Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.51K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On YT sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-02-22 17:26:27 Here is another testimony …

በአሜሪካ ምድር በኬንታኪ ግዛት የዊልሞር ከተማ በአስበሪ የቲዮሎጂ ዩኒቨርስቲ ውስጥ (Asbury Theological Seminary ,ky ) የነደደውን የመንፈስ ቅዱስ ጉብኝት ለመካፈል እኔ እና የምወደው ወዳጄና ጓደኛዬ 538mile 8ሰዓት ነድተን ከዚያ ደረስን።

በዚያ ስንደርስ ያየነውን ማመን አቃተን። ከቤተክርስቲያን ሕይወት ይልቅ ይህችን ብልጭልጭ ዓለም ወዶ ሄዷል ብለን የምናማው ወጣት ትውልድ የእግዚአብሔርን ጉብኝት ናፍቆ ከመሰብሰቢያ አዳራሽ ውጪ ስኪሪን ተተክሎ ተበርክኮ ሲፀልይ ፤ አጥንትን በሚሰብር ብርድ መሐል ቆሞ የጌታን ፍቅርና ታላቅነት እየጮኸ ሲዘምር። ከአንተ ውጪ ከክክብርህ ውጪ የምመኘው ነገር የለኝም እያለ ሲያውጅ። ኢየሱስ ስምህ ቅዱስ ነው፤ ስምህ ሕይወት ነው እያለ ከእንባ ጋር ጌታ ሲያወድስ በአይኔ እያየው ውስጤ ጌታን በመናፈቅ ተሞላ።

እግዚአብሔር የለም ተብሎ ሲማር ያደገ ወጣት እግዚአብሔር ሕያው ነው እያለ ሲመሰክር ሲታይ በእውነት ለባዖል ያልሰገዱ ቅሬታዎችን እግዚአብሔር ለራሱ ለይቷል አልኩኝ በልቤ።
ያንን ሁሉ ሠልፍ ተሰልፈን እዳይደርስ የለም ወደ አዳራሽ ውስጥ ለመግባት እድል ደረሰን። ከአዳራሹ ስንዘልቅ የጠበቅነው የቤተክርስቲያን ስነስርዓት በዚያ የለም። መባ የሚሰበስብ ሰው ለጌታ ስራ ስጦታ ስጡ ብሎ በሕዝቡ ጉሮሮ ላይ ቆሞ ጥቅስ እየጠቀሰ የሚያስገድድ ፓስተር ከምድረኩ ዝር አላለም።

ጊታራቸውን በአንገታቸው አንግተው በታላቅ ደስታ አንዴ በለሆሳስ፤ አንዴ በቀጭን ፤ አንዴ በወፍራም ድምፅ ያለ ምንም ግርግር ምንም አሙቁልኝ ሳይፈጥሩ ዜማ ከሆዳቸው የሚያፈልቁትን ዘማሪዎችን ሕዝቡ እየተከተለ ይዘምራል፤ ይጮኻል ፣ ያላቅሳል።

በዚህ ውስጥ ከቀዝቃዛው ወለል ላይ በጉልበታቸው ተበርክከው የጌታን ስም የሚጠሩና የሚያለቅሱ ወጣቶችን ሳይ በእውነት ጌታ በሥራ ላይ ነው አልኩኝ። በዚያ ፓስተሮች ከሕዝቡ ጋር ይፀልያሉ። እኔም በዚያ ካለ አንድ መጋቢ ጋር ተያይዘን አጥብቀን ፀለይን እና በመጨረሻ ስንበራረክ "He said we will meet in heaven" አለኝ ኤልትሪክ እንደያዘው ሰው አንዳች ነገር ውስጤ ነዘረኝ ዓይኖቼ በእንባ ተሞሉ እርሱም እያየሁት ማልቀስ ጀመረ ። እንደገና ተያይዘን ጌታ ሆይ ከበጉ ዙፋን የሚፈሰውን የሕይወት ውሃ ናፍቀናል ስምህን በእኛ ላይ ፃፍ እያልን እደገና ፀለይን ።

አንዳዶች የተነኩበትን የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ከፍተው አይሰብኩም አያብራሩም ማንበብ ብቻ ። ጉባዔው አሜን ይላል ። እንደዚ ቆመው አንብበው ወደ መቀመጫቸው የሚመለሱ ብዙዎች ናቸው ። በዛው ውስጥ ጌታ በቃሉ ብዙዎችን ተናግሯል።

ኢየሱስን ጌትነት አምነው ክርስቶስን የነብሳቸው አዳኝ አድርገው የሚቀበሉም ብዙ ናቸው። ከክፉ ልምምድና ኃጢይት በንሰሃ የሚመለሱም ብዙዎች ናቸው።
ዝማሬው አይቆምም ባለ ጊታሮቹ ያለ አንዳች ድካም ይዘምራሉ እኛ ወዳ አዳራሹ ከ3ሰዓታት ሰልፍ ቡኻላ 4 pm ላይ ዘልቀን ከገባንበት ሰዓት ጀምሮ እስከ 11:30pm ድረስ ለ8 ሰዓታት ያለ መታከት የምስጋና የውዳሴ ፥ የአክብሮት የአድናቆት ዝማሬዎችን አሳርገዋል ። የእሁድ feb19 መርሃ ግብሩ የሚያበቃው 1am ላይ ነው ሰዓታችንን ስናይ መርሃ ግብሩ ሊፈፀም ቢበዛ 2ሰዓታት ቀርተውታል። እኔም ባልጀራዬም በረጅሞ የመገድ ጉዞ በረጅም ሰልፍ ተሰልፈን ስጋችን ስለደከመ የምናርፍበትን ማረፍያ ቤት ፍለጋ ጌታን እያበረክናና እያመሰገንን አዳራሹን ለቀን ወጣን።

በ Cincinnati Ohio በጣም የምወደው ወንድሜ Henok Tadese እና Helen Hailu ከቤታቸው ጣራ በታች በታላቅ እግድነት ተቀበለው ተከባክበው መገቡን። እኛም ከቅዱስ ቃሉ መግበን አፅናንተን ባርከን ፀልየን ተሰናበተን ወጣን። የጂፒኤስ ኮፖሳችን ወደ ቨርጂንያ አስተካክለን ሞልተን እየዘመርን እየፀለይን ስለ ተሀድሶ አስፈላጊነት እየተጫወትን ከቤታችን ደረስን። እኔም የሆነውን እና ያየሁትን ሁሉ እንዲ በፅሑፍ ለታሪክ ጫርኩት።

መጋቢ ተሊላ ፍቃዱ
@nazrawi_tube
231 viewsΒενιαμίν, 14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 23:00:40 የማያልፍ የመሰለ
ዘማሪ ጌዲዮን አስቻለው

በዚህ መዝሙር ተባረኩበት

@nazrawi_tube
143 viewsΒενιαμίν, 20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 22:20:35
የማያልፍ የመሰለ
ዘማሪ ጌዲዮን አስቻለው
360p, 53.5MB,
በዚህ መዝሙር ተባረኩበት

@nazrawi_tube
265 viewsΒενιαμίν, 19:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 13:05:59 ሁለት ዓይነት ዐይኖች (ማቴ. 6፡22-23)

የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ!

በዚህ ክፍል ውስጥ (ቁ. 22–23) ያለውን ሀሰብ ከተገለጸበት አውድ ውጪ መረዳት በጣም አሰቸጋሪ ነው፡፡ ይህ ክፍል የተከበበው ስለባለጠግነት በሚያወሩ ክፍሎች ነው (ከቁ.19-21 እና 24 ጋር ያነጻጽሩ)፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የሚገኙት ὁ ὀφθαλμός . . . ἁπλοῦς ሚገኘው “ጤናማ ዐይን” እና ὁ ὀφθαλμός . . . πονηρὸς “ታማሚ ዐይን” የሚለው ሀረግ በቀጥታ የዐይንን ጤናማነት እና ታማሚነት የሚያመለክት ተደርጎ መወሰድ የለበትም፡፡ ይልቁንም በዚህ ክፍል ውስጥ ምሳሌያዊ ይዘት ያለው ነው፡፡

በጥንት ዘመን ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦች አይሁዳዊያንንም ጨምሮ ዐይን እሳት ወይም ብርሃንን በውስጡ ይዟል የሚል እምነት ነበራቸው፡፡ ሰዎች ማየት የሚያስችላቸው ይህ ብርሃን እንደሆነ ይታመን ነበር፡፡ ለምሳሌ ምሳ. 15፡30 “የዓይን ብርሃን ልብን ደስ ያሰኛል፥ . . .” ይላል፡፡ በዘፍ. 27፡1፣ 48፡10፣ ዘዳ. 34፡7፣ ሰቆ. 5፡7 ላይ ደግሞ ዐይን እንደሚጨልም ይናገራል፡፡ እንዲሁም እግዚአብሔር የሰዎችን ዐይን እንደሚያበራ በዕዝ. 9፡8፤ 1ኛ ሳሙ. 1፡12፣ 1ኛ ሳሙ. 9፡8 ላይም መመልከት ይቻላል፡፡ በዚህ ሳያበቃ በብሉይ ኪዳን መጻሐፍት ውስጥ ዐይን እንደ ፀሐይ ብርሃንን እንደሚያፈልቅ የሚያሳዩ ክፍሎች አሉ (2ኛ ሳሙ. 12፡11፣ መክ. 23፡19 ይመልከቱ)፡፡ እንዲያው በአንዳንድ ክፍሎች ውስጥ ከዐይን የሚወጣው የብርሃን ጨረር በጣም ጠንካራ ከመሆኑ የተነሣ በግልጽ እንደሚታይ የሚናገሩ ክፍሎች አሉ (ዳን. 10፡6፣ ራዕ. 1፡14፣ 2፡18. 19፡12 ይመልከቱ)፡፡

በዚህ ክፍል ውስጥ “ታማሚ ዐይን” ተብሎ የተተረጎመው ὁ ὀφθαλμός . . . πονηρὸς ሀረግ በጥንት መካከለኛው ምስራቅ ባሕል መሠረት “ክፉ ዐይን” ተብሎ የሚታወቀው ነው፡፡ ይህ አገላለጽ በጥንት መካከለኛው ምስራቂ ባሕል ውስጥ ብቻ የሚገኝ ሳይሆን በአይሁዳዊያን ባሕል ውስጥ ጨምር ውስጥም ነበር፡፡ እንዲሁም በአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ውስጥ ማቴ. 20፡15 እና በማር. 7፡22 ላይ ተጠቅሶ እናገኛል፡፡ ትርጉሙም በሌላ ሰው ነገር የሚቀናን፣ የሰውን ነገር የሚፈልግ፣ ስግብግብ ወይም ስግብግብ ዐይን የሚል ትርጉም ነበረው፡፡

በክፍሉ ውስጥ ὁ ὀφθαλμός . . . ἁπλοῦς ሚገኘው “ጤናማ ዐይን” የሚለው አባበል ከὁ ὀφθαλμός . . . πονηρὸς “ታማሚ ዐይን” ጋር ተነጻጽሮ በመቅረቡ ምክንያት ትርጉሙም የታማሚ ዐይን ትርጉም ተቃራኒ ነው፡፡ ማለትም ቃሉ ከልግስና ጋር የተያያዘ መሆኑን መመልከት ይቻላል (ያዕ. 1፡5፣ ሮሜ. 12፡8፤ 911፣ 13 ይመልከቱ)፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቃሉ “ከአንድ ሀሳብ” ጋር የተያያዘ ትርጉም እንዳለው እና ለአንድ ዓላማ መሰጠትን የሚያመለክት መሆኑን ቃሉን ያጠኑ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ በቁ. 24 ላይ የተገለጸው ሀሳብ ይህንን ትርጉም ይበልጥ ያጠናክረዋል፡፡ ስለዚህም “ጤናማ ዐይን” ያላቸው ለጋሾች (6፡22) ሲሆኑ “ታማሚ ዐይን” ያላቸው ደግሞ ለጋሾች አይደሉም/ ስግብግቦች ናቸው (6፡23 እና 20፡15 ይመልከቱ)፡፡ እነዚህ “ታማሚ ዐይኖች” ያላቸው የብልጽግናቸው ሎሌዎች/ ባሮች ናቸው፡፡ እንዲህ ያሉ ሰዎች ሀብታቸውን ለራሳቸው የሚያከማቹት በምድር ላይ ብቻ ነው፡፡

ὁ λύχνος τοῦ σώματός ἐστιν ὁ ὀφθαλμός, “የሰውነት መብራት ዐይን ናት።” ይህንን ሀረግ አስመልክቶ የሥነ-መለኮት ምሁራን የተለያዩ አስተያየቶችን ተሰጥተዋል፡፡ በዋናነት ሁለት አመለካከቶች ጎልተው ወጥተዋል፡፡ የመጀመሪያው አመለካከት “የሰውነት ብርሃን ዐይን ናት” ማለት ሰው ማየት የሚችለው በዐይኑ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህም በቁ. 22ለ - 23ሀ ድረስ የተገለጹት “ጤናማ ዐይን” እና “ታማሚ ዐይን” ምሳሌያዊ አገላለጾች ናቸው፡፡ የደቀ መዛሙሩ “ጤናማ ዐይን”፣ ለጋስ ዐይን የብርሃን ምንጭ ሲሆን “ታማሚ ዐይን”፣ ቀናተኛ ዐይን የጨለማ ምንጭ ነው፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ጤናማ ዐይን ካላቸው በብርሃን የሚመላለሱ ሲለሚሆኑ ትክክለኛውን መንገዳቸው ያውቃሉ፣ የማያወላውሉ፣ ለአንድ ዓላማ የቆሙ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ተጣብቀው የሚኖሩ ይሆናሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ “የሰውነት መብራት ዐይን ናት” ማለት የሰው የውስጥ ማንነቱ መገለጫ መስኮት ዐይን ናት፡፡ አንድ ሰው ከገንዘብ ጋር ያለው ግንኙነት እርሱ በብርሃን ወይስ በጨለማ ውስጥ እንዳለ ያሳያል፡፡ ከእነዚህ ሁለት አመለካከቶች መካከል የመጀመሪያው ክፍሉ ከሚገኝበት አውድ ጋር አብሮ የሚሄድ ይመስላል፡፡ ይኼውም ይህ ክፍል የሚገኘው ኢየሱስ ስለ“ሚበልጥ ጽድቅ” ባስተማረበት አውድ ውስጥ ነው፡፡ ደቀ መዛርቱ ከገንዘብ ይልቅ እግዚአብሔርን የሚወዱ፣ ስግብግቦች ሳይሆን ለጋሶች፣ በሌሎች ሰዎች የማይቀኑ ሊሆን ይገባል፡፡ ይህ ልሆን የሚችለው ስለእግዚአብሔር እና ስለመንግስቱ ትክክለኛ ጤናማ ዕይታ፣ ያልተንሸዋረረ ምልከታ ሲኖራቸው ነው፡፡ በአጠቃላይ ዐይናቸው “ጤናማ” ሲሆን ነው፡፡ ጠናማ ዐይን ካላቸው በብርሃን ይመላለሳሉ፡፡

በቁ. 23 ላይ የሚገኘው εἰ οὖν τὸ φῶς τὸ ἐν σοὶ σκότος ἐστίν , τὸ σκότος πόσον, “ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል።” የሚለው ሀረግ ደቀ መዛሙርቱ ስለሀበት ያላቸው ዕይታ የተበላሸ፣ የታመመ ከሆነ ሁለንተናቸው የታመመ እንደሆነ ያሳያል፡፡

በአጠቃላይ የማቴዎስ ወንጌል ጸሐፊ በዚህ ክፍል ውስጥ ὀφθαλμὸς ἁπλοῦς “ጤናማ ዐይን” እና ὀφθαλμὸς πονηρός “ታማሚ ዐይን” በሚሉ ሀረጋት አማካኝነት ያስተላለፈው መልዕክት እንደ አይሁድ ባሕል መሠረት የመጀመሪያው ለጋስ የሆኑ ሰዎች የሚያመለክት ነው፡፡ ማለትም ሀብትን ሳይሆን እግዚአብሔር ብቻ ጌታቸው ያደረጉ፣ መዝገባቸውን በሰማይ የሚያከማቹ ሰዎችን ያመለክታል፡፡ ሁለተኛው ድግሞ ለጋስ ያልሆኑ፣ ስግብግብ ሰዎችን የሚያመለክት ነው፡፡ እነዚህኛዎቹ ሐብታቸው አምላካቸው የሆነባቸው፣ በምድር ላይ ሀብትን የሚያከማቹ ሰዎችን የሚያመለክት ነው።

Dr. Tekalign Duguma
@nazrawi_tube
613 viewsΒενιαμίν, 10:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 19:56:25 አዳምን ኤደን ገነት ውስጥ ከእግዚአብሔር የሕይወት እስትንፋስ ውጭ ሊያነቃው የሚችለው አቅም አልነበረም: አዳም ኤደን ገነት ውስጥ ፈፅሞ በራሱ መንቃት አይችልም ነበር: የግድ ከእርሱ ቁጥጥርና እውቅና ውጭ የሆነ እስትንፋስ በአፍንጫው ሊገባበት ያስፈልገው ነበር::

ሰውን ማንም ሰው በፖለቲካም ሆነ በሃይማኖት አያነቃውም: ማናችንም ማንንም በሚያማምሩ ስብከቶቻችንና የትወና ብቃታችን ከተኛበት ጥልቅ እንቅልፍና ድንዛዜ ማባነን አንችልም: የእግዚአብሔር እስትንፋስ ግን ይችላል::

ሁልጊዜ እውነተኛ መንቃት እግዚአብሔር ራሱ በሚጭረው እሳት የሚመጣ ነው: በናዳብና በአብድዩ እሳት አይደለም: ማናችንም እሳት አናዋጣም: እሳቱን የመጠበቅ ግዴታ ግን አለብን::

እግዚአብሔር እርሱ በፈለገው ቦታና የታሪክ ፍሰት መሃል የሰው ልጅ ፈጽሞ በፖለቲካና በሃይማኖት ሊያመጣው የማይችለውን መለኮታዊ ጉብኝት ወይም ጣልቃ ገብነት ያመጣል።

ሰው ሁሉ ቀልቡ በሌላ ነገር በተወጠረበትና ርሃብና ጥማቱን ለማስታገስ ውሃ ሊይዙ የማይችሉትን ጉድጓዶች በሚቆፍርበት አንድ የታሪክ አንጓ ላይ የታሪክ ባለቤትና ጠቅላይ የሆነው እግዚአብሔር የሆነ ቦታ በለሆሳስ ነገር ግን ለሁሉ በሚሰማና ሊደበቅ በማይቻል መልኩ ይናገራል፡፡

በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ በፈለገው ሰአትና ቦታ ጣልቃ መግባት የሚችለው እግዚአብሔር ባልጠበቅነው ቦታና መንገድ ራሱን በመግለጥ ባዶ ሆነው ነገር ግን የምንመጻደቅባቸውን ማድጋችንንና ኮሮጆአችንን ያስጥለናል፡ እንዲህም በማድረግ ወደማይነጥፈውና ወደማይደርቀው የራሱ ባህርና ወንዝ ይጋብዘናል፡ እርሱ ራሱ ወንዝ እርሱ ራሱ ባህር ይሆነናል።

ጭው ባለው ምድረ በዳችን ላይ ርጥበት ይለቅበትና ጽጌሬዳ እንዲያበቅል ያደርገዋል።

ከኛ እንዳልሆነና የጽድቃችን ውጤት አለመሆኑን ለማሳየት እርሱ ራሱ ሞት፣ ጭንገፋና፣ ድርቀት በነገሰበት ሰፈራችን ሕይወትን፣ ፍሬአማነትንና፣ ልምላሜን ይልክበታል - ስለ ራሱ እንጂ ስለ እኛ ግን አይደለም።

እንጸልይ፦
አቤቱ ሕይወታችን ከማይነጥፈው ከአንተ ሕይወት ይቀዳልና አትተወን፡ አቤቱ አቁማዳችንና ጉድጏዶቻችን ነጥፈዋልና እንደገና ሙላቸው: ሕይወትህ - የራስህ ሕይወት በመካከላችን ይፍሰስ፡

አቤቱ ስለ እኛ አይደለም ስለ ታላቁ ስምህ እንጂ።

. . . አንተ አይደለህምን?!

ይሉ ዳኑ
@nazrawi_tube
535 viewsΒενιαμίν, 16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 19:41:37 በKentucky ግዛት Lexington ከምትባል ከተማ ሃያ ማይል ያህል ርቃ የምትገኝ ትንሽ የመንደር ከተማ ነች Wilmore. ከተማዋን ከተማ ያደረጋት ግዙፍ የክርስቲያን ዩኒቨርሲቲ Asbury University እና Asbury Theological seminary ነው ማለት ይቻላል። የመማሪያ ሕንጻዎች፣ ላይብሬሪዎች፣ ቢሮዎች፣ መሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የተማሪ ማደሪያዎች፣ ካፍቴሪያዎች፣ የመኪና ማቆሚያዎች ለዚያች የመንደር ከተማ ውበት ሆነዋል። ለቀጣይ ትምህርቴ ያንን ግቢ ከረገጥኩ ገና ዓመት አልሞላኝም። ለጸሎት የሚሰጡት ትኩረት፣ ለግል የጥሞና ጊዜ፣ ለጋራም አምልኮ ያላቸው ትርጉም ከፍተኛ ነው። ትምህርት ቤቱ የዌስሊ አሻራ ያለበት መሆኑንና አንዳንዶቹ መንፈሳዊ ልምምዶች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ከመሆናቸው ባሻገር እንደ ዌስሊ ለጋሲ እንደሚታዩ ሰምቻለሁ።

ባለፈው ሳምንት የተለመደው የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ቻፕል (ሳምንታዊው የማለዳ ጸሎት) በሚደረግበት ወቅት ያልተጠበቀ መለኮታዊ መገኘት በመካከላቸው መከሰቱንና እንግዳ ነገርም ሆኖ እንደነበር በበቀደሙ ልጥፌ ነግሬያችሁ ነበር። የ አሜሪካ ቤተ ክርስቲያን ደክማለች ለዓለማዊነት እጇን ሰጥታለች በሚባልበት፣ ሠይጣን በምድሪቱ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶአል ትውልዱን በልቶታል ተብሎ በሚወራበት፣ ክፋትና ርኩሰት ጣራ ነክቶአል ወንጌልን መስበክ ነውር ሆኗል ግለኝነትና ቁሳዊነት ምድሪቱን ወርሷል፣ ትውልዱም ከሃዲዱ ወጥቶ ወደ ሞት እየተነዳ ነው በሚባልበት በዚህ ጊዜ ተስፋን የሚያጭር ነገር በዩኒቨርሲቲው ቻፕል ውስጥ ተከስቷል።

ዛሬ ዓይኖቼ ያዩትን ከጓደኞቼም ስለሁኔታው የሰማሁትን ልመስክር። “አቤቱ፥ ትመለሳለህ ታድነንማለህ፤ ሕዝቡም በአንተ ደስ ይላቸዋል።” (መዝ. 85:6) ይኼውላችሁ:- እገሌ የሚባል ታዋቂ አገልጋይ ይመጣል ተብሎ አልታወጀም። የማነቃቂያ ኮንፈራንስ አለ ተብሎ ማስታወቂያ አልተለጠፈም፣ አልተለፈፈም። ዕቅድ ተይዞ፣ ስልት ተነድፎ ምንም ዝግጅት አልተደረገም። ጥቂት የአምልኮ መሪዎች ዝማሬያቸውን አቀረቡ… የተለመደው ዓይነት አጭር የቃል መልዕክት ተላለፈ፣ ከመልዕክቱ በኋላ በቃሉ የተወቀሳች ሁ ወደፊት ኑ ጥሪ ቀረበ፣ ጸሎት ተጀመረ ዝማሬው ቀጠለ፣ ንስሓ መግባት ምስክርነት መስጠት ሆነ አልቆም ብሎ ይኼው ዛሬ ድረስ ቀጥሏል። መች እንደሚያቆም የሚያውቅ ሥጋ ለባሽ የለም። እሳቱ እንደ ነደደ ነው።

ይነጋል ይመሻል ያለማቋረጥ ይመለካል፣ ይጸለያል፣ ቃል ይነበባል፣ ንስሓ ይገባል፣ ምስክርነት ይተላለፋል። የሙዚቃ ድምቀት የለም። የመዝሙር ውበት የድምጽ ውህደት ለረጅም ጊዜ ሲያጠኑ የቆዩ መዘምራን የሚዘምሩ ይመስላል። የክብሩ ሙላት አለ። ከተለያዩ ግዛቶች የመጡ ሰዎች በሠልፍ ወደ አዳራሹ ይገባሉ። ዝናብ ብርድ ጨለማ የማይበግረው ረሃብተኛ ሕዝብ በክብሩ ጥማት የተጎዳ ትውልድ በአዳራሾች በራፍ ይንገበገባል። የክብሩ ብርሃን ቤቱን ሞልቶአል። እንደ ወትሮው ፕሮግራም መሪ ተነስቶ “ከዚህ ቀጥሎ ይህና ያ ይሆናል” የሚልበት ዓይነት formal አካሄድ የለም። መንፈስ እንደ መራው አንዱ ተነስቶ የመጣበትን ግዛት ጠቅሶ ከቃሉ አንድ ክፍል አንብቦ ይወርዳል። ሕዝቡ ያንን የቃሉን ክፍል በዘመኑ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደሚሰማ ሰው በመደነቅ ይሰማል። የገንዘብ ማሰባሰብ የሌለበት፣ ታዋቂና ታላላቅ ሰባኪዎችና ዘማሪዎች ያልተጋበዙበት፣ የሙዚቃ ግርግርና የመድረክ ድምቀት የማይስተዋልበት፣ የማስታወቂያ የፖስተርና የካሜራ ግርግር የማይታይበት የተለመደው የፕሮግራም አካሄድ ሥርዓት የማይነበብበት፣ የመንፈሱ የበላይነት ብቻ የክርስቶስ ማዕከላዊነት ብቻ የተጠበቀበት ሪቫይቫል ነው።

አራት ትላልቅ አዳራሾች በሰው የተሞሉ ናቸው። ሁሉም ጋ ጸሎት አለ፣ ንስሓ አለ፣ የቃል ንባብ አለ፣ ምስክርነት አለ፣ ዝማሬ አለ፣ ማልቀስ አለ፣ እንደ ምርኮኛ እጅ ወደ ላይ አንስቶ ወደ መድረክ እየተመሙ መምጣት አለ፣ እጅ መጫን አለ። ወንድሜ ፋሲል አረጋ ቅድም ሲነግረኝ “በነዚህ ቀናት ውስጥ ወደ ጉባኤው ገብቼ ሳላለቅስ የወጣሁበት ጊዜ የለም” ነበር ያለኝ። እኔም ያንን ነገር አይቻለሁ። ቀስ ብዬ አጠገቤ የተቀመጠቺውን ባለቤቴን ሳይ ጉንጯ ርሷል። ወንድሜ ዶ/ር ተድላ ወልደዮሐንስ ከሚያስተምርበት ዩኒቨርሲቲ ሃምሳ የሚያህሉ ወጣቶችን ከሌሎች ፕሮፌሰሮች ጋር ይዞ መጥቶ ነበር። ወጣቶች ውስጥ የተፈጠረው የጌታን ፊት የመፈለግ ልብ ይደንቃል። አሜሪካ ተስፋ አላት ያስብላል። ጌታ እንዲህ አለኝ የሚል ሰው እንደ ተንባይ የመሆን ዝማሚያ የሚታይበት ሰው አላየሁም ግን ቃሉ ሲነበብ ሕዝቡ የሚሰጠው ምላሽ ጌታ ራሱ የሕዝቡን ልብ ወደ ቃሉ መልሶት ካልሆነ በቀር ሊሆን የማይችል ነው።

በየመሃሉ ሽማግሌዎችና አሮጊቶች እንደ አሥር ዓመት ሕጻን ሲፈነጩ ወዲያና ወዲህ በደስታ ሲወዛወዙ ይታያሉ። እጅግ ያስደስታል!! አንድ ቃል በተነበበ ቁጥር ከኋላ እየተምዘገዘጉ መጥተው ከመድረኩ ሥር ዘፍ ብለው የሚወድቁ ወጣቶችን ሳይ ልቤ በሐሴት ይሞላ ነበር። መድረኩን የያዙት በ አብዛኛው ወጣቶቹ ናቸው። መጋቢያን በዕድሜ ጠና ያሉት አስተናጋጅ ናቸው። አንድ ትልቅ ቤት ውስጥ ምግብና ውሃ ሞልቶ ነበር የራበው ወጥቶ በነጻ በልቶ ጠጥቶ ይመለሳል። የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ሁለት ቤተ ክርስቲያን ተደገመች ብያለሁ። በተሳታፊዎች ፊት የሚነበበውን  ፍቅርና ፈገግታ እውነት ለመናገር አሜሪካ ከመጣሁ ጊዜ ጀምሮ አይቼ አላውቅም። መጸለይ ያለበት ነገር ምንድነው? 1. ይኼ ሪቫይቫል በወንጌል ምስክርነትና በክርስቶስ ተልዕኮ ላይ ልዩ ትኩረት የሚሰጥ መሆን እንዲችል ጸሎት ያስፈልጋል። 2. የሰው እጅ ጣልቃ እንዳይገባ ታዋቂ ለመሆን ክብርንና ጥቅምን የሚፈልጉ ሾልኮ ገቦች ሪቫይቫሉን እንዳይጠመዝዙት መጸለይ አስፈለጊ ነው እላለሁ።

Workneh D. Koyera
@nazrawi_tube
443 viewsΒενιαμίν, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 19:41:24
410 viewsΒενιαμίν, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 09:22:17 ቻርለስ ፊኔ
(Divine Encounter)

“ከብዙ የጸሎት ትግል በኋላ አንድ ምሽት ‘ለእግዚአብሔር ነፍሴን በሚገባ ማፍሰስ አለብኝ’ የሚል ሐሳብ በውስጤ ፈሰሰ። የነፍሴ ለጸሎት መነሣቷ እጅግ አስደስቶኝ ነበርና ወደ ቢሮዬ ሄጄ መጸለይ ጀመርሁ።

“ክፍሉ ውስጥ እሳት አልነበረም፣ ብርሃንም አልነበረም። ነገር ግን ክፍሉ በብርሃን እንደ ተሞላ ይሰማኝ ነበር። የክፍሉን በር ለመዝጋት ተነሥቼ እየተመለስሁ ሳለሁ፣ ጌታ ኢየሱስን ፊት ለፊት በአካል ያየሁት መሰለኝ።

“ነገሩ የሚታየኝ በአእምሮዬ ነበር (mental state)። ልክ አንድን ሰው በአካል እንደማየው ነበር ማየቴን እያየሁት የነበረው። እርሱ ምንም አላለኝም። እጅግ አትኩሮ ያየኝ ነበርና ልቤ እጅግ ቀለጠ፤ ከዚያም በእግሩ ሥር ተደፋሁ። ነፍሴን አንድም ሳይቀር በፊቱ አፈሰስሁ፤ እንደ ሕፃን ልጅ ነበር ያለቀስሁት። በእንባ እግሮቹን እያራስኳቸው እንደ ነበር ነው የተሰማኝ።

“ለረጅም ጊዜ ተመስጦ ውስጥ ነበርሁና ነቅቼ ከቢሮ ውጭ አቀጣጥዬው የነበርኩትን እሳት ሳየው፣ የጨመርኩትን ማገዶ ሙሉ በሙሉ በልቶታል። እሳቱ ጋ መቀመጫ ወስጄ ልክ እንደ ተቀመጥሁ፣ በመንፈስ ቅዱስ ተጠመቅሁ። የመንፈስ ቅዱስ እሳት ውስጤን አጋየው።

“ልክ እንደሚነዝር ኤሌክትሪክ ነበር መንፈስ ቅዱስ ወደ ውስጤ ዘልቆ የገባው። የገጠመኝ ሰማያዊ ጉብኝት ልቤን በፍቅር አቀለጠው። በውስጤ የፈሰሰውን ፍቅር፣ ደስታና ሰላም ለመግለጽ ቃላት ያጥረኛል። የጌታ ፍቅር ልቤን በኀይል አሟምቶት ነበርና ጮክ ብዬ አለቀስሁ።

“መለኮታዊ ሞገዱ ደጋግሞ ደጋግሞ በላዬ ላይ ይዥጎደጎድ ስለ ነበርና ‘ይህ ሞገድ ከቀጠለ ወዮልኝ እሞታለሁ’ አልሁ። ነገር ግን ምንም የሞት ፍርሃት አልነበረኝም። በዚህ ሁኔታ ለምን ያህል ጊዜ እንደ ቆየሁ አላስታውስም።

“የነበርሁበት ክፍል ውስጥ የመዘምራን ቡድናችን መሪ የሆነ ባልደረባዬ ሲመጣ፣ በኀይል እየጮኽኩና ስቅስቅ ብዬ እያነባሁ ነበር ያገኘኝ። እርሱም ‘አቶ ፊኔ አሞሃል ወይ?’ አለኝ። ነገር ግን ልመልስለት አልቻልሁም። እርሱም ከቀድሞው ድምፁን ጨመር አድርጐ ‘ሕመም ይሰማሃል ወይ?’ ብሎ ጠየቀኝ። እኔም እንደ ምንም ኀይሌን አሰባስቤ ‘አይደለም እጅግ ደስተኛ ነኝ። ነገር ግን መኖር አልችልም’ አልኩት።”

@nazrawi_tube
662 viewsΒενιαμίν, 06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 09:21:59
ቻርለስ ፊኔ
(Divine Encounter)
607 viewsΒενιαμίν, edited  06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 20:56:06 ሪቫይቫል ምንድን ነው? ምንስ አይደለም?
ከተስፋዬ ሮበሌ (ከ4 ዓመታት በፊት የተለጠፈ)

(1) "የሪቫይቫል" ቀዳማይ ግብ፣ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት እንጂ፣ ልሳንና ተኣምር አይደለም! የጸጋ ስጦታዎችም ቀዳማይ ግብ፣ እውነተኛ የሕይወት ተሐድሶና የሰዎች ድነት (ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስን እንደ ግል አዳኛቸውና ጌታቸው መቀበላቸው) ነው!

(2) "ሪቫይቫል" ነገን እውን ይሆናል ብለን የምንጠብቀው ክሥተት ሳይሆን፣ ዛሬን የምንተገብረውና የምንኖረው ክርስቲያናዊ ሕይወት ነው! እውነተኛ የሕይወት ለውጥና የነፍሳት ድነት ባለበት ቦታ ሁሉ "ሪቫይቫል" አለ:: ይህ በሌለበትም ቦታ "ሪቫይቫል" የለም!

(3) ዛሬ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በልዩ "በሪቫይቫል" ውስጥ ነች የሚሉ ሰዎችን አስተሳሰብ በጭራሽ አልጋራም:: ምክንያቴም አንደኛ እነርሱ "ሪቫይቫል" የሚሉትን ሁካታ መጽሐፍ ቅዱስ "ሪቫይቫል" ስለማይለው:: ሁለተኛ ከየትኛውም የታሪክ ጊዜ ይልቅ የክርስቶስ ወንጌል የተነቀፈበት ይህ ወቅት "ዘመነ ሪቫይቫል" ሊሆን አይችልም (በእኔ የድነት ዘመን ማለቴ ነው):: ሦስተኛ በርካታ ሰዎች ወደ ትክክል ወዳልሆነ ሃይማኖትና ወደተሳሳተ እምነት እየጎረፉ ያሉበት ወቅት በመሆኑ::

(4) "ሪቫይቫል" የመጻኢ ዘመን ክሥተት ነው ብለው ያስተማሩ ሰዎች ጎዳና ስተው ሕዝብን አስተው የተገኙት "ሪቫይቫል" የመጻኢ ዘመን ክሥተት ነው በሚለው ጠማማ አስተሳሰባቸው ምክንያት ነው!

(5) ሐዲስ ኪዳን "በመጨረሻው ዘመን" መንፈሳዊ ተሐድሶ ይሆናል ሲለን፣ ዘመነ ሐዲስን በጥቅሉ የሚጠቅስ እንደ ሆነ ልብ ይሏል! ስለዚህ ነገ "ሪቫይቫል" ይሆናል የሚለው አስተሳሰብ ለአውሬውና ለአባይ ነባዮቹ እየዳረገን እንደሚገኝ ልብ ይሏል! (according to Historical Premillennialism OR Dispensationalism Theology ከሺህ ዓመቱ በፊት ያለው መጻኢ ዘመን ብሩህ አይደለም)::

(6) እግዚአብሔር አምላክ ለኢትዮጵያውያን ብቻ አመጣለሁ ያለው "ሪቫይቫል" የለም! አምላክ ሕዝቦችን ሁሉ የሚያውቀው በክርስቶስ ኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ አማካይነት ብቻ ነው! በዚህ አግባብ ኢትዮጵያውያንና ኬኒያውያን ወይም የግብፅ ክርስቲያኖች አንዳችም ልዩነት የላቸውም:: ኢትዮጵያ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ተደጋግማ መጠቀሷ ጥንታዊት አገር መሆኗን እንጂ በክርስቶስ ቤዞታዊ ሥራ ውስጥ ልዩ ቦታ እንዳላት ሊያሳይ አይችልም! "ለማርያም በዐሥራት የተሰጠች ነች" ወይም "ኢትዮጵያውያን ልዩና ምርጥ ሕዝቦች ናቸው" የሚለው አስተስሰብ መንፈሳዊ ዘረኝነት ነው (መንፈሳዊ "ወያኔነት" ነው)! በቅዱሳት መጻሕፍት ኢትዮጵያ የሚለው ስም ከተጠቀሰው በላይ ባቢሎን፣ ግብፅ፣ ሮም ፣ ግሪክ...የሚሉ ስሞች በስም ተጠቅሰዋል:: በብዛት መጠቀሳቸው በክርስቶስ ድነታዊ ውጀት ውስጥ ልዩ ጥቅም ወይም ቦታ እንዳላቸው በጭራሽ አያሳይም! ያለመጠቀስም ከድነት አያጎድልም—ለምሳሌ አገረ አሜሪካንን ይመለከቷል:: አልተጠቀሰችም ግን የጠንካራ ሚስዮናውያን እናት ምድር መሆኗን ማን ይክዳል? (ለበለጠ ማብራሪያ "አባይ ነባይ" መጽሐፍን ይመለከቷል)::

(7) ሁሌም ተኣምራት ሰዎችን ወደ መንፈሳዊ ለውጥም ሆነ ብስለት ያደርሳሉ ብሎ ማሰብ ትክክል አይደለም:: ተኣምራት እውን ስለሆነ ብቻ ነፍሳት ዳኑ የዳኑትም ታነጹ ማለት አይቻልም:: ለምሳሌ ከግብፅ የወጣው የእስራኤል ሕዝብ በተኣምር ባሕር ሲከፈል ማየቱና ሰማያዊ መና መብላቱ የጥጃ ጣዖት ሠርቶ ከግብፅ ባርነት ዐርነት ያወጣኝ ይህ ጥጃ ነው ከማለት አላቀበውም:: "ከሙታን መኻል አንዱ ሄዶ ክርስቶስን ቢሰብክላቸው ቤተሰቦቼ ያምኑ ነበር" ያለውን ሰው፣ ስብከተ ወንጌልን የማያምን ሰው፣ ተኣምራትን ሊያምን እንደማይችል ወንጌል በግልጽ ነግሮታል:: ስለዚህ ተኣምራት ባለበት ቦታ ሁሉ የነፍሳት ድነትና የሕይወት ለውጥ አለ የሚለው አስተሳሰብ ትክክል አይደለም::

(8) "ሪቫይቫል" በአምላክ በጎ ፈቃድና እርሱን ከልብ በመሻት እውን የሚሆን እንጂ፣ በሰዎች ክህሎትና በግርግር የሚፈጠር አይደለም! ያልሆነን ሆነ ብሎ ማውራት የሐሰት ምስክሮች እንጂ የወጌል ዐርበኞች አያደርገንም::

(9) "ሪቫይቫል" በእግዚአብሐር መንፈስ ረዳኢነት እውን ክሥተት በመሆኑ ምክንያት፣ በመንፈስ ቅዱስ ነጂነት (አፊዎትነት) እውን የሆኑትን የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት የሚያስወድደን እንጂ፣ እርሱን ጥለን ነባዮችን እንድናሳድድ የሚያደርገን አይደለም! እንግዲያው ቅዱሳት መጻሕፍትን ማጥናትና ማስጠናት "የአእምሮ ሰው" የሚያሰኝ "ሪቫይቫል" ጤናማ ሊሆን በጭራሽ አይችልም:: በውኑ አምላክ ያሰበልንን ነባዮች ያስቀሩብናልን? ያላሰበልንንስ እጅ ጠምዝዘው ሊሰጡን ይችላሉ? እንግዲያው መንቀዥቀዡ ከምን የመነጨ ይሆን?

በአጭሩ እነዚህን ዘጠኝ ነጥቦች ያለማወቅና በዚህ እንጻር ያለመኖር:- (1) በአባይ ነባዮች ይስበላል! (2) ተኣምራት ናፋቂ ያደርጋል (3) ቅዱሳት መጻሕፍትን እያነበቡና እይተነተኑ ከመኖር ይልቅ በአባይ ነባዮች የውሸት ትንቢትና መገለጥ እንድንዳረግ ያደርጋል (4) መንፈሳዊ "ወያኔነት" (ዘረኝነት) እንዲጣባን ዕድል ይሰጣል:: ወዘተና ወዘተ

ይህ እኔ ስለ "ሪቫይቫል" ያለኝ አንቀጸ ሃይማኖት ነው! ይህን ሐቅ እንደ አሸንክታብ ዐንገቴ ላይ አንጠልጥዬው እንደምኖር፣ እንደምሰብከው፣ እንደማስተምረው... ታቅፌው እንደምሞት ዓለም ይወቅልኝ!

ሠናይ ውእቱ
158 viewsΒενιαμίν, 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ