Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.01K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On Utube sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-01-28 11:22:38 መጽሓፍ ቅዱስ ስለ ምስላዊ እይታ (Visualization ) ያስተምራል?( Does the Bible teach about visualization?)

እባካችሁ ይነበብ...... ይነበብ !

አዲሱ ዓመት ከገባ ወዲህ በከፍተኛ ፍላጎትና መደነቅ ( with passion and fascinated) በጥልቀት እያነበብሁና ጥናት እያደረግሁ ያለሁት ሰለ ኳንተም ፊዚክስ ፣ ስለ ጥንታዊ ኅይማኖቶች ልምምድ እና ወጎቻቸው ነው። በርዕሰ - ጉዳዩ ላይ በጥልቀት ለማንበቤ ምክንያቱ "ንጹሁ የጸጋ ወንጌል" በከፍተኛ ሁኔታ ከዘመናዊው የሳይንስ መንፈሳዊ አስተሳሰቦች፣ ከጥንት ኅይማኖታዊ ልምምዶች እና ወጎች ጋር እየተቀየጠ እና እየተሸቀጠ የመምጣቱ አደጋ ነው። ይህንን ስመለከት በእውነት( really) አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የወንጌሉ ማዕከላዊ ጽንሰ ሓሳብ ገብቶናል ወይ? በእውነትና በትክክለኛ መንገድስ እግዚአብሔርን እናውቀዋለን ወይ ? እኛ ስለ ወንጌል እና ስለ እግዚአብሔር ያለን አስተሳሰብ የተለየ ( different) እና መጽሓፍ ቅዱስ እንደሚለው ዓይነት ባይሆንስ ብዬ ጥያቄ እንዳነሳ እገደዳለሁ። አዲስ ኪዳን ስለ "ሌላ ኢየሱስ፣ ስለ ልዩ ወንጌል፣ ስለ ልዩ መንፈስ ማንሳቱ እሙን ነው( 2ቆሮ11፣ 4) ። እዚህ ላይ ስማቸውን መጥቀስ አያስፈልገኝም እንጂ አንዳንዶች ችግሩን ቀድመው አይተውታል :: ምናልባትም አሁንም ዐይናቸውን ጥለው የአገሪቱን መንፈሳዊ አካሄድ የሚከታተሉ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ አስባለሁ።

ምንም እንኳ ከምድሪቱ በአካል ርቄ የምኖር ሰው ብሆንም ፣ ይህ ዘመናዊና ሳይንሳዊ ኅይማኖታዊ አስተሳሰብ፣ የጥንት ኅይማኖቶች ልምምድና ወግ ግን በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ አብላጫው ወጣት እና ምሁር እየተወሰደበት እንዳለ አስተውላለሁ። የነገረ ክርስትና መጽሔት አዘጋጁ ሽመልስ ይፍሩ በአንድ አስተያየቱ ላይ እንዳለው “ ጉዳዩ በአነቃቂ ተናጋሪዎች እጅ ከመግባቱ በፊት በአንዳንድ የወንጌላውያኑ ሰባኪ እና አስተማሪ - ፓስተሮች (ነብያት) እጅ ገብቶ ነበር" ብሏል። እውነቱን ነው ። አስተሳሰቡ ከታችኛው ክፍል (from the Grassroots ) እስከ ላይኛው የመንግሥት ባለ ሥልጣናት ውስጥ ሰርጾ ስታዩ፣ አንዳንዴም አገር በዚህ ዓይነት አስተሳሰብና ፍልስፍንና ትመራለች እንዴ ? ብላችሁ እንድትጠይቁ ያደርጋችኋል። ከጉዳዩ አሳሳቢነት የተነሳ በዛሬው ጽሑፌ የማነሳላችሁ ርዕሰ ጉዳይ ስለ ምስላዊነት ወይም “የዐይነ - ሕሊና አይቶታ” (Visualization) ነው።

በእርግጥ ምስላዊነት (Visualization) የአእምሮአችን ምስል (images) ሂደታዊ ውጤት እንደሆነ የሙያው ተንታኞች ይናገራሉ። ብዙውን ጊዜ ምስላዊነት (Visualization) ያልተከሰቱና ገና ሊገሰቱ ዝግጅት ላይ ያሉ ሁኔታዎችን የማየት አቅም ነው፤ ይሁን እንጂ እንደ ሁኔታው፣ እንደ ምስላዊነቱ እና ምስሉ (Visualization and images) ምክንያቶች ( reasons) ፤ በመንፈሳዊ ጤናማ የሆኑ ወይም በመንፈሳዊ ጤናማነት የጎደላቸው ሊሆኑ ይችላሉ።

ለምሳሌ አንድ የቅርጫት ኳስ ተጨዋች የቅርጫት ኳስ ግጥሚያ ላይ እንዴት አስቸጋሪ ሁኔታዎችን እያለፈ በቅርጫት ኳስ ጨዋታው ለቡድኑ ነጥብ ሊያስመስገብ እንደሚችል፣ ምን ቢያደርግ ደግሞ ተሳክቶለት ዋንጫዋን እንደሚያገኝ በዓይነ ሕሊናው አስቀድሞ ሊያይ ይችላል። ወይም ደግሞ አንድ አትሌት ከበቂ አካላዊና ሥነ - ልቦናዊ ዝግጅቱ ውጭ በውድድሩ ላይ በየትኛው ጊዜ ምን አድርጎ አሸናፊ ሊሆን እንደሚችል፣ ውድድሩን ከመጀመሩ በፊት በዓይነ ሕሊናው ሊመጣበት ይችላል ። ሙዚቀኞች፣ ተዋናዮች፣ ጸሓፊዎች እና ሌሎች አርቲስቶች ከመፃፋቸው ወይም ከመስራታቸው በፊት በአእምሯቸው ውስጥ ምስሉን (images ) ለመፍጠር ምስላዊነትን (Visualization) ሊጠቀሙ ይችላሉ።

ማንም ሰው አእምሮውን እስካልጣለ ድረስ በተወሰነ ደረጃ ምስላዊነትን (Visualization) መጠቀሙ ተፈጥሮአዊ ነው። አንዳንድ ጊዜ ወደ ዘመናዊው "ኩቺና" አማርኛው ቀጥታ የላቲን ቃል እንደሆነ ልብ በሉ ( kitchen) ገብቼ ቁርስ ፣ ምሳ ወይም እራት አንዳንዴም ለእንግዳዎቻችን ምግብ ከማብሰልና ከማዘጋጀቴ በፊት በዐይና ሕሊናየ እስከ ውብ / አርቲስቲክ አቀራረቡ ድረስ አየዋለሁ። ምን አይነት ሳህን ፣ ምን አይነት ብርጭቆዎችና የጠረጴዛ ልብስ እንደምጠቀምና ስለ አበባውና ሻማዎቹ አስባለሁ :: ማናችንም ውይይቶች እና ስብሰባዎችን ከመምራታችን በፊት አስቀድሞ ምን ብናደርግ ምን አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ነገርም ሊከሰት እንደሚችል እናስባለን ። ምስላዊነትና ምስል (Visualization and images) በየእለት እርምጃዎችንን ከመውሰዳችን በፊት እራሳችንን የምናዘጋጅበት ተፈጥሮአዊ መንገድ ነው። በዚህ መንገድ ኢ- መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ ነገር የለውም። እንዲያውም እርምጃ ከመውሰዳችን በፊት ውጤቱን ማጤን ብልህነት ይሆናል (ሉቃስ 14፡28)።

ይህ አይነቱ አእምሮአዊ ሂደት ለክርስቲያኖች ኢ መጽሓፍ ቅዱሳዊ የሚሆነው ግን ከጉሩዎች የአስተሳሰብ ፍልስፍናና ልምምድ ጋር ሲያያዝ ነው ። ይህን ነገር በአሁኑ ወቅት በቀጥታና በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ውስጥ ተስፋፍቶ ይታያል ። ዘመናውያኑ የራስ አገዝ ጉሩዎች ( modern self-help gurus) ብዙውን ጊዜ እውነታውን ለመለወጥና የሚፈልጉትን በቀላሉ ለማግኘት ምስላዊነትን ( Visualization) ይለማመዳሉ :: ሌሎችም እንዲለማመዱት ያስተዋውቃሉ ፣ ያስተምራሉ ፣ መጽሓፍቶች ይጽፋሉም። ይህን “የፈጠራ ምስላዊነት” ( creative visualization,”) ብለው የሚጠሩት ሲሆን፣ በዚህ ቴክኒክ፣ በሰው የአእምሮ ኅይል ላይ ተመስርተው ከገንዘብ ስኬት እስከ ተሻለ የፍቅር ሕይወት ፣ የአንድን ሰው ሀሳብ “ቁሳዊ” ለማድረግ፣ ስኬትን “መሳብ” እና ተመራጭ እውነታን “መፍጠር” እንደሚቻል ቃል ገብተዋል።

ይህ የአዲሱ ዘመን ሰብአዊነት ( New Age humanism) አመለካከትና ፍልስፍና ፈጽሞ መጽሓፍ ቅዱሳዊ አይደለም ። በራሱም ደግሞ ምንም እንዳይደለ እና ኢ መጽሓፍ ቅዱሳዊ እንደሆነ ንቁ ነገረ መለኮታውያን ይናገራሉ። ይህ በሰብአዊ የአዕምሮ ኅይል ላይ የተመሰረተው ኢ- መጽሐፍ ቅዱሳዊ ልምምድ ከመሳብ ህግ ( law of attraction)፣ ከአዎንታዊ አስተሳሰብ ኅይል ፣ ከቃለ- እምነት እና የብልጽግና ወንጌል ( word of faith and Prosperity Gospel) የውሸት ትምህርቶች እና ተስፋዎች ጋር የተያያዘ ነው።

ናፓሊዮን ሂል እና ሌሎች ተመሳሳይ ጸሃፍት አስተሳሰቡንና ፍልስፍናውን ሲያስፋፉ በምንም ዓይነት መልኩ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የምናወራለትን መንፈሳዊነት በማሰብ አይደለም። አንዳንድ የሩቅ ምስራቅና የምዕራባዊያን የመጽሓፍ ቅዱስ ሰባኪዎችና አስተማሪዎች ግን ሓሳቡን ከሚስማማ የመጽሓፍ ቅዱስ ጥቅስ ጋር በማዳቀል ልምምዱ በቤተ ክርስቲያን እንዲገኝና ንጹሑም የጸጋ ወንጌል እንዲበረዝ አድርገዋል ። ከብዙዎቹ አንዱን ልጥቀስ። ለምሳሌ፦ በአንድ ወቅት ኮርያዊው ሰባኪ ፓስተር ዲቪድ ዋንኪቾ ከዚህ አስተሳሰብ በተቀዳ “የማየት ሕግ” የሚል ርዕሰ በተሰጠው ኢ- መጽሓፍ ቅዱሳዊ ትምህርቱ “የምትፈልጉትን ነገር በዐይነ ሕሊና አይቶታችሁ” በውስጣችሁ ሳሉት፣ በመቀጠልም ትኩር ብላችሁ እየተመለከታችሁ በውስጣችሁ ጽንሱት፣ የጸነሳችሁትን በእምነት ትወልዱታላችሁ
1.2K viewsΒενιαμίν, edited  08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-26 20:38:11 Q: ይኼኛው አካኼድ ከድጥ ወደ ማጥ መሆኑን አይተናል። አሁንስ ብንመለስ ምን ይሆናል?

“ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን?” (ሮሜ. 2:4)

በክርስትና እምነት ከሚገኙ መንፈሳዊ ልምምዶች አንዱ ኃጢአትን የመናዘዝና ተጸጽቶ በንስሓ የመመለስ ልምምድ ነው። ንስሓና መመለስ አንዴ ለሁሌ ሳይሆን በቃሉ መነጽር ሕይወታችንን እየፈተሽን አካኼዳችንንም በመንፈሱ ሚዛን እየመዘንን በየጊዜው የምንፈጽመው ክርስቲያናዊ የእርምት እርምጃ ነው።

ንስሓ በኔ እምነት ምዕመናን ኃጢአታቸውን ተናዝዘው፥… በድርጊታቸው ተጸጽተው፣ … ወደ ፊት ሌላ ጊዜ ወደዚያ ትፋት ላይመለሱ ወስነው፥… የጌታን ምሕረትና ይቅርታ ለመቀበል ወደ ፊቱ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው የሚቀርቡበት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት ነው።

ንስሓ በተለያዩ ጥፋቶች ውስጥ የሚገኝ ሰው ራሱን የሚያነጻበት ሻወር ነው። የልጁ የክርስቶስ ኢየሱስ ደም ከኃጢአት ሁሉ እንደሚያነጻ ያመነ ሰው ከቁጭትና ከሕሊና ጸጸትም የሚጸዳበት ሳሙና ነው ንስሓ። ንስሓ ሁለንተናን ከዕድፍና ከጉድፍ ያጠራል። “ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤ የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል። (ምሳ. 28:13) በተባለው መሠረት መናዘዝ፣ መመለስ፣ መተው በንስሓ ውስጥ አሉ።

ባለንበት ዘመን በምትገኝ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከመቼውም በላይ ዓለማዊነት፣ አመጸኝነት፣ ግፈኝነት፣ ጨካኝነት፣ ጠላትነት፣ ቂም በቀለኝነት፣ ርኩሰት፣ ዝሙት፣ መዳራት፣ ስካር … ሁሉ ልንደብቀው በማንችልበት ሁኔታ ሞልቶ ወደ ውጪ እየፈሰሰ ነው። በዚህም ምክንያት ትዳር እየፈረሰ፣ ኑሮ እየታመሰ፣ ሕይወት በብዙ ውጥንቅጥ ውስጥ እየገባ ነው። ማኅበረሰብ ገብቶ በማያውቀው የሕይወት ዝቅጠት ውስጥ ገብቶአል። በዘመነ ኤሊ ክብር በሌለበት ኢካቦድ ሆኖ እየተሸነፈችና እየተማረከችም እሥራኤል እልልታዋ ደማቅ ጩኸቷ ከፍተኛ እንደነበረ ያንን እየደገምን ኖረናል።

የልጅነትና የቃል ኪዳን ሚስታቸውን ፈትተው ልጆቻቸውን ሜዳ ላይ በትነው ሌላ ሚስት ያገቡትን ሰዎች በአደባባይ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት መሪ ወደ ማድረግ ተደርሷል። አስደንጋጭ የነበሩ ነገሮችን ለምደን ቤተኛ አድርገን ኖረናል። በጣም ግዴለሾች ሆነናል። ከጋብቻ በፊት በሚደረጉ ወሲባዊ ልምምዶች ውስጥ ከርመው እያስረገዙና እያስወረዱ መሆናቸው እየታወቀ ሰዎችን ማስጨፈር ስለቻሉ ብቻ በታላላቅ የአደባባይ ላይ ኮንፈራንሶች የሚጋበዙ አገልጋዮች ቁልል ናቸው። ቁጥር አይገልጻቸውም። የወንጌል አማኞች የምናምነው ወንጌል የቱ እንደሆነ በሚያጠያይቅ ደረጃ በርዘናል። ዝሙት በመዝሙር ካባ ይሸሸጋል።

በርግጥ አስተውለን ከሆነ ራሳቸውን ወደ እግዚአብሔርነት ያጠጋጉ አስተምህሮዎችን አምጥተውብናል የምንላቸው “መንፈስ ነን” ባይ የርኩሰት መምህራኖች ከዘሩት መራራ ዘር አንዱ “በሥጋ የምንፈጽመው ማንኛውም ነገር ከሟችና ፈራሽ ሥጋ ጋር ይቀራል እንጂ መንፈሳችንን አያረክስም” የሚል ነው። ይኼው አደናቃፊ ክፉ የአጋንንት ትምህርት መናዘዝንና ንስሓን ከቤተ ክርስቲያን አካባቢ አርቆአል። እነዚህ የሰይጣን መልዕክተኞች ፍልፈል ላይ እንሰት ተካይ ተላላ ትውልድ አፍርተዋል።

ቃሉ ግን በግልጽ “በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።” (1ዮሐ. 1:9) ይላል። የወንጌል አማኞች ነን የምንል ወገኖች በዓለም ዘንድም የነበረንን ክብርና ሞገስ ባጣንበት በዚህ ሁኔታ አማኙ ማኅበረሰብ ንስሓ ገብቶ ክርስቶስን ወደ መምሰል ተልዕኮውንም ወደመፈጸም እንዳይመለስ በውድቀቱ እንዲጸና ካደረጉት ከንቱ አስተምህሮዎችና ልምምዶች ለመውጣት ከኃጢአታችን መናዘዝና በንስሐ መመለስ አማራጭ ሳይሆን ግዴታ ነው። ጥያቄዬ ወደዚያ የቀደመው ልምምድ ብንመለስ ምን ይሆናል? የሚል ነው።

ሰዎች በኃጢአት ሲገኙ ወይም ድንገት ሲሰናከሉ ተናዝዘው በንስሓ ከመመለስና ለቃሉ ሥልጣን ከመታዘዝ ይልቅ አስጨፋሪና አዝናኝ ዜማ ባላቸው ዝማሬዎች ሥር ራሳቸውን ሸሽገው ምንም እንዳልተፈጠረ በማስመሰል እልልታቸውን አድምቀው ተጯጩኸው ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ የሚያደርግ ልምምድ እነዚህን አዳዲስ #ቃል አልባ ቃል አውጪዎችን ተከትሎ ወደ ወንጌላውያን አማኞች ኅብረት ሰተት ብሎ ገብቶአል። ይኼንን ከንቱ ልምምድ ጠራርገን ለማስወጣት ወደ ቃሉ ልምምድ መመለስ የግድ ነው።

የንስሓ… የጸጸትና የመመለስ ሕይወት ከሌለን ራሳችንን እያሳትን፣ ምንም ሳንሆን የሆንን እያስመሰልን፣ እንደተለሰነ መቃብር ውጪውን አሳምረን በውስጣችን ግን በስብሰን መቅረታችን አይቀርም። “… ነገር ግን ንስሐ ባትገቡ ሁላችሁ እንዲሁ ትጠፋላችሁ።” (ሉቃ. 13:3) ተብሏልና። “ሊቆም አይችልም ነገሬ፣…” “ጩኸት አለኝ እኔስ ጩኸት…” “ነገር አለኝ እኔስ ነገር…” በሚሉና በሌሎችም ከዝሙትና ከመዳራት ከስካርም መልስ በተገኙ የማደናገሪያ አስጨፋሪ ዜማዎች መዝለል አዋጭ አካኼድ አይደለም። አዎን አይደለም። እኔ በበኩሌ በነዚህ ዘፈኖች መዝለል ካቆምኩ ሰነበትኩ። ምንጩን ልይቻለሁ። ወደ ቀደመው ከጥፋት በንስሓ የመመለስ ልምምድ መመለሱ ይሻላል።

“ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን?” (ሮሜ. 2:4)

ወርቅነህ ኮይራ
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
1.7K viewsΒενιαμίν, 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-23 11:45:38 ሃገራዊ ቤተ ክርስቲያኖች (National Churches)

እንዲህ እንደዛሬው Free Churches (ነጻውያን) ከመብዛታቸው በፊት ሃገርን የሚወክሉና በሃገርም የሚወከሉ ቤተ ክርስቲያናት ብዙ ነበሩ። እንደ ምሳሌ የጀርመኗ ሉተራውያን፣ የእንግሊዟ አንገሊካን፣ የራሺያዋ ኦርቶዶክስ፣ የኢትዮጵያዋ ኦርቶዶክስ ... ወዘተረፈ ይዬኹሉ መጥቀስ ይቻላል። እነዚህን ሁሉ ለመዘርዘር አይደለም የዚህ ልጥፍ ዓላማ።

የሃገራዊ ቤተ ክርስቲያን ባሕርይ እና በመቦዳደስ የተከፈቱ (የተተከሉ አልልም መቼም) ጠባይ ለየቅል ነው። የ free churchesም ባሕርይ ይለያል፤ በተለይ አሁን አሁን ሃገራችንን ከወረሩት Customers Oriented Churches በጣም ይለያል። እነዚሁ Customers Oriented Churches ደግሞ ሃገራዊ ቅኝትና ሃገራዊ ይዘት ያላቸውን 'ሲዘልፉ'ና ንግርት ሲያወጡባቸው (ያው ትንቢት ነው የሚሉት እነሱ) የባሰ ግራ ያጋባል።

መጀመሪያ ቤተ ክርስቲያን ሁኑ! ምክሬ ነው። What makes the church - church? የሚለውን ጥያቄ አስቀድማችሁ መልሱ። ዘመንና የሚለዋወጥ ጊዜ ቤተክርስቲያንን ቤተክርስቲያን አያደርጋትም። መንግሥታዊ ድጋፍም ይሁን ፈቃድ ቤተክርስቲያንን ቤተክርስቲያን አያደርጋትም። እሳት የላሰ ጮሌ ተናጋሪም (አንዳንዶች እንዲህ ዓይነቱን 'የተቀባ' ይላሉ) ስላለን ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን አትሆንም። የእግዚአብሔር በመካከሏ መኖር ነው ቤተክርስቲያንን ቤተክርስቲያን የሚያደርጋት።

እናም እግዚአብሔር በመካከላችን አለ ወይ ብለን እንጠይቃለን። ስሜታችንንና ግላዊ መረዳታችንን ለመልስነት ከማቅረባችን በፊት በመካከላችን ሊኖር የወደደው አምላክ የሁሉ አምላክ እንጂ በአምሳላች እንደ ምሳሌያችን የፈጠርነውና ለስሜታችን ቅርብ የሆነ 'አምላክ' አለመሆኑን እናረጋግጥ (የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ያንብቡ)።

እና ምንድነው? ሃገራዊ አብያተክርስቲያናትን ስትናገሩ ባሕርያቸውን አብራችሁ ብታውቁ ጥሩ ነው። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የገጠማትን ችግር ተናግሬ ነበር ብሎ ልከኝነትን ለማግኘት መጣጣር እብደት ነው። የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ኅብረትም እንዲህ ዓይነት ንግርተኞችን አደብ ቢያስገዛ ነው (ነግ በ'ኔ ነውና)።

ሰላም ኹኑ

ተገኝ ሙሉጌታ
2.3K viewsΒενιαμίν, 08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-22 17:35:56 ከጥያቄ መልሶች መካከል........

“ኢየሱስም፣ “በሕግ የተጻፈው ምንድን ነው? እንዴትስ ታነበዋለህ?” ሲል መለሰለት።”
—ሉቃስ 10፥26 (አዲሱ መ.ት)

ይህ ጌታችን ኢየሱስ አንድ የህግ አወቅ ሊፈትነው ፈልጎ ስጠይቀው የመለሰለት መልስ ነው።
እጅግም በጣም አስፈለጊ ነገር ነው አንድን የምናውቀውን የእግዚአብሔር ቃል በተግባር እንዴት መኖር ይቻላል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስልን ክፍል ነው።

አንድን ነገር ከውጤቱ ተነስተን ለማስተካከል ብንጥር ትርፉ ድካም ልሆን ይችላል ውጤቱን ለማስተካከል መንገዱን ማስተካከል መልሱ ነው!!!

አንድን የምናውቀውን የቃል እውነት በተግባር ለመኖር መከተል ያለብን ይህን መርህ ነው...
በተግባር መኖር እና አለመኖር ውጤት ነው ለእነዚህ ነገሮች እንድንበቃ የሚያደርገው ግን መንገዱ ነው። በትክክል ለመኖር በትክክል የተጻፈው ምንድነው? እንዴትስ አነበዋለሁ? የሚለውን ቅድመ ጥያቄ መመለስ አለብን በዚህም አግባብ ውጤቱን መቀየር እንችላለን።
እንዴት እንደ ምንሰማው እና እንደ ምናነበው ያላወቅነውን ቃል በተግባር ላይ ብንቸገር አይገርምም!

የእግዚአብሔር ቃል እንደ እግዚአብሔር ቃል ስትሰሙ እና ስታነብ የእውነት በእናንተ ዘንድ መክበድ እና ሚዛን መድፋት ይጀምራል ያንጊዜ የቃሉን እውነት ማንም ሰያስገድዳችሁ እና ራሳችሁ እንኳ ሰትጨነቁ በፍቅር ማድረግ ትጀምራላችሁ!!!

አንድ አብዝታችሁ የምትወዱትን/ የምተፈቅሩትን ነገር ደግማችሁ ደጋግማችሁ ለማሰብ ብሆን፣ ማድረግ ያለባችሁን ነገር ለማድረግ ብሆን ማንኛውንም ነገር ለማድረግ አይከብዳችሁም የሚታያችሁ የምታደርጉት ነገር ሳይሆን የያዛችሁ ፍቅር ነው!!!
ስለዚህ አንድን የእግዚአብሔር ቃል በተግባር ለመኖር እንዴት እንደ ምትሙ እና እንደ ምታነቡ መጠየቅ ነው።

#እባካችሁ #መልዕክቱን #ለወዳጆቻችሁ #መጋራት #አትርሱ

@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
2.2K viewsΒενιαμίν, 14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-21 15:17:35 ጥያቄ
እንዴት ነው አንድን የምናውቀውን ወይም የሰማነውን የእግዚአብሔር ቃል በተግባር መኖር የምንችለው
በዚህ መስመር ላይ መልሱን ማስቀመጥ ትችላለችሁ @TheSonOfVictor

@TheDeepThingsOfGod
2.3K viewsΒενιαμίν, 12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 14:31:20
˙ የኢየሱስ አማላጅነቱና ማንነቱ
Pastor tesfaye haile
360p, 58.4MB,


@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
ጠቃሚ ጠቃሚ ትምህርቶችን ለማግኘት ቻናላችንን Join እና ሼር ያድርጉ።

ሼር ስላደረጉ እናመሰግናለን
677 viewsΒενιαμίν, 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 10:37:56 ˙         #በእምነት_እኖራለሁ
ተስፋዬ ጋቢሶ./ አስናቀች ተ./ ደስታ ቢ./   አባይነህ ሻ. / አቤል ተ. / አስራት ሙ./
New song 2015/2023
6.5MB,

share & join us
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
319 viewsΒενιαμίν, 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 10:33:16
˙ #በእምነት_እኖራለሁ
ተስፋዬ ጋቢሶ./ አስናቀች ተ./ ደስታ ቢ./ አባይነህ ሻ. / አቤል ተ. / አስራት ሙ./
360p, 25.6MB,

share & join us
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
357 viewsΒενιαμίν, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-15 17:29:49 ይሄን ቪዲዮ በእንባ ሆኜ ካየው በኋላ ክርስቶስን ይበልጥ ወደድኩት
"ዘ ፓሺን ኦፍ ዘ ክራይስት"
የተሰኘው ክርስቶስ ለእኛ የከፈለውን ዋጋ የሚያሳይ ፊልም

አውርዳችሁ ተመልከቱ ሼርም አድርጉ
@nazrawi_tube
380 viewsΒενιαμίν, edited  14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-13 22:47:01 ጳውሎስ ስለቈላስይስ አማኞች የሰማው በወንጌል አጋሩ ከነበረው ኤጳፍራ ነበር። ለእነርሱ መንፈሳዊ ሕይወት ጤንነት እንዲሁም ፍሬያማነት ዘወትር በመንፈስ ይጋደል ነበር። "ስለ እናንተና በሎዶቅያ ስላሉት እንዲሁም በአካል አይተውኝ ስለማያውቁ ሁሉ ምን ያህል እየተጋደልሁ እንደሆነ እንድታውቁ እፈልጋለሁ . . ." (ቈላስይስ 2:1-2)። መጋደል (ἀγῶνα agōna - agonize) የሚለው ቃል ከልብ የሆነ፣ ያማያቋርጥ የውስጥ ብርቱ መሻትንና ያልተቆጠበ ታጋትን ያሳያል። ይህም የሐዋርያው ጳውሎስ ከጌታ ለተቀበለው አገልግሎትና ለቤተ ክርስቲያን ያለውን የመሰጠት ጥልቀት ያሳየናል።

ጳውሎስ የሚጋደለው ስለ ምንድነው?

1) ልባቸው በፍቅር እንዲጽናና - በሰሙት ወንጌል ጸንተው እንዲኖሩ፣ እንዳይናወጡ እንዲሁም በየጊዜው እግዚአብሔር በማወቅ እንዲያደጉ ይጸልያል፤ ደግሞም ያስተምራቸዋል። "ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ተቀበላችሁት እንዲሁ በእርሱ ኑሩ" (2:6)።

2) እርስ በእርስ ያላቸው ኅብረት በፍቅር የተሳሰረ እንዲሆን። ለኤፌሶን አማኞች፣ “ይልቁንም እውነትን በፍቅር እየተናገርን፣ ራስ ወደ ሆነው ወደ እርሱ በነገር ሁሉ እናድጋለን፤ እርሱም ክርስቶስ ነው፤ ከእርሱም የተነሣ፣ ** አካል ሁሉ በሚያገናኘው ጅማት እየተያያዘና እየተጋጠመ፣ እያንዳንዱ ክፍል የራሱን ሥራ እያከናወነ በፍቅር ያድጋል *፤ ራሱንም ያንጻል።” (ኤፌ. 3:15-16)” በማለት እንደጻፈው፣ ለቈላስይስ የነበረውን ተመሳሳይ ታጋት እንመለከታለን።

3) ቤተ ክርስቲያንን አያይዞ ያጸናው ፍቅር መሆኑን እንዲረዱ - አማኞች የተሳሳሩበት ዘላላማዊ የሆነው የክርስቶስ ፍቅር ነው! ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጥግና አግኝተው የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስን እንዲያውቁ - ይህ የፍቅር ትስስር የእግዚአብሔር ቀጥተኛና ሙሉ መገለጥ የሆነውን ክርስቶስ በማወቅ ላይ የተመሠረተ ሊሆን ይገባዋል።

4) በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ የተገኘውን ድነት የማይጨመርበት፣ ሙሉ የሆነ፤ ዘላለማዊና የአንድ ጊዜ ሥራ መሆኑን የበለጠ እንዲያውቁ። ይህን ማወቅ ብቻ ነው ሰውን ምሉዕ (complete) የሚያደርገው። ይህ ፍቅር ከስሜት ያለፈና ክርስቶስን በማወቅ ላይ ያረፈ ነው። “ፍቅራችሁ በጥልቅ እውቀትና በማስተዋል ሁሉ በዝቶ እንዲትረፈረፍ (overflow) እጸልያለሁ።” (ፊል. 1:9)። ክርስቶስ በልባቸን በማደሩ ዐይናችን በርቷል፤ ይህን የሚተካ ዕውቀት የለም! ክርስቶስ ሙሉ ነው! ምክንያቱም፣ “የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የሚገኘው በእርሱ ዘንድ ነውና”። እግዚአብሔር ራሱን በክርስቶስ ገልጧል። ሰው እንዴት ከኀጢአት ድነት እንደሚያገኝ እግዚአብሔር ያዘጋጀው መንገድ አሁን እውን ሆኗል። ምስጢር አይደለም - እርሱ በክርስቶስ እቅዱን ሁሉን እውን አድርጓል። “በክርስቶስ ያቀደውንም የፈቃዱን ምስጢር እንደ በጎ ሐሳቡ እንድናውቅ አደረገ። በዘመን ፍጻሜ ይሆን ዘንድ ያለው ሐሳቡ በሰማይም በምድርም ያሉትን ነገሮች ሁሉ ራስ በሆነው በክርስቶስ ሥር ለመጠቅለል ነው: (ኤፌ. 1:9-10):: ነቢያትና ጻሕፍት የመሰከሩለትና በተስፋ የተጠበቀው መድኅን ክርስቶስ ተገልጧል።

5) እርሱን ማወቅ ለሰው ልጅ እንቆቅልሽ ሁሉ መልስ መሆኑንን እንዲረዱ! ሰውን ከኀጢአት ጨለማ፣ ከተለየበት የእግዚአብሔር መንገድና ከሚሄድበት የዘላለም ሞት የሚያስጥል ሌላ ልዩ ዕውቀት የለም! ክርስቶስ ብቻ - እርሱን ማወቅ እግዚአብሔርን ማወቅ ነው! ይህን መረዳት የሚተካ ሌላ የተሻለ የተሰወረ ዕውቀት “hidden” (apocryphi) የለም! ስለዚህ ከዚህ መረዳት “ማንም ንግግር በማሳመር (enticing words) እንዳያታልላችሁ (እንደ ጎደላችሁ፣ የሆነ ተጨማሪ ሌላ ዕወቀት እንደሚያስፈልጋችሁ በማሳመን የእምነታችሁን መሠረት እንዳይሸረሽር) ይህን እነግራችኋለሁ። ምንም በሥጋ ከእናንተ ርቄ ብገኝ በመንፈስ ከእናንተ ጋር ነኝና በሥርዐት (በተገለጠው ክርስቶስና በቅዱሳን ኅብረት በመሰጠት፣ በትጋትና በጽናት እያደገ በሚሄድ ሕይወት) መኖራችሁንና በክርስቶስ ያላችሁን ጽኑ እምነት (ከክርስቶስ ጋር አንዲሁም እርስ በእርስ) እያየሁ ደስ ይለኛል"።

ለእኛም ክርስቶስን በማወቅና በማሳወቅ የማያቋርጥ የማደግ ተጋድሎ ይሁንልን። አሜን!
Dr. Girma Bekele
@nazrawi_tube
217 viewsΒενιαμίν, 19:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ