና ሰጥቶት አልፏል፡፡ በዚህ ድርጊት መንግሥት በጸጥታ መዋቅሩ ውስጥ ያሉ እና መንግሥትንና ሕዝብን እንዲሁም ተገቢ ያልሆነ ያለመግባባት የሚያባብሱትን ግለሰቦች እና አመራሮች ለይቶ እርምት ከመውሰድ ይልቅ ሕዝብና መንግሥትን ሆድና ጀርባ የሚያደርግ ተግባሩን አስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡

በመሆኑም መንግሥት ለዘመናት የኖረች እና ከግማሽ የሀገሪቱ ሕዝብ በላይ የያዘችን ቤተ ክርስቲያን ክብርና ልዕልና በሚዳፈር መልኩ በተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር ላይ የተሳተፉ እና ይህን ድርጊት የፈጸሙ የጸጥታ አካላትና እንዲፈፀም ያዘዙ የመንግሥት ኃላፊዎችን በ፲፭ ቀናት ጊዜ ውስጥ ለይቶ በሕግ እንዲጠየቁ እንዲያደርግ እና ይህንንም ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሆነ ለሕዝበ ክርስቲያኑ በግልጽ እንዲያሳውቅ እንዲሁም በተለመደው የሐሰት ውንጀላ በዓላችንን በማክበር ላይ እያሉ የመንግሥት የጸጥታ አካላት በፈፀሙት ሕገ ወጥ ተግባር ምክንያት በተፈጠረው ግርግር መነሻት የታሰሩ ምእመናንን ያለምንም ቅድመ
1.4K viewsDrshaye Akele, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 20:48:28
1.2K viewsDrshaye Akele, 17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-03 16:42:42 የንስሃ መንገዶች
በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

አምስት የንስሃ መንገዶች አሉ ። የተለያዩ ቢሆኑም ቅሉ ሁሉም የሚያደርሱት ግን ርስት መንግስተ ሰማያት ነው ። እነርሱስ ምን ምን ናቸው ? ያልከኝ እንደሆነ እንድህ ብየ እመልስልሃለሁ፦

፩ኛ • የመጀመሪያው መንገድ "የራስን ኃጢአት ማመን፣ መጥላትና ማውገዝ ነው።

ይኽውም ልዑል ቃል ኢሳይያስ "እንድትጸድቅ መጀመሪያ ኃጢአትህን ተናገር እንዳለው" (ኢሳ 43 ፥26 )፤ ክቡር ዳዊትም "በደሌን አልሸፈንኩም፤ ለእግዚአብሔር መተላለፌን እንግራለሁ አልሁ ፤ አንተም የልቤን ኃጢአት ተውኽልኝ" ብሎ እንደተናገረ መዝ 31፥5 ስለዚህ አንተም ስለ ሰራኽው ኃጢአት እራስህን ውቀሰው። በዚህ እግዚአብሔር ይቅር እንዲልህ ታደርገዋለህና። ይህ ብቻ ሳይሆን ስለ ኃጢአቱ እራሱን የሚወቅስና ኃጢአቱን የሚኮንን ሰው በተመሳሳይ ኃጢአት በቀላሉ አይወድቅምና። ስለዚህ በጌታ የፍርድ ዙፋን የሚወቅስህ እንዳይኖር ዛሬ እውነተኛ ወቃሽ በኾነው ሕሊናህን አንቅተህ በራስህ ላይ ወቃሽና ከሳሽ አድርገህ ሹመው። ይህ አንዱና ደገኛው መንገድ ነው ።

፪• ሁለተኛው የንስሐ መንገድ ደግሞ
የወገኖቻችንን በደል ይቅር ማለትና በበደሉህ ላይ ቅሬታና ቂም አለመያዝ ነው።

እንዲህ ስናደርግ "ለሰወች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ የሰማዩ አባታችሁ  እናንተንም ደግሞ ይቅር ይላችኋል" እንዲል እኛ በጌታችን ላይ ያደረግነውን በደል ይቅር እንባላለንና። ማቴ 6 ፡14

፫• ሦስተኛውን የንስሃ መንገድ መንበረ ጸባዖት የደርስ በትጋትና በጥልቅ ስሜት የሚደረግ "ከልብ የመነጨ ጸሎት ነው"

ጨካኙ ዳኛ እንዲርፈድላት ያደረገችው ያች መበለት እንዴት እንዲፈርድላት እንዳደረችገው አታያትም? ( ሉቃ 18፥3) አንተ ግን ሩኅሩኅና  መሐሪ የኾነ ጌታ ነው ያለህ። እርሷ በጠላቶቿ ላይ እንዲፈርድላት ነው የጠየቀችው፤ አንተ ግን እምትጠይቀው ስለራስህ ድኅነት ነው።

፬• አራተኛ መንገድ አለ እርሱም "ምጽትዋ ነው " ይህም እጅግ በጣም ታላቅ የኾነ ኃጢአትን የሚስተርይ ኃይል አለውና።

ናቡከደነጾር ኃጢትን ንቅስ ጥቅስ አርድጎ ወደ ክኅደት ሁሉ በገባ ጊዜ እንድህ ብሎታልና፦ "ንጉስ ሆይ ! ምክሬ ደስ ያሰኝህ ኃጢአትህም ለጽድቅ በደልህን  ለድኾች በመመጽወት አስቀር" (ዳ.ን 3፥27 ) ይህ ቸርነትና ሰውን መውደድስ ምንስ ይስተካከለዋል? እንዴት ያልከኝ እንደሆነ ስፍር ቁጥር የሌለውን ኃጢአት ከሰራ በኋላ ከዚያ ኹሉ በደል በኋላ እንደርሱ ለሆኑ ሰወች ርኅራኄን ቢያደርግ ከተገዳደረውና ከተጣላው አምላክ ጋር መታረቅ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታልና ።

፭• አምስተኛው መንገድ "እንዲሁም ትሕትናና እራስን ማዋረድ ኃጢአትን ያደክማል"

ይህንንም ቀራጩ ያረጋግጥልናል አይኖቹን ወደ ሰማይ ለማንሳት እንኳንስ እስኪፈራ ድረስ በታላቅ ትሕትና ራሱን ባዶ ባደረገ ጊዜ "ጻድቅ ሆኖ ሄደ ተብሏልና ።(ሉቃ 18፥13) ስለዚህም ምንም ምግባር ቢኖርህም እንኳን በደልህን ከመናር በቀር በጎ ምግባርህን አታስበው። ያን ጊዜ እግዚአብሔር የበደል ሸምክህን ያራግፍልሃል።

ስለዚህ እነዚህን መንገደኞች ተመላለስባቸው እንጅ ሰነፍ አትኹን ።
479 viewsDrshaye Akele, 13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-24 20:06:36 በውጪ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በዚህ በፆም ወቅት ሙሉ ቅዳሴ በዜማ ከጽሑፍ ጋር በንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ የዩቲዩብ ቻናል ያገኙታል ያዳምጡ ተሰጥኦውን ይመልሱ
             








1.0K viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-23 20:44:08 በውጪ ሀገር እና በሀገር ውስጥ ለምትገኙ ውድ ኦርቶዶክሳዊያን በዚህ በፆም ወቅት ሙሉ ቅዳሴ በዜማ ከጽሑፍ ጋር በንቁ የቤተክርስቲያን ድምፅ የዩቲዩብ ቻናል ያገኙታል ያዳምጡ ተሰጥኦውን ይመልሱ
             








545 viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 22:25:52 ታሪክ ጌታ ከቅድስት ሰኞ ጀምሮ እስከ ዓርብ ኒቆዲሞስ ከቆመ ሳያርፍ ከዘረጋ ሳያጥፍ ዓርባ ቀን በትህርምት ጾሟል ሐዋርያት እሑድ እሑድን አውጥተው ቢቄጥሩ ጎደለባቸው አስቀድመው አምስት ቀን ጹመው ለስብከተ ወንጌል ይፋጠኑ ነበርና …

የኋላውንም ሁለት መነሻ ሊሆኑ የሚችሉ ታሪኮች ደግሞ እንዲህ ያብራራልናል።

① በኢየሩሳሌም ፎቃ በሮም ህርቃል ነገሠ ፎቃ በኢየሩሳሌም ባሉ ምእመናን መከራ አጸናባቸው ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን እኛ ላንተ እንገዛለን ብለው ወደ ሕርቃል ላኩበት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን "ግዙራን ይነሥእዋ ለመንግሥትከ" የሚል ራእይ አየ።

መንግሥቱን የሚወስድበት ኡመር ወልደ አድ እንደሆነ ባያውቅ "ግዙራን የተባሉ ሌላን እለ? አይሁድ አይደሉምን" ብሎ "ያን የላካችሁብኝ ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጅ" አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ሰባ ሰማንያ ዘመን ነው ይህንንስ እኛ እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በኢየሩሳሌም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቁትን ግን ቀድሞም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥራት አድርገው በዓመት በዓመት የሚጾሙት ሁነዋል!

② የሮም ሊቃነ ጳጳሳት ቀሳውስት ዲያቆናት ምእመናን ጹመውታል የሮሙን ንጉሥ ከፋርሱ ንጉሥ ተጋብቶ ሲኖር ሚስቱን በድሎ ሰደዳት ሒዳ ለአባቷ አንተን ያህል አባት እያለኝ በድሎ ሰደደኝ አለችው። እሱም ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብሎ ሒዶ እኔ ከሀገሩ ጠብ የለኝም ጠቤ ካንድ ሰው ነው ጠላቴን ስጡኝ ባትሰጡኝ ግን ጠቤ ከናንተ ጋራ ነው አላቸው ቢትወደዱ «ፎቃ» ይባላል ባንድ ሰው ምክንያት ብዙ ሰው እናስጠፋለን። አውጥተን እንስጥ እንጂ አላቸው። ማን ይነግሣል አሉት እኔ እነግሣለሁ አላቸው አወጥተው ሰጡት ፎቃ ነገሠ።

የጥጦስን የአስባስያኖስን ዘመን ለመመለስ በሮም ባሉ ምእመናን አገዛዝ አጸናባቸው ኋላ ባሪያውን ለማይገባ ገረፈው ህርቃልን ቢትወደድነት ሹሞት ነበረና ሔዶ በማይገባ ገረፈኝ ብሎ ነገረው አትገድለውም አለው ማን ይነግሣል አለው እኔ እነሣለሁ አለው ጊዜ አይቶ ገደለው ህርቃል ነገሠ። ከዚህ በኋላ የሮም ምእመናን መጥተው እኛም ከወገኖቻችን ካነገሥክልን ብድራችንን እንድንመልስ አይሁድን አጥፋልን ብለው አማሉት እሱም ከአይሁድ ጋራ ጨዋታ መሐላ ነበረውና ቸል ብሎ ተዋቸው ኋላ ግን ግዙራን ይነሥእዋ ለመግሥትከ የሚል ራእይ አየ ግዙራን የተባሉ ሌላ እለን አይሁድ አይደሉምን ብሎ ያን ያላችሁኝን ነገር አልረሳሁትም ነገር ግን ሐዋርያት ነፍስ የገደለ መላ ዘመኑን ይጹም ብለዋል ጾሙን ብፈራ ነው እንጂ አላቸው ያንድ ሰው ዕድሜ ቢኖር ስባ ሰማንያ ዘመን ነው። ይህነንስ #እኛ_እንጾምልሃለን አሉት መጥቶ አጥፍቶላቸዋል በሮም ያሉ ምእመናን አምስት አምስት ቀን ተካፍለው ጹመውለታል ያላወቁት አንድ ጊዜ ጹመው ትተውታል ያወቅቱ ግን ቀድሞውም ሐዋርያት ጹመውታል ብለው ሥርዓት አድርገው ባመት ባመት የሚጾሙት ሁነዋል።

ወደ እኛ የደረሰው እንዴት እንደሆነ ለማሳየትም ለመሰናዶው ሳምንት የሕርቃልነቱን ስያሜ ተቀብለው ከዐቢይ ጾም ቀድሞ ባለው ሳምንት እንዲዘከር በድንጋጌ ያጸኑ በዘመነ ሕርቃል በእስክንድርያ የነበሩ ፴፯ኛው ፓትርያርክ አቡነ አንደራኒቆስ መሆናቸውን ዜና ጳጳሳቱ ይነግረናል።

"Pope Adronicus, the 37th Patriarch of Alexandria, acknowledged this request. From that time, “Heraclius Week” began to be observed."

በአጋዥ የታሪክ ማነጻጸሪያ ደግሞ በስንክሳራችን ዕረፍቱ ጥር ፰ የሚዘከረው በቅዱስ ማርቆስ መንበር ፴፯ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ ቅዱስ አንደራኒቆስ በዘመኑ የፋርስ ንጉሥ ክስራ [Kessra the king of Persia] ከሮሙ ንጉሥ ህርቃል ጋር ስላደረገው ጦርነትና እስክንድርያ ባሉ ምእመናንም ላይ ይደርስ ስለነበረው መከራ ተከታዩን ታሪክ ይነግረናል።

«በሹመቱም ወራት ፀሐይን የሚያመልክ የፋርስ ንጉሥ ክስራ ተነሣና የሶርያንና የፍልስጤምን ከተሞች ወርሮ ዘረፋቸው፡፡ ወደ ግብጽም መጥቶ እስክንድድርያ ከተማ ደረሰ፡፡ በዙሪዋ በመነኮሳት የተሞሉ ሰባት መቶ ገዳማት ነበሩ፡፡ እነርሱም ገንዘብ ያላቸው በተድላ የሚኖሩ ነበሩ፡፡ ስለዚህም በእነርሱ ላይ እግዚአብሔር ሥልጣንን ሰጥቶት ገዳማቱን አፈረሰ፡፡ እነርሱንም ሸሽተው ካመለጡት በቀር ሁሉንም ገደላቸው፡፡ ገንዘባቸውንም ሁሉ ማረከ፡፡

የእስክንድርያ ሰዎችም ንጉሥ ክስራ ያደረገውን ባዩ ጊዜ የከተማውን በር ከፈቱለት፡፡ እርሱም ‹ይህችን አገር በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁ አታፍርሳት፣ በውስጧ ያሉትን ብርቱዎች ግደላቸው-ዐመፀኞች ናቸውና› እንደሚለው በሕልሙ አየ፡፡ በዚህም ጊዜ የሀገሩን ንጉሥ ይዞ ካሠረው በኋላ ለሀገሩ ሰዎች ‹‹በጦር ሠራዊት አደራጃቸዋለሁና ከ18 ዓመት ጀምሮ ያሉትን ብርታት ያላቸውንም ሁሉ ሰበስቡልኝ፣ ለእያንዳንዳቸው ደመወዛቸውን 20 የወርቅ ዲናር እከፍላለሁ›› አላቸው፡፡ ሕዝቡም ሁሉ እውነት ወርቅ የሚቀበሉ መስሏቸው 8 ሺህ ብርቱዎችን ቆጥረውና መዝግበው በሰጡት ጊዜ ንጉሡ ክስራ ሁሉንም በሰይፍ ገደላቸው፡፡ ወደላይኛው ግብጽ በመሄድም ኒቅዮስ ደርሶ ሰባት መቶ በሥራቸው ክፉ የሆኑ መነኮሳትን በሰይፍ ገደላቸው፡፡ የሮም ንጉሥ ሕርቃልም የፋርሱ ንጉሥ ክስራ ያደረገውን በሰማ ጊዜ ሠራዊቱን ሰብስቦ መጥቶ ንጉሥ ክስራን ከነሠራዊቱ ሀገሩንም ጭምር አጠፋቸው፡፡ ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የአባ እንድራኒቆስ ገድሉ እጅግ ያማረ ነበር፡፡ … »

ሕርቃል ከአርመናውያን ቤተሰቦች በ575 ዓ.ም. በቀጰዶቅያ ተወልዶ በ641 ዓ.ም. በቁስጠንጥንያ ያረፈ በእምነቱም የመለካውያኑ (Chalcedonian Christianity) ተከታይ የነበረ የሮማውያን ንጉሥ ቢሆንም ካቶሊካውያኑ የእኛውን ንጉሥ አፄ ካሌብን [Saint Elesbaan] በቅድስና እንደሚዘክሩት «ምንም አንድ አካል ሁለት ባሕርይ በማለት ብንለያይ ወረደ ተወለደ በማለት አንድ ነንና መጥተህ አጥፋልን» ብለው ደጅ ለጠኑት በእስክንድርያ እና በኢየሩሳሌም ለነበሩ ምእመናን ባለውለታ በመሆኑ ኦርቶዶክሳውያኑ የልዩነት ድንበሩን ጠብቀው ሲያከብሩት ኖረዋል።

የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ሰላም ፣ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያም ፍቅርና የኢየሱስ ክርስቶስ የረድኤቱ ሀብት የቅዱስ መስቀሉም ሞገስ ሁል ጊዜ ለዘለዓለሙ ከሁላችን አይራቅ!

ከሰሙነ ሕርቃል በረከት ያሳትፈን!

reposted from ቴዎድሮስ በለጠ መጋቢት ልደታ ፳፻፲፫ ዓ.ም. ተጻፈ
581 viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ