Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.01K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On Utube sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2023-01-12 21:11:30 ቅረበኝ፣ እዚያው ሁንና!

(...ጥሞናን ለሚያውቅ፣ አሰላስሎትን ለለመደ)

አባትነቱን አስበው ቢቀርቡትም፣ ቅድስናው የሚያስፈራ ነው። በመገለጡ ብናውቀውም በስውርነቱ ሚስጥር ነው። በመንፈሱ ቢያድርብንም፣ በስፍራዎች ሁሉ መገኘቱ ከእኛ ውጭና በላይ ነው። ያለ እርሱ ቅርበት ህይወት የለም፣ የቅርበቱም ክብር አስፈሪ ነው። እግዚአብሔር የአንተ አይደለም፣ አንተ ግን የእርሱ ነህ። ስትቀርበው ትፈራለህ፣ ስትርቀው ትሞታለህ፣ እዚያው ሆኖ ቢቀርብህ ይሻልሃል፣ ቀርቦህም ቢርቅህ ይበጅሃል፣ እናም እግዚአብሔር ሚስጥር የሆነ ግልጥ ነው፣ ተገልጦልህም ስውር ነው። ስለዚህ ስለ እርሱ የማታውቀውን እወቅ፣ ያወቅኸውንም እንዳልጨረስክ እወቅ፣ ለገባህ ነገር በአደባባይ ስትቆም የእርሱ ጠበቃ የሆንክ እንዳይመስልህ፣ በሰው ልክ እርሱ ወረደልህ እንጂ በአምላክ ልክ ከፍ አላልክም! እናም በርሱ ሐሳብ ባህር ውስጥ መሆንን ግን አታቋርጥ ..።

ሰለሞን ጥላሁን
@nazrawi_tube
708 viewsΒενιαμίν, 18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 17:23:04 አዚም

ከተማ ውስጥ ሱፍ ለብሰው ሽክ ብለው ሰውን እያደነዘዙ ከሰው ያለውን ነገር ሁሉ የሚወስዱ ሰዎች ነበሩ እና አንድ ቀን አንድ የቅርብ ዘመዴን መንገድ ላይ አቁመው ለሠላምታ እጅ ሰጡት እና "ወዴት ነው የምትሄደው" አሉት፤ እርሱ ወደቤት ብሎ መለሰላቸው እና "እዚህ ከተማ ነው ምትኖረው አሉ?" አይ ከዚህ የአሥር ብር መንገድ ነው ቤቴ አላቸው። ከዛም "ስልክህን አምጣ አሉት" ሰጣቸው። "በኪስህ ያለውን ብር አምጣ" አሉት እና አሁንም ከፊተኛውም ከኃለኛውም ኪሱ ሰጣቸው እና እሱ ከሰጣቸው መልሶ ደግ ስለሆነ የትራንስፖርት አሥር ብር መልሰው ሰጡት እና "ሂድ" አሉት። እርሱም "እሺ" ብሎ በደመነፍስ ሄደ እነርሱም ከፊቱ ሸሹ እና በኪሱ ምንም እንደሌለ ያወቀው ቤት ከገባ በኃላ ነበር።

ሐዋርያው ጳውሎስ የማያስተውሉ የገላትያ አማኞችን "ማን አዚም አደረገባችሁ" ብሎ ይጠይቃቸዋል። "አዚም" የሚለውን አዲሱ መደበኛ ትርጉር "መተት" ይለዋል።
ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች የተሰበከው ወንጌል
የእግዚአብሔር ወንጌል፤ ክርስቶስ የገለጠለት ወንጌል፤ ወደ እግዚአብሔር የተጠሩበት ወንጌል፤ የዳኑበት ወንጌል እንደሆነ ያሳስባቸውና ይህንን የከበረውን ወንጌል ምን አይነት መተት ሰርተውባችሁ ነው የነጠቀባችሁ ብሎ ይጠይቃቸዋል።

በዚህ ክፍል "አዚም" የሚለውን ቃል እንግልዝኛው "bewitched" ይለዋል፤ ይህም ማለት በአንድ ነገር ከመጠን በላይ ተስቦ ሌላውን ነገር በትክክል ለማሰብ አለመቻል ማለት ነው።
ለምሳሌ "አንድ ወጣት በአንዲት ኮረዳ ውበት ፈዝዞ በዜብራ ላይ እንደቆመ መዘንጋት እንደማለት ነው።"

በኢየሱስ ክርስቶስ አምነን የዳንን ሰዎች በተለይ በዚህ ጊዜ በብዙ ነገር ፈዝዘን የያዝነውን እንቁ ነገር ትተን አላፊ በሆነ ነገር ላይ ልባችንን ጥለናል።
በልባችን ከተሳለው ከክርስቶስ በላይ፤ እግዚአብሔር ከገለጠልን ከወንጌሉ እውነት በላይ፤ ከአስደናቂው ከክርስቶስ መስቀል ሥራ በላይ ልባችንን ያፈዘዘው ገንዘብ፣ ዝና፣ በእርካሽ መንገድ መነጋገርያ መሆን እና ጊዜአዊ የሆኑ ነገሮች መሆኑ እጅግ የሚያሳዝን ነገር ነው።
የገላትያ ሰዎች የፈዘዙት "በሌላ ወንጌል ነው፤"
ዛሬ ላይ ልባችን ወርድ የሚያደርገው፤ አቅላችንን የሚያስተው፤ በክርስቶስ አምነን እንደዳንን እንዳናስተውል የሚያደነዝዘን ምን ይሁን?

አንባቢው ሆይ አይንህና ልብህ የፈዘዘው ምን እያዬ ነው?

ክብሩ
@nazrawi_tube
92 viewsΒενιαμίν, 14:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 09:14:17 አምላክ የሆነው እርሱ ሰው ሲሆን ስኬቱ ምንድነው?

ሁሉም ክርስቲያን ሊሰማው የተገባ የእግዚአብሔር ሀሳብ
በ21ኛ ክፍለዘመን መንፈስ ቅዱስ እንድንሰማለት የፈለገው ጬኸት

#እንኳን #ለጌታችን #ለኢየሱስ #ክርስቶስ #የልደት #መታሰቢያ #በዓል #በሰላም #አደረሳችሁ!!

#ለሌሎች እንዲደርስ ሼር አድርጉት

@TheDeepThingsOfGod
@TheDeepThingsOfGod
495 viewsΒενιαμίν, 06:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 22:07:30 ˙ "የዘላለሜ ፈውስ"
ሺንሺቾ ፌሎሺፕ መዘምራን
አዲስ መዝሙር 2023/2015

ሼር
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
549 viewsΒενιαμίν, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 22:07:30
˙          "የዘላለሜ ፈውስ"
    ሺንሺቾ ፌሎሺፕ መዘምራን
አዲስ መዝሙር 2023/2015

360p, 25.6MB,

ሼር
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
545 viewsΒενιαμίν, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 21:03:18 “ስጦታው ደርሶሃል?”

ልደቱ ቤተ መንግሥት አናውጧል ፤ ቤተ ክህነት በጥብጧል፤ በሜዳ የነበሩ እረኞችን በደስታ አስደንግጧቸዋል ፤ ሰማይና ምድርን በአንድነት አስዘምሯቸዋል ፤ ሰብአ ሰገል አገር አቆራርጠው ሊሰግዱለት ተጒዘዋል። ንጉሥ ሄሮድስ ሊገድለው ሤራ ይጠነስስ ነበር። መጽሐፍ ዐዋቂዎችም ስለ መሲሑ ልደት ቦታ ጥቅስ ጠቅሰው ወደየቤታቸው ተመለሱ።...ገሚሱ በደግነቱ ሲያምን ገሚሱ እንደ “አሳች” ፈረጀው።

ይኸ መናወዝ ላለፉት ኹለት ሺህ ዓመታት እንደ ቀጠለ አለ። በተወሰኑ ሰዎች ታላቅ የምግባር መምህር ተደርጎ ተወድሷል፤ በሌሎች ደግሞ “ጻድቁ ነቢያቸው ” ኾኗል። መናፍቅ ብለው ራሳቸውን ያሳመኑም ነበሩ ፤ አሉም። ነገር ግን “እርሱ እንደ ተናገረው እንዲሁ የእግዚአብሔር ልጅ መሲሑ ነው ” በማለት ያመኑበትና በጌትነቱ ስር ወድቀው የሰገዱ እልፍ አእላፋት ሞልተዋል። በአጠቃላይ ማንም ይኹን ማን ፥ ስለ ኢየሱስ አንድ ነገር ሳይል እንዳያልፍ ሰማይ ወስኗል፤ ኢየሱስ “ጥያቄ” ነው።

[ይኼ አንቀጽ የተቈረሱ ነፍሶች መጽሐፍ ውስጥ ጸሐፊው የመሲሑ መምጣት ከመደበኛው ክስተት የተለየና አነጋጋሪ መሆኑን ከሚያስረዳበት ክፍል የተወሰደ ነው]

ጸሐፊው ይቀጥልና ከላይ አነጋጋሪ ጥያቄ ያለውን - መልሱም ራሱ ነው ይለናል። (እንዴት አይነት ማራኪ አገላለጽ ነው?)

እግዚአብሔር የዓለምን ጥያቄ ሁሉ የመለሰው በልጁ በክርስቶስ በኲል ነው። እርሱ ካልመለሰልን ሕይወታችን አልተመለሰም ፤ ዘላለማችን ተስፋ የለውም ፤ ነፍሳችን ተቅበዝብዛ መጥፋቷ ነው።
ለሕይወታችን መትረፍ የሚያስፈልገው መድኃኒቱ መጠን የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስን ያህል ነው ።

***
ዛሬም፤

በመልአኩ የተበሰረው “ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች ” አዋጁ ትኩስ ነው። በሰብአ ሰገል አምልኮ ውስጥ የተመሠጠረው የልደቱ ፋይዳ ሕያው ነው። በእናቱ ማርያም ቅኔ ውስጥ “አምላኬ...መድኃኒቴ” ያለቺው እርሱ የፍጥረታት ሁሉ ጌታና አዳኝ ነው።

በዚህ “መሲሕ” በኩል ለሚመጡና በስሙም ለሚያምኑ የሰው ልጆች ሁሉ “የእግዚአብሔር ልጅ” እንዲሆኑ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል። ሐዋርያው ጴጥሮስ ጮክ ብሎ እንዳለው፡- መዳን በሌላ በማንም የለም! እንድንበት ዘንድ ከሰማይ በታች የተሰጠን ሌላ ስምም - አዳኝም - ምግባርም - አቋራጭ መንገድም የለም!

እግዚአብሔርም ዓለሙን የወደደበትን ጥግ ሊያሳይ አንዲያ ልጁን ሰጠን። በውልደቱ፣ በትምህርቱ፣ በተግባሩ፣ በሞትና ትንሣኤውም ከርሱ ጋር ሕይወትና ተስፋን ተቀበልን። የልደት መታሰቢያውም ትርጉም የሚኖረው ወደ ሰጪው አሻቅበን “የላክልኝ ውዱ ስጦታህ ደርሶኝ ተቀብያለሁ፤ አመሰግናለሁ” ማለት የቻልን እንደሆነ ብቻ ነው!

ይኼ የሰማይ ውድ ስጦታ ደርሶሃል?ደርሶሻል? የደረሰው ከልቡ ያመስግን - ያልደረሰው በነጻ ይቀበል!

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ።

ፍጹማን ግርማ
@nazrawi_tube
690 viewsΒενιαμίν, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 18:03:02
ልደቱ --የለውጥ አብነቱ

የዚህ ምድር ቋጥኝ የደም ግብር ምሱ ነው፤ ድንጋዩ ሁሉ፥ አፈሩ ሁሉ ሲቀለብ የኖረው የአዳምን ልጆች የደም ዥረት ነው። የዓለማችን ቋሚ መልክ ጠብ ነው።ከዚያች የገነት ደጅ ጠብና ሽሽት በኋላ ሰብአውያን ግጭትና ቁርሾ፥ሁካታና ቱማታ መታወቂያችን ሆኗል። የሰማይ መላእክት አፍ አድጧቸው ቢናገሩ ምን ይሉን ይሆን?
"ውይ ! እነዚያ ሁከተኞች፥ እኒያ የሰላም ባይተዋሮች፥እኒያ የጠብ ዐርበኞች፥ ወርቅ ሲሰጧቸው ጠጠር የሚወረውሩ ሞገደኞች"ሳይሉን አይቀርም።እኔ የሰው ልጅ የምጣላው ባጣ፥ ዐናቴ ላይ ከበቀለው ጉተና ጋር፥ጉልበቴ ላይ ከፈረጠመው ሎሚ ጋር፥ከራሴውም ጋር ቢሆን ጠብ ማብቀሌ አይቀርም።
ቢርበኝ፥ ብጠግብም መዝናኛዬ ጠብ ነው። ታላላቅ መንግሥታት ፥ታናናሽ መንግሥታት ፥ የተማሩ ሕዝቦች፥ ማይማን ብሔረ ሰቦች፥ ሁሉም የሠለጠኑት ጠብ በመለኰስና ልኵሱን በማፋፋም ነው።

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት የሰላም ልደት ነው።
"ስሙም ድንቅ መካር ፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል"....."ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም፥ሰላምም በምድር".....ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጦር በተሰበቀበት፥ የፈረስ ኮቴ በጎደፈረው ምድር ላይ የሰላም ባንዲራ ተከለ። ሃሌሉያ! መጀመሪያ ከአባቱ ጋር፥አያይዞም ከራሳችን፥ ከሰው ሁሉ ጋርም አስታረቀን። እርሱ የሰላም መንገድ ጠቋሚ ብቻ አይደለም፤ የሰላም ሰባኪም ብቻ አይደለም።" እርሱ ሰላማችን ነው።" በሰው ጥበብ ና ጉልበት የማይበቅል ሰላም ምንጭ ሆኖ ኢየሱስ ተወለደልን።

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን።

"መስተአየት"ገጽ 133/4
ጋሽ ንጉሤ ቡልቻ
@nazrawi_tube
883 viewsΒενιαμίν, 15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 15:56:01 በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ

ዛሬ ይኸን ቃል እንደ ገና አነበብሁ። “እነሆ የመረጥሁት ብላቴናዬ፥ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ወዳጄ፤ መንፈሴን በእርሱ ላይ አኖራለሁ፥ ፍርድንም ለአሕዛብ ያወራል። አይከራከርም፥ አይጮኽምም፥ ድምፁንም በአደባባይ የሚሰማ የለም። ፍርድን ድል ለመንሣት እስኪያወጣ፥ የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም፥ የሚጤስን የጥዋፍ ክርም አያጠፋም። አሕዛብም በስሙ ተስፋ ያደርጋሉ” (ኢሳ. 42፥1-4)።
.

እንደምታውቁት፥ በኀጢአት ስንዋከብ ኖረናል። …

በሰው ልጆች መካከል የሚገማሸሩና ለትከሻ ቀርቶ ለጆሮ የሚከብዱ ሰቀቀናም የጥቃት፥ የበደል፥ የግፍና የርኵሰት ሸክሞችን መጥቀስ ይቻላል። ነገር ግን፥ የኾነውን ኹሉ ትተን፥ እኛ የምናውቀውን እንኳ መተረኩ ያደክማል። ዋናውን ጕዳይ ግን ዘልለነው አንኼድም፤ ከዚህ ኹሉ የመንኰታኰት አዘቅት ውስጥ ወርውሮ የዶለን ምንድን ነው? ኀጢአት ነው። በመተላለፍ ጦስና በዐመፃችን መታለል የተሰባበርን እንክልካዮች ኾነናል፤ በእግዚአብሔር መልክ የተሠራንበት ዐላማ ደምቆ እንዳያበራ በውድቀት ጦስ ተዳፍነን የምንጤስ ሻማዎች ነበርን። ሕግ የተሰጠውም ኾነ ሕግን በነቢይ ያልተቀበለው አረማዊ “ኹሉ ከኀጢአት በታች እንደ ኾኑ” በአንድነትና በይፋ ተከስሰዋል (ሮሜ 3፥9)። ማን ተርፏል?
.

የሕይወታችን ቅስም በዘላለም ብርታት እንዲታደስ ቤዝዎታዊ ትድግና አስፈልጎናል፤ እንደ ገና እንድንቆምና በብርሃኑም ብርሃንን እንድናይ ስለ እኛ ኾኖ የሚፈስ የሕይወትን ምንጭ ያስፈልገናል። ውርደታችን ጥልቅ ስለ ኾነ አዳኛችን ምርጥ መኾን አለበት። በብርቱ ስለ ተሰበርን ድንቀኛ በኾነ መንገድ መጠገን አስፈልጎናል። ይህን እውን ለማድረግም እግዚአብሔር ምርጡን ብላቴናውን አዘጋጅቶ ወደ ዓለም ልኮታል። “እኛም አይተናል፤ አባትም ልጁን የዓለም መድኀኒት ሊኾን እንደ ላከው እንመሰክራለን” (1ዮሐ. 4፥14)።
.

እግዚአብሔር ፍጥረት ኹሉ እንዲመለከትለት የሚፈልገው እውነት አለው። አስቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ በኋላም በሐዋርያው ማቴዎስ አማካይነት ትኵረታችንን በመቀስቀስ ዓለም ኹሉ ወደ ምርጡ ብላቴና እንዲመለከት ይጣራል። መሲሑ ከእልፍ አቻዎቹ መካከል የተገኘ አለቃ አይደለም፤ ብቸኛው ምርጥ ነው። ወደር የለሽ አንድያ ነው፤ አንድዬ ነው። እግዚአብሔር “ምርጤ” ብሎ ይጠራዋል። ለእኛም ዋጋ የማይተመንለት ውድ-ብርቅ-ድንቅ ዕሴታችን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኾነ።
.

ምርጡ መሲሕ ደግሞ፥ ሸክማቸው የከበደባቸው ሰዎች ወደ እርሱ እንዲመጡና እንዲያሳርፋቸው “በመንፈስ ድኾች” ለኾኑ ኹሉ በግልጽና በይፋ ጥሪውን አቅርቧል። ጥሪውም፥ “እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ኹሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ” (ማቴ. 11፥28) የሚል ነበር። “ተወለደ” ማለትን ስናስብና ስናከብር ይኸን እያሰላሰልን ነው። የዓለሙ ቤዛ ተወለደ። ሲወለድ ለቤዛነት ይሰቀል ዘንድ ነው። ሲሰቀልም እኛን ለማጽደቅና ለመሻር በትንሣኤ ክብር ይነሣ ዘንድ ነው። ትንሣኤውው ዳግመኛ መገለጡን ያረጋግጣል። እነሆ በቶሎ ይመጣል።
.

“ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ” እንደምንል ኹሉ “እግዚእ ኵሉ ዓለም ይመጽእ ካዕበ” እንለለን።
.

መልካም በዓል።
መጋቢ ሰለሞን አበበ ገ/መድህን
@nazrawi_tube
251 viewsΒενιαμίν, 12:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 12:40:01 የኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ እግዚአብሔር "ለአባቶች የተሰጠውን የተስፋ ቃል ያጸና ዘንድ" እንደሆነ የአዲስ ኪዳን ምንባባት ያስረዳሉ። ኢየሱስ የተስፋ ፍጻሜ መሆኑን ማወቅ መቻል አለብን። እግዚአብሔር በብሉይ የሰጠው ተስፋ ሁሉ እውን የሆነው ወይም "አዎን" የሆነ በኢየሱስ ነው። የተስፋ ፍጻሜ መዳረሻ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ።

"ለአባቶች የተሰጠውን የተስፋ ቃል ያጸና ዘንድ ለእግዚአብሔር እውነት ሲል ክርስቶስ የአይሁድ አገልጋይ እንደሆነ እነግራችኋለሁና፤" (ሮሜ 15:8)

እግዚአብሔር በነብያቱ በኩል ትድግናና መቤዠትን ለእስራኤል አብስሯል (ኢሳ 40-42)። ተስፋን ሰጥቷል። ማዳን እንደሚፈልግ፣ ለማዳን ደግሞ ችሎታው እንዳለውና ጊዜው ሲደርስ በታማኝነት እንደሚያድን አብስሯል። ይሄ የማዳን ተስፋ ፍጥረቱን ሁሉ እንደሚጠቀልል አስቀድሞ ተናግሯል። የማዳን ተስፋው ለአይሁድ ብቻ ሳይሆን ለአሕዛም ጭምር ነው። አሕዛብ ወደ እርሱ ዘወር እንዲሉ የሚያደርጋቸውን ተስፋ ሲናገር (ኢሳ 42፥1-9) ይህንን ይላል፦

“እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል [...] አሕዛብም በስሙ ይታመናሉ [...] ለሕዝብ ቃል ኪዳን ለአሕዛብም ብርሃን አድርጌ እሰጥሃለሁ።”

የጌታ ባሪያ “አሕዛብንና እስራኤልን” በአንድ ላይ በማድረግ የእግዚአብሔርን ትድግና ወደ የሚያወጣ አገልጋይ ነው። በምርጡ በኩል ለሁሉም የሚበቃን የትድግና ተስፋ ሰጠ።

ለምን ተወለደ? ስንል አለሙን ሁሉ፣ አሕዛብንና አይሁድን ሁሉ እንደ ተስፋ ቃሉ ይታደግ ዘንድ ተወለደ። ስለዚህም እግዚአብሔር የሰጠው ተስፍ ይጸና ዘንድ ወይም እግዚአብሔር ታማኝ መሆኑ ያስመሰክር ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ ተወለደ። መወለዱ የእግዚአበሔር ታማኝነት መገለጫ ነው። ክርስቶስ የእግዚአብሔር እውነት በመሆን የእግዚአብሔር ታማኝነት ማሳያ ይሆን ዘንድ ተወለደ። የተሰጡ የተስፋ ቃሎችን በሙሉ ኢየሱስ በመወለዱ ፈጽሟቸዋል። ርቀን ለነበርነው ለእኛ ለአሕዛብ ታላቅ የምሥራች ነው መወለዱ!

መልካም የልደት መታሰቢያ በዓል!
መልካም ቀን!
አማኑኤል አሰግድ
@nazrawi_tube
462 viewsΒενιαμίν, 09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 10:33:57
በርካታ የሃይማኖት መሥራቾችና ታላላቅ ተጽዕኖ የፈጠሩ መሪዎች በየዓመቱ በደማቅ ሥነ ሥርዓት የሚከበበር የልደት መታሰቢያ አላቸው። "እንኳንም ተወለደ" በማለት በሕይወት ባይኖርም እንኳ፣ ተከታዮቻቸው ወይም አድናቂዎቻቸው የተወለዱበትን፣ ይኽን ዓለም የተቀላቀሉበትን ዕለት ይዘክራሉ።

የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ፈጽሞ ከዚኽ ይለያል። እሱ በመወለድ ያልጀመረ፣ ጀማሪ፤ ያልተፈጠረ ፈጣሪ ነው። ርሱ ሥጋ የኾነበትን ማሕጸን የፈጠረ፤ የሚተነፍሰውን አየር የፈጠረ፤ በኋላም የተሰቀለበትን እንጨት አስቀድሞ የፈጠረ፤ ኹሉ ከርሱ፣ በርሱና ለርሱ የኾነ ዘላለማዊ አምላክ። ልደቱ መለኮት ሥጋ የመልበሱን [ሰው የመኾኑን] እውነት ይነግረናል እንጂ ጅማሬውን አያሳየንም። ከማርያም ሳይወለድም እሱ በሕይወት ለዘላለም ነበር።

ትሥጒቱን ለምዘክርበት ቀን እንኳን አደረሳችኹ።
የአምላክ ቸርነት
@nazrawi_tube
598 viewsΒενιαμίν, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ