Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.01K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On Utube sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 19

2022-11-16 22:15:07 <<ክርስቲያን ንቅሳት ሊያሰራ ይችላልን?>>

መጋቢ ጆን ፓይፐር በ desiringod.org ላይ የሰጠው ምላሽ ወንድም አማኑኤል እንዳለ እንደተረጎመው
በየቀኑ ልንል በምንችልበት መንገድ ስለ ንቅሳት ከአድማጮቻችን ጥያቄዎች በኢሜይል ይደርሱናል። መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ንቅሳት ምን ይላል?
መጋቢ ዮሐንስ ፓይፐር (Pastor. John Piper)
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ንቅሳት የሚናገር አንድ ግልጽ ምንባብ እናገኛለን ዘሌዋዊያን 19፡28። ጥቅሱም እንዲህ ይላል <<ለሞተ ሰው ሰውነታችሁን አትንጩ በሰውነታችሁም ላይ ንቅሳት አታድርጉ እኔ እግዚአብሔር ነኝ።>> (አዲሱ መደበኛ ትርጉም) አሁን ይህንን ምንባብ ስናስብና ቀጥሎ ለመወሰን ጥቂት ደቂቃዎች ቆም ብለን ማሰብ ይገባናል። ቢያንስ ሁለት ምክንያቶችን አቅርበን ይህንን ምንባብ ለምን ለምን ቆም ብለን ማሰብ እንደሚገባን እንመልከት።

“ሕግ እና ባሕል”

አንደኛው ምክንያት እኛ ከሙሴ ሕግ ሥር አለመሆናችን ነው። “ስለዚህ ወንድሞች ሆይ እናንተም በክርስቶስ ኢየሱስ ሥጋ ለሕግ ሞታችኋል ይህም ከሙታን ለተነሳው ለእርሱ ለሌላው ሆናችሁ ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ ነው። (ሮሜ 7፡4 አመት) ስለዚህ እኛ በእግዚአብሔር ፊት ለመጽደቅ ወይንም በእግዚአብሔር ተቀባይነት ለማግኘት እንደ ሕግ አሰራር ከሙሴ ሕግ በታች አይደለንም። አሁን ከክርስቶስ ጋር ወዳለ ሕብረት መጥተናል የዚህም ሕብረት መገለጫ ደግሞ በእግዚአብሔር ፊት እንደ ጅረት የሚፈሰው የጽድቅ ፍሬያችን ነው። “አሁን ግን ቀድሞ ጠፍሮ አስሮን ለነበረው ሞተን ከሕግ ነጻ ወጥተናል ይህም አሮጌ በሆነው በተጻፈው ሕግ ሳይሆን በመንፈስ መንገድ እንድናገለግል ነው። (ሮሜ 7፡6 አመት) ስለዚህ በዚህ ምክንያት ዘሌዋዊያን 19ን የምንረዳበትን መንገድ በቀጥታ ከእኛ ጋር አያይዘን መሆን እንደሌለበት ያመለክታል።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በዚህ ምንባብ (ዘሌ 19) በዚህ ሁኔታ ውስጥ ስለሞቱ ሰዎች ተብሎ ቆዳን መቁረጥ ሆነ ንቅሳት ማድረግ እጅግ አደጋ የሚያደርስ ስለሆነ እየከለከለ ነው ማለት የሚቻል አይምስለኝም ወይም ደግሞ ከንፈርን ሊፒስቲክ መቀባትንም የኒከለክል ነው ማለት ይሆናል። ነገር ግን ከዚህ ይልቅ እነዚህን ምልክቶች ለሞቱ ሰዎች ብለው እስራኤላዊያን ሰውነታቸውን እንዳይነጩ የሚከለክለው በዙሪያቸው ያለው እውነተኛ የሆነውን አንድ አምላክ የማያውቁና የማያመልኩ ማዕበረሰቦች የሚያደርጉት በመሆኑ ምክንያት ነው። ይህንን በማድረግ ውስጥ አንድ እስራኤላዊ ለእግዚአብሔር ከገባው ቃል ኪዳን ይህም ለእግዚአብሐኢር ራሳቸውን የለዩ ሕዝቦች መሆናቸውን በመተው ርህጽስብ ግስር መመሳሰላቸውን የሚያሳዩበት ነው። ይህም ቆዳ ላይ የሚደረግ ንቅሳት ብቻ ሳይሆን በልብ ውስጥ ያለኝ ለእግዚአብሔር የሚገባውን ቁርጠኝነት ማጉደልን የሚያሳይ ነው።
ስለዚህ ከእንግዲህ ዘሌዋዊያንን በመጥቀስ ማንንም ንቅሳት እንዳያደርግ ልከለክል አልችልም። ይህንንም አይነት ትዕዛዝ እጅግ በጥእም ከባድ ነው። ከእነዚያ ከላይ ካስቀመጥኩት ሁለት ምክንያቶች ውስጥ ስለ ክርስቲያናዊ መርሆች (Christians principles) ልንመሰርት እንችላለን።ለዚህም ሮሜ ምዕራፍ 7 መነሻ ከሆነን በመርህ ደረጃ ልንጠይቅ የሚገባን ነገር በዚህ ነገር ለእግዚአብሔር ፍሬ ማፍራት እችላለሁ? የሚለው መሆን አለበት። አሁን ይህንን የማደርገው ለእግዚአብሔር ባለኝ ታማኝነትና ፍቅር እንዲሁም በመድሐኒቴ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ብደሙ በዋጀኝና በዓለም ክብሩን እገልጥ ዘንድ ነው? የሚለው ጥያቄ ዋና የክርስቲያን መርሕ ሊሆን ይገባል።

“ለእግዚአብሔር ፍሬ ማፍራት”

ለመነቀስ ስትሄድ ልትጠይቅ የሚገባህ ጥያቄ ከላይ ያለውን ይሁን። ይህንን በማድረግ ለእግዚአብሔር መንፈሳዊ ፍሬ ማፍራቴ ነው? ይህንን የማደርገው እውነተኛውን አምላክ የማያውቁ አህዛብን ለመምሰል ነው የማደርገው? ይህንን በቁም ነገር መጠየቅ ይገባናል። ለምን ይህንን አደርጋለሁ? እግዚአብሔር የማይመስሉ ሕዝቦችን ለመምሰል ነው? ወይስ እኔ በሆነ ሁኔታ ውስጥ በእውነተኛው ወንጌል መነፈስ ሳይሆን በባዕድ መንፈስ እየመራሁ ነው?
ቀጥሎ የምናደርገው ስለ ጌጣጌጥ አዲስ ኪዳን የሚሰጠው ትምህርት ጥቂት መመልከት ይሆናል። ጳሎውስ የሰጣቸው ትምህርቶች ውስጥ የክርስቶስ ተከታይ መሆን ከአለባበስ፣ከመዋብና ጸጉር አሰራር ጋር በተገናኘ በአማኙ ላይ ለውጥ የሚያመጣ እንደሆነ አስባለሁ። አዎ በትክክል አዲስ ኪዳን በግልጽ ይናገራል።እንዲያውም ከብሉይ ኪዳንም ይልቅ ግልጽ ነው። ለምሳሌ እግዚአብሔር እስራኤልን ያስውባታል። ይህም በትንቢተ ሕዝቄል ላይ በግልጽ ተቀምጦልናል “በጌጣጌጥ አንቆጠቆጠሁሽ በእጅሽ አንባር በዐንገትሽም ድሪ አጠለቁሁልሽ………….በወርቅና በብር አጌጥሽ ልብስሽም ያማረ በፍታ ሐርና ወርቅ ዘቦ ነበር …” (ሕዝ 16፡11,13 አመት) ይህ እግዚአብሔር ለሙሺራዋ እስራኤል ምን ያህል እንክብካቤና ውበት እንዳረገላት ያሳያል። ከዚህ በተቃራኒ ደግሞ ሆሴዕ ሁለት ላይ ትዕቢቷንና አለማመኗን ሲገልጽ “ለበኣል አማልክት ዕጣን ሰላጠነባቸው ቀናት እቀጣታለሁ በጌጣ ጌጥና በቀለበቶች ራሷን አስጊጣለች ውሽሞቿንም ተከትላ ሄዳለች እኔን ግን ረስታለች” ይላል እግዚአብሔር። (ሆሴዕ 2፡13) በአንድ ጽሁፍ ውስጥ አዎንታዊ የነበረው ተመሳሳይ ጌጣጌጥ በሌላኛው ላይ አሉታዊ ወይንም የክፋትና የኩራት ምልክት ሆኗል። ስለዚህ ቀድሞውኑ በብሉይ ኪዳይ ማስጠንቀቂያው እግዚአብሔርን መከተል በልብስህና በጸጉርህ በምትሰራው ለውጥ ያመጣል። ስለዚህ እዚህ ላይ በ1ኛ ጢሞቲዮስ ላይ ያለውን ለመረዳት ዕድል እናገኝእለን “እንዲሁም ሴቶች በጨዋነትና ራስን በመግዛት ተገቢ የሆነ ልብስ ይልበሱ እንጂ በሹሩባ ወይም በዕንቁ ወይም ዋጋቸው ውድ በሆኑ ልብሶች አይሽቀርቀሩ።” (1ጢሞ 2፡9 አመት) ወይም ደግሞ “ውበታችሁ በውጫዊ ነገሮች በመሽሞንሞን ይኸውም ሹሩባ በመሠራት በወርቅ በማጌጥና በልብስ አይሁን ነገር ግን ውበታችሁ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ ገርና ጭምት መንፈስ ያለበት ምንጊዜም የማይጠፋ የውስጥ ሰውነት ውበት ይሁን።” (1ጴጥ 3፡3-4 አመት)

ጥያቄው ለሴቶችና ለወንዶች እንድምታው ተመሳሳይ ነው። ወንዶች በሚለብሱት ልብስና በሚጠቀሙት ጌጣጌጥ እና በጸጉር ውስጥ ለማስዋብ በሚያስገቧቸው ነገሮች እና ሁሉንም አይነት መዋቢያ ነገሮች በተመለከተ ለሁሉም ተመሳሳይ መመሪያ አለው። ይህ ሁሉ ለሴቶችና ለወንዶች ሁሉ ነው። ምክንያቱም ለሁለቱም አንድ አይነት መርህ መሆኑ ነው። ይህ ንቅሳት የእነዚያ መልካም ስራዎች መገለጫ ነው? ከልብ በመነጨ፣ እግዚአብሔርን መምሰል ነው? እግዚአብሔር ለእሷ ወይም ለእሱ ባለው ቸርነት የሚረካ የዋህ እና ከተረጋጋ መንፈስ አካል የመነጨ ነው?

ስለዚህ ይህ ሁሉ የእኔ አስተሳሰብ ነው። እኔ እንደማስበው ኃላፊነት የሚሰማው ክርስቲያን ለመነቀስ ሲያስብ ማለት ያለበትን ገልጫለሁ። ይህንን ሁሉ ካልኩ በኋል አንድ ሰው ወደ እኔ መጥቶ መነቀስ እንዳለበት አስቦ ምክሬን ቢጠይቅ እንዳይነቀስ ለማሳመን እሞክራለሁ።

መጋቢ ጆን ፓይፐር (https://www.desiringgod.org/interviews/tattoos-in-biblical-perspective)

@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
778 viewsΒενιαμίν, edited  19:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-14 22:02:32 poem wiz bethel :
poem wiz bethel :
poem wiz bethel :
ዘፍጥረት 32
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁴ ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፤ አንድ ሰውም እስከ ንጋት ድረስ ይታገለው ነበር።
²⁵ እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ የጭኑን ሹልዳ ነካው፤ ያዕቆብም የጭኑ ሹልዳ ሲታገለው ደነዘዘ።
²⁶ እንዲህም አለው፦ ሊነጋ አቀላልቶአልና ልቀቀኝ። እርሱም፦ ካልባረክኸኝ አልለቅቅህም አለው።
²⁷ እንዲህም አለው፦ ስምህ ማን ነው? እርሱም፦ ያዕቆብ ነኝ አለው።
²⁸ አለውም፦ ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባል እንጂ ያዕቆብ አይባል፤ ከእግዚአብሔር ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና።
²⁹ ያዕቆብም፦ ስምህን ንገረኝ ብሎ ጠየቀው። እርሱም፦ ስሜን ለምን ትጠይቃለህ? አለው። በዚያም ስፍራ ባረከው።
³⁰ ያዕቆብም፦ እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው።
                  ጵኒኤል
                 ____
       በጠፋ ጨረቃ በፀና ፅልመት
       ጎህ እስኪቀድ የሞት ሞት
       ኳተነ ሳይታክት በአስፈሪ ውድቅት
       ለአይን በሚይዝ በአውራ ለሊት

       ትልሙ ገብቶኛል ውጥኑ ግልፅ ነው
        የጭኔ ሾልዳ ብርክ እስኪይዘው
         በውርጭ በቁር ሲሞግተኝ ያነጋው
          ትግሉ ፍለጋ ነው የበሰለ ሰው


በዚያ በአውራ ለሊት ሲሞግተው ሲታገለው ያነጋው ፤ ጎህ ሲቀድ ሊባርከው አታላይ ሚለው መታወቅያ እስራኤል በሚለው ሊቀየር ነው። ምን አልባት ትግሉ ህመም  ሊኖረው ፤ከህመሙም የተነሳ ማንከስ ይኖረው ይሆናል።
ለካስ ያስጨነቀኝ ወደፊት ላለው እያዘጋጀን፣አስተዋይ እንድንሆን ደግሞም እያበሰለን ነው።
ተባረኩ
ፀጋ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን  
Bethel Birhanu

                 Join
https://t.me/poemwizbethel
                 share
1.3K viewsΒενιαμίν, 19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-11 09:36:01 በመንፈሳዊ ህይወትህ ለማደግ እነዚህን ሁለት ነገሮች ብቻ እንድታደርግ ላሳስብህ፤
1, ጸልይ
2, ቃሉን ማንበብ ብቻ አይደለም አጥናው
ተባረክ ይሄን ብቻ ነው አድርግ የምልህ።

@nazrawi_tube
438 viewsΒενιαμίν, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-09 08:24:11 የጸሎት ሸክም ዋጋውና ባርኮቱ!

“ወገቤ ሕመም ተሞላ፤ እንደምትወልድ ሴት ምጥ ያዘኝ፤ ከሕመሜ የተነሣ አልሰማም፥ ከድንጋጤም የተነሣ አላይም። ልቤ ተንበደበደ፥ ድንጋጤ አስፈራኝ፥ ተስፋ ያደረግሁትም ድንግዝግዝታ መንቀጥቀጥ ሆነብኝ።….ጌታ ሆይ፥ ቀኑን ሁሉ ዘወትር በማማ ላይ ቆሜአለሁ፥ ሌሊቱንም ሁሉ በመጠበቂያዬ ላይ ተተክያለሁ፥…..።” (ኢሳ.21፥3-4፣ 8)፡፡

በታላላቅ ሪቫይቫሎች ላይ መሪ በመሆኑና በውጤታማ የወንጌል ሥራዎቹ የሚታወቀው ቻርለስ ፊኒ (Charles Finney)፣ ከአንዱ ሪቫይቫል ፍንዳታ በፊት በጸሎት ያሳለፈውን የጸሎት ትግል (agonizing prayer) ሲመሰክር እንዲህ ብሏል፡-

“ነፍሴ በከባድ ጭንቀትና ምጥ ውስጥ ነበረች፡፡ በመሆኑምቀኑን ሙሉ ክፍሌ ውስጥ ስጸይልና ስቃትት ሰነበትሁ፡፡ በነፍሴ ላይ የነበረው የጸሎት ሸክም እንዳደቀቀኝ ነበር የሚሰማኝ፡፡ አብረውኝ ለነበሩት ሠራተኞች ለአንዱም ነገሩን ለመግለጽም ሆነ በቃል ለመተንፈስ አልቻልኩም፡፡ የጸሎት መንፈስ ነበር እላዬ ላይ የነበረው፡፡ ሆኖም ግን እንዲህ ዓይነት የጸሎት መንፈስና ጉብኝት በእዚህ መጠን ኖሮኝ አያውቅም፡፡

አብዝቼ የእግዚአብሔርን ፊት እየፈለግሁ በመጽናት የበለጠ ለሥራው ግሩም ዕቃ እሆን ዘንድ ራሴን አመቻቸሁ፡፡ ጊዜው ረጅም የበጋ ወራት ነበር፡፡ በቃላት ሊነገር በማይችል የጸሎት ትግልና የነፍስ ምጥ (agony in my soul) ውስጥ ለረጅም ጊዜ አሳልፌ፣ በመጨረሻው የጸሎቴ ቀን ያ ያደቀቀኝ የጸሎት ሸክም ከላዬ ላይ ተነሣ፡፡ ወዲያው የእግዚአብሔር መንፈስ የጸለይኩበት ጉዳይ እንደሚከናወን አረጋገጠልኝ፡፡ እረፍት ሊሰማኝ እንደሚገባኝ አመለከተኝ፡፡”

ውጤቱ፡-ከዚያ የጸሎት ትግል በኋላ ተከታታይ መንፈስ አነቃቂና የደረቁ ጉልበቶችን ለጸሎት እንዲታጠፉ የሚያደርጉ ተከታታይ ግሩም ትምህርቶች ለሳምንታት አስተማረ፡፡ ከዚያም እጅግ ከባድ ዓለምን ያናወጠ ሞገድ ያለው ሪቫይቫይል ተነሣ። የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ብዙ ድንቃ ድንቆችን ታደርጋለችና (ያዕ.5፥16)!

“Revival is a renewed conviction of sin and repentance, followed by an intense desire to live in obedience to God. It is giving up one's will to God in deep humility.” Charles Finney

ጌታ ሆይ፣ የጸሎትን መንፈስ ስጠን!!
Dr. Beke
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
266 viewsΒενιαμίν, 05:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-07 21:54:46
ታላቁ ሪቫይቫሊስት ጆን ዌስሊ 40,000 ስብከቶች የሰበከ፣ 233 መጻሐፍት የጻፈ፣ በስሩ 750 ሰባኪዎች እንግሊዝ 350 ሰባኪዎች በአሜሪካ ያሰለጠነና ያሳደገ፣ ሜቶዲስት የሚባል ቤተ ክርስቲያን መሥርቶ እርሱ ስሞት 76,968 በእንግሊዝ፣ 57, 621 በአሜሪካ ነበሩ። ዛሬ በአለም ሁሉ ላይ ከ 50, 000, 000 በላይ አባላት አላቸው።  ከወንድሙ ቻርልሲ ዌሲል ጋር በጥምረት 9,000 እሰከ ዛሬ በስፋት እየተዘመሩ ያሉ ክርስቶስንና መስቀሉን ማዕከል ያደረጉ መዝሙሮች ደርሷል። በሪቫይቫል እሳት የተነካ ሰው እንዲህ ለክርስቶስ ቀልጦ፣ በምሳሌነት ኖሮ በድል አንቀላፍቶ ለትውልድ ሁሉ ከመቃብር በላይ ክርስቶስን እያሳየ ይኖራል።
ጌታ ሆይ በ መንፈስ እሳት ነክተኸን ለትውልድ በረከት አድርገን
Abeni Nigussie

@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
375 viewsΒενιαμίν, 18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 20:57:39 ' ነፍሴ ባንተ
Yishak Sedik
ድንቅ ዝማሬ ሰምታችሁ ተባረኩበት

@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
818 viewsΒενιαμίν, 17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-05 20:57:39
'         ነፍሴ ባንተ
  Yishak Sedik
360p, 30.3MB,
ድንቅ ዝማሬ ሰምታችሁ ተባረኩበት

@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
817 viewsΒενιαμίν, 17:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-03 21:53:31 በመንፈስ ቅዱስ የተነካ ሰው መገለጫው መንቀጥቀጥ ወይ ደግሞ መጮህ ብሎም የተለያዩ እንቅስቃሴ ማሳየት ሳይሆን የተለወጠ ህይወት መኖር ነው።
1.5K viewsΒενιαμίν, 18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 16:48:21 የቀጠለ..
ዘላለማውያን ነን፤ ግን ያለፈውን ሳይሆን የሚመጣውን ብቻ። ተቀድሰናል፤ ፍጹም ቅድስና፥ የራሳችን ውስጣዊ ቅድስና ግን አይደለም። እነዚህ የምንካፈላቸውና የተካፈልናቸው መለኮታውያን ባሕርያቱ ናቸው።

ሰው በመልኩና በምሳሌው ተፈጠረ፤ በኃጢአት ወደቀ፤ ከእግዚአብሔር ተለየ፤ እንደተስፋው ቃል በክርስቶስ ዳነ። ያ ተስፋ በወደቁ ቀን የተነገረው የተስፋ ቃል ነው፤ መቅድመ ወንጌል የተባለው ቃል ነው፤ በአንተና በሴቲቱ መካከል፥ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፥ አንተም ሰኰናውን ትቀጠቅጣለህ። የሚለው በዘፍ. 3፥15 የሚገኘው። ይህ ተስፋ ተፈጸመ? አዎን ተፈጸመ። መቼ? ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤ እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ፥ ከሕግ በታች ያሉትን ይዋጅ ዘንድ። ገላ. 4፥4-5። የተባለው በተፈጸመ ጊዜ። ይህ ቃል፥ ፤እንደ ልጆች እንሆን ዘንድ’ የተባለው ቀደም ሲል ያየነው υἱοθεσία ሁዮቴሲያ የተባለው ቃል ነው። ልጆች እንደረግ ዘንድ። በመልኩና በምሳሌው መፈጠር አምላክ ሆኖ መፈጠር አይደለም። አምላክ አይፈጠርም፤ ከተፈጠረ አምላክ አይደለም። እኛ ደግሞ ተፈጥረናል፤ ስለዚህ አምላክ አይደለንም።

መፈጠር ብቻ አይደለም ተወልደናልም፤ ልጆች ሆነናልም። ልጆች ሆነናል፤ የልጅነትን ሥልጣን ተቀብለናል የሚለውን ቀደም ሲል አይተናል። ያዕ 1፥18 ለፍጥረቱ የበኵራት ዓይነት እንድንሆን በእውነት ቃል አስቦ ወለደን። (እዚህ ወለደን የሚለው ቃል በሌሎች ቦታዎች ወለደን ከሚለው ይለያል፤ አስገኘን ወይም አደረገን ማለትም ነው፤ ቃሉ ἀποκυέω አፖኩዌኦ የሚል ነው። ያዕቆብ ብቻ እዚህ እና ቁ. 15 ላይ ተጠቅሞታል።) መወለድ ብለን ብንወስደውም እንኳ በምን ወለደን? በቃሉ፤ በእውነት ቃል። ከላይ ከቁ. 17 እስከ ታች እስከ ቁጥር 25 ያለውን የተያያዘ ክፍል አንብብ። ስለ አባትነቱ ይናገርና ስለ ልጅነታችን ይናገርና በቃሉ መወለዳችንን ተናግሮ ቃሉን ያብራራዋል። ቃሉ፥ የእውነት ቃል ሰምተነው የተንበረከክንለት ቃል ነው። የተቀበልነውና ዳግም የተወለድንበት መሣሪያ ነው። ቃሉ ደግሞ ሕያውና የሚሠራ ነው። የዳንነው የእውነትን ቃል ሰምተን ነው፤ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤ ኤፌ. 1፥13። የእውነትን ቃል ሰምታችሁ አመናችሁ፤ በእውነት ቃል አስቦ አስገኘን፤ አደረገን፤ ወለደን።

1ጴጥ. 1፥23 ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ። ይህም የሚናገረው ስለተወለድንበት ቃል ነው። በቃሉ ነው ዳግመኛ የተወለድነው። የማይጠፋ ዘር የተባለው ቃሉ ነው። ዳግም የተወለድነው በዚህ የማይጠፋ ዘር፥ በቃሉ አማካይነት ነው። ዳግም ተወልደን ልጆቹ ሆነናል።

ልጅነት ግንኙነት ነው እንጂ መለኮትነት አይደለም። የአካሉ ብልት መሆን ነው። እርሱ ራስ እኛ ብልቶች መሆናችንን ቃሉ ይነግረናል። ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ ሙሽራ ተብላለች። ይህ ጥልቅና ድንቅ ግንኙነት ነው። የምንጋራቸው ባሕርያቱ አሉ። እነዚያን እንካፈላለን፤ ተካፍለናል። በተለይ ጴጥሮስ አጠንክሮ በመልእክቱ አጠንክሮ እየተናገረ ያለው የቅድስና ባሕርይን ነው። የባሕርዩ ተካፍዮች ስለመሆን ሲናገር፥ ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለ ጥፋት እንዲድኑ እንዲያመልጡ፥ እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚያስፈልገው ሁሉ እንደተሰጣቸው ነው። ሁሉ ተሰጥቶናል ነው የሚለው፤ የተሰጠንም እርሱን በማወቅ ነው። እርሱን፥ የጠራንን ማወቅ ቁልፉ ነው።

2ጴጥሮስ ስለ ሐሳውያን በስፋት ያስተማረበት መልእክት ነው። በተለይ ምዕራፍ 2ን ብናይ ይህንን የቅድስና ጉዳይ አብዝቶ፥ አድምቆ ጽፎታል። ሐሰተኞች ነቢያት ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ የዋጃቸውን ጌታ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል። በቀን ሲዘፍኑ እንደ ተድላ ይቆጥሩታል፤ ነውረኞችና ርኵሳን ሆነው ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣ ይዘፍናሉ፤ ምንዝር የሞላባቸው ኃጢአትንም የማይተዉ ዓይኖች አሉአቸው፤ የማይጸኑትን ነፍሳት ያታልላሉ፤ መመኘትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ናቸው። ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ፦ የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል። ይህ የሐሰተኞችን ያልተቀደሰና የሚያረክስ አካሄድ አመልካች ነው። ብዙ ካብራራ በኋላ ጠቅላላውን መልእክት ሲደመድም፥ እንግዲህ እናንተ፥ ወዳጆች ሆይ፥ ይህን አስቀድማችሁ ስለምታውቁ፥ በዓመፀኞቹ ስሕተት ተስባችሁ ከራሳችሁ ጽናት እንዳትወድቁ ተጠንቀቁ፤ ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን። ብሎ ይደመድማል፤ 3፥17-18።

ይህ ጴጥሮስ ያተኮረበት ቅድስና አንዱ የምንካፈለው መለኮታዊ ባሕርይ ነው። እነዚህን፥ ‘መለኮት ነን፤ ትንንሽ እግዚአብሔሮች ነን’ የሚሉትን አሜሪካ ያሉ ሰዎችና (ይህ በሽታ አሜሪካ ነው የተወለደው) እና እነሱን ሰምተውና ኮርጀው፥ ‘እኔና አብ አንድ ነን፤ ከአብ የወጣሁ ነኝ፥ የትልቅ ወንድሜ ዓይነት ነኝ፤ እሱ የሆነውን እኔም ነኝ’ የሚሉትን ሰዎች ስትሰሙ፥ እነዚህን እንደ ቅድስና ያሉትን ተሻጋርያን ባሕርያቱን አይሰብኩም፤ አይነኳቸውም። ስማ! እርሱ የሆነውን ማንም ሌላ አይደለም፤ እርሱ ከዘላለም የነበረ የከበረ ፈጣሪ አምላክ ነው። አንተ ፍጡር ነህ። ሰው ነህ። እኛ ሰዎች ነን። ልጆች የተደረግን ሰዎች ነን። ይህ እኮ ብናውቀው ክብር ነበር። ይህ አነሰን ብለን ያልሆንነውን እና የማንሆነውን ለመሆን ስንዘረጋ የሆንነውን እንዳናጣ እፈራለሁ። ቀንድ አበቅላለሁ ብላ ጆሮዋን አጥታ እንደተመለሰችው አህያ።

እንግዲህ ባሕርይ የሚለው ይህ ቃል ነው። የአብንና የወልድን አንድ ዓይነትነት የሚገልጥ ቃል ከሆነ አብና ወልድ አንድ ወይም አንድ ዓይነት በሆኑበት መልክ ከፍጥረት ማንም ያንን ነኝ ማለት አይችልም። እኔና አባቴ ወይም እኔና ወንድሜ በፍጥረታችን አንድ ነን። ፍጡራን ነንና። እኔና አብ ግን አንድ አይደለንም። እነዚህ፥ ‘እኔና አብ አንድ ዓይነት ነን፤ ከአብ ወጥቼ መጥቻለሁ፤’ የሚሉ ንኮችና ወፈፌዎች ሲናገሩም ሲዘምሩም ሰምተናል። ይህ ስድብ ነው። ከአብ ወጥተህ ከመጣህ ከመምጣትህ በፊት የት ነበርክ? ለመሆኑ ነበርክ? ሰውነታችን፥ ሰው መሆናችን በራሱ ክቡርነት ነው። አምላክ ራሱ እኮ፥ ጌታ ክርስቶስ እኮ ሰውን ሊያድን ሰው የሆነበት ማንነት ነው ሰው። ጌታ እኮ ይህንን ሰውነት ለዘላለም ነው የሆነው። ሰው ከመሆኑ በፊት ሰው አልነበረም። ሰው ከሆነ በኋላ ግን ያንን ሰውነት ላይፍቅ፥ ላይጥል ለዘላለሙ ሊይዘው ሰው ሆነ። ሰውነት፥ ሰው መሆን ክቡር ነው።

እኛ አማልክት አይደለንም። እኛ እግዚአብሔርን ልንመስል ተጠርተናል፤ የልጁን መልክ ልንመስል ተወስነናል፤ የእርሱ ዓይነት ግን አይደለንም። እርሱ የሆነውን ባሕርዩን በመካፈል ነን፤ እርሱ የሆነውን ሁሉ ግን አይደለንም። የእርሱ ዓይነት ከእርሱ ሌላ፥ ከእርሱ በቀር የለም። ሰው የመለኮት ባሕርያትን ሲካፈል መለኮትን ሳይሆን ተጋሪ የሆኑትን የማንነቱን ገጽታዎች ወይም ባሕርያት እንደ ቅድስናው ያሉትን መካፈሉ ነው።

ዘላለም መንግሥቱ
@nazrawi_tube
1.8K viewsΒενιαμίν, edited  13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-02 16:48:21 የመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች ነን? እንዴት? የእግዚአብሔር ልጆችስ ነን? እንዴት?
ክፍል አምስት (#የመጨረሻው)

ቀደም ሲል ያየናቸው ሁለቱም ቃላት οὐσία እና φύσις ባሕርይን ወይም ኹነትን ገላጮች ናቸው። አብ የሆነውን ሁሉ ወልድም ነው፤ ኹነታችው በሁሉ አንድ ነው። እግዚአብሔርን የሚመስል እግዚአብሔር ብቻ ነው። ከፍጥረት ወይም ከፍጡር የሚመስለው ምንም እና ማንም የለም። አብ፥ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ የአንዱ አምላክ አካላት ናቸውና በባሕርይ ወይም ኹነት አንድ ናቸው። ይህ እግዚአብሔርን ሰውን በመልኩና በምሳሌው ከመፍጠሩ ጋር ምንም አይገናኝም። ሰው በአምሳለ እግዚአብሔር መፈጠሩ፥ ሰውን የመለኮት ባሕርይ አያላብሰውም ወይም አያቀዳጀውም። ሰው ሲፈጠር ሰው ብቻ ነው እንጂ መለኮትነት የለውም። ለነገሩ መለኮት መለኮትን አይፈጥርም፤ መለኮት አይፈጠርምና። የሰው አምሳልነት የተሰጠው ሥልጣን አለው እንጂ አምላክነት አይደለም። መንፈሳዊነት እንጂ መንፈስነትም አይደለም። ሥልጣኑ ደግሞ ያኔ ብቻ ሳይሆን ሰው ከወደቀ በኋላም ቀጥሏል።

የባሕርይ ተካፋይነት በሚለው ጴጥሮስ ስለምን ስለምን እንደተናገረ ብናይ፥ እውነት የልጅነታችን ነገር አደናጋሪ ጉዳይ ነው? ከእግዚአብሔር ልጅ ልጅነት ጋርስ ትከሻ የሚያለካካን ነው? ብለን ብንጠይቅ ፈጽሞ አይደለም ነው መልሳችን። በመጀመሪያ 2ጴጥሮስ በጠቅላላው የስሕተት አስተማሪዎችን ለመግለጥና ለመመከት የተጻፈ መልእክት ነው። 2ጴጥሮስ እና የይሁዳ መልእክት በይዘት ተመሳሳይ ናቸው። አሳቾችን እንዲያውቁና እንዲጠነቀቁ በተጻፈው በዚህ መልእክት መንፈሳዊነት፥ ቅድስናና እግዚአብሔርን መምሰል በጥንካሬ ተጽፈዋል።

2ጴጥ. 1፥4 ከፊቱ ካሉት ጥቅሶች ጋር ነው መታየት ያለበት፤ ከ1-4 እንዲህ ይላል፤ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያና ሐዋርያ የሆነ ስምዖን ጴጥሮስ፥ በአምላካችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ ካገኘነው ጋር የተካከለ የክብር እምነትን ላገኙ፤ የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን።

ይህ ቃል ጴጥሮስ በክርስቶስ ጽድቅ በኩል እነርሱ ካገኙት ጋር እኩል የሆነ ክቡር እምነትን ላገኙ ቅዱሳን የጻፈው ነው። የክርስቶስ ጽድቅ እና እምነት ተያይዘዋል። የመለኮቱ ኃይል በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ እንደሰጣቸው ይናገራል። እውቀት፥ ሕይወት፥ እርሱን መምሰል የተሰጡ ነገሮች መሆናቸው ተጽፎአል። ይህ ከሆነ፥ ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጠው ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንዲሆኑ፥ የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን እንደሰጠ ነው የሚናገረው። ተካፋይነት ተሳታፊነት፥ ሱቱፋን መሆን ነው። የግዕዙም፥ ‘ሱቱፋነ ለመለኮተ ዚአሁ’ ይለዋል። በተጻፈበት በግሪኩ κοινωνός ኮይኖኖስ፥ ተሳታፊ፥ ኅብረት አድራጊ፥ ማኅበረተኛ ማለት ነው።

እዚህ መርሳት የሌለብን፥ ተሳታፊ ከሆንክ ያሳተፈህ አለ ማለት ነው። እንድትሳተፍ የፈቀደልህ፥ የጋበዘህ፥ ወደ ግብዣው የጠራህ አለ ማለት ነው። ጴጥሮስ፥ የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ ያለው ይህንን ነው። ይህ ጥሪ የእርሱ በጎነትና ጋባዥነት እንጂ ያንተ/ያንቺ ብቃት አይደለም። እኛ በራሳችን እንኳን ለመጠራት ጥሪውን ለመቀበልም ብቃት አልነበረንም። በበጎነቱ እንደጠራን አንርሳ። አንዳንድ የሐሰት ትምህርት አስተማሪዎች ልክ ራሳቸው ራሳቸውን ጋብዘው ተካፋይ እንደሆኑ ይመስላቸዋል። የመለኮቱ ባሕርይ ተካፋዮች ሳይሆን የራሱ የመለኮቱ ተካፋዮች አድርገው ራሳቸውን ይቆጥራሉ። ይህ አመለካከታቸው ሰይጣን ለራሱ የሰጠውን የተለየ ስፍራ ሰፍሮ ያካፈላቸው ይመስላል። እኛ የመለኮቱ ሳይሆን የመለኮቱ ባሕርይ ተካፋዮች ነን።

በዚህ ጉዳይ ተደጋግሞ የተጠየቅሁት ጥያቄ፥ 'አስቀድሞ የእግዚአብሔር ልጆች ነበርን፤ የራስ የሆነ እንዴት በ adoption ይወሰዳል?' የሚለው ነው። አስቀድሞማ ልጆች አልነበርንም። ቢሆንማ ኖሮ፥ ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ (ዮሐ፣ 1፥12) ለምን ይባላል? መቀበል ወደ ስሌቱ ለምን ይገባል? ቀድሞም የነበረን ከሆነ የልጅነት ሥልጣን ለምን ይሰጠናል? ቢሆንማ ኖሮ፥ በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ (ገላ. 3፥26) በሚለው እምነት ወደ ስሌቱ ለምን ይገባ ነበር? ቢሆንማ ኖሮ፥ በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው። በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። (ኤፌ. 2፥1-3) ለምን ተባልን? አስቀድሞማ ልጆች አልነበርንም። ወደ መለኮቱ ባሕርይ እንለፍ።

የመለኮቱ ባሕርይ ምንድር ነው? ባሕርይ ምን መሆኑን ቀደም ሲል አየን። ባሕርይ ለፍጡር ፍጥረቱ፥ አፈጣጠሩ፥ የተፈጠረበት ማንነቱ ወይም ምንነቱ ነው። ሥሪቱ፥ የተሠራበት ሥራ፥ የተገነባበት ጡብ ነው። እግዚአብሔር የተሠራ ወይም የተፈጠረ ስላልሆነ ፍጥረቱ ወይም ሥሪቱ አንልም። ግን የሆነው ኹነት ነው ባሕርይው። መለኮታዊ ባሕርይ ስንልም የመለኮት ወይም አምላካዊ ማንነቱ ነው። ስለ ሰው ስንናገር ሰውን ሰው ያደረገው ነገር ነው። ይህ የሚታየውንም የማይታየውንም ማንነቱን ይይዛል። ሥጋና ደምነቱ፥ ሕያውነቱ፥ መዋቲነቱ፥ መንፈስና ነፍስ ያለውነቱ፥ ሕሊና፥ አእምሮ፥ ስሜት፥ እነዚህ ሁሉ የሥሪቱ ድርና ማግ ናቸው።

ወደ እግዚአብሔር ስንመጣም እግዚአብሔር የራሱ የብቻው ባሕርያት አሉት። አምላክነት፥ ብቻነት፥ ልዕልና፥ ሁሉን ቻይነት፥ ሁሉን አዋቂነት፥ በሁሉ ቦታ ተገኚነት፥ ሕያውነት፥ ፍጹምነት፥ ዘላለማዊነት። እነዚህ በመለኮት ብቻ እንጂ በሌላ በማንም ዘንድ የማይገኙ ባሕርያት ናቸው። ሰው ይህ የለውም። እኛም ዳግም ስንወለድም ይህንን አልሆንንም። አይደለም ዳግም፥ የለም እንጂ፥ ሣልስም፥ ራብዕም ብንወለድ ይህንን መሆን አንችልም። አምላክ መሆን አንችልም፤ ፍጥረታችን አምላክነት የለበትም። እኛ ሰዎች ነን።

ተጋሪ፥ ተሻጋሪ የሚባሉ፥ የምንካፈላቸው፥ ተካፋይ የምንሆንባቸው ባሕርያት ደግሞ አሉ። ቅድስና፥ አዋቂነት፥ ቻይነት፥ ሕይወት ወይም ሕያውነት፥ ዘላለማዊነት፥ ፍቅር፥ እውነት፥ መልካምነት፥ ወዘተ። እነዚህ ባሕርያቱ ከሆኑ፥ እኛ ደግሞ የመለኮቱ ባሕርይ ተካፋዮች ከሆንን የትኞቹን ነው የተካፈልነው? የመጀመሪያዎቹን አይደለም። ሊሆንም አይችልም። እርግጥ የተወሰኑትን እንጋራለን። እነዚህ እኛም የምንጋራቸው፥ የምንካፈላቸው ተሻጋሪ ወይም ተካፋይ የምንላቸው ናቸው። አዋቂ ነን፤ ግን ሁሉን አዋቂ አይደለንም። በአንድ ቦታ እንገኛለን፤ በሁሉ ቦታ አንገኝም፤ እንኳን በሁሉ ቦታ፥ በሁለት ቦታዎችም አንገኝም። መለኮት አይደለንም፤ የመለኮት ባሕርይን እንጂ መለኮትን አልተጋራንም።
1.4K viewsΒενιαμίν, 13:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ