Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.51K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On YT sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 21

2022-10-24 20:18:48 https://telegra.ph/ዳግማዊ-አበርክቶት---በአገራችን-ስለ-ወንጌል-ሰማዕት-ለሆኑ-10-24
2.0K viewsΒενιαμίν, 17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 20:10:02 https://telegra.ph/ዳግማዊ-አበርክቶት---በአገራችን-ስለ-ወንጌል-ሰማዕት-ለሆኑ-10-24
2.8K viewsΒενιαμίν, 17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 10:11:29 የመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች ነን? እንዴት? የእግዚአብሔር ልጆችስ ነን? እንዴት?
ክፍል አንድ

የመለኮት ባሕርይ ተካፋይነት ጥቅስ በ2ጴጥ. 1፥4 የሚገኘው ነው። ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን። 2ጴጥ. 1፥4

መጀመሪያ ያልሆንነውን ነገር እናስተውል።

1. እኛ መለኮት አይደለንም። መለኮት አንድ ብቻ ነው። እኛ አማልክት አይደለንም። እኛ በምድር ላይ ውር ውር የምንል ትንንሽ እግዚአብሔሮች አይደለንም። መዝ. 82፥6 ላይ የሚገኘው፥ እኔ ግን፦ አማልክት ናችሁ፥ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ፤ የሚለው ቃል ስለ አምላክ ሳይሆን ስለ ሰዎች እንደሚናገር ቀጥሎ ቁጥር 7 ላይ ያለው፥ ነገር ግን እንደ ሰው ትሞታላችሁ፥ ከአለቆችም እንደ አንዱ ትወድቃላችሁ አልሁ። የሚለው ቃል ይመሰክራል። አምላክ አይሞትምና እነዚህ ከሞቱ ቃሉ ስለ መለኮት አለመናገሩ መሆኑን እናውቃለን። ጌታም በዮሐ. 10፥34 ኢየሱስም እንዲህ ብሎ መለሰላቸው፦ እኔ፦ አማልክት ናችሁ አልሁ ተብሎ በሕጋችሁ የተጻፈ አይደለምን? ብሎ ሲጠቅስ ያንኑ አሳብ መግለጡ ነው። ቃሉ ኃያላን፥ ክቡራን ማለት ነው። ‘እነዚያ እንኳ እንደዚያ ከተባሉ፥ እኔ ከአብ የመጣሁት ያንን ብል ተገቢ ነው።’ ማለቱ ነው።

2. እኛ በፍጥረታችን የመለኮት ባሕርይ የለንም። ስንፈጠር ሰዎች ነን እንጂ አማልክት ወይም መናፍስት አይደለንም። ሕይወት ያለን፥ የሕይወት እስትንፋስ እፍ የተባለብን፥ ሕያዋን ወይም ከተፈጠርንባት ቅጽበት ጀምሮ ዘላለማውያን የሆንን ሰዎች ነን። ይህ ስለ አዳምም ስለ እኛም፥ ወይም በአዳም በኩል ስለ እኛም ነው።

3. የመለኮት ባሕርይ ተካፋይነት በምንም መልክ የክርስቶስ እኩዮች ወይም አቻዎች አያደርገንም። ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው፤ ወይም ከሥላሴ አካላት አንዱ ነው። እኛ ግን ፍጡራን እና ፍጡራን ብቻ ነን።

4. የኛ ልጅነት ከክርስቶስ ልጅነት በሁሉ ረገድ፥ በመልኩም፥ በዓይነቱም፥ በደረጃውም የተለየ ልጅነት ነው። ግን ልጅነት ነው። እኛ ልጆች የተደረግን ልጆች ነን። ጌታ፥ ‘አባቴና አባታችሁ’ ሲል ይህንን ያሳያል። ‘አባታችን’ አላለም። “‘አባቴና አባታችሁ’ ሲል ያው አባት አንድ መሆኑን መናገሩ ነው፤ አይደል?” ሊባል ይቻላል። ልክ ነው፤ አባት አንድ ነው፤ አባትነቱ ግን የተለያየ ነው። ‘አባታችን ሆይ’ ብለን እንጸልይ የል?’ ሊባል ይቻላል። አዎን፤ ግን፥ ‘ብላችሁ ጸልዩ’ ነው ያለው። እዚያው ያንን ባስተማረበት ክፍል ውስጥ፥ ‘የሰማዩ አባታችሁ’ እያለም አስተምሯል፤ ‘የሰማዩ አባታችን’ አላለም። ለአይሁድ አባታችን እያለ ሳይሆን አባቴ እያለ መናገሩ ምን ማለቱ እንደሆነ፥ በግልጽ ራሱን ከአብ ጋር ማስተካከሉ እንደሆነ ገብቷቸዋል። ሊወግሩት የቃጡት አሳልፈውም የሰጡት ስለዚህ ነው። ይሁን እንጂ ልጆች ሆነናል፤ በመደረግ።

5. እኛ ከፍጥረታችን ወይም በተፈጥሮአችን የአዳም፥ የወደቀው አዳም ልጆች ነን። በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ኤፌ. 2፥3። እነዚያ ‘የአብርሃም ልጆች ነን’ እያሉ ለሚኩራሩት የአብርሃም ሳይሆን የዲያብሎስ ልጆች መሆናቸውን በግልጽ ነበር የነገራቸው፤ ዮሐ. 8፥39-44።

ቀጥሎ የሆንነውን እንመልከት። . . .

ይቀጥላል።

ዘላለም መንግሥቱ
@nazrawi_tube
2.0K viewsΒενιαμίν, 07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 09:34:14 ቅዱስ አውግስጢኖስ (354-430)

በነገረ መለኮት እውቀቲ ትልቅ ተጽእኖን የፈጠረው (The most influential theologian ever!) ቅዱስ አውግስጢኖስ በ32 ዓመቱ በንግግር ጥበብ (Rhetoric፡-the art of effective or persuasive speaking or writing) የፕሮፌሰር ማዕረግ ያገኘ ሲሆን፣ በአፍላ የወጣትነት ፈተና መከራውን አይቷል፡፡ በልቡ ክርስቶስ እውነት እንደ ሆነና ከጋብቻ በፊት ወሲብ መፈጸም ደግሞ ልክ እንዳልሆነ ቢያውቅም፣ ያለ ወሲብ ሕይወት ምንም ጣዕም እንደሌለው ነበር የሚያስበው፡፡ በዚያ የሕሊና ግጭትም ከባድ ወቀሳ ነበረበትና እጅግ ብዙ ተቸግሯል፡፡ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጪ መሆኑን በመረዳቱም ራሱን እስኪጠላ ድረስ ይጨነቅ ነበር፡፡

አንዲት ልዩ ቀን በአስጨናቂ ሁኔታ በልቅሶ (ተማጽኖአዊ) ውስጥ እያለ ከአቅራቢያ ጎረቤት ያሉ ሕጻናት “አንሣና አንብበው አንሣና አንብበው” እያሉ ሲዘምሩ ሰማ፡፡ ወዲያው “ይህ መልእክት ከእግዚአብሔር ቢሆንስ?” ብሎ አስቦ የያዘውን መጽሐፍ ቅዱስ አንሥቶ ሲገልጠው፣ ሮሜ.13፥13-14 ላይ ያለውን መልእክት አገኘና አነበበው፡፡ ምንባቡ እንዲህ ነው የሚለው፡-“በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም ለሥጋ አታስቡ።”፡፡

መልእክቱን አንብቦ ሲጨርስ በሚገርም ሁኔታ ተለወጠ (At once, with the last words of this sentence, it was as if a light of relief from all anxiety flooded into my heart. All the shadows of doubts were dispelled.)፡፡

ከዚያ አስደናቂ ለውጥ በኋላ ቁርጠኛ ደቀ መዝሙር በመሆን ስለ ተጋ በአጭር ጊዜ እስከ ጵጵስና ማዕረግ የደረሰ የነገረ መለኮት ሊቅ ሲሆን፣ በብዙ መንፈሳዊ ነገሮች የክርስቲያን አማኞችን አስተሳሰብ የለወጠ የእምነት አርበኛ ነው (ከጌታ ኢየሱስና ከሐዋርያው ጳውሎስ ቀጥሎ ታላቅ ተጽእኖን የፈጠረ)፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራዎችን ለንባብ ያቀረበ ሲሆን፣ Confessions እና City of God እስከ አሁንም ድረስ እጅግ በጣም ተወዳጅና ተነባቢ ሥራዎቹ ናቸው፡፡ (Gerald R.McDermott, The Great Theologians, 49-62)

➢Faith is to believe what you do not see; the reward of this faith is to see what you believe.

➢Pray as though everything depended on God. Work as though everything depended on you.

➢If you believe what you like in the Gospel, and reject what you don't like, it is not the Gospel you believe, but yourself.

➢In order to discover the character of people we have only to observe what they love.

መልካም ቀን ተባረኩልኝ!
Dr. Beke
@nazrawi_tube
2.5K viewsΒενιαμίν, 06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-22 00:24:06 ስሙልኝ እስቲ

@nazrawi_tube
2.0K viewsΒενιαμίν, 21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ