Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የቴሌግራም ቻናል አርማ orthodox1 — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
የሰርጥ አድራሻ: @orthodox1
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 38.52K
የሰርጥ መግለጫ

✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ
ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye
ማናገር ይችላሉ
🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹
Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-04-16 04:40:12 እግዚአብሔርን የሚያምንና የሚወድ ቢኖር፥ እርሱ በዚህ አንፀባራቂና የደስታ በዓል ደስ ይበለው፡፡ ብልህ አገልጋይ ቢኖር፥ እርሱ ወደ ጌታው ሐሴት ገብቶ ዕልል ይበል፡፡

በጾም የደከመ ቢኖር፥ አሁን ደመወዙን ይቀበል፡፡ በመጀመሪያው ሰዓት ወደ አምላኩ የቀረበ ቢኖር፥ ዛሬ ሽልማቱን ይውሰድ፡፡
በሦስተኛው ሰዓት የመጣ ቢኖር፥ እርሱ በዓሉን በምስጋና ያክብር፡፡  በስድስተኛው ሰዓት የደረሰ ቢኖር፥ አይጎድልበትምና አይጠራጠር፡፡ እስከ ዘጠነኛ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ሳይጠራጠር ይቅረብ፡፡ እስከ ዐሥራ አንደኛዋ ሰዓት የዘገየ ቢኖር፥ ስለ መዘግየቱ አይደንግጥ፡፡ ጌታ ቸር ነውና፤ በመጨረሻ የመጣውንም እንደ መጀመሪያው አድርጐ ይቀበሏልና፡፡ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ለመጣው ከመጀመሪያው ሰዓት አንሥቶ ሲደክም ከነበረው ጋራ እኩል ይሰጧልና፡፡
መጨረሻ ለመጣው ጌታ ምሕረቱን ይለግሰዋል፤ መጀመሪያ ለመጣውም ያስብለታል፡፡ ለአንደኛው ይሰጠዋል፤ ለሌላኛውም ጸጋውን ያድለዋል፡፡ ለአንደኛው መልካም ምግባሩን ይቀበልለታል፡፡ ለሌላኛውም መልካም ፍቃዱን ይቀበልለታል፡፡ ለአንዱ ምግባሩን ያከብርለታል፤ ለሌላኛውም በቅን ልቡና የሚያደርገውን ጥረት ያደንቅለታል፡፡ ስለዚህ ኹላችሁም ወደ ጌታችሁ ደስታ ግቡ፡፡

ፊተኞች ኋለኞችም ሆይ! እኩል ደመወዛችሁን ተቀበሉ፡፡ ባለጸጐች ድኾችም ሆይ! በአንድነት ዘምሩ፡፡ እናንተ ብርቱዎች ደካሞችም ሆይ! በዓሉን አክብሩት፡፡ እናንተ የጾማችሁ መጾም ያልቻላችሁም ሆይ! ዛሬ ላይ ደስ ይበላችሁ፡፡
መሠዊያው ሙሉ ነውና ኹሉም በማዕዱ ደስ ይበለው፡፡ ፍሪዳው የሰባ ነውና አንድ ሰው ስንኳ እንደ ተራበ እንዳይሔድ፡፡ ኹላችንም የእምነት በዓሉን እንካፈል፤ ከቸርነቱና ከፍቅሩ ሀብትም እንቋደስ፡፡

ማንም ስለ ድኽነቱ አይዘን፥ ኵላዊቷ መንግሥት ተገልጣለችና፡፡ ማንም በኃጢአቱ አያንባ፥ ከመቃብሩ የይቅርታ ብርሃን ተንቦግቧልና፡፡ ማንም ሞትን አይፍራ፥ የመድኃኒታችን ሞት ከዚህ ነጻ አውጥቶናልና፡፡ ለእርስዋ  በመታዘዝም ጌታ አጥፍቷታልና፡፡
በሞቱ ሞትን ገደለው፡፡ ወደ ሲዖል በመውረድ ሲዖልን በዘበዘው፡፡

ኢሳይያስም አሰምቶ እንደ ተናገረ ሲዖል ከጌታችን ጋር ፊት ለፊት ተገናኘች፤ መረራትም! ከንቱ አድርጓታልና መረራት! ሸንግሏታልና መረራት! ሽሯታልና መረራት!
ነፍሳትን ይዛ እንዳታስቀር አስሯታልና መረራት!
[መቃብር የዕሩቅ ብእሲ] ሥጋ አገኘሁ ብላ ዋጠችው፤  ስትውጠው ግን እግዚአብሔር ኾኖ አገኘችው - መረራትም!

ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


╭══•:|★✧♡ ♡✧★|: ══╮
  @orthodox1 @orthodox1
  @orthodox1 @orthodox1
  @orthodox1 @orthodox1
╰══•:|★✧♡ ♡✧★|:  ══╯
257 viewsDrshaye Akele, 01:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 20:38:54 ከልቤና ከሰውነቴ የክፋት መንፈስን ሁሉና የተናቀ ነገር ማሰብን አስወግድ ። ልቡናዬንም የጸሎት ቤት አድርገው፤ ልቤንና ሐሳቤንም ስምህን ለማክበርና ለማመስገን አንቃቸው። …]

አሜን! ሆሣዕና በአርያም

【 . . ከቴዎድሮስ በለጠ Яερ๑รтεδ ƒя๑๓ ሆሣዕና ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም. 】
1.6K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 20:38:54 ገዳማዊው አባ ዳንኤል መታበይ ሲመጣበት ሔዶ ያየው ዘንድ እግዚአብሔር ወደ ንጉሥ አኖሬዎስ ልኮታል፤ ተወዳጁ ንጉሥ ሰሌን በመታታት በዘንባባ ቅጠል ምንጣፍ በመሥራት ይደክም ሸጦም ይመጸውት እንደነበር አይቶ ተምሯል (ስንክሳር ዘሕዳር ፲፮)

ታላቁ አባ ሙሴ ዘደብረ ሲሐት ልብሱ ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነበር (ስንክሳር ዘመስከረም ፫)

በሌላ መንገድ ደግሞ በዘመነ ሰማዕታት ዘንባባው የክብር መቀበያ ከሥጋ ድካም የማለፋቸው ምክንያትም የሆነላቸውን ቅዱሳንም እናገኛለን። ከነዚህም ውሥጥ በሚያዝያ ወር የሚዘከሩ በሰማዕትነት ያረፉ ቅዱስ በብኑዳና ቅድስት ኮሮና (እሥጢፋና) በዘንባባ ላይ ተሰቅለው በዘንባባ መኃል ታሥረው ለክብር መብቃታቸውን የታሪክ መድብላችን ይመሰክራል።

ሰላም እብል ለበብኑዳ ሰማዕት፣… ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳】

ሰላም ለእስጢፋና እንተ ፃመወት በሕቁ፡
ለፊቅጦር ሰማዕት ተላዊተ ዐሠሩ ወጽድቁ፡
እለ ኰነንዋ ሐራ እስከ እምፍርሀት ወድቁ፡
በጒንደ በቀልት ዘአስተላጸቁ፡
ማኅፈቀ ሥጋሃ ለ፪ኤ ሠጠቁ፡፡ [የሰማዕቱ ፊቅጦርን ፍለጋና እውነት (ሕይወትና ሃይማኖት) የተከተለች የፈረዱባት ጭፍሮች ፈርተው እስከሚወድቁ ድረስ፤ በሰሌን ዛፍ በዘንባባ ግንድ ላይ አሥረዋት ሥጋ አካሏን ለሁለት እስኪሰነጥቁት ድረስ በእጅጉ ለደከመች ለእስጢፋና (ኮሮና) ሰላም ይሁን።] 【ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፯】

ወደ ሆሣዕናው ታሪክ ስንመለስ የዝክረ ቅዱሳን እስትግቡእ የሆነው መጽሐፈ ስንክሳር ስለዘንባባው የትመጣና ትርጉም ተከታዩን ሐሳብ ያስቀምጥልናል ።

«ማቴዎስና ማርቆስ የዘንባባን ነገር አላስታወሱም፤ ሌሎች ከዛፍ ላይ ቅርንጫፍ፡ ዘንጥፈው በመንገድ ላይ ጐዘጐዙ አሉ እንጂ ። ሉቃስም ዝንጣፊውንም ሆነ ዘንባባውን አላወሳም፤ ሲሄዱም ልብሳቸውን በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር አለ እንጂ ። ዮሐንስ ግን ብቻውን የሰሌን ዛፍ ዝንጣፊ ከኢየሩሳሌም ያዙ አለ ። ሰሌን በኢየሩሳሌም የለም ነበርና ጌታችን በሕፃንነቱ ከእናቱ ከክብርት ድንግል ማርያም ጋር ወደ ግብጽ ምድር በወረደ ጊዜ እስሙናይን ከተባለ አገር ደረሱ፤ በዚያም ሰሌን አገኙ ። ጌታችንም ከሥርዋ ተነቅላ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ትተከል ዘንድ አዘዛት ። ያን ጊዜም ወደ አየር ወጥታ በረረች በደብረ ዘይትም ላይ ተተከለች ። ከእርስዋም ዘንባባ ወስደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ተቀበሉት፤ ሥርዓተ ሆሣዕናን እየዞረ አሳይቷልና ።»

ዘንባባው የመጣውና ደብረ ዘይት የተተከለው ከእስሙናይ (Eshmunen) ነው ያለውን ይዘን ታላቁ ሊቅ የእስሙናይ ሊቀጳጳሳት ቅዱስ ሳዊሮስ (Severus ibn al-Muqaffa) በበዓለ ሆሣዕናው ዙሪያ በመጽሐፉ የጻፈውን በድርሳኑ ፯ኛው ክፍል ላይ የምናገኘውን እናስታውስ

* እስከ ፴ ዓመቱ ድረስ በክርስቶስነቱ ማንም ሳያምንበት ኖረ ይህም ሮማውያንን ፈርተው እንደነበር በእሑድ ሰንበት በዕለተ ሆሣዕና ግን ሰማንያ አራቱ ደቀመዛሙርት (ሰባ ሁለቱ አርድእትና አስራሁለቱ ሐዋተርያት) ከደብረዘይት ይዘውት ሲወርዱ የሚነግሥና ከሮማውያኑ አገዛዝ ነጻ የሚያወጣቸው መስሏቸው በእብራይስጡ ሆሣዕና በአርያም በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው እያሉ ሲያመሰግኑት ህዝቡ ሁሉ የወይራ ዛፍ ከዘንባባ ዝንጣፊ ጋር ይዘው ልብሳቸውን እያነጠፉ እንደተቀበሉት ወደኢየሩሳሌምን ገብቶ ወደምኩራባቸውም አምርቶ እንደነገሥታቱ ተግባሩን ሲፈጽም ታየ እያለ እንደሚከተለው አስፍሯል። *

ወደ ምሥጢራዊው ትርጉም ስናልፍ ደግሞ ለምን በዕለተ ሆሣዕና በቦታው የተገኙት ዘንባባ በመያዝ ዘመሩ ለሚለው ተከታዩ አንድምታዊ ሐተታ በሊቃውንቱ ይነገራል ፦

☞ ዘንባባ ወይም ሰሌን እሾኻም ነው ትእምርተ ኃይል ትእምርተ መዊዕ (የኃይልና የድል ነሺነት ምልክት) አለህ ሲሉ እነርሱም ዘንባባውን ይዘው ታይተዋል ። (አንድም) ዘንባባን እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል፤ ባሕርይህ አይመረመርም ሲሉ ከነዘንባባቸው እያጀቡት ወደ ኢየሩሳሌም ገብተዋል። (አንድም) ዘንባባ ረጅም / ልዑል/ ነው አንተም ባሕርይህ ልዑል ነው ሲሉ ዘንባባ ይዘው ተቀብለውታል፡፡

☞ የተምር ዛፍ ዝንጣፊ ነው ያሉ እንደሆነ ተምር ልዑል / ረዥም ነው ⇨ ልዑለ ባሕርይ ነህ ሲሉ። የተምር ፍሬውም በእሾህ የተከበበ ነው (ፍሬው በእሾህ የተከበበ ነው (በቀላሉ መለቀም አይቻልም) የአንተም ምስጢር አንተ ካልገለጠከው አይመረመርም ሲሉ) ⇨ በባሕርይህ አትመረመርም ሲሉ ነው፡፡ በዚያውም ላይ ፍሬው አንድ ነው ⇨ ዋህደ ባሕርይ ነህ ሲሉ ነው።

☞ ሰሌን ነው ያሉ እንደሆነ አብርሃም ይስሐቅን ይስሐቅ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፤ እስራኤል ከግብፅ በወጡ ጊዜ፤ ዮዲት ሆሎፎርኒስን በገደለች ጊዜ፣ ሰሌን ቆርጠው ይዘው አመስግነዋልና በዚያ ልማድ።

(በዚያ ልማድ የተባሉትን ታሪኮች በአጭሩ ለማስታወስ እንዲረዳን ጥቂት ነገር እናውሳ… )

አብርሃም ላዳነውና በሔደበት ሀገር ደስ ላሰኘው ለእግዚአብሔር በዚያ መሠዊያን ሠራ… ደስ ብሎት አከበራት የዚህችን በዓል ስሟን የእግዚአብሔር በዓል አላት … የዘልዓለም ሥርዓት ሆኖ ተጽፏልና ለዚህ ሥርዓት የተወሰነ ዘመን የለውም፤ አብርሃም የሰሌኑን ጫፍ ለጋውን ያማረ የእንጨቱን ፍሬ ይዞ በየቀኑ ዘንባባውን ይዞ ሰባት ቀን የመሰዊያውን ዙርያ ይዞር ነበር" 【ኩፋ ፲፫፥ ፱,፲፯,፳,፳፩】

የሆሣዕናው ቅዳሴም የአብርሃምና የመልከጼዴቅን ነገር ሰፊ ቦታ ሰጥቶ ሲያወሳው እናያለን። ለዑደተ ሆሣዕና መነሻውም የአብርሐም ተግባር መሆኑን የመጋቢት ፳፪ቱ ስንክሳር እንደሚከተለው ይመሰክራል

« አብርሃምም ይቺን በዓል ደስታን የተመላች የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሎ ጠራት፤ የሰሌን ዝንጣፊና ዘንባባን ይዞ መሠዊያውን ዙሮአልና»

መልከ መልካምና ደመግቡ የነበረች ታላቋ ሴት ዮዲት መቅደሱን ያሳደፉ ማደሪያውን ያረከሱ የእግዚአብሔር ጠላቶች ድል ስትነሳና የናቡከደነፆር ቢትወደድ የነበረውን ሆሎፎርኒስን ገድላ በበቅሎ ላይ ተቀምጣ ሠረገላ እየነዳች ወደ ሀገርዋ ስትገባ የእስራኤል ሴቶች ሊያይዋትና ሊመርቋት ሮጠው ወጡ "ደግ በዓል አደረጉላት ዘንባባም በእጇ ያዘች ከእርሷ ጋር ለነበሩትም ሠጠች" 【ዮዲ. ፲፭፥፲፪】

ለመቋጫ እንዲሆን ንጹሕ ክቡር የሚሆን ዐምዳዊው ስምዖን የደረሰው የሆሣዕና በዓል በተደረገ በከበረች የክርስቲያኖች ሰንበት የሚነበበውን ጸሎት ከግብረ ሕማማቱ በማስታወስ እንሰነባበት

[ … ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዘይት (የወይራ ዛፍ) ዝንጣፊና የሰሌን ዘንባባ ተሸክሜ ከአርያም የተገኘ መድኃኒት መባል ለአንተ ይገባል እያልኩ ከሕፃናት ጋራ እጮኽ ዘንድ አድለኝ ። የዳዊት ልጅ ሆይ አማኑኤል እግዚብሔር ከእኛ ጋር ነው ማለት እንደሆነ ከአንተ ጋር አንድ አድርገኝ ። ወገኖችህ እንሆን ዘንድ አድርገን፤ በልቡናችን የጌትነትህን ብርሃን አብራ ። ከወገንህ ልጆች ውስጥ አድርገን ። እንተ ጠባቂያችን፣ መጋቢያችን፣ መሪያችን ነህ ። አንተም ንጉሣችን እኛም የወገንህ ልጆች፤ ንጉሣችንና አምላካችን ወደ እኛ መምጣትህ የተባረከች ናት፤ ከጨለማውም ግዛት አድነህ ብርሃንንና ክብርን ወደ ተመላች መንግሥትም አድርሰን ።በጨለማው ገዥ ከመረገጥ አድነን፤ ቃል ኪዳንህንና አምላካዊ ሕግህን በላያችን አጽና፤ በስምህ የሚያድን ሕይወትህን እንወርስ ዘንድ። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ወደ ቤተ መቅደስ ገብተህ ርግቦች የሚሸጡትን ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ እናንተ ግን የሌባና የወንበዴ ዋሻ አደረጋችሁት በማለት ያሳደድኻቸው ።
1.6K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 20:38:54 #ዘንባባ_እና_ሆሣዕና
✠. ✠ ✠ .✠

ሙሽራይቱ የሆነችውን ቅድስት ቤተክርስቲያኑን መሠረት ሆኖ ያጸናት ፣ ራስ ሆኖ የሚገዛት ፣ በደሙም የዋጃትና አካሉ ሆና ያከበራት ክርስቶስ እንኳን ለዘንባባው በዓል አደረሳችሁ። ሆሣዕና በአርያም

የቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮምን ምስክርነት መነሻ እናድርግ "ቤተክርስቲያን እንቲአነ ፍሬሃ ከመ በቀልት እንዘ አሐቲ ለሊሃ ወብዙኃት ሕንባባቲሃ … የእኛ የሆነች ቤተክርስቲያን ፍሬዋ እንደዘንባባ ፍሬ ነው ለራሷ አንዲት ስትሆን ቅርንጫፎቿ ብዙዎች ናቸው" 【ቀሌ. ፰፥፷፯】

ዘንባባ የሚለው ቃል ሰሌን፣ ጸበርት/ፀመርት ፣ ተምር፣ በቀልት … የሚሉትን ሁሉ ተክቶ የተነገረ ነው። ይሆንና ግን በቀልት የሚለው ግንዱን ፀመርት ደግሞ ቅጠሉ ሲሆን ተምር ፍሬው እንደሆነ መተርጉማን ያስረዳሉ።
በዚህ መንገድ ዘንባባ የሚለው ፍሬው ተዘርቶ የሚበቅል ቁመታም ሰሌን የቴምር ዛፍ ግእዙ በቀልት እያለ የሚጠራው ነው።

በእብራይስጡ ደግሞ ተምር (תָּמָר) ወይም ቶሜር (תֹּמֶר) የሚለው የቴምር ዛፍ ዘንባባን ወክሎ የሚነገር ሲሆን በግሪኩም ፎይኒክስ (φοῖνιξ) የሚለው የዘንባባ ዛፍን ወክሎ ተነግሯል።

በምሥጢር ግን ዘንባባ ራሱ ሆሳዕና ተብሎም ተጠርቷል!

ለምሳሌ ለቅዱስ ማቴዎስ ክርስቶስ በአምሳለ ወሬዛ(ወጣት) ተገልጾለት ካህናተ ጣዖት ወዳሉበት ሀገር ሲገባ ምን ማድረግ እንዳለበት ሲነገረው ሆሣዕና በእጅህ ያዝ እንዳለው ስንክሳራችን ይነግረናል ይህንንም ዘንባባ ነው ሲል መልሶታል።

“አንተሰ ኢትክል ከመ ትባእ ውስተ ዛቲ ሀገር ዘእንበለ ትላፂ ርእሰከ ወጽሕመከ ወዘእንበለ ትእኅዝ ሆሳዕና በእዴከ … አንተ ግን ጽሕምህን (ፂምህን) ካልተላጨህ በእጅህም ሆሣዕና/ ዘንባባ ካልያዝክ መግባት አትችልም”【ስንክሳር ጥቅምት ፲፪ ቁጥር ፲፫ 】

ይህንንም ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እየደጋገመ ለእመቤታችን ምሳሌ አድርጎ አስታውሶታል።
☆ በኆኅተ ብርሃን "ወደ ካህናቱ በገባ ጊዜ ለማስተማር የያዛት የማቴዎስ የሰሌን ዘንባባ አንቺ ነሽ… "
☆ በመዓዛ ቅዳሴም "የእንድርያስ የሕይወቱ መርከብ፣ ለያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ የስብከቱ መጽኛ፣ ብፁዕ ለሚሆን ለማቴዎስም የምልክቱ ዘንባባ የምትሆኚ ማርያም ሆይ ነዪ"

#ሆሣዕና ለሚለው ቃል የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍ ሆሳና (ὡσαννά) የሚለውን የጽርእ ቃል ቀጥታ ይጠቀመው እንጂ መነሻው የእብራይስጡ «ሆሺዓህናእ» የሚለው ጥምር ቃል ነው። ይህም ሆሺዓህ (יָשַׁע) ናእ (נָא) ከሚሉት ሁለት ቃላት የተገኘ ነው።
ትርጉሙም ሆሺዓህ= አድን፣
ናእ ደግሞ አሁን/እባክህ/አቤቱ በሚለው ይገለጻል።
☞ አሁን አድን ፣ እባክህ አድን፣ አቤቱ አድን ማለት ነው።

ዘንባባ በሕይወታችን ስላለው ትርጉም ውዳሴ አምላክ የቀዳሚት ምንባብ ይህን ይላል "መልካም ፍሬን እንደምታፈራ እንደ ሰሌን ሥር ጽናት በልቡና ጽናትና በነፍስ ዝምታ በቦታዬ ትከለኝ" ከዚህ ጸሎት በመንፈሳዊው ሕይወት የዘንባባን ሃይማኖታዊ መገለጫ በሥሩ ጽናት ከቦታ አለመናወጽ ለነፍስ አለመታወክ ምሳሌ ሆኖ መጠቀሱን እንረዳለን። ውኃ በሌለበት በረሐ እየበቀለ ባለ ፍሬ መሆኑ መከራ በበዛበት ዓለም እየኖሩ ፣ በተኩላዎች መኃል እንደበግ ተልከው ስለእውነት እየመሰከሩ ፣ በመልካም ምግባር ጸንተው ፍሬ ላፈሩ… ጽኑዓን መስተጋድላን ሁሉ ምሳሌ ሆኖ ይነገራል።

በቅዱስ መጽሐፍ ዘንባባ ያለውን ቦታ መረዳት እንድንችል ተከታዮቹን ተጨማሪ ታሪኮች እንመልከት ፦

✧ ታላቋ ባለቅኔ ሴት ዲቦራ በእስራኤል ላይ ስትፈርድ ትቀመጥ የነበረው ከዘንባባ በታች ነው። ዛፉም በስሟ ይጠራ እንደነበር መጽሐፍ እንዲህ ሲል ዘግቦልናል “እርስዋም በተራራማው በኤፍሬም አገር በራማና በቤቴል መካከል ካለው የዲቦራ ዛፍ ከሚባለው ከዘንባባው በታች ተቀምጣ ነበር፤ የእስራኤልም ልጆች ወደ እርስዋ ለፍርድ ይወጡ ነበር።” 【መሳ ፬፥፭】

✧ በኦሪቱ መቅደስ ጠቢቡ ሰሎሞን እንዲቀርጽ (እንዲሥል) ከታዘዙት ሦስት ሥዕላት ውስጥ ሥዕለ ኪሩብ የፈነዳ አበባ እና የዘንባባ ዛፍን ነው። 【፩ኛ ነገ. ፮፥፳፱–፴፯】

✧ ታላቁ የዜና አይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን (Flavius Josephus / Yoseph Ben Mattithyahu) በዜና አይሁድ በሦስተኛው ክፍል በ፳፱ኛው ምዕራፍ ስለ ልማደ አይሁድ ሲዘግብ «በቂጣ በዓል ላይ የደስታና የክብር መገለጫ አድርገው በዘንባባ ዝንጣፊ የመማታት ጨዋታን እንደ ሕግና ልማድ ይፈጽሙት ነበር» ይላል።

✧ ሌላው በአይሁድም በሮማውያንም ዘንድ ዘንባባ ያለው ተምሳሌታዊ ሥፍራ ትልቅ ነው። ለድል አድራጊዎች በእምነታቸው ለጸኑትና ለሰላም አብሳሪዎች እንደ መገለጫ ሆኖ ያገለግላል። በተለይ ነቢያቱ የሰላም ዘመን እንዲመጣ ለሕዝቡ ለማብሰር በአሕያ ላይ ተቀምተው የዘንባባ ዝንጣፊ ይዘው ወደ ከተማ ሲገቡ ይታዩ ነበር ፤

ቅዱስ መጽሐፋችንም ድል ነሺዎች የክብራቸው መገለጫ አድርገው በሰማዩ መቅደስ ዘንባባ ይዘው መገለጣቸውን እንዲህ ሲል ይመሰክርልናል።

“ከዚህ በኋላ አየሁ፥ እነሆም፥ አንድ እንኳ ሊቆጥራቸው የማይችል ከሕዝብና ከነገድ ከወገንም ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ነጭ ልብስም ለብሰው የዘንባባንም ዝንጣፊዎች በእጆቻቸው ይዘው በዙፋኑና በበጉ ፊት ቆሙ፤” 【ራእ ፯፥፱】

በምሳሌነቱም ዘንባባ (በቀልት) የኢየሱስ ክርስቶስ ፣ የድንግል ማርያምና የሌሎቹም ቅዱሳን ጻድቃን ወኪል ሆኖ በየአገባቡ ሲመሰገኑበትና ክብራቸው ሲገለጥበት እንመለከታለን።

. . ዘንባባ = ክርስቶስ

『 ስነ ቆምከ በቀልት ወመልክእከ ሕይወት ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ አምደ ሃይማኖት፣ ሥርግው ስነ ስብሐት በሰጊድ ስብሐት 』 ⇨ የቁመትህ ውበት ዘንባባ መልክህም ሕይወት የሆነ የሃይማኖት አምድ ክርስቶስ ሆይ ባማረ ምስጋና የተሸለምክ በመስገድ ላንተ ምስጋና እናቀርብልሃለን።

. . ዘንባባ = ድንግል ማርያም

『 ለሕሊናኪ ንጽሕት እምነ ኵሉ ትውዝፍት፡ ለንጽሐ ሥጋኪ ዘአልቦ ርስሐት፡ ለቆምኪ ስነ በቀልት በሰጊድ ሰላም』 ⇨

. . ዘንባባ = አቡነ ተክለሃይማኖት

『ተክለ ሃይማኖት በቀልት ወጽጌ ገነት ፡ ዘናቄርብ ለከ መዓዛ ስብሐት 』 ⇨

. . ዘንባባ = አቡየ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

『 ጻድቅሰ ከመ በቀልት ይፈሪ ወይበዝኅ ከመ ዘግባ ዘሊባኖስ አባ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡፡ ኖመ ኖመ ኢየሩሳሌም በፍሥሓ ወበሐሴት፡፡ 』 ⇨

በይበልጥ ደግሞ "ጻድቅ እንደዘንባባ ያፈራል" በሚለው የነቢዩ ንጉሥ ዳዊት ቃል መነሻ በማድረግ 【መዝ ፺፪፥፲፪】በጽድቅ የኖሩ አያሌ ሰማዕታት መስተጋድላን መገለጫቸው ሆኖ ሲወሱበትና ሲወደሱበት ይታያል።

በኋላኛውም ዘመን ገዳማውያኑ መናንያን ሕይወታቸው ከዘንባባ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ሆኖ ታይቷል። ሥራቸው ሰሌን መታታት (ሠርቶ ሰፍቶ ለምንጣፍ ለቅርጫት፣ ለቆብና ለቀሚስ ማዘጋጀት) ፣ ለራሳቸውም የሚለብሱት ቆባቸውና ልብሳቸው ጭምር ከሰሌን የሚሠራ ነበር። ኋላም ዐረፍተ ዘመን ሲገታቸው የከበረ ሥጋቸው በሰሌን ተከፍኖ ግብኣተ መሬት ይፈጸምላቸዋል።

ከሰይጣን ውጊያ ለማረፍ እና ከስንፍና ለመለየት ከጸሎት ጋር መነኮሳት ሊተገብሩት ከሚገባ ተግባረ እድ ዋናው ሰሌን መታታት ሊሆን እንደሚገባ ቅዱስ መልአክ ለርእሰ መነኮሳት አባ እንጦንስ አስተምሮታል (ስንክሳር ዘጥር ፳፪) የባህታዊው አባ ጳውሊ ቀሚስ የአባ እንጦንስም ቆብ ከሰሌን የተሠራ ነበር መጽሐፈ መነኮሳቱና ዜና ገድላቸው ይነግረናል።
1.4K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 20:38:51
1.3K viewsተεพ๑δr๑ร (አግናጥዮስ)𝕿𝖊𝖜𝖔𝖉𝖗𝖔𝖘 𝕭𝖊𝖑𝖊𝖙𝖊 𝕸𝖊𝖓𝖌𝖎𝖘𝖙𝖚 Ignatius Theophoros (Ἰγνάτιος Θεοφόρος), 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 14:21:40
በደቡብ ምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት በእንደርታ ወረዳ ለሰሰማት ትኩል ምዕራፈ ቅዱሳን ቤተ ደናግል ገዳም ሙሉ ገቢው የሚውለው "ከሞት ባሻገር" መጽሐፍ ሁለተኛ እትም

እና

ለኳታር ዶሃ ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ሕንፃ ማሠሪያ ሙሉ ገቢው የሚውለው አበረታች መድኃኒት መጽሐፎች በዘመነ ትንሣኤ በአዲስ አበባና በዶሃ ታትመው በገበያ ላይ ይውላሉ::

ሁለቱም መጻሕፍት ለሁለተኛ ጊዜ የታተሙ ሲሆን ከሞት ባሻገር በገጽ ብዛት ጭማሪ የተደረገበት ክልስ እትም (revised edition) ነው::
2.5K viewsሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን, 11:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 11:35:29
እንኳን አደረሳችሁ!

"ከሰውስ እንደኔ ኃጢአት የሚሠራ፤
ከመሐሪዎችስ እንዳንተ 'ሚራራ፤
አይገኝምና በዚያ የፍርድ ሥፍራ፤
ስለ ደምህ ብለህ ለኃጥኡ ራራ!"

"አልቦ ዘከማየ አበሳ ኃጢአት ገባሪ፤
ወአልቦ ዘከማከ እግዚአብሔር መሐሪ፤

አመ ለኮንኖ ዓለመ ትመጽእ ደኃሪ፤
ቀደመ ገቦከ ኃጢአትየ አስተስሪ!"

(መልክአ መድኃኔ ዓለም)

https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
1.3K viewsDrshaye Akele, edited  08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 11:53:41 በሌሊት ወደ ኢየሱስ

(ሽራፊ ሃሳብ 1 ከኒቆዲሞስ ምንባብ)

ኒቆዲሞስ በውድቅት ሌሊት ወደ ጌታችን መጣ። ሌሊት እንግዲህ በቂ ብርሃን የሌለበት ፣ እንቅፋት የሚበዛበት ፣ ጭልም የሚልበት ፣ ግራ ቀኝ ቢያዩ ሰው የሚታጣበት ፣ ማጅራት ከሚመቱ ወንበዴዎች በቀር በመንገድ ሌላ ሰው የማያጋጥምበት ፣ ብርድና ቆፈን ሰውነትን የሚያስጨንቅበት ሰዓት ነው። ይህ የአይሁድ መምህር በሌሊት የመጣበት ምክንያቱ ብዙ ሲሆን ለእምነት ማነስ ማሳያ የሚሆን ሰው ነው።

ዛሬ ደግሞ ለአፍታ ኒቆዲሞስን "በሌሊት ወደ ኢየሱስ በመምጣቱ" በጥቂቱ እናመስግነው። ብዙ እግሮች ወደ ኃጢአት በሚሮጡባት ሌሊት ወደ ክርስቶስ የሮጠውን ይህንን ሰው እስቲ እናድንቀው! ይህንን የሌሊት ግርማ ሳይበግረው ወደ ኢየሱስ የተጓዘ የጨለማ ተጓዥ ፣ ይህንን ሰዓታት ቋሚ ፣ ይህንን ማሕሌት ቋሚ በጥቂቱ ብናመሰግነው ምን አለ? ከጌታ ፊት ቆሞ ቅኔ የተመራውን ፣ ስለ ልደት እየተናገረ ስለ ጥምቀት የሚያመሰጥረውን የፈጣሪን ቅኔ ተቀብሎ ሊያዜም ከጀመረ በኋላ መቀበል ሲያቅተው ጌታችን "አንተ የአይሁድ መምህር ስትሆን ይህንን አታውቅምን?" ብሎ የገሠፀውን ኒቆዲሞስን እስቲ ዛሬ በበጎነቱ አርኣያ እናድርገው።

በሕይወታችን ውስጥ የተስፋ ብርሃን ጭልም ባለብን ጊዜ ፣ እንቅፋት በበዛብን ወቅት ፣ ግራ ቀኝ አይተን ሰው ባጣንበትና ብቸኝነት በዋጠን ሰዓት ፣ ክፉ ከማድረግ በማይመለሱ ጨካኞች በተከበብን ሰዓት እኛስ ወዴት እንሔዳለን?

ሕይወቱ "ሌሊት" የሆነበት ሰው ሁሉ ወደ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ቢሔድ እንደሚሻለው ከኒቆዲሞስ የተሻለ ምሳሌ የለም። ሕይወቱ የጨለመ ባይሆን እንኳን ልቡ የጨለመበት ፣ በኃጢአት ጠል የጠቆረ ፣ በበደል ብርድ ቆፈን እጅ እግሩ የታሰረ ከእኛ መካከል ስንት አለ?

እመነኝ ፣ ተስፋ ቆርጠህ ቁጭ ብለህ እስከሚነጋልህ ብትጠብቅ አይነጋም። ይልቅ ተነሥና "በሌሊት ወደ ክርስቶስ ሒድ" እርሱ ተስፋ ለቆረጠው ማንነትህ ዳግመኛ መወለድ እንዳለም ይነግርልሃል። ኒቆዲሞስ ጌታችንን ሊያየው ሔዶ ራሱ ታይቶ እንደመጣ አንተም ወደ እርሱ የቀረብህ እንደሆነ ራስህን ታያለህ።

በ"ሌሊት" ውስጥ ለሚኖር ሰው ነግቶ ፀሐይ ትወጣልኛለች ብሎ ከሚጠባበቅ ይልቅ በሌሊት እንደ ኒቆዲሞስ ተነሥቶ ወደ ጽድቅ ፀሐይ ወደ ክርስቶስ ቢሔድ ይሻለዋል። ወደ እርሱ ለሚሔድ ሰው ሌሊቱ ይነጋል ፣ ክርስቶስ ያለበት ሌሊት ከቀን ይልቅ ብሩሕ ነው ፣ እውነተኛው ብርሃን ያለበት ጨለማም ጨለማ አይደለም። ስለ እርሱ "ጨለማም በአንተ ዘንድ አይጨልምም" ተብሎ ተጽፎአልና።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
መጋቢት 16 2010
ኒቆዲሞስ
ናይሮቢ ፣ ኬንያ

https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
365 viewsDrshaye Akele, 08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 08:31:54 አባ ጊዮርጊስ በሦስትዮሽ ስልት (Trio) ራሱን ከጌታና ከእናቱ
ጋር የሚያዛምድበት ውብ ሥነ ጽሑፋዊ ሦስት ማዕዘንም አለ ፡-

‘እኔ የተጠማሁ ነኝ ፤
አንቺ የወርቅ መቅጃ ነሽ ፣
ልጅሽ የሕይወት ውኃ ነው፡፡

እኔ ነጋዴ ነኝ ፤
አንቺ መርከብ ነሽ ፤
ልጅሽ ዕንቈ ነው፡፡

እኔ ገደል ተሻጋሪ ነኝ ፤
አንቺ ድልድይ ነሽ ፤
ልጅሽ የደስታ ሥፍራ ነው፡፡

እኔ ደሃ ነኝ ፤
አንቺ የክብር ማከማቻ ነሽ ፤
ልጅሽ የከበረ ጌጥ ነው፡፡

እኔ ቁስለኛ ነኝ ፤
አንቺ የመድኃኒት ብልቃጥ ነሽ ፣
ልጅሽ መድኃኒት ነው፡፡

እኔ ዕርቃኔን ነኝ ፤
አንቺ የሸማኔ ዕቃ ነሽ ፣
ልጅሽ የማያረጅ ልብስ ነው’

የግዮን ወንዝ ገጽ 27-28

https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
1.7K viewsDrshaye Akele, edited  05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 08:31:45
https://t.me/joinchat/AAAAAEILHwyFiBuqHNVyRw
1.5K viewsDrshaye Akele, edited  05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ