Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.51K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On YT sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-04-14 19:23:14 የእግዚአብሔር የመስቀል ማሕተም!

ሐዋርያው ዮሐንስ የፍቅር እርግጠኝነትን የሚያስረዳው ፍቅር በእኔ መውደድ ሳይሆን በእግዚአብሔር መውደድ እንደሆነ በማሳየት ነው (1ዮሐ 4፥10)። የእግዚአብሔር መውደድ ደግሞ ልጁን የኅጢአት ማስተሰረያ ይሆን ዘንድ በመስቀል ላይ በሚኖር መከራ አዋለው።

መቼም ለፍቅር መስቀልን መምረጥ ከሚከስተው መጥፎ ምስል አንጻር ትክክል አይመስልም። ሮማውያን በመስቀል መሰቀልን በራሳቸው ዜጎች ላይ እንዳይፈጸም በህግ ከልከለዋል። ከዜጎቻቸው ሕሊና ምስሉን ለማራቅም ይተጉ ነበር። መስቀል በጣም ዘግናኝ የመግደያ መንገድ ነው። የሚፈጥረው ስቃይና ጣር ከፍተኛ ነው። ጣሩ ብቻ ሳይሆን መሰቀያ ቦታው ራሱ የሞት ድባብ የሚያደባበት ነበር።

እግዚአብሔር ፍቅሩን በዚህ መንገድ ገለጸ። «መድቀቁና መሠቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፤ እግዚአብሔር ነፍሱን የኀጢአት መሥዋዕት ቢያደርገውም እንኳ» (ኢሳይያስ 53:10)። ልጁን አሳልፎ ለመስቀል ሞት ሰጠው። በዘመኑ በነበረው የመጨረሻው የጭካኔ ግድያ ክርስቶስ ኢየሱስ ተላልፎ ተሰጠ። በኢየሱስ ስቃይና ጣሩ ውስጥ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አሳየ። አለም ደካማ ባለችው መንገድ እግዚአብሔር ፍቅሩንም ጽድቁንም እውን አደረገ።

የእግዚአብሔር ትድግና አንድያ ልጁን በመስቀል በመስጠት ተገለጠ። ትድግናውን በአጀብ ሳይሆን በውርደት መስቀል ላይ ፈጸመ። በኅጢአቱ አመጽ የተመታው አለም አመጹን በሙሉ ክርስቶስ ላይ በማኖር የማስተሰርያ መስዋእት አድርጎ አቅርቦታል (ሮሜ 3፥25)። በደካማው መንገድ ብርቱው ጠላት ተረታ፥ ድነትና ትድግናም ተበሰረ።

በመስቀሉ ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅን፣ ቀረብን፣ ተቀባይ ሆንን። ፍቅሩንም ጽድቁንም እግዚአብሔር ገለጠልን! እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ላይ በሰራው ስራ ርቀን የነበርነውን ታርቆናል!

በክርስቶስ ኢየሱስ፣ አምላክ-ሰው ስቃይና ህማም በኩል የጸጋውን ባለጠግነት ተገልጧል። ለእኛ ለምናምን መስቀሉ የእግዚአብሔር መውደድ ማህተም ነው!

አማኑኤል አሰግድ
@nazrawi_tube
1.4K viewsΒενιαμίν, 16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 22:05:02 ኮከቡ ኢየሱስ ነው
ዘሪቱ ከበደ
አዲስ ዝማሬ

@nazrawi_tube
1.6K viewsΒενιαμίν, 19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 10:33:40 የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግሮች፣ በአማኞች ወደ መስቀሉ የሚደረጉ ጸሎቶች ናቸው!

1. የመጀመሪያው የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግር

ሉቃስ፡23፡ 33-34፤ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ። 34፤ ኢየሱስም። አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ።

ጸሎት፦ ምን ብለን እንጸልይ ጌታ ሆይ እኛም እያወቅን በድለን እነርሱም እያወቁ በደሉን፣ ለነገሩ የሁላችን እውቀት ጥላቻ ነው እንጂ ፍቅር የለበትም። ለገዳይ ማላጅ መሆን ካንተ የሚሰጥ ስጦታ ነው፣ ለእስጢፋኖስ ሰጠኸው እባክህ ለእኛም ስጠን፣ “የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” እንድንል፣ በቁም ለሚሰቅሉን ይቅር ማለትን አስተምረን። መጀመሪያ ስታስተምረን “እኛ” ብለን እንድንጸልይ እንዳስተማርከን “የበደሉንን ይቅር እንደምንል” ብለን ስንጸልይ ድምጻችን እንዳያንስ የበደሉን እስኪሰሙን የበደልናቸውንም እስክንሰማ በቂ የይቅርታ ድምጽ ስጠን! አሜን እንበል!

2. ሁለተኛ የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግር

ሉቃስ 23: 39 - 43 ከተሰቀሉት ከክፉ አድራጊዎቹም አንዱ። አንተስ ክርስቶስ አይደለህምን? ራስህንም እኛንም አድን ብሎ ሰደበው። 40፤ ሁለተኛው ግን መልሶ። አንተ እንደዚህ ባለ ፍርድ ሳለህ እግዚአብሔርን ከቶ አትፈራውምን? 41፤ ስለ አደረግነውም የሚገባንን እንቀበላለንና በእኛስ እውነተኛ ፍርድ ነው፤ ይህ ግን ምንም ክፋት አላደረገም ብሎ ገሠጸው። 42፤ ኢየሱስንም። ጌታ ሆይ፥ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ አለው። 43፤ ኢየሱስም። እውነት እልሃለሁ፥ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ አለው።

ጸሎት፦ በአንተ ፊት ኃጢአት በተባለ ወንጀል የማንጠየቅ የለንም፣ ካንተ ካገኘነው ውጪ የተሰማን ነጻነት ካለ ፈትሸን፣ በመስቀል ጎዳና እለት እለት አብረንህ ስንሰቀል አንተ የእኛ ዓይነት እንዳልሆንክ እንድናውቅ እንደዚህ አብሮ ተሰቃይህ ዓይነት ሰው፣ ፈጣን ጸሎት አስተምረን፣ እኛ በኃጢአታችን፣ አንተ ለጽድቃችን፣ መሰቀልህን አውቀን “ዛሬ በመንግሥትህ አስበን” እንድንል እርዳን! አሜን እንበል! ።

3. ሶስተኛ የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግር

ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር። 26፤ ኢየሱስም እናቱን ይወደው የነበረውንም ደቀ መዝሙር በአጠገቡ ቆሞ ባየ ጊዜ እናቱን። አንቺ ሴት፥ እነሆ ልጅሽ አላት። 27፤ ከዚህ በኋላ ደቀ መዝሙሩን። እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት። ዮሐ. 19:26-27

ጸሎት፡ እናትነት መውለድ ብቻ ሳይሆን ከሥራ ሁሉ የሚበልጥ ሥራ ነው ፣ ይህንን ለእናቶች ስለ ሰጠህ እናመሰግንሀለን፣ አቤቱ ለእናቶች ጸጋን ስጥ! “ይህችን እናትም እነሆ” መባልም ከውርስ የሚበልጥ አደራ ነው፣ አቤቱ ለልጆች የእናትዬን ዐደራ እንዳይበሉ ጸጋን ስጥ። ለሁላችን የቤትህ ሥራ የዐደራ ሸክም ይክበድብን፣ ጌታ ሆይ ዐደራን የሚበላውን ክፉ ሐሳባችንን የአንተን ራስ የወጋው እሾህ ይውጋው፣ አደራ መቀበልን ከዮሐንስ አስተምረን፣ ማሪያም በስሟ ሳይሆን በስራዋ እንደተጠራች እኛንም በሥራችን ጥራን፣ ያን ጊዜ አደራችን ይገባናል፣ አሜን እንበል!
4. ዐራተኛ የኢየሱስ የመስቀል ንግግር
ማቴ. 27 45፤ ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። 46፤ በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ። ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው። 47፤ በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው። ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
ጸሎት፦ ሁሉን የምትገዛ ያለኽ የነበርህ እውነተኛና ጻድቅ የሆንህ ጌታ እግዚአብሔር ፣ ሊመለስ በማይችል የመስቀል መከራ ውስጥ ስናልፍ፣ ወደማይመለከተው እንዳንጸልይ እርዳን፣ ሁላችን ስለ ክርስቶስ ይህንን የመስቀል ጽዋ ስናልፍበት “አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ብሎ መጸለይ ካንተ ጋር መነጋገሪያ መክፈቻ ቃል እንጂ ማጉረምረም እንዳልሆነ ይግባን። አሜን እንበል!

5 አምስተኛ የኢየሱስ ንግግር
ዮሐ.19:28 “ከዚህ በኋላ ኢየሱስ አሁን ሁሉ እንደተፈጸመ አውቆ የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ። ተጠማሁ አለ። 29፤ በዚያም ሆምጣጤ የሞላበት ዕቃ ተቀምጦ ነበር፤ እነርሱም ሆምጣጤውን በሰፍነግ ሞልተው በሁሶፕም አድርገው ወደ አፉ አቀረቡለት።”

ጸሎት፦ ጌታ ሆይ እኛ ቢጨምቁን የሚወጣን ሆምጣጤ ነው፣ የሕይወትን ውሃ በልባችን አብዝተህ ካላፈሰስክ ሌላም የለን፣ ይህን ለማለት እንኳ ኩራታችን ይተናነቀናል፣ አንተ የሕይወት ምንጭ ሆይ ፍለቅ፣ እባክህ ፍለቅ ከሆምጣጤ እንድንላቀቅ! አሜን እንበል!
6. ስድስተኛ የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግር

ዮሐ. 19፡ 30፤ ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥

ጸሎት፦ እንደ ሔሮድስ አንተን ስናይ ደስ የሚለን ምልክትህን ፈልገን እንዳይሆን፣ ዝም ስትል እንዳንዘብትብህ፣ ስንፈልግህ ልትፈጽም የመጣኸውን ፈልገን እንከተልህ፣ የአንተ መንገላታት አንተ ለሌለህበት አጀንዳ አንዳይሆንብን እርዳን፣ በፈጸምከው ሥራ ላይ የእኛን ሥራ ስንደርት እንዳንገኝ ባሪያዎችህን በተፈጸመው ስራህ ውስጥ ማረፍን አስተምረን! አሜን እንበል!

7. ሰባተኛ የኢየሱስ የመስቀል ላይ ንግግር

ስድስት ሰዓትም ያህል ነበረ፥ ጨለማም እስከ ዘጠኝ ሰዓት በምድር ሁሉ ላይ ሆነ፥ ፀሐይም ጨለመ፥ 45፤ የቤተ መቅደስም መጋረጃ ከመካከሉ ተቀደደ። 46፤ ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ። 47፤ የመቶ አለቃውም የሆነውን ነገር ባየ ጊዜ። ይህ ሰው በእውነት ጻድቅ ነበረ ብሎ እግዚአብሔርን አከበረ። 48፤ ይህንም ለማየት ተከማችተው የነበሩ ሕዝብ ሁሉ፥ የሆነውን ባዩ ጊዜ፥ ደረታቸውን እየደቁ ተመለሱ።

ጸሎት፡ - ሁሉ ባለቀ ጊዜ የከበረው ነገራችንን ራሳቸውን ማዳን ለማይችሉ አሳልፈን እንዳንሰጥ እርዳን - አቤቱ ላንተ ኖረን በመሞት ስለአንተ ሞተን መኖርን አስተምረን፡ ጌታ ሆይ እንኳን ስንሞት አሁን በሕይወት እያለን ነፍሳችንን በእጅህ አደራ እንሰጣለን፡፡ አሜን እንበል!

ሰለሞን ጥላሁን
@nazrawi_tube
664 viewsΒενιαμίν, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 13:52:30 Bereket tesfaye
New song
@nazawi_tube
676 viewsΒενιαμίν, 10:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 20:13:10 ውዱ ነፍስ የትኛው ነው?

“መቶ በግ ያለው ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ፥ ዘጠና ዘጠኙን በበረሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሄድ ከእናንተ ማን ነው?” ሉቃ 15፡4

“የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቶልና።” ሉቃ 19፡10

ሰዉ ሁሉ ንጹሕ ሆኖ እኔ ግን ብቆሽሽ
ምድር ላይ እኔ ብቻ በኃጢአት ብበላሽ
መሞት የሚገባኝ እኔ ብቻ ብሆን
ኢየሱስ ለብቻዬ ይመጣልኝ ነበር፡፡
ዘማሪ በረከት ተስፋዬ

የሰውን ዋጋ ከልቡ ለጠየቀ ልከኛው ምላሽ በክርስቶስ የተከፈለው የደም መስዋእትነት ነው፡፡ የሰው ክቡርነት የሚመነጨውም ከዚሁ ነው፡፡ ሰውን ምን ክቡር ያደርገዋል ከተባለ ምላሹ የተከፈለለት ዋጋ ነዋ የሚል ነው፡፡

በመንፈሳዊ እና ማኅበራዊ መስተጋብሮቻችን የሰውን ዋጋ የምንተምንበት የተለያየ መስፈሪያ እንዳለን ጥርጥር የለውም፡፡ የነፍስን ሁሉ ዋጋ አስተካክሎ ያለማየት ጉዳይ በቤተክርስቲያንም ሆነ በውጭ በጉልህ ይታያል፡፡ የሰውን ክቡርነት የሚያጎላልን መነጽር ሀብት፣ ዕውቀት፣ ዘር …የመሳሰሉት ይመስላሉ፡፡

በደጅ አካባቢ ለሕመማቸው ከንፈር የማይመጠጥላቸው፤ ለሞታቸው ደረት የማይደቃላቸው፣ መኖራቸው ከመኖር የማይደመርላቸው በርካቶች ናቸው፡፡ በቤተክርስቲያንም ልክ እንዲሁ እጃቸውን አንስተው ጌታን በተቀበሉበት ቅጽበት እልልታ የማይደቅምላቸው፤ መምጣታቸው እንደማይሞላን፣ መቅረታቸውም እንደማያጎድለን የሚታሰብባቸው፤ ሙሉ ፈገግታ የማይቸራቸው፣ መሪዎቻቸው የማያተኩሯቸው፣ የጌታ ቤት የተቀደሰ አሳሳም የሚናፍቃቸው፣ ደጃቸው ለጉብኝት የማይንኳኳባቸው ምእመናን ብዙ ናቸው፡፡

በእግዚአብሔር ቤት VIP እና VVIP ምእመናን የመኖራቸው ጉዳይ በእጅጉ ያስደንቃል፤ ያሳዝናልም፡፡ ያዕቆብ በመልእክቱ ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የሰላ ሐሳቡን አስፍሯል፤

“ወንድሞቼ ሆይ፤ ክቡር በሆነው በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የምታምኑ እንደ መሆናችሁ አድልዎ አታድርጉ። የወርቅ ቀለበት ያደረገና ያማረ ልብስ የለበሰ ሰው ወደ ጉባኤአችሁ ቢመጣ እንዲሁም ያደፈ ልብስ የለበሰ ድኻ ሰው ቢገባ፣ ያማረ ልብስ ለለበሰው የተለየ አክብሮት በማሳየት፣ “ለአንተ የሚሆን መልካም ስፍራ ይኸውልህ” ብትሉትና ድኻውን ሰው ግን፣ “አንተ በዚያ ቁም” ወይም “ከእግሬ በታች በወለሉ ላይ ተቀመጥ” ብትሉት፣ በመካከላችሁ አድልዎ ማድረጋችሁ አይደለምን? ደግሞስ በክፉ ሐሳብ የተያዛችሁ ፈራጆች መሆናችሁ አይደለምን? የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ስሙ፤ እግዚአብሔር በእምነት ባለጠጋ እንዲሆኑና እርሱን ለሚወድዱም ተስፋ የተሰጣቸውን መንግሥት እንዲወርሱ የዚህን ዓለም ድኾች አልመረጠምን?” አዲሱ መደበኛ ትርጉም ያዕቆብ 2÷1-6

አዎን ጌታ አምላክ የሰዎች ሁሉ ወዳጅ የምስኪኖችም ወዳጅ ነው፡፡ በእርሱ ዘንድ መታወቂያችን አንድ ነው፤ ሁላችን የእርሱ ምሕረት የሚገባን ኃጢአተኞች ነን፡፡ አምነን በዳንበት ቅጽበትም ወደ መንግሥቱ የፈለስን ውድ ልጆቹ፣ በአካሉ ውስጥ ብልቶች እና በእርሱ የቤተሰብ ተቋም ውስጥ የቤተሰቡ አባላት ነን፡፡ በፊቱ ርካሽ እና ቀላል ግምት የሚሰጠው አንዳችም የለም፡፡

በተለይም በቤተክርስቲያን “ቀላል ሰው እንዳይመስላችሁ” እያልን የምናንቆለጳጵሰው፤ አይረቤ እንደሆነ ቆጥረንም የምናዋድቀው ማንም ሊኖር አይገባም፡፡ ድቤ እየደለቅን እንኳን ደኅና መጣህ የምንለውም፤ ጥግህን ያዝ ብለን እንደነገሩ የምናስተናግደውም ሊኖር አይገባም፡፡ እገሌን ማረክን ብለን ግዳይ እንደጣለ አርበኛ የምንፎክርለት፣ እንደዘበት አይተንም የምናልፈው ሊኖር አይገባም፡፡

በመንግሥቱ ውስጥ ለተገኘ ዕድል ፈንታ ለሁሉ እኩል ዋጋ ተከፍሏል፡፡ በአገልግሎት እውነተኛ ተጋድሎ የምንተጋ ወገኖች ክርስቶስ የሞተለትን ሰው ሁሉ በእኩል ዓይን እንይ፣ በእኩል መጠንም እናገልግል፡፡ በቤተክርስቲያን ውስጥ በዚህ መልኩ የሚደረግ ነገር ትልቅ ኃጢአት፣ ከእምነት መጉደል እና ሕግ ተላላፊነት እንደሆነ ያዕቆብ በመልእክቱ መስክሯል፡፡ ውዱ ነፍስም ያለ ልዩነት ክርስቶስ የሞተለት ሁሉ ነው፡፡

ጌታ ይርዳን!!
መጋቢ ስንታየሁ በቀለ
@nazrawi_tube
38 viewsΒενιαμίν, 17:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 19:15:07 ለእስራኤል እንደ
ጠል እሆነዋለሁ!

መንፈስ ቅዱስ ነፍስን ይመልሳል። የደረቀ ሕይወትን እንደ ገና ሕያው ያደርጋል። ተስፋን ያለመልማል። የደከመን ጉልበት አበርትቶ ፍሬያማ ያደርጋል!
ዛሬ ማለዳ ያንን restoration/ renewal በሚናፍቅ ድባብ ዮሐንስ 7፥37-39 ላይ ያለውን ምንባብ እያነበብሁ ሳለሁ፥ መንፈሴ ወደ ሌሎች ክፍሎች ወሰደኝ።

በተለይ ልቤን እጅግ የነካው "ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ (I will be like a dew)፤ እንደ አበባም ያብባል፥ እንደ ሊባኖስም ሥሩን ይሰድዳል። ቅርንጫፎቹም ይዘረጋሉ፥ ውበቱም እንደ ወይራ፥ ሽታውም እንደ ሊባኖስ ይሆናል።" (ሆሴ.14፥5-6) የሚለው ክፍል ነው። እንደ ጠል!

የእግዚአብሔር መንፈስ የሰውን መንፈስ ሕያው በማድረግ የታወቀ ነው። ግን አንድ ልዩ መስፈርት አለው። እሱም መጠማት ነው (ዮሐንስ 7፥37-39)። ቅዱስ ቃሉ "ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው ይጠግባሉና።" (ማቴ.5፥6) ብሏልና!
የእግዚአብሔር ጊዜ ነበርና ከላይ በቃሉ ውስጥ የተጠቀሱትን መንፈሳዊ ባርኮቶች እያሰብሁ ብዙ ተመሳሳይ ክፍሎችን አነበብሁ። እስቲ አራቱን ልጋብዛችሁ:-

➣"በተጠማ ላይ ውኃን በደረቅም መሬት ላይ ፈሳሾችን አፈስሳለሁና፤ መንፈሴን በዘርህ ላይ በረከቴንም በልጆችህ ላይ አፈስሳለሁ፥ በፈሳሾችም አጠገብ እንደሚበቅሉ እንደ አኻያ ዛፎች በሣር መካከል ይበቅላሉ።" (ኢሳ.44፥3-4)፤

➣"ጕልበቴን ይያዝ፥ ከእኔ ጋር ሰላም ያድርግ፤ ከእኔ ጋር ሰላም ያድርግ። በሚመጣው ዘመን ያዕቆብ ሥር ይሰድዳል፥ እስራኤልም ያብባል ይጨበጭብማል፤ "በፍሬያቸውም የዓለሙን ፊት ይሞላሉ።" (ኢሳ.27፥5-6)፤

➣"ፍርድህን በምድር ባደረግህ ጊዜ በዓለም የሚኖሩት ጽድቅን ይማራሉና ነፍሴ በሌሊት ትናፍቅሃለች፥ መንፈሴም በውስጤ ወደ አንተ ትገሠግሣለች።....ሙታንህ ሕያዋን ይሆናሉ፥ ሬሳዎችም ይነሣሉ። በምድር የምትኖሩ ሆይ፥ ጠልህ የብርሃን ጠል ነውና፥ ምድርም ሙታንን ታወጣለችና ንቁ ዘምሩም።" (ኢሳ.26፥9፣19)፤

➣"ዛፍ ቢቈረጥ ደግሞ ያቈጠቍጥ ዘንድ፥ ቅርንጫፉም እንዳያልቅ ተስፋ አለው። ሥሩም በምድር ውስጥ ቢያረጅ፥ ግንዱም በመሬት ውስጥ ቢሞት፥ ከውኃ ሽታ የተነሣ ያቈጠቍጣል፤ እንደ አትክልት ቅርንጫፍ ያወጣል።" ( ኢዮ.14፥7-9)!

መልካም ጊዜ ተባረኩልኝ!
Dr. Beke
@nazrawi_tube
378 viewsΒενιαμίν, 16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 12:51:04 ናዝራዊ Tube pinned «#የእኔነት አባዜ፣ የግለኝነት ስካር! የዚህ ዘመን የቤተክርስቲያን አንዱ ምናልባትም ዋነኛው ተግዳሮት እኔነት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዞ ማገልገል፣ ተከባብሮ መንግሥቱን ማስፋት፣ አንተ ትብስ የሚል መንፈስ ጨርሶ እየጠፋ ይመስላል፡፡ ባመዛኙ በቤተክረስቲያን መካከል ያለ ክፍፍልም ምንጩ ይኸው ነው፡፡ እኔነት አዙሪቱ ከባድ ነው፡፡ እኔነት ራስን የማንገሥ ሩጫ ነው፡፡ እኔነት ዙሩ ሲከርር “ከእኔ…»
09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-02 12:50:01 #የእኔነት አባዜ፣ የግለኝነት ስካር!

የዚህ ዘመን የቤተክርስቲያን አንዱ ምናልባትም ዋነኛው ተግዳሮት እኔነት ሳይሆን አይቀርም፡፡ እጅ ለእጅ ተያይዞ ማገልገል፣ ተከባብሮ መንግሥቱን ማስፋት፣ አንተ ትብስ የሚል መንፈስ ጨርሶ እየጠፋ ይመስላል፡፡ ባመዛኙ በቤተክረስቲያን መካከል ያለ ክፍፍልም ምንጩ ይኸው ነው፡፡ እኔነት አዙሪቱ ከባድ ነው፡፡ እኔነት ራስን የማንገሥ ሩጫ ነው፡፡ እኔነት ዙሩ ሲከርር “ከእኔ በቀር!” ያሰኛል፤ ይህ ደግሞ አንጋጦ ከመትፋት አይተናነስም፡፡ “ከእኔ በቀር” ሊል የተገባው አንዱ አንድዬ ብቻ ነውና፡፡

ለእኛ “እኔነት” ከፍጥረታችንም ጋር እንኳ አይገጥምም፡፡ ስሪታችን በእኔነት ክንፍ ለብቻ ለመክነፍ የሚያበቃ አይደለም፡፡ አንዳችን ያለሌላችን ምንም ነን፡፡ የቤተክርስቲያን ክብር ደግሞ በአብሮነት ውስጥ የሚገለጥ ልምላሜ ነው፡፡ ማንም ብንሆን ለብቻችን ምንም ነን፡፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ ምንነታችንን በአካል መስሎ የሚያስተምረን፡፡ ከአካል ክፍሎች አንዱ የጎደለ እንደሁ፣ በሙሉነት መድመቅ አይቻልም፡፡ ያው “ጎዶሎ” የሚል ተቀጥላ ያስከትላል፡፡

ብቻ የመድመቅ አባዜ የሉሲፈር መንገድ ነው፡፡ የገነነ እኔነት ውስጥ ትእቢት አሸምቆ አለ፡፡ ዶ/ር ኃይሉ ቸርነት በአንድ ወቅት “ትእቢት በእኔነት ጢም ብሎ መሞላት ነው” ሲል ሰምቼዋለሁ፡፡ እውነት ነው፤ የገነነ እኔነት መጨረሻን ያከፋል፡፡ አብሮት በሚያገለግለው ወንድም ምክንያት በቂ ከበሬታ ያጣ የመሰለው ወንድም፣ “ሁለት ፀሐይ በአንድ ሰማይ ላይ አይደምቅም” በሚል አመክንዮ ከወንድሙ ተለይቶ ብቻውን የሚደምቅበትን የገዛ ቸርቹን ከፍቷል፡፡ (በነገራችን ላይ የአገልግሎት ጥሪ ግብ ራስን ማድመቅ ሳይሆን፣ ራስን መደበቅ ነው፡፡) እዩኝ እዩኝ ማለት የልከኛ መንፈሳዊነት መገለጫ አይደለም፡፡ የአገልግሎቱ እና የጸጋው አሠራር ግብ እርሱን እዩልኝ የማለት ነው፡፡

የዚህ ዘመን የአገልግሎት ዝንባሌ ግን ባመዛኙ ሐዲዱን የሳተ ይመስላል፡፡ የአዲስ ኪዳን ጸሐፍት አብሮነትን በእጅጉ ያበረታታሉ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ በአብዛኞቹ መልእክቶቹ ውስጥ እኔ በማለት ፈንታ “እኔና…” ሲል እናነባለን፡፡ ሰላምታ እንኳ ሲያቀርብ “እኔና አብረውኝ…” ይላል፤ ምን ጸጋ የበዛለት ቢሆን፣ ብቻውን እንዳልቆመ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡

አሁን የእኔነት አባዜ በእጅጉ ገንኖ ይታያል፡፡ እኔነት በአልባሌ ጭብጨባ ይፋፋል፤ ያልተካደ እኔነት የመስቀሉ ጠላት አድርጎ ያቆማል፡፡ የደረስንበት ጥግ እኔነትን የሁሉ መፍትሔ እና መላ አድርጎ እስከማቅረብ የተለጠጠ ነው፡፡ “እኔ እንደሌላው አይነት አይደለሁም” እስከማለት ደፍረናል፡፡

በየግል ቤተክርስቲያኖቻችን እንደነገሥን ለማሳየት በየደጆቻችንን ደማቅ ፎቶዎቻችንን በየአቅጣጫው ሰቅለናል፡፡ በየመርሐግብሮቻችን “ዋነኛው እኔ ነኝ!” ለማለት፣ ከጋበዝናቸው ሰዎች አናት ላይ ደማቅ ፎቶዎቻችንን እናኖራለን፡፡ በአዳራሹ መካከል የተለየ የከበሬታ ወንበር አሰናድተን በእርሱ ላይ እንሰየማለን፤ በሌለን ጊዜ እንኳ ሌላ አይቀመጥበትም፡፡ ክርስቶስ ራስ በሆነለት አካል ውስጥ፣ ከአካሉ ብልቶች መካከል እንደ አንዱ በመሆን ፈንታ፣ ከ“ራሱ” በላይ ጠቃሚ መሆናችንን ለፍፈን በሕዝቡ ላይ ሰልጠነናል፡፡ የመለኮት ሙላት ሁሉ ተጠቅልሎ እጃችን እንደገባ አምነን በእኔነታችን ሰክረናል፡፡ ክርስቶስ በእኛነታችን እንዳይገለጥ እኔነት ትልቁ መጋራጃ ነው፤ ቢያምም የእኔነትን መጋረጃ ገፍፎ መጣል የተገባ ነገር ነው፡፡

ይኸው ሩጫችን ደግሞ መጨረሻ ያለው አይመስልም፡ በየዕለቱም በእኔነት የፋፉ ሰዎች ብቅ ብቅ እያሉ ነው፡፡ በዘመን እላቂ እንደመኖራችን ብዙ ተስፋ ማድረግ ላይኖርብን ይችል ይሆናል፡፡ ነገር ግን ደግሞ ልኩ ይኸው መስሏቸው በቅንነት እና ባለማወቅ በዚህ መንገድ የተጠመዱትን ማዳን ይቻል እንደሆን እውነትን እንናገራለን፡፡ ከገነነ እኔነት መዳን ከብዙ ነገር መዳን ነው፡፡ የእኔነት ስካር ወስዶ ወስዶ የት እንደሚደፋ አይታወቅም፡፡ ከእኔነት መዳን ሌለውን በልኩ ለማየት እና ንጉሡን በእውነት ለማላቅ ዕድል ይሰጣል፡፡

ሕዝብ ሁሉ ግርርርር ብሎ ይከተለው የነበረው መጥምቁ ዮሐንስ በጮክታ “እኔ አይደለሁም!” ብሎ ወደ መሲሁ እጁን ጠቁሟል፡፡ ይህ አይነተኛው ማምለጫ ነው፡፡

“እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።” ዮሐ 3፡30

መጋቢ ስንታየሁ በቀለ
@nazrawi_tube
578 viewsΒενιαμίν, 09:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-01 11:03:17 ሶስት እግዚአብሔር ?

የክርስትና ልዩትነት የነገረ መለኮት መፅሐፍ ቅዱሳዊ አረዳዳችን ነው።ለቃሉ ታማኝ መሆን ፣ያለውን ማለት ፣ተቀበሉ ያለንን መቀበል ነው ።እንደምንፈልገው ቅዱስ ቃሉ እንዲፅፍልን አናስገድደውም ይህንን እንዲህ ቢፅፈው ጥሩ ነበር ብለን ስሁት ሙግት አንገጥምም ይልቅ ቃሉ ምን ይላል ብለን እንጠይቃለን ያለውን እናምናለን ።

የነገረ መለኮት አረዳዳችን ይህንን ታሳቢ ያደረገ ነው ። ነገረ ክርስቶስ (christology )ነገረ መንፈስ ቅዱስ (pnumatology ) ነገረ ሥላሴ (Trinity )ነገረ መፅሐፍ ቅዱስም ቢሆን ሌሎቹም በዚህ አረዳድ ያዋቀርናቸው ናቸው ።

ይህ እንዲሁ እንዳለ ስለ ነገረ ሥላሴ ሲነሳ ሁለት ነገሮች መነሳታቸው ግድ ነው ብዬ አስባለሁ ።

አንደኛው የትምርቱ እውተኛነት ነው ። መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአጥጋቢ መረጃዎች የተሰጠን አስተምህሮ ቢኖር ወይም በአጥጋቢ መረጃ የተደራጀ ትምህርት ቢኖር ነገረ ሥላሴ ነው። ከዘፈጥረት ጀምሮ እስከ ራዕይ ድረስ መረጃዎችን ( biblical data)ማቅረብ እንችላለን ።

ሁለተኛው ደግሞ ክርስቲያኖች ስለዚህ ትምርት ያላቸው መረጃ አናሳነት ነው ።ይሄ አሳሳቢው ጉዳይና ሁሉም ሊሰራበት የሚገባው አንገብጋቢ የቤት ስራ ነው ። ወደ ጉዳዬ ስመለስ ነገረ ሥላሴ ማለት ሌላ ነገር አይደለም የመፅሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር ማለት ነው ። ይህንን እንዲህ ብለን ልንገልፀው እንችላለን እግዚአብሔር ሥላሴ ነው።

ይህ ማለት አንዱ እግዚአብሔር (መለኮት )ሶስት የተለያዩ አካላት እንዳሉት (distinct personality ) የተገለፀበት ነው ።እግዚአብሔር አብ እግዚአብሔር ወልድ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ !! ይህንን እኛ ፈልገን ያደረግነው ሳይሆን መፅሐፍ ቅዱስ የነገረን እውነታ ነው ።

ታዲያ የስላሴ አማኝ ያልሆኑ ሰዎች ስለ ሶስት እግዚአብሔሮች እንደምናስተምርና ይህም ትምርት ከአንድ በላይ እግዚአብሔር እንዳለን የሚያሳይ ነው በማለት ሲወነጅሉ ይታያሉ። ነገርን ከስሩ እንደሚባለው ምን ታምናላችሁ ተብለን መጠየቅ ያለብን እኛ ነን እንጂ እንዲህ ታምናላችሁ ስለዚህ እንዲህ ናችሁ ተብለን ልንፈረጅ አይገባንም።

እኛ አንዱ እግዚአብሔር ሶስት አካለት አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አሉት አልን እንጂ ሶስት እግዚአብሔር አሉን አላልንም ።አስተምህሮተ ሥላሴ ስለ ሶስት እግዚአብሔር የሚያስተምር ሳይሆን ስለ አንድ እግዚአብሔር እንዲሁም ስለ ሶስት አካላት የሚያስተምር መፅሐፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ነው ።

አንድ እግዚአብሔር አለን!

“#አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5

ሶስት አካላት

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ #በአብ #በወልድና #በመንፈስ_ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”
— ማቴዎስ 28፥19-20

Girum difek
@nazrawi_tube
210 viewsΒενιαμίν, 08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-31 20:03:14
ኤይደን ዊልሰን ቶዘር
(መንፈሳዊ ስብከትን በተመለከተ የተናገሩት)

ሰባኪን በሰዓሊ እመስለዋለሁ፡፡ ሰዓሊ በውኃ፣ በዘይት፣ በአሸዋ፣ በድንጋይ፣ በወርቅና በመስተዋት ነው የሚሠራው፡፡ በተቃራኒው ሰባኪ የሚሠራው የሰው ልጅ ላይ ነው፡፡ ሰዓሊ አንድ ያሰበውና በልቡናው ያየው ውበት አለ፤ ያንን ነው ለማየት በስዕሉ የሚተጋው፡፡ ሰባኪ ደግሞ በልቡ የተሳለውን ክርስቶስ ነው በሰዎች ሕይወት ለመሳል የሚጥረው፡፡ ሰዓሊ የስዕል ክህሎት ሲኖረው፣ ሰባኪ መንፈስ ቅዱስ ነው ያለው፡፡ ሰዓሊው ያንን ብርሃንና መረዳት የሚቀበለው ከሌሎች ሰዓሊዎች ነው፡፡ ሰባኪ ግን በጸሎት ከአምላኩ ይቀበላል፡፡

ሰዓሊ ብሩሾች፣ መንደፊያ ሸራና ቀለም ይኖሩታል፡፡ ሰባኪ ግን ቃሎች ናቸው ያሉት፡፡ ዘጠና በመቶ አገልግሎቱ ቃላትን በመጠቀም ነው፡፡ ስለዚህ እንደ ሰዓሊ ሥራውን በሚገባ ማወቅ ይገባዋል፡፡ ብዙ ትጋትም ያስፈልገዋል፡፡ ሲጀምር ብዙ መስማት የማይገባቸው ስሕተቶች ይሠራ ይሆናል፡፡ እያደር ግን የተዋጣለት ሠራተኛ መሆኑ የማይቀር ሃቅ ነው፡፡

@nazrawi_tube
580 viewsΒενιαμίν, 17:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ