Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.01K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On Utube sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2022-12-10 19:01:01 ነገርኩህ እኮ አልኩት። አልጋዬ ጫፍ ላይ ቁጭ እንዳልኩኝ። ምንም ሳይል ትቶኝ ሄደ።

ነጋ። ምንም ነገር የለም። ሁሉም አኩርፎኛል የሚያናግረኝ የለም። አንዳንዱ በቁጣ ያየኛል። በተለይ መጀመሪያ ከሪያድ ኤርፖርት የተቀበለኝ እና በዙ ያገዘኝ አብዱረሃማን በጣም እንደተቆጣ ያስታውቅበታል። ግቢው ውስጥ ለሁሉም ሰራተኛ ውሃ መጠጫ እንዲሆን የተዘጋጀ ከአልሙኒየም የተሰራ ትልቅ ማጣሪያ እና ማቀዝቀዣ አለ። አዚያ ጋር ወሃ ለመጠጣት ስንሄድ በአጋጣሚ ሁለት ሶስት ሰው በአንድ ጊዜ ይገናኛል። ዛሬ ግን በአጋጣሚ እኔ ልጠጣ ስሄድ ሌላ ሰው ካለ ቶሎ ዞር ይላል። አጠገቤ መገኘት እንኳን ተፀየፉ። ባጭሩ የሚችሉትን ያክል አገለሉኝ።

በዚህ ዕለት ቀኑን ሙሉ ግቢ ውስጥ ዋለኩ። የስድስት ሰዓቱንም፥ የዘጠኝ ሰዓቱንም፥ የአስራ ሁለት ሰዓቱንም ሆነ የማታውን ስግደት መስጊድ አልገባሁም። እነርሱ ሰግደው ሲመጡ እኔ ግቢ ውስጥ ነኝ። በሸቁ። እኔ ደግሞ ምንም አልመስለኝም። በቃ የመጨረሻው ነገር ሞት ነው። ለእርሱ ደግሞ ለወራት ያክል ተዘጋጀቻለሁ። አስቤበታለሁ። በዚህ ሁኔታ ሶስት ቀን ሆነኝ። በቃ ነፃ ወጣሁ (ከፊቴ የተደገሰልኝ ምን እንደሆነ ባለውቅም)። ትልቅ ነፃነት ተሰማኝ። ለካ ለመሞት በመወሰን ውስጥ ነፃነት አለ። አሁን እኔ በዚያው ግቢ ውስጥ የክርስቶስ ነኝ።

ነገር ግን ሁሉም ዝም ስላለ ምን እንደታሰበ ማወቅ አልቻልኩም። እናቴ ታለቅሳለች ሃበሻ ጓደኞቿም በጣም ተጨንቀዋል። በዚህ መካከል አህመድ ከሳዌ አንድ ፍንጭ ይዞ እናቴ ጋር ሄደ...ይቀጥላል (ነገ ማታ 1 ሰዓት)

ቴዎድሮስ ተጫን
@nazrawi_tube
490 viewsΒενιαμίν, 16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 19:00:06 የዛሬ 21 ዓመት #7

ሳውዲ በቆየሁባቸው ጊዜያት ዓሚር ስዑድ ከማናችንም ጋር ከሰከንዶች በላይ ሲያወራ አይቼው አላውቅም። እርሱም የሆነ ጥያቄ ኖሮን ለዚያ መልስ ለመስጠት ሲል ነው የሚያወራው። ንግግሩም ሁሌ አጭር ናት። “አዎ” ወይም “አይ” ነው የሚለው። በቃ። በጣም ግድ ከሆነበት ጥቂት ማብራሪያ ያክልበታል። ሁሌ ኮስተር ያለ ፊት ነው ያለው። በተለይ ከእኔ ጋር በተያያዘ ከሁለት ጊዜ በቀር ፈገግ ብሎ እንኳን አይቼው አላውቅም።

አንዱ፤ የሼፉ ረዳት በነበርሁበት ጊዜ የሚገዙ እቃዎችን ዝርዝር በአረቢኛ ፅፌ የሰጠሁት ጊዜ (ያው በሳውዲ አድርጌ ወደ አውሮፓ እሾልካለሁ ብይ አስብ ስለነበር አረቢኛውን ለማጥናት ጥረት አደርግ ነበርና መፃፍ እና ማንበብ እሞክር ነበር)። አረቢኛ ፅፌ የሰጠሁት ዕለት ደስ ብሎት ጥቂት ፈገግ ብሎ አይቼው ነበር። ሁለተኛው ደግሞ “ጣይፍ” (አየር ለመቀየር የሚሄዱበት ሌላኛዋ የሳውዲ ከተማ ነች) ወደ ሚባል ከተማ በአይሮፕላን የተጓዝን ጊዜ ሙሉ ለሙሉ የሳውዲ አለባበስ ለብሼ ስለነበር ከአይሮፕላን ስንወርድ ፈገግ ባለ ፊት ያየኝን አስታውሳለሁ። በተረፈ ዓሚር ስዑድ ኮስታራ አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው። ሰራተኛው ሁሉም ይፈራዋል። ዛሬ ደግሞ ባለንጣ ሆነን ተገናኝተናል።

ሳሎኑ በር ላይ ፊት ለፊት ስንገናኝ፤ “ዓሚር ላናግርህ ፈልጌ ነበር” አልኩት። እርሱም ኮስተር ብሎ ተመለከተኝና (ሁኔታዬ ግር ያለው ይመስላል) “አሁን ልንወጣ ነው ምንድነው በአጭሩ ንገረኝ” አለኝ። ምንም አላሽሞነሞንኩትም ያለኝም ሰዓት አጭር ነው። በቀጥታ እንዲህ አልኩት “ወደዚህ ሀገር ከመምጣቴ በፊት ክርስቲያን ነበርኩ እዚህ ከመጣሁ በኋላ ግን እስልምና ውስጥ ገባሁ። አሁን ስረዳ ግን ከገሀነብ የሚያድነው መሀመድ ሳይሆን ኢየስስ ነው” አልኩት እና ፀጥ ብዬ ቆምኩ።

ያ ቀይ ፊቱ መቅላት ጀመረ። ራሱን ተቆጣጥሮ ጥቂት ስለ መሃመድ እና ስለ ኢየሱስ (ኢሳ) ልዩነት ሊያስረዳኝ ሞከረ። እኔም መለስኩለት። ለሁለት ደቂቃ የሚህል አወራን።ተከራከርን ማለት ይቻላል። መጀመሪያ ቀለል ያለ መስሎት ነበረ መሰለኝ። ሲያየኝ ደግሞ ቁፍጥን ያለ ሁኔታ ነው ያለኝ። “ለማንኛውም አሁን እየወጣሁ ነው” አለና ትቶኝ ወደ መኪናው ገባ። ሹፌሩም ይዟቸው ከግቢ ወጣ።

በዚያው ዕለት ከሰዓት በኋላ የአሚር ስዑድ ሹፌር “አህመድ አደም” ይባላል። "አሚር ስዑድ አንድ ቦታ ውሰደው ብሎኛል" አለኝ። የት ነው ስለው ሃበሻ ሙስሊሞች ያሉበት ቦታ ነው አለኝ። እሺ ችግር የለውም አልኩትና ይዞኝ ሄደ (በኋላ ሲገባኝ እንግዲህ ያን ጊዜ ትምህርቱን የተማርኩት በፊሊፒን ኡስታዝ እና በእንግሊዘኛ ስለነበር “ያልገባው ነገር አለ” ብለው አስበው ነው)። ከሰዓት በሁዋላ ነበር የሄድነውና ቦታው ላይ ስንደርስ ለዓይን ያዝ አድርጎ ነበር። መጀመሪያ አህመድ አደም ገብቶ አናገራቸውና ቀጥሎ “ግባ” ተባልኩ። አህመድ አደምም ወጪ ሊጠብቀን ከውስጥ ወጣ። ይህ ቢሮ በኋላ እንደተረዳሁት የኢትዮጵያን እስልምና ጉዳዮች በተመለከተ በሳውዲ የተከፈተ ቢሮ ነው።

ስገባ ሰፋ ያለ ቢሮ ነው። አራት በጎልማሳ ዕድሜ አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊሞች ቢሮው ውስጥ ተቀምጠዋል። አንደኛው የቢሮው ዋናው ጠረጴዛ ጋር ያለው ወንበር ላይ ተቀምጧል። ቁጭ በል አሉኝ። ተቀመጥሁ። እንደነገርኳችሁ ነው ይሄ ነው፤ የሚባል ፍረሃት በውስጤ የለም። ከቤትም ስመጣ ፀልያለሁ። ዋናው ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠው ሰው ትንሽ ንቀት በተቀላቀለበት ድምፀት “እስኪ ስለሃይማኖትህ ንገረን” አለኝ።

እኔም ፈጠን ብዬ “አዳምና ሄዋን” ብዬ ንግግሬን ስጀምር አቋረጠኝና ስለሃይማኖትህ ነው ያልኩህ አለኝ። እኔም ቆፍጠን አልኩና “ኢየሱስ ያድናል ወይም ጌታ ነው ብልህ ለምን? እንዴት? እያልክ መጠየቅህ ስለማይቀር እኮ ነው ከአዳምና ሄዋን የጀመርሁልህ አልኩት (ሁኔታዬን ሲያየው ነገሩ ቀላል እንደማእሆን ያሰበ ይመስለኛል። ምናልባት እርሱ የእኔን ጉዳይ በአጭሩ ፈትቶ በአሚሮች ቤት ሞገስ ማግኘት ፈልጎ እሆናል)። "በል እሺ ቀጥል" አለኝ።

ከዚህ በኋላ ከአዳምና ሄዋን ጀምሬ ስለሰው መፈጠር እና በሃጥያት ምክንያት ከእግኢአብሔር ስለመለየቱ፥ የአብረሃም መጠራት፥ የአብረሃም ዘር የቀጠለው በይሰሐቅ እንጀ በእስማኤል እንዳልሆነ፥ ስለ መሲሁ ክርስቶስ መምጣት እና ለሃጥያታችን ስለ መሞቱ በእርሱም ላይ ባለን እምነት የዘላለም ህይወት እንደሚገኝ፥ ክክርስቶስ ውጪ ሌላ የመዳኛ መንገድ እንደሌለ በዝርዝር አስረዳኋቸው። እኔ እራሱ በዚህ መጠን እንደተረዳሁት ያወቅሁት ለእነርሱ ስነግራቸው ነው። ስናገርም በጣም በድፍረት እና ድምፄን ከፍ አድርጌ ነበር።

አሁን ነገሩ ጫን ያለ እንደሆነ ያሰቡ ይመስላል። አቀማመጣቸውን አስተካከሉ እና ሞቅ ያለ ክርክር ተጀመረ። ብቻ ምን አለፋችሁ አራት ለአንድ ከባድ ክትከት ሆነ። የምናገርውንም ቃል እግዚአብሔር ራሱ አፌ ላይ ቁጭ ቁጭ ሚያደርግልኝ ይመስለኝ ነበር። ያ ለወራት የተጠራቀመ ሁሉ ወጣ። የክርክሩን አቅጣጫ እግዚአብሄር አጠፋባቸው። አንድ ሰዓት ተኩል የሚሆን ተነጋገርን። ያለማጋነን አንድ ሰዓት ሚሆነውን እኔ ነበር ያወራሁት። በመጨረሻ ከመካከላቸው አንዱ “እሺ!! ተዓምር አሳየንና እናምንበታለን!” አለኝ በታላቅ ቁጣ። ምን ጥቅስ ቢመጣልኝ ጥሩ ነው? “እግዚአብሔር አምላክህን አትፈታተነው ተብሎ ተፅፏል” የሚለው ጥቅስ። ልክ ይህንን ስለው “የምትሉትማ አታጡም” ብሎኝ ከመቀመጫው ተነስቶ እጁን እያወናጨፈ ከቢሮ ወጣ።

አሁን መከራከር ብቻ እንጂ ምንም ወጤት እንደሌለው ሲገባቸው ዋናው ወንበር ላይ የተቀመጠው ሰው አሳቢ መስሎ ሊያስፈራራኝ ሞከረ። “ስማ፤ ሰዎቹ ጥሩ ሰዎች ስለሆኑ ነው እንጂ ይህ ሁኔታህ በዚህ ሃገር ህግ ያስገድልሃል” አለኝ። እኔም ልክ ነህ ይህንንም በደንብ አውቃለሁ ስለክርስቶስ ለመሞትም ዝግጁ ነኝ አልኩት። ፍርጥም ብዬ። በቃ እንደዚህ ከሆነ መሄድ ትችላለህ! ጨርሰናል! አለኝ። ንዴት በተቀላቀለበት ቃል። ከቢሮ ወጣሁ። አህመድ አደም እደጅ እየጠበቀኝ ነበርና ወደ ቤት ይዞኝ ሄደ። አሁን እኔ ጨርሻለሁ! የሚመጣውንም ለመቀበል ተዘጋጅቻለሁ። የቀረው የእግዚአብሔር ውሳኔ ነው።

መሸና እንደ ተለመደው እራቴን ልበላ ወደ መመገቢያ ክፍል ሄድኩኝ። ሁላችንም አንድ ላይ ነው የምንመገበው። ይህ የቤቱ ህግ ነውና። መመገቢያ ክፍሉ ሰፊ ነው። ምግቡም የሚደረደረው መሬት ላይ በተነጠፈ ፕላስቲክ ላይ ነው። በቅድሚያ አሚሮቹ ይገቡና ይበላሉ። ከዚያ እነርሱ ሲጨርሱ ሰራተኛው (ወንዶቹ) አንድ ላይ እንገባለን። ዛሬም እንደተለመደው ለራት ስገባ አህመድ አደም ቀድሞ ነገሩን አድርሷቸዋልና ሁሉም አኩርፈዋል። ለበቻዬ እንድቀመጥ የሆነ ቦታ ሰፋ አድርገውልኝ እነርሱ ወደ አንድ አካባቢ ናቸው። ማንም ያናገረኝ የለም፤ እራቴን በልቼ ወጣሁና እደ መኝታ ቤቴ ሄድሁ።

በጌታ ፊት ተንበርክኬ አቅም እንዲሰጠኝ ፀለየኩ። መፀሐፍ ቅዱሴን አንብቤም ተኛሁ። ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የለኝም። ምክንያቱም ግቢው ሁሉ ስላኮረፈኝ ምነ እንደታሰበ መገመት አልቻልኩምና። ለሊቱ አልፎ የንጋቱ አዛን ሲጣራ ከእንቅልፌ ነቃሁ። ትንሽ ቆይቶ ሁለም መኝታ ክፍሉን እየከፈተ ወጣ። እኔ ያለሁበት ክፍል ውስጥ የእኔን ጨምሮ ሶስት አልጋ ቢኖርም ብቻዬን ነው የምተኛው። ትንሽ ቆይቶ የመኝታ ክፍሌ በር ተንኳኳ። አሚር ስዑድ ነበር (ከዚህ ቀደም ቀድሜ ካልወጣሁ ቀስቅሶኝ ነበርና የሚያልፈው)። ተስፋ አልቆረጠም ማለት ነው ብዬ አሰብሁ። “ሰላት” “ሰላት” አለኝ። ለስግደት ተነስ ውጣ ማለቱ ነው። ምንም አላንገራገርኩም። ትናንት
471 viewsΒενιαμίν, 16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 19:02:25 የዛሬ 21 ዓመት #6 መድረስ አይቀርም ሳምንቱ ደረሰና አዲሶቹ ወዳጆቼ መጡና ወደ ቤተክረስቲያን ይዘውኝ ሄዱ። እንደ ባለፈው ሳምንት በታላቅ ጥንቃቄ ተራ በተራ ወደ ፀሎት ቤቷ ውስጥ ገባን። መርሃ ግብሩ ተጀመረ። ይዘምራሉ። ታዲያ ሲዘምሩ ከልባቸው ነው። በትግሪኛ ይዘመራሉ። በአማርኛም ይዘምራል። “አዚእካ ኣቢይካ መውዳድርቲ ዘይብልካ…..ንስዕካ ዕይካ ጎይታ” ("በጣም ትልቅ ነህ ተወዳዳሪም የለህም...…
641 viewsΒενιαμίν, 16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 19:01:36 የዛሬ 21 ዓመት #6

መድረስ አይቀርም ሳምንቱ ደረሰና አዲሶቹ ወዳጆቼ መጡና ወደ ቤተክረስቲያን ይዘውኝ ሄዱ። እንደ ባለፈው ሳምንት በታላቅ ጥንቃቄ ተራ በተራ ወደ ፀሎት ቤቷ ውስጥ ገባን። መርሃ ግብሩ ተጀመረ። ይዘምራሉ። ታዲያ ሲዘምሩ ከልባቸው ነው። በትግሪኛ ይዘመራሉ። በአማርኛም ይዘምራል።

“አዚእካ ኣቢይካ መውዳድርቲ ዘይብልካ…..ንስዕካ ዕይካ ጎይታ”
("በጣም ትልቅ ነህ ተወዳዳሪም የለህም... አንተ ነህ ጌታ" ማለት ነው)።

“ከኢየሱስ ጋር ኑሮ ይሻለኛል……

አክሊል ከምደፋ በአለም
የኢየሱስን መስቀል ልሸከም
ሰይጣን ከሚያቆላምጠኝ
ኢየሱሴ በእግሩ ይርገጠኝ”

እያሉ በአማርኛም ደግሞ በደስታ ይዘምራሉ። እኔም ከስር ከስር ከእነርሱ እየሰማሁ አብሬ እዘምራለሁ። እዚህ ስብስብ ውስጥ ሁሉም ነገር ከልብ እና በፍቅር ነው የሚደረገው። ከውጪ ያለባቸውን ጫና የሚቋቋሙት በዚህ መንገድ ነውና።

የዛሬው ለእኔ ሁለተኛ ፕሮግራሜ ነው። ሁሉም መሬት ነውና የሚቀጠው እኔም ቀጭኗ ፑልፒት ስር ግድግዳ ተደግፌ ተቀምጫለሁ። የስብከቱ ሰዓት ደርሶ ሰባኪው ይሰባካል። የስብከቱም ትኩረት "በዚህ ፍፁማዊ የእስልምና ተዕዕኖ ባለበት ምድር በመንፈስ ቅዱስ ኀይል መኖር" የሚል ነበር። ሁሉም የመንፈስ ቅዱስን ሃይል አጥብቆ መፈለግ እንዳለበት ያስረዳል። የተለያዩ ጥቅሶችን እያነሳ ይሰብካል። በአጋጣሚ ሆኖ ደግሞ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቦታ ያገኘሁት እና ወደ እዚህ ያመጣኝ ሰው በመንፈስ ስለ መሞላት የሚያብራራ መፅሐፍ ሰጥቶኝ ሳምንቱን ሳነበው ነበር የቆየሁት።

ሰባኪውም ስብከቱን ሲጨርስ ፀሎት የምትፈልጉ ወደ መሃል ኑና እንፀልይላችሁ አለ። የተወሰኑ ሰዎች ወደ መካከል ወጡ። እኔም አብሬ ወጣሁ እና ተንበረከኩ። የዚያን ዕለት በልዩ ሁኔታ የሆነ ሃይል ተሰማኝ። በአዲስ ቋንቋም ተናገርሁ። በጣም ደስ አለኝ። ይህ ለእኔ ልዩ ክስተት ነበር። መርሃ ግብሩ አልቆ በወንድማዊ ፍቅር ወደ ምኖርበት ጊቢ እያበረታቱ ወሰዱኝ።

በመንፈሳዊ ህይወቴ እየጠነከርኩ መጣሁ። ማንበቤን እና መፀለዬንም ቀጥያለሁ። የእግዚአብሔር ቃል በተለየ ብርሃን ነው በውስጤ የሚገባው። እግዚአብሔር ያስተምረኛል። አንድ ቀን እንዲያውም የሆነ ድምፅ ከቤት እንድወጣ ይገፋፋኛል። ተነስቼ ወጣሁ። ማታ ነው። "በዚህ ሂድ" "በዚህ ታጠፍ" የሚለኝ አይነት የውስጥ ግፊት ነበር። መጨረሻ ላይ አርብ አርብ የምንሰግድበት “መስጂድ ሳራ” የሚባለው ትልቅ መስጊድ ጋር ስደርስ “ቁም” አለኝ። ከዚያ ዝም ብዬ መስጊዱን ተመለከትኩት። ማታ ስለሆነ መስጊዱ አናት ላይ ያሉት ጨረቃና ኮከብ በመብራት (ውስጣቸው በተገጠመላቸው) ደምቀው ይታያሉ።

ከዚያ ውስጤ የሚጮህ ድምፅ ይሰማኝ ጀመር “እየሰገድክ ያለኸው ለጨረቃና ለከዋክብት ነው። ይህ ደግሞ ጣዖት አምላኪነት ነው። ጣዖትን ማምለክ ደግሞ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነው” እያለ ያነበብኳቸውን የተለያዩ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች እያስታወሰ ለረጅም ደቂቃ ወቀሰኝ። ተቆጣኝ ብል ይሻላል። ከዚያ ወደ ቤት ተመልሼ ላብ በላብ እስከምሆን ድረስ የምጥ ፀሎት ፀለይኩ። የዛኑ ዕለትም "ስዕለት" ተሳልኩ። “እግዚአብሔር ሆይ ከዚህ ወስጥ ብታወጣኝ እድሜዬን ሁሉ ለአንተ እኖራለሁ የምትፈልገውን ሁሉ አደርጋለሁ” ብዬ ተሳልኩ።

ከዚህ በኋላ...በየቀኑ እየሔድኩ የመንጃ ፈቃድ ትምህርቴን እማራለሁ። ከእነዚያ ሶስት ሙስሊም ሃበሾች ጋር እከራከራለሁ። በዚያች ድብቅ ቤተክርስቲያን አርብ አርብ እየሄድኩ እማራለሁ። የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮችም የደህንነት ትምህርት መማር አለብህ አሉኝና ከጥቂት አዲስ አማኞች ጋር መማር ጀመርሁ። በቤቴ ያለኝ ፀሎትና ንባብም ቀጥሏል። በቃ አሁን ውስጤ በደንብ እየተደራጀ መጣ። የደህንነት ትምህርቱንም ቶሎ ቶሎ አስተማሩን እና የጥምቀት ጊዜያችን ደረሰ። እዚያችው ቤት ውስጥ ከሳሎኗ አጠገብ ባለች ክፍል ውስጥ ከፕላስቲክ በተሰራ ተገጣጣሚ ገንዳ ውሃ ተሞላና ተጠመቅን።

የመጠመቂያ ልብስ ብሎ ነገር የለም። ሰፋ ያለ ቢጃማ ተሰጠን ተጠመቅን። የጥምቀት መርሃ ግብሩ ደስ የሚል ነበር። አርብ ቀን ነው የተካሄደው። የገባነው ሃሙስ ማታ ነው። ለሊቱን በአዳር ፀሎት ነው ያሳለፍነው (በነገራችን ላይ ብዙ ጊዜ አዳር ፀሎት ይደረጋል)።

ከዚህ በኋላ ወደዚያ መስጊድ መግባት በግልፅ “ክረስቶስን መካድ” መስሎ ተሰማኝ። “ከስራ የተለየ እምነት የሞተ ነው” የሚለውና “በሰው ፊት የሚክደኝ...” የሚለው ቃል አይምሮዬን ሊለቀኝ አልቻለም። በሐዋርያት ስራ መፅሐፍ ላይም ያነበብኳቸው ለክርስቶስ ሲሉ የተሰዉ ሰዎችንም አስባቸዋለሁ። በቤተክረስቲያንም በየ ፕሮግራሙ በአረብ ሃገራት ስለ ክርስቶስ ሲሉ የተሰዉ ሰዎች ታሪኮች ይነበቡ ነበርና እንርሱንም አስባለሁ። አሁን አንድ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ ደመደምኩ። ለአሰሪዎቼ የክርስቶስ ተከታይ መሆኔን መናገር እና የሚመጣውን መቀበል። ነገር ግን የእናቴ ጉዳይ በጣም አሳሰበኝ።

እናቴ በድህነት ነው ያሳደገችኝ። ገና በአስራ ሰባት ዓመቷ ከአክሱም ተሰዳ አዲስ አበባ መጥታ በነበረበት ጊዜ ነው ከአባቴ ጋር ተጋብተው የወለደችኝ። አባቴም የአየር መንገድ ሰራተኛ ማህበር ሰብሳቢ ስለነበር ከኢሃፓ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ደርግ አሰረው። እናቴ እኔን አርግዛ ነበር እርሱ የታሰረው። ሲፈታ ተወልጄ የወራት ዕድሜ ላይ ነበርኩ። እንደ ተፈታም ከአገር ጠፍቶ ሄደ። በቃ ሄደ። ሲሄድ ለአጭር ጊዜ ነው ብሏት ነበር የሄደው ነገር ግን ድምፅም ጠፋ።

እናቴ አዲስ አበባ ከአንድ ወንድሟ በቀር የምታውቀው ሰው አልነበረምና እርሱ ጋር ተጠጋች። በዚያም ለመኖር ምቹ ስላልነበር ምርጫ ስታጣ እኔን ይዛኝ ሰው ቤት በሰራተኝነት ተቀጠረች። በቃ ከዚያ በሁዋላ ስራዋ የሰው ቤት ሰራተኝነት ሆነ። እኔን ለማሳደግ ህይወቷን ነው የከፈለችው። በመጨረሻም ሳውዲ ሄደች። ከአምስት አመት በኋላ እኔን ወደ ሳውዲ እንድመጣ አደረገች።

ሳውዲ ከገባሁበት ምሽት ጀምሮም እንግዲህ እሰከ አሁን የተረክሁላችሁ ታሪክ ተፈጠረ። እናቴ እኔን በጣም ተስፋ ታደርግ ነበር። ሳውዲ ውስጥ እኔን መስመር አስይዛ ከሌላ የወለደቻት ታናሽ እህትም አለቺኝ (አዲስ አበባ ዘመድ ጋር የተወቻት) እርሷንም መስመር አስይዛ ከዘመናት የሰው ቤት ስራ ማረፍ ነው የምትፈለወገው። ይህንን በደንብ አውቃለሁ። እንደ አንድ እናቱ ዋጋ እንደከፈለችለት ልጅም የሚገባትን ማድረግ ግዴታዬ ነው።

ነገር ግን በልዩ ብርሃን የተገለጠልኝን ክርስቶስን የሚያስክድ ህይወት ውስጥ እየኖርኩ ይህንን ለማድረግም ከበደኝ። የእናቴም ሁኔታ አስጨነቀኝ። ነገር ግን ከእናቴ ክርስቶስን ማስቀደም እንዳለብኝ ስለተረዳሁ በብዙ እንባ ውስጥም ሆኜ ቢሆን የእናቴ ጉዳይ ለእግዚአብሔር ተውሁለት። “ማንም እናቱን ክእኔ ይልቅ ቢወድ ለእኔ ሊሆን ኤእችልም” የሚለው ቃል ገዢ ሆኖ በልቤ ተቀምጧል።

አሁን ውስጤ ጢም ብሎ ሞልቷል። የክረስቶስ ተከታይ መሆኔን ለማንኛውም ሰው ለመናገር ድፍረት አግኝቷል። መጀመሪያ ውሳኔዬን ለእናቴ ነገርኳት። ከዚህ በኋላ የክርሰቶስ ተከታይ መሆኔን ለዓሚር ስዑድ ልነግረው ነው አልኳት። እሪታዋን አቀለጠችው። አንዲት ኤርትራዊ እና አንዲት ኢትኦጵያዊ ሰራተኞች ነበሩ እነርሱም ተጠሩ። በብዙ ለመኑኝ። ይህ አቋሜ መሆኑን ብዙ እንዳሰብኩበትም አስረዳኋቸው። ሊገባቸው አልቻለም ተነስቼ ወደ መኝታ ቤቴ ሄድኩና በጌታ ፊት ብዙ አለቀሰኩ (በእነርሱ ፊት ማልቀስ አልፈለኩም)። ውሳኔዬ ግን አልተለወጠም።
609 viewsΒενιαμίν, 16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 19:30:56 የቀጠለ
ከእነዚህ ከአዲሶቹ ወገኖቼ ጋር ተያይዘን ወደ ፀሎት ቤታቸው ሄድን። ደረስን። ዝም ተብሎ ዘው አይባልም። ተራ በተራ ነው የሚገባው። ምክንያቱም ድንገት ሙጠዋዎች ሊጠራጠሩ ይችላሉና። በየተራ ከመኪና እየወረድን ወደ ውስጥ ገባን። ቀድመን ነበር ደረስነው። ቤቷ ምድርና ፎቅ ቤት ነች የራሷ አነስተኛ ግቢ አላት። ፀሎት የሚደረገው ሳሎን ውስጥ ነው (አነስ ያለች ሳሎን ነች)። መሬቱ ምንጣፍ ነው። ግድግዳውን ስመለከተው በሲጥ ሲጥ ጥቅጥቅ ተደርጓል። ድምፅ ወደ ውጪ እንዳይወጣ ለመከላከል ነው።

አነስ ያለች ኪቦርድና አንድ ትንሽ ስፒክር መሬቱ ላይ ተቀምጧል። መዝሙር ለመስማት መሰለኝ አንዲት አነስተኛ ቴፕም እዚያው መሬት ላይ አለች። ወንበር የሚባል የለም። ከእንጨት የተሰራች ቀጭን ፑልፒት በአንዱ ጥግ በኩል ቆማለች። እኔም ገብቼ መሬት ላይ ነው የተቀመጥሁት። ጥቂት ቆይቶ ሰዎች መምጣት ጀመሩ። ሁሉም የሚገባው ግን በየተራ ነው። ግር ተብሎ አይገባም። ሴቶቹ ሲመጡ ሙሉ ለሙሉ ጥቁር ሂጃብ ተሸፍነው ነው የሚመጡት። ቀስ እያለም ያቺ ትንሽዬ ሳሎን በታዳሚዎቿ ጢም አለች። በግምት ከ25 ሰው በላይ ይሆናሉ።

የመጣ ሁሉ ግን ይተቃቀፋል። ታዲያ ረዘም ላለ ደቂቃ ነው ሰላምታ የሚለዋወጡት። በጣም ተነፋፍቀው ከብዙ አመታት በኋላ የተጋናኙ ነው የሚመስሉት (በኋላ ስረዳ ግን በየ ሳምንቱ ነው የሚገናኙት)። እኔንም የመጣ ሁሉ ሰላም አለኝ። ይዘውኝ የመጡትም ሁለቱ ሰዎችም ለመጣው ሰው ሁሉ አስተዋወቁኝ። አብዛናዎቹ ትግሪኛ ነው የሚያወሩት። አማርኛም የሚናገሩ ጥቂቶች አሉ። በርግጥ እኔም አዲስ አበባ ተወልጄ ልደግ እንጂ ቤተሰቦቼ ከአክሱም እና ከአድዋ ስለሆኑ ትግሪኛ በደንብ ባልችልም የተወሰነ እሰማለሁ።

ፕሮግራሙ ተጀመረ። ይዘውኝ ከመጡት መካከል አንደኛው (መጀመሪያ የገኘሁት ሳይሆን ሁለተናው ሰው) ፑልፒቷ ጋር ቆመና ፀሎቱን አስጀመረ። ደስ የሚል መረጋጋት የሚታይበት መካከለኛ ቁመና ያለው ወጣት ነው። ካልተሳሳትኩ በዚያ ወቅት ዕድሜው ከሰላሳ አይበልጥም (አሁን የት እንዳለ ስላማላውቅ ስሙን አልጠቀምም)። ሁሉም ይፀልያል ማንም ማመንንም አያይም። ለመፀለይም ጉትጎታ የሚፈልግ የለም። አብዛኛው ሰው የሚፀልየው በዕንባ ነው። በማይታወቅ ቋንቋም የሚፀልዩም አሉ። በእርግጥ ጴንጤዎች “ልሳን” የሚሉት የፀሎት ቋንቋ እንዳላቸው ቀድሞም አውቃለሁ። የፀሎት ሰዓቱም አለቀና መዝሙር ተዘመረ፥ ስብከትም ተሰበከ መጨረሻ ላይ የፕሮግራሙ መሪ (ፓስተሩ) “ዛሬ አዲስ ሰው በመካከላችን አለ” ብሎ በትግሪኛና በአማርኛ ተናገረ። እርሱ ወደ እዚህ ይወጣና እንፀልይለታለን አለ።

ወደ ፊት ወጣሁና ተንበረከኩ። በዚያች ቀንም ከ21 ዓመት በፊት በይፋ ጌታን ተቀበልኩ። ፓስተሩ ፀሎቱን ቀደም እያለ በሚመራኝ ወቅት፤ እኔ በጣም ጮክ ብዬ በትልቅ ስሜት ነበርና የምደግመው ብዙዎቹ ያለቅሱ ነበር። በእርግጥ እኔ ከዚያ በፊት በዚያች መኝታ ክፍሌ ደጋግሜ ጌታን ብቀበልም የዚህ ቀኑ ግን የተለየ ነበር የሆነብኝ። እጅግ ደስ አለኝ። ፕሮግራሙ ሲያልቅ ሁሉም እየመጣ ሰላም አለኝ። እንደየ አቅሙም አበረታታኝ። አይዞህ አሉኝ (ያለሁበትን ሁኔታ ፓስተሩ ታነግሮ ነበርና)።

መርሃ ግብሩ አልቆ ወደ ቤቴ መለሱኝና ሳምንት መጥተው እንደሚወስዱኝ ነግረውኝ ከአዲሶቹ ወገኖቼ ጋር ተለያየን። አሁን እኔ ፍፁም ተለውጫሁ። እውነተኛው አዳኝም ሆነ መድሃኒት ክርስቶስ እንደሆነ በግልፅ ተረድቻለሁ። ነገር ግን ደግሞ በኑሮ ጥያቄ ገፊነት፣ በእናቴ መካሪነት፣ በሁኔታዎች ግጥምትሞሽም ምክንያት የሳውዲ እስልምና ጉዳዮች ቢሮ የሚያውቀው ባለ “ሰርተፊኬት” ሙስሊም ሆኛለሁ። ምንድነው ማድረግ ያለብኝ? ሁለቱንስ አብሮ ማስኬድ እንዴት ነው የምችለው? በውስጤ ደግሞ ሁለት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ሰቅዘው ይዘውኛል። “ከስራ የተለየ እምነት ሙት ነው” የሚለውና “በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ” የሚለው ጥቅስ።

እነዚህ ሁለት ጥቅሶች በጆሮዬ ላይ በየቀኑ ይደውላሉ። የአዛን ጥሪውም ደግሞ ከመስጊድ ሰዓቱን እየጠበቀ ይደውላል። አጣብቂኝ ውስጥ ገባሁ። ይህ በእኔ ውስጥ የሚከናወነውን ነገር ከጌታ በቀር የሚያውቅ ማንም አልነበረም። አሁን የሆነ ከባድ ውሳኔ የሚፈልግ የህይወት ጫፍ ላይ አንደደረስኩ ይሰማኛል። ይህ ውሳኔ ደግሞ ህይወቴንም ሊያሳጣኝ የሚችል ዓይነት ውሳኔ ነው። ምን ላድርግ………ይቀጥላል (ነገ ማታ 1 ሰዓት)

ቴዎድሮስ ተጫን
@nazrawi_tube
461 viewsΒενιαμίν, 16:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 19:29:01 የዛሬ 21 ዓመት #5

“አሊ መንጃ ፈቃድ ያውጣና ስራ ፈልጎ ከዚህ ቤት መውጣት ይችላል” የሚል ዜና ነበር የአብድረሃማን ዜና። በጣም ደስ አለኝ። አንደኛ ከዚህ ቤት የምወጣበትና በነፃነት ክርስቶስን የምከተልበት ዕድል አገኛለሁ። ወጥቼ የምሰራ ከሆነ ለብቻዬ ነውና የምኖረው። ሁለተኛው ግን እግረ መንገድም ለጊዜውም ቢሆን ከመስጊድ የምጠፋበት ሰበብ አገኛሉሁ። ምክንያቱም መንጃ ፈቃድ ለማውጣት የሚኬድበት ቦታ እኔ ካለሁበት ሩቅ ነውና። “ደላ” ይባላል አካባቢው። መንገዱን ተጉዞ ተምሮ ለመምጣት ሙሉ ቀን ይፈጃል። ስለዚህ በዚህ ሰበብ ጠፍቼ እውላለሁ ማለት ነው። አሁን እንደ ከዚህ በፊቱ አብድረሃማን ሊያንቀሳቅሰኝ አያስፈልገኝም። ከተማውን በከፊል አጥንቼዋለሁ።

ከዚህ ቀን በኋላ ሊነጋጋ ሲል ያለውን ስግደት ገብቼ እሰግዳለሁ ከዚያ አልተኛም። የአውቶብስ እንቅስቃሴ ልክ ሲጀመር ተሳፍሬ ወደ ደላ (መንጃ ፈቃድ የምማርበት ቦታ) እሄዳለሁ። ሪያድ ከተማ ላይ በሁሉም አቅጣጫዎች ላይ ባስ አይገኝም ነገር ግን እኔ ከምኖርበት ወደ "ደላ" አለ። ሪያድ ውስጥ ሃያ ስድስት ሰው አካባቢ የሚይዘውን (እኛ እዚህ ኮስትር የምንለውን) መለስተኛ አውቶብስ ነው የሚጠቀሙት። ስለዚህ በማለዳ ኮስትር ላይ እሳፈራለሁ በየቀኑ ጉዞ ወደ “ደላ” ነው። “ደላ” ብዙ ተማሪዎች ከተለያየ ቦታ የሚመጡበት በጣም ትልቅ የመኪና መለማመጃ ስፍራ ነው። ታዲያ እንደኛ ሃገር "የመንጃ ፈቃድ ትምህርት ቤቶች" ትምህርቱ የሚጀመረው ከክፍል ውስጥ አይደለም።

አንድ ሰው ሊሰለጥን ሲመጣ መጀመሪያ መኪና ላይ ነው የሚወጣው። ከጉን (ጋቢና) አስተማሪው ይቀመጣል። መቆጣጠሪያ ፍሬን እግሩ ስር አለው። ንዳ ይለዋል። ከዚያ አያያዙን ያይና “አንድ ወር ይማር” ወይም “አስራ አምስት ቀን ይበቃዋል” ይላል። የሚማርበትን ቀን ብዛት የሚወሰነው ችሎታው ነው። አስተማሪውም እኔን ፈተሸኝ። በህይወቴ መኪና ነድቼ አላውቅምና ጥሩ አልነበርኩም (ኢትየጵያ እያለሁ እናቴ መንጃ ፋቃድ አውጣ ብላ ብር ልካልኝ ነበር እኔ ግን ብሩን ቅሜበት ነበር)።

አስተማሪውም አነዳዴን አይቶ አንድ ወር አዘዘልኝ። ገላገለኝ ማለት አይደል? አንድ ወር ሙሉ “ደላ” ተመላለስሁ። ሁል ጊዜ ጠዋት ከመውጣቴ በፊት እፀልያለሁ ወደ ቤት ስመሰስ ደግሞ ንባቤንና ፀሎቴን እቀጥላለሁ። የኪችን ረዳትነቴን ናጂር ተክቶኛል። አልፎ አልፎ አግዘዋለሁ። አሁን የእኔ ስራ መማር እና መፀለይ መፅሐፍ ቅዱስ ማንበብ ብቻ ሆኗል። ግቢ ውስጥ ካለሁ ግን መስጊድ መግባቴ ግድ ነው።

ታዲያ በጣም ደስተኛ ነኝ። ድሮ የማውቃቸውንና በርቀት የምሰማቸውን የጴንጤ መዝሙሮች እዘምራለሁ። ማንም ስለማይሰማኝ (አማርኛ ስለሆነ) በየ አውቶብሱም በየመንገዱም እዘምራለሁ። ጀለቢያዬን ለብሼ ያቺን ቆብ አድርጌም እዘምራለሁ። ከላይ ለሚያየኝ ሙስሊም እመስላለሁ ውስጤ ግን የተቀጣጠለ ክርስቲያን ሆኗል።

በዚህ መካከል ልክ እንደ እኔው መንጃ ፈቃድ ለመውጣት ደላ የመጡ ሶስት ሃበሾች አገኘሁ። ሶስቱም ሙስሊሞች ናቸው። ስናወራ እና ስንጫወት ስለ ክርስቶስ አዳኝነት ነገርኳቸውና ደነገጡ። ምክንያቱም ሲያዩኝ ጀለቢያና ቆብ አድረጌያለሁ። የምሰራውም ዓሚሮች ቤት እንደሆነ ነግሪኣቸዋለሁ። ፍርጥም ብዬ የማወራው ደግሞ ስለ ክርስቶስ ነው። አንድ ሁለት ቀን ተደነቁ ከዚያ በኋላ ግን በከፍተኛ ንዴት እና ቁጣ (ያው ሳውዲ መሆኑ ጠቅሟቸዋል) ስለ እሰልምና ሊያስረዱኝ ሞከሩ በተለይ ሁለቱ። እኔም ስለ ክርሰቶስ ከመፅሐፍ ቅዱስ ያነበብኩትን በድፍረት እነግራቸዋለሁ። ከእነኚህ ልጆች ጋር በየቀኑ እንገናኛለን፥ በየቀኑም እንከራከራለን። በአብዛኛው ግን የሚከራከሩኝ ሁለቱ ናቸው። አንደኛው ዝም ነው የሚለው። ግራ የገባው ነገር ያለ ይመስላል።

ብዙ ጊዜ ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ (ደላ ሆነን) መስጊዱ ለስግደት ሲጣራ (አዛን ሲል) እነዚህ ሶስቱም ሃበሾች ወደ መስጊድ ይሄዳሉ እኔ ግን አልሄድም። ይህም በጣም ያናድዳቸዋል። ከእነዚህ ልጆች ጋራ በየቀኑ ክርክርና ጭቅጭቅ ሆነ። አንድ ቀን እንደተለመደው ስንከራከር (እየተጯጯህን ነው የምንከራከረው) ቆየንና ከመስጊድ የስግደት ጥሪ ተሰማ። እዚያው ግቢ ውስጥ መስጊድ አለና። ልክ አዛኑን ሲሰሙ ሁለቱ ዋነኛ ተከራካሪዎች “ስንመለስ እንቀጥለዋለን” ብለው ሄዱ ያ ዝምተኛው ልጅ ግን ለመቅረት የዳዳው እምስላል። እነርሱ ግን ፋታም አልሰጡት “አትመጣም እንዴ” ብለው ይዘውት ሄዱ። ይህ ልጅ ኢትዮጵያ እያለ ከአባቱ ጋር ሲኖር ኦርቶዶክስ እንደ ነበረና። ሳውዲ ሲመጣ ግን እናቱ ሙስሊም ስለነበረች ወደ እስልምና እንዲገባ እንዳደረገችው ከቀናት በኋላ አጫውቶኛል።

እነርሱ ተያይዘው ወደ መስጊድ ልክ አንደ ሄዱ አንድ ጎልማሳ ሃበሻ ሰው ወደ እኔ ጠጋ አለና ሰላም ካለኝ በኋላ “በጌታ ነህ?” አለኝ (ለካ እያዳመጠን ነበር ስንከራከር) ምንድነው በጌታ ነህ ማለት? አልኩት። “አይ ክርስቲያን ነህ ወይ ማለቴ ነው” ብሎ መለሰለኝ። አዎ ክረስቲያን ነኝ አልኩት። በጣም ተገረመና እዚህ ከተማ ውስጥ እኮ ክረስቲያኖች አለን። በአንድነት ተሰብስበንም ክርስቶስን እናመልካን አለኝ። በጣም ደስ አለንኝ። በፍፁም ገምቼ የማላውቀው ጉዳይ ስለሆነ። ሰውዬውም በጣም ደስ አለው። አድራሻዬን ነገርኩት የግቢያችንንም ስልክ ሰጠሁት።

በማግስቱም ደወለልኝ። ከአንድ ወንድም ጋር ወደአንተ ልንመጣ ነው አለኝ። ስልከኛውም ሱዳናዊ የግቢያችንን አድራሻ በደንብ አድርጎ አስረዳልኝ። መሸት ሲል ሁለት ሆነው መጡ። አስጠሩኝና ወጣሁ። በመኪና ነው የመጡት “ግባ” አሉኝና መኪና ውስጥ ገባሁ። የፈሩ ይመስላል። ለነገሩ ግኢያችን እንኳን በድብቅ ለሚያመልክ ጴንጤ ለመንገደኛ ሙስሊም ሰውም ያስፈራል። መኪና ውስጥ ከገባሁ በኋላ ትንሽ ፈቀቅ ብለው አቆሙና ጥያቄዎች ይጠይቁኝ ጀመር። ለካ እየፈተሹኝ ነበር (ከቀናት በኋላ ነው የገባኝ)።

እኔ ግን የሚመስሉኝን ስላገኘሁ በደስታ ስለ ክርስቶስ እናገራለሁ። ከላይ እንደነገርኳችሁም ያለፍኩበትን ስቃይ አወራለሁላቸው። በደንብ ሰሙኝ። ከዚያ እዚህ ከተማ ላይ ቤተክርስቲያን አለ። ግን በድብቅ ነው የምንሰበሰበው። ፈቃደኛ ከሆንክ ነገ መጥተን እንውስድህ አሉኝ። የመጡት ሃሙስ ቀን ነበርና። በማግስቱ አርብ ነው (አርብ በሳውዲ እሁድ እንደማለት ነው)። በጣም ደስ እለኛል አልኳቸው።

ልክ በዚህ ወቀት እግዚአብሔር የሆነ ነገር እየሰራ እንደሆነ ማስተዋል ጀመርሁ። እስከዛሬ የሚሆነው ሁሉ የህይወት ገጠመኝ እና የእኔ ጭንቀት ብቻ ነበር የሚመስለኝ። ምሽቱን ደስ ብሎኝ አመሸሁ። አይነጋ የለም ነጋ። በማግስቱ (አርብ) በተቃጠርንበት ሰዓትም መጡ። በጣም ተጠንቅቀው ነው የሚንቀሳቀሱት። “ሙጠዋዎቹ” አሉዋ። ሙጠዋዎች ሲቪል ለባሽ እስላማዊ ፖሊሶች ናቸው። ስራቸውም የሸሪዓውን ህግጋት ማስከበር እና እንዲህ ያሉትንም ክርስቲያኖች ማደን ነው። በኋላ አንደሰማሁት እነኚህ "ሙጠዋ" የሚባሉት ፖሊሶች የተጠራጠሩትን ቤት ድንገት ገብተው ያለማስጠንቀቂያ በርብረው የመፈተሽ ስልጣን አላቸው። ሳውዲ ውስጥ በግል ክረስእቲያን መሆን ይቻላል። መገለሉንና ጫናውን ለቻለው። ነገር ግን ተሰብስቦ መፀለይ፣ መፅሐፍ ቅዱስ በግልፅ እዞ መንቀሳቀስ እንዲሁም ለሌላ ሰው ወንጌል መንገር እና ትራክት መስጠት በፍፁም የተከለከለ ነው።
433 viewsΒενιαμίν, 16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 19:00:51 የቀጠላ
ጓደኛዬ ግርማ ደግሞ በላከልኝ ፅሁፎች ላይ “የተፃፈ ፀሎት” አግኝቼ ነበር። ካልተሳሳትኩ ከአርባ ጊዜ በላይ ፀልዬዋለሁ (ፀሎቱ እኛ አሁን ጌታን ለሚቀበሉ ሰዎች እንዲፀልዩት የምንመክረው ዓይነት ፀሎት ነበር)። ጌታን መቀበሌን ግን አላውቅም ነበር። ሳይታወቀኝ ግን ልቤ ወደ መፅሐፍ ቅዱሱ አምላክ አዘንበሏል። ስህተት ውስጥ እንዳለሁም በደንብ ገብቶኛል። እንዴት ገባህ የሚለኝ ካለ? እኔንጃ ነው መልሴ። ግን በቃ ገባኝ። እግዚአብሔር አጠገቤ ቆሞ የሚያወራኝ ሁሉ ይመስለኝ ጀመር።

በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አቅጣጫዬ ተቀየረ። እውነተኛው አምላክ የመፅፍ ቅዱሱ አምላክ እንደሆነ እና እውነተኛው መዳን በክርሰቶስ በኩል እንደሚገኝ ተረዳሁ። ማንም የሚያስተምረኝ ሰው አጠገቤ አልነበረም። በእርግጥ ነቢዩም ሆነ ግርማ የላኩልኝ መፅሃፍት የተወሰነ እገዛ አድርገውልኛል (ነቢዩ የላከልኝ መፅሐፍ ውስጥ ስለ ገሃነብ ፍርድ የሚናገር ነገር ነበረውና)። ነገር ግን መፅሐፍ ቅዱስ በልዩ ሁኔታ ነበር የበራልኝ። መፅሐፍ ቅዱስ ሳነብ የሆነ ሰው የሚያወራልኝ እንጂ የተፃፈ ነገር የማነብ አይመስለንም ነበር። በአጭሩ እኔ አልገባኝም ነበር እንጂ ደንበኛ የክርስቶስ ተከታይ ሆኛለሁ።

ነገር ግን አሁንም “አዛኑ” ይጣራል። መስጊድም መሄድ አለብኝ። መስገዴም ግድ ነው። እንዲያውም አንዳንድ ጊዜ መፅሐፍ ቅዱሴን እያነበብሁ ወይም እየፀለይሁ በመሃል ከተማው “አላሁ አክበር” በሚል የመስጊድ አዛን (ጥሪ) ድብልቅልቅ ይል ነበር። ምን ደርጋለሁ? ተነስቼ (አቋርጬ) መሄዴ ግድ ነው። በአጭሩ ምን መሰላችሁ የሆነው በክርስቶስ የሚገኘውን እግዚአብሔር ሳመልክ እቆይና መስጊድ ሄጄ ደግሞ በመሃመድ ይገኛል ወደ ተባለው አላህ አሰግዳለሁ።

በዚህ ጉዳይ ሁልጊዜ እጨነቃለሁ። አንዳንድ ጊዜም እየሰገድኩኝ ወደ ክርስቶስ ለመፀለይ እሞክራለሁ። ይህ ምን ዓይነት የውስጥ ስቃይ እንደሚፈጥር አስቡት? ምንድነው ማድረግ ያለብኝ? የገባሁበትም ወጥመድ ደግሞ እንዲህ በቀላሉ ዘልዬ የምወጣበት ዓይነት አልነበረም። በዚህ ጭንቀቴ መካከል እያለሁ አብድረሃማን ከአሰሪዎቼ ዘንድ አንድ አዲስ ዜና ይዞልኝ መጣ……ይቀጥላል (ነገ ማታ 1 ሰዓት ከ30)

ቴዎድሮስ ተጫን
@nazrawi_tube
70 viewsΒενιαμίν, 16:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 18:59:01 የዛሬ 21 ዓመት #4

ከዚህ ውሳኔዬ በኋላ በሪያድ ከተማ በተለይ ለምኖርበት ጊቢ አቅራቢያ የሆኑና እስላማዊ ትምህርቶች በእንግሊዘኛ የሚሰጥባቸውን መስጊዶች ሁሉ አሰስኳቸው። ብዙ ጊዜ የምንቀሳቀሰው ደግሞ ከሰዓት በኋላ ነው። ምክንያቱም ከሰዓት በኋላ የግቢው ሰው እንዳለ ይተኛል። ወይም በየክፍሉ ማቀዝቀዣውን ከፍቶ ይቀመጣል።

ሪያድ ከተማ ከሰዓት በኋላ በጣም ይሞቃልና (ይሞቃል ብቻ ከማለት እሳት ይዘንባል! ማለት ይቀላል) ያቺን ሰዓት እኔ እጠቀማታላሁ። በሜትር ታክሲም ሆነ በእግሬ እዞራለሁ። በየመስጊዱ። አንዳንድ ጊዜ በመንገድ ላይ በእግር የሚሄድ ሰው እኔ ብቻ ልሆን እችላለሁ። በዚያ ጠራራ ፀሃይ የከፋ ጉዳይ ከሌለው ማን ይንቀሳቀሳል። ግን አይደክመኝም የፀሃዩም ሃይል ብዙም አይሰማኝም። ምክንቱም አሁን እኔ እስልምናን በምችለው ያክል ማውቅ እና ልክነቱን አረጋግጬ ከጭንቀቴ ቶሎ ማረፍ ፈልጌያለሁና።

በየሄድኩበት ቦታ የሚሰጡኝን መፅሐፍት ሰብስቤ እመጣለሁ። መኝታ ቤቴ አስቀምጣለሁ። ቀስ እያለም አንድ መለስተኛ ካርቶን ሞላ። በምችለውም አነባለሁ። በተለይ ደግሞ አንድ ቦታ እንግሊዘኛ ቁረዓን ከማብራሪያ ጋር የሆነ ትልቅ መፅሐፍ ሰጡኝ (እኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ከማብራሪያው ጋር የምንለው ዓይነት) እርሱንም ቢሆን ተያያዝኩት። ነገር ግን እንዲህም እያደረግሁ ነፍሴ እረፍት ማግኘት አልቻለችም። ከጭንቀት ነፃ ሆኜ እንደማንኛውም ሙስሊም መስጊድ መሄድ፣ መስገድ እና እስላማዊ ስረዓቶችን መፈፀም አልቻልኩም። ብዙ ለማወቅ ብሞክርም በውስጤ ግን ምንም የተለወጠ ነገር አልነበረም። ተስፋ ቢስነቴ እንዳለ ነው።

ነገር ግን በዚህ እስልምናን የማወቅ ጥረቴ መካከል እስከ ዛሬ ድረስ በሚገርመኝ ሁኔታ አንድ ነገር ተከሰተ። የምር እና ከልቤ የሆነ ፀሎት ፀለይኩኝ። ሳውዲ በገባሁ በሰባተኛው ወር መኝታ ክፍሌ ገብቼ በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ በጉልበቴ ተንበርክኬ እውነተኛ ፀሎት ፀለየኩ። “እግዚአብሔር ሆይ አንተ በእውነት ካለህ ትክክለኛውን ሃይማኖት ጠቁመኝ” ብዬ በምጥ ፀሎት ለመንሁት። እስከዚያ ጊዜ ድረስ በራሴ እጨነቃለሁ እንጂ እግዚአብሔርን ለምኜ አላውቅም ነበርና። ከዚያም ቀን በኋላ በልቤ አንድ ሃሳብ መጣልኝ “እስልምና እውነተኛ ሃይማኖት ከሆነ የምሬን ሙስሊም ልሁን ነገር ግን እስኪ ስለ ክርስትናም ልወቅ ለዚህ ጥረቴም ያግዘኛል” ብዬ አሰብሁ።

ለዚህም እርምጃዬ እንዲረዳኝ በቅድሚያ “መፅሐፍ ቅዱስ ማንበብ አለብኝ” ብዬም ወሰንኩ። ነገር ግን በሳውዲ አረቢያ ምድር ደግሞ መፅሐፍ ቅዱስ ከየት ይገኛል?። ሳውዲ አረቢያ እኮ ነው! ሳውዲ እስልምና መቶ እጅ ነው ተብሎ የሚነገርባት ሀገር ነች። መፅሐፍ ቅዱስ በሪያድ ከተማ ካሉ መጽሃፍት መደብሮች ሮጥ ተብሎ የሚገዛ ነገር አይደለም።

በጣም የሚያስደንቀው እንደ አጋጣሚ ሆኖ በዚያው ሰሞን እኔ የምኖርበት አካባቢ ይኖር የነበረ አንድ ሃበሻ ወደ ኢትዮጵያ ሊሄድ እንደሆነ ነገረኝ። ይህ ሰው ለእኛ ግቢ አቅራቢያ በሆነ ቦታ ላይ የቅመማ ቅመም መሸጫ ሱቅ ውስጥ ተቀጥሮ ይሰራል። ረጅም ዘመን ሳውዲ ኖሯል ሚስትና ልጆቹም እዚያው ናቸው። አንዳንድ ጊዜ ሲደብረኝ እርሱ ጋር እየሄድኩ ሱቅ ውስጥ እንጫወት ነበር። አክራሪ ሙስሊም ነው። በተቻለውም መጠን እስልምናን እንድረዳና የሳውዲን አኗኗር እንዳውቅም ይጥራል። ደግና ጥሩ ሰው ነው።

ይህ ሰው ወደ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ጥየቃ ሊሄድ መሆኑን ሲነግረኝ "መፅሐፍ ቅዱስ" ለማግኘት ጥሩ አጋጣሚ እንደተፈጠረልኝ አሰብሁ። ወዲያው እንግሊዘኛ መዝገበ ቃላትን ጨምሮ አንዳንድ የምፈልጋቸው መፅሐፍቶች አሉ ታመጣልኛለህ አልኩት። ችግር የለውም አለኝ። የተወሰነ ብር ሰጠሁትና “ይህንን ብር ለጓደኛዬ ስጠውና እርሱ ገዝቶ ይሰጥሃል አልኩት። ፈቃደኛ ነበርና የጓደኛዬን ስልክ ጨምሬ ሰጠሁት።

ከዚያ አዲስ አበባ ላለ ወዳጄ (ነብዩ ይባላል) ደወልኩለትና መፅሐፍ ቅዱስ እንዲገዛልኝና ከኦክስፎርድ መዝገበ ቃላት ጋር አንድ ላይ በወረቀት በደንብ አድርጎ ጠቅልሎ እንዲልክልኝ ነገርኩት። ግርማ ለሚባል አንድ የጫት ዘመን ጓደኛዬም ነብዩን እንዲረዳው ነገርሁት። ነብዩ እንደምፈልገው አድርጎ መፅሐፍቱን ጠቅልሎ ሰውዬው በአስራ አምስተኛ ቀኑ ወደ ሳውዲ ሲመለስ ላከልኝ።

በአስገራሚ ሁኔታ በሙስሊሙ ሰውዬ በኩል የሳውዲን ኤርፖርት ጥብቅ ፍተሻ አልፎ መፅሐፍ ቅዱስ እጄ ገባ። ያው ነብዩ ጿሚ ፀላይ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነበርና የላከልኝ ሰማኒያ አሃዱ የሚባለውን መፅሐፍ ቅዱስ ነበር። ስለ ማሪያም ማንነት እና ገድል የሚተርክም መፅሐፍ መርቆልኛል። ለፀሎት እንዲያግዘኝም ብሎ መሰለኝ ትንሽዬ የፀሎት መፅሐፍም ጥቅሉ ውስጥ አግኝቻለሁ። ግርማ ጓደኛዬም ምንም እንኳን ቃሚ ቢሆን እህቶቹ በጌታ ነበሩና እርሱንም አልፎ አልፎ ወደ ቸርች ይዘውት ይሄዱ ስለ ነበር ያግዘዋል ብሎ መሰለኝ ስለ ዳግም ልደት የምታብራራ ትንሽዬ መፅሐፍ አብሮ ልኮልኛል። እኔ ግን የጓጓሁት ለመፅሐፍ ቅዱሱ ነበር። ከግቢው ነዋሪዎች ለመሰወርም ብዬ ወዲያው በወረቀት ለበድኩት።

እጅግ በጣም እንደ ተራበ እና የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን በከፍተኛ ፍቅር ማንበብ ጀመርሁ። ከዘፍጥረት መፅሐፍ ከመጀመሪያው ምዕራፍ ከመጀመሪያው ቁጥር ጀምሬ ማንበብ ተያያዝሁት። መፅሐፍ ቅዱስን ወደድሁት። ከዚያን ቀን በኋላ ስራዬን ቶሎ ቶሎ ጨርሼ ሩጫ ወደ መፅሐፍ ቅዱስ ሆነ። ከመስጊድም በፍጥነት ተመልሼ ወደ መፅሐፍ ቅዱስ ነው። በቀን ውስጥ ረጅም ሰዓት አነባለሁ። ደስ!! ብሎኝ ነው የማነበው። ብሉይ ኪዳንን አዲስ ኪዳንን አነበብሁት “የተጨመረ” የተባለውን ሁሉ አነበብሁት። እዝራ ሱተኤል የለ፣ መቃብያን፣ መፅሐፈ ጦቢትም አልቀረኝ ሁሉንም ጥርግ አድረጌ አነበብሁት። ስራዬን እሰራለሁ መስጊድ እሄዳለሁ። ተመልሼ መፅሐፍ ቅዱስ አነባለሁ። የሲጋራው ሱስ በጣም ከአቅሜ በላይ ሲሆንና ማንበብ ሲያቅተኝ ደግሞ እወጣና አጨሳለሁ።

በዚህ ሁኔታ አንድ ወር የሚሆን ያክል ቆየሁ። በተለይ የነቢያቱን መፅሐፍ ሳነብ እደነግጥ ነበር “ለሰማይ ሰራዊት ለጨረቃና ለፀሐይ” መስገድ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ እንደሆነ የሚናገሩ ምንባባትን ሳነብ ያለሁበት ሁኔታ ፍንትው ብሎ ይታየኝ ጀመር። አነብ አነብ እና ተንበርክኬ ደግሞ እፀልያለሁ። በተለይ ወንጌላትን ሳነብ ውስጤ ተቃጠለ። አንዳች ነገር በልቤ ውስጥ እየተከናወነ እንደሆነ ይገባኝ ጀመር። በአጭሩ ከመፅሐፍ ቅዱስ ጋር ፍቅር ያዘኝ። ከዚያ ቀደም ስለ እስልምና ለማወቅ ፈልጌ የቁርዓን ትምህርት በእንግሊዘኛ በሚሰጥባቸው መስጊዶች ተዘዋቀወሬኣለሁ። አንዳንድ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተፃፉ እስላማዊ መፅሐፍቶችም ሰጥተውኛል። እንግሊዘኛው ቁርዓንም አለኝ። መፅሐፍ ቅዱስን ማንበብ ግን ነፍሴ ሆነ።

አሁን የሆነ በማላውቀው ሁኔታ የተወሰነ የመረጋጋት ስሜት ይሰማኝ ጀምሯል። በእርግጥ ምንም የተለወጠ ነገር የለም። ሁሉም እንዳለ ነው። ግን ያለማቋረጥ አነባለሁ። በከፍተኛ ሁኔታም እፀልያለሁ። በጣም ረጅም ሰዓት አልፀልይም ፀሎቴ ግን የምጥ ነበር። ሰውነቴ ላብ በላብ እስከሚሆን ድረስ እየቃተትኩ ነበር የምፀልየው። ጓደኛዬ ነብዩ የኦርቶዶክስ መዝሙርም ልኮልኝ ነበርና እርሱን በጆሮ ማዳመጫ እሰማለሁ። በተለይ ከንሰሃ ጋር የተያያዙ መዝሙሮችን በከፍተኛ ፍቅር ነበር የምሰማቸው።
71 viewsΒενιαμίν, 15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 19:01:21 መስጊድ ገብተን ስግደት ካለቀ በኋላ ወደ ኋላ ዞር ብሎ (እርሱ ፊት ተሰላፊ ስለሆነ) መምጣት መቅረቴን ቼክ ያደርገኛል። ለግቢው ሰራተኛ መስጊድ መገኘት በስራ ገበታ ላይ የመገኘት ያክል ነው። ሁሉም መስጊድ ተገኝቶ ፊቱን ለዓሚሮቹ ያስመታል። በነገራችን ላይ የንጉሳዊያን ቤተሰቦች አንዱ ስራ በየአካባቢያቸው እስልምናን ማስከበር ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ በተለይ በረመዳን ወር በርካታ ስራዎችን ይሰራሉ።

ያቺን “ለአጭር ጊዜ ነው’ኮ” እያልኩ የምፅናናባትን ነዳጄን ጨረስኩ። አለቀች። አሁን እኔ የሳውዲ እስልምና ቢሮ የሚያውቀው ባለ ሰርተፊኬት ሙስሊም ነኝ። ውልፍት ብል “ከሃዲ ነህ” ብሎ ሸሪዓው በእኔ ላይ ተፈፃሚ ነው የሚሆነው። አይምሮዬ ሊፈነዳ ደረሰ። ስድስት ወር ሙሉ የማላምንበትን አደረግሁ። ያለሁት ሳውዲ ሪያድ ነው። ሰዉ ሁሉ ሙስሊም ነው። መንገድ ላይ የሚታየው ነገር ሁሉ ሙስሊም ነው። ፀሃዩ እና አየሩ ሁሉ ሙስሊም መስሎ ታየኝ። እዚህ መከካል ብቻዬን ሆኜ እሰከ መቼ አስመስላለሁ? ብዬ አሰብኩ። በመጨረሻም አንድ ውሳኔ መወሰን አለብኝ ብዬ ቆርጬ ተነሳሁ። “እስልምና ትክክል ከሆነ በቃ የምሬን ሙስሊም ልሁን” ወሰንኩ!……ይቀጥላል (ነገ ማታ 1 ሰዓት)

ቴዎድሮስ ተጫን
@nazrawi_tube
192 viewsΒενιαμίν, 16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-06 19:01:21 የዛሬ 21 ዓመት #3

ከረጅም ጉዞ በኋላ አንድ ህንፃ ስር ሲደርስ አውቶብሱ ቆመ። አሰልፈው አወረዱን እና ወደ አንድ ሰፊ ቢሮ ውስጥ አስገቡን። የት እንደመጣን ለማወቅ ዞር ዞር እያልኩ እንግሊዘኛ ፅሁፍ ስፈልግ “የሳውዲ እስልምና ጉዳዮች ቢሮ” እንደሆነ ቢሮው በር ላይ ከተለጠፈው ፅሁፍ ተረዳሁ። ለምን እንደ መጣን አሁንም አልገባኝም።

ከዚያ ያ ፊሊፒናዊው መምህራችን በሀገሩ ቋንቋ የሆነ ነገር አወራ እና ሁሉም (ፊሊፒኖቹ) ክብ ሰርተው ማውራት ጀመሩ። ምን እንደሆነ የገባኝ ግራ መጋባቴን የተረዳው ፊሊፒናዊ ኡስታዝ በእንግሊዘኛ ሲነግረኝ ነው። ለካ ነገሩ አሁን ለአቅመ ሙስሊምነት በቅተናል። መሰረታዊ ትምህርቶችም ተምረናል። ስለዚህ አሁን ጊዜው የስም ቅየራና እስልምናን መቀበላችንን የሚያረጋግጥ ሰርተፊኬት የምንቀበልበት ጊዜ ነው። ሳይነግሩን እያከነፉ ያመጡን እንግዲህ እዚያው ቢነግሩን የሚያንገራግር እንዳይኖር ይሆናል ብዬ አሰብሁ።

ነገሩ ሁሉ ጥድፍድፍ ያለ ነበር። ቶሎ በህግ ሊያስሩን የቸኮሉ ይመስላሉ። አንዴ ከፈረምን ምን እናመጣለን። ከዚያ በኋላ ሸሪዓው ነው የሚዳኝህ። ይህንን ስረዳ ነገሮች እየከፉ እንደመጡ ውስጤ በደንብ ተረዳ። ፊሊፒኖቹም ክብ ሰርተው የሚያወሩት ለካ አሪፍ የሙስሊም ስም ፍለጋ ነው። “አንተስ ማን ይባል አዲሱ ስምህ” አለኝ ፊሊፒኑ ኡስታዝ አይን አይኔን እያየ። ግርም አለኝ (እዚህ ጋር መድረሴ)። ባለ ሰርተፊኬት ሙስሊም ልሆን እንደሆነ ሳስበው ለራሴው ደነቀኝ።

ኡስታዙ ቆሞ እየጠበቀኝ ነው። “አሊ” አልኩት። አሊ ሙስሊም የሰፈሬ ልጅ ነው። አብረን ነበር ጫት የምንቅመው። ወደ ሳውዲ ልጓዝ ጥቂት ሲቀረኝ ስለ አረብ አገራት ባህል ያጫውተኝ ነበር። እርሱ ትዝ አለኝና አዲሱን ስሜን “አሊ” ይሁንልኝ አልኩት። ኡስታዙም ወደ ቢሮ ገብቶ አዲሱ ስሜ የተፃፈበትን ወረቀት አምጥቶ በፈቃዴ ሙስሊም መሆኔን በፊርማዬ እንዳረጋግጥ ጠየቀኝ። ፈረምሁ። እዚህ ደረሼ ታዲያ ምን አደርጋለሁ? አንድ ጊዜ ጀምሬዋለሁ (በልቤ ግን አሁንም ለአጭር ጊዜ ነው አልሁ)።

ከፈረምን በኋላ ሰርተፊኬቱንም ሳይሰጡን ወደ ስልጠናው ማዕከል መለሱን። ምናልባት ለአሰሪዎቻችን ልከውላቸው ይሆናል። ሳውዲ ሁሉም ዶክመንታችሁ ፓስፖርታችሁን ጨምሮ አሰሪዎቻችሁ (እነርሱ ከፊል ይሉታል) ጋር ነው የሚቀመጠው። ከስልጠና ማዕከሉ ሁሉንም አሰሪዎቻቸው እየመጡ ይወስዷቸው ጀመር። እኔንም አብድረሃማን ሲመጣ የሶስት ቀን ወዳጆቼን ተሰናብቼ ሄድሁ። ከአብድረሃማን ጋር በዚያው ወደ ገበያ ሄድንና ሁለት ጀለቢያ (ነጭ እነርሱ ቶብ ይሉታል)፥ ከውስጥ የሚለበስ ነጭ ሱሪ ሁለት፥ ነጯን ቆብም ሁለት እንዲሁም ቀዩን ዥንጉርጉር ሻሽ ከነ ጥቁሩ ክብ መደገፊያው ገዛልኝ። በጀቱ ከዓሚር ስዑድ ነው። እግቢያችንን እንደደረስን ግቢው በደስታ ዘለለ። ሁሉም ደስ አላቸው። ከመጣሁ ጀመሮ እንደዚህ በደስታ ሲመለከቱኝ አላየኋቸውም ነበር። ለካ “ክርስቲያን” መሆኔ ምቾት ነስቷቸው ነበር። ያልተደሰተ አልነበረም።

ከዚያን ቀን ጀምሮ ለየልኝ ማለት ነው። ነጩን ጀለቢያ ለበስሁ፥ ቆቧን አደረግሁ፥ መስጊድ ገብቼ እሰግዳለሁ፥ ስሜ አሊ ነው፤ “ያ አሊ” ሲባል አቤት እላለሁ። በቃ ደንበኛ ሙስሊም መሰልኩ። ግን ያለማቋረጥ በልቤ “ለአጭር ጊዜ ነው” እላለሁ። ከአንድ ሳምንት በኋላ ናጂር (የግቢው ፅዳት የነበረው) ወደ ሀገሩ ለእረፍት ሄደ።

ይህን ጊዜ “አሊ ስራ ተፈልጉለት እስኪወጣ ድረስ ለምን በናጂር ቦታ ለጊዜው አይሰራም” ተባልኩ። አሁን መፍራት ጀመርሁ። እነኚህ ሰዎች እዚሁ ሊያስቀሩኝ ነው እንዴ? አልኩኝ ለራሴ። ቢሆንም ናጂርን ተክቼ መስራት ጀመርሁ። አንድ ወር ሞላኝ እና ስድስት መቶ ሪያል ደሞዝ ተብሎ ተሰጠኝ። በህይወቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ደሞዝ በላሁ ማለት ነው። ሰንበት ሲል ጭራሽ የፅዳት ስራዬ ተስፋፍቶ የመስጊዱን ምንጣፍ በማሽን እንዳፀዳው ተወሰነ። ከሰለሙ አይቀር አንዲህ ነው እንግዲህ።

እኔ ወደ ሳውዲ የሄድኩት በነፃ ቪዛ የፈለግሁበት ቦታ (ፋብሪካ ውስጥ) ትሰራለህ ተብዬ እንጂ እዚያ ቤት ልሰራ አልነበረም። እንዲያ ቢሆን ኖሮ እግሬንም አላነሳ ነበር። አሁን የሚሆነው ሁሉ ከቁጥጥሬ ውጪ ነው። አይደርስ የለ በምጥም ቢሆን ሁለት ወሩ ሞላ። ናጂር የምር ነበር የናፈቀኝ። ናጂር የእረፍት ጊዜውን ጨርሶ መጣ። አሁን ይለቁኛል ብዬ ተስፋ አደረግሁ። ነገር ግን ናጂር አንደ መጣ ምግብ ከኪችን ወደ መመገቢያ ክፍል የማቅረብ ስራ እንድሰራ ተወሰነ። ቀጠልኩ። እሺ አሺ ብል ያዝኑልኝ ይሆናል ብዬም አስቤያለሁና “እሺ” ነው። ህይወትም እንደተለመደው ቀጥሏል። እበላለሁ፥ እጠጣለሁ፥ እሰግዳለሁ፥ በልቤ ግን አልጎሞጉማለሁ።

ከሁለተኛው ወር በኋላ ሁነታውን እየጠላሁት መጣሁ። ለአጭር ጊዜ የተባለው ጉዳይ ወራት አስቆጠረ። ውስጤ መጨነቅ ጀመረ። እስከ መቼስ እስመስላለሁ? ነገሩ እየረበሸኝ መጣ። እናቴንም “አንድ ነገር ማድረግ አለብሽ እያልኩ በየቀኑ እጨቀጭቃተት ያዝኩ። (እናቴ እዚያ ቤት ውስጥ ለብዙ አመታት የሰራች በታታሪነቷ ተወዳጅ ሰራተኛ ነበረች)። እርሷም ግራ ገባት። ምን ታድርገኝ። እኔስ ምን ላድርግ? ብድግ ብዬ እንዳልጠፋ ሰዎቹ ራሳቸው መንግስት ማለት ናቸው። ልሞክረው እንኳን ብል እናቴ እዚያው ቤት ነው የምትሰራው እርሷን መያዣ ማድረግ ነው። ምን ላድርግ? አስቡት አስኪ አንድ የሃያ አንድ ዓመት ወጣት ከኋላው ሱስና ስራ አጥነት የሚያሳድደው ከፊቱ የገንዘብ እና የጥሩ ኑሮ ተስፋ የሚያባብለው ከጎኑ በመከራ ያሳደገችው እናቱ ጉዳይ የሚያሳስበው፤ የማይፈልገውን ለማድረግ ደግሞ ግዳጅ ውስጥ የወደቀ፤ ምስኪን ወጣት።

ስድስት ወር ሞላኝ። እሰራለሁ እበላለሁ እሰግዳለሁ። የጭንቅ ኑሮ። ሰዎቹም የእኔን ጉዳይ እረሱት። እዚያው እንድሰራ ሁላ ፈለጉ። ቀስ በቀስም የህንዳዊው ሼፋቸው ረዳት ወደ መሆን አሳደጉኝ (በነገራችን ላይ ግቢው የራሱ ሼፍ አለው)። ደሞዜም ተጨመረ። በሚስጥር ቁጥር የምትዘጋ ትንሽዬ ጥቁር ሻንጣ ገዝቻለሁ ደሞዜን አየወሰድሁ አስቀምጠዋለሁ። ምንም ወጪ ስላልነበረብኝ ተጠራቀመ። ልቤ ግን ከሰመ።

እያስመሰልኩ የመኖሬ ጉዳይ ያለማቋረጥ ይረብሸኝ ያዘ። ሃዘንተኛ ሆንኩኝ። በቶሎ ከዚያ ግቢ እወጣለሁ የሚለውም ሃሳብ ተስፋ እያስቆረጠ መጣ። ከእናቴ ጋር መጨቃጨቅ ጀመርን። ግን እርሷ ምን ልታደርግ ትችላለች? መንም። ሁሉም ነገር አስጠላኝ። ለምንድነው እዚህ ሁሉ አረንቋ ውስጥ የገባሁት? መጀመሪያውኑ እንቢ ብዬ ለምን አልተመለስኩም? በእርግጥ ህይወትስ ራሱ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ነው? ራሴን ቀኑን ሙሉ እጠይቃለሁ። በቃ ተስፋዬ ተሟጠጠ። ሚጢጢዬ ፈላስፋም ሆነኩ።

ከስድስት ወር በኋላ ወደ ተውሁት ሱስ ተመለስኩ። እንደገና ሲጋራ ማጨስ ጀመርሁ። ሰራዬን እሰራሁ፥ አበላለሁ እጠጣለሁ፥ “እሰግዳለሁ”፥ ሲጋራ አጨሳለሁ። ደነዘዝኩ። አንዳንድ ጊዜ እያለቀስኩ ነው ወደ መስጊድ የምሄደው። መቀበል አቃተኝ። አሚር ስዑድ ደግሞ በደንብ ይከታተለኛል። የእኔ መኝታ ክፍል እርሱ ወደ መስጊድ ሲሄድ በሚያልፍበት መንገድ ላይ ስለሆነ። በተለይ ለሊት ካልተነሳሁ ቀስቅሶኝ ነው የሚያልፈው። በተለየ ሁኔታ እኔ ላይ ያተኩራል። ከልቤ እንዳልሆነ ጠርጥሮም ሊሆን ይችላል።
107 viewsΒενιαμίν, 16:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ