Get Mystery Box with random crypto!

ናዝራዊ Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ nazrawi_tube — ናዝራዊ Tube
የሰርጥ አድራሻ: @nazrawi_tube
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.51K
የሰርጥ መግለጫ

ናዝራዊ: ማለት የተቀደሰ ወይም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው።
@biblicalmarriage
On YT sub☞ https://bit.ly/2ZCsqFN
Inbox👉 @Nyouth_bot
--
" እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ።
-- ኤር 6:16

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-05-20 12:03:49 የቱንም ያህል ብንወራጭ መቼ እንደሆነ ነው የማናውቀው እንጂ የሆነ ቀን የሆነ ቦታ በሥጋ እንደ ተወለድናት ከሥጋ እንለያታለን፡ ቤንጃሚን ፍራንክሊን ተናገሩት እንደሚባለው ከሆነ በዚህ ዓለም ውስጥ ከሞትና ከግብር በስተቀር ምንም ነገር እርግጠኛ አይደለም፡ የግብሩን እርግጠኞች ባንሆንም ከቀን ወደ ቀን ሞት በሰውነታችን እየጨመረ ስለሚሄድ የሥጋን ሞት ልንክደው አንችልም።

በዚህ ዓለም ውስጥ በመወለድ “እልልልል….” በመሞት ደግሞ “ወዮ…” ማለት ብርቅ አይደለም፡ ነገር ግን ትልቁ ጉዳይ መወለድና መሞቱ ሳይሆን በመወለድና በመሞት መካከል የምንሆነው ነገር ወይም የምንኖረው ኑሮ ነው።

እነዚህ ከታች ምስላቸው የሚታየው ሰዎች ይብዛም ይነስም እንደ ተቀበሉት ፀጋና እንደ አቅማቸው፣ እንዲሁም በገባቸው መጠን የወንጌልን ስራ ወይም የእግዚአብሔርን ሐሳብ አገልግለው ባለፉት 15 ዓመታቶች ውስጥ በሥጋ ከተለዩን ወገኖች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው።

መጽሃፍ የሚለውን የምናምን ከሆነ እያንዳንዳችን በሥጋ ለሰራነው ብድራት እንቀበል ዘንድ በክርስቶስ ፊት እንቀርባለን፡ ሰው እንደ ጳውሎስ፣ ወይም እንደ ጴጥሮስ፣ ወይም እንደ አጵሎስ ሊሮጥ ይችላል፤ መጨራሻ ላይ ግን ሁሉ ብድራቱን ያገኛል፡ ብድራቱ ታዲያ እዚህ ሰዎች በሰፈሩን ልክ ወይም በሚሰፍሩበት መስፈሪያ ሳይሆን ጻድቅ ፈራጅ በሚሰፍርበት መስፈሪያ ነው፡ በሥጋ ለተለዩን ብናዝንም ለራሳችን “ማዘንን” ግን አንርሳ፤ ገና ሮጠን አልጨርስንምና፡ ዛሬ ወይም ነገ ልንጠራ እንችላለን: እስተዛ ግን እድል አለን: ምን ይታወቃል፣ ነገ ሲነጋ ፌስ ቡክ ላይ አልፅፍ ይሆናል::

ጉዳዩ የሥጋ ቆይታችን ማጠሩና መርዘሙ ሣይሆን በአጭሩም ቢሆን በረዥሙ ከእሣት የሚያልፍ ስንቅ ይዞ መሄዱ ላይ ነው፡ እዚያ ያለው ቋታችን የሚሞላው እዚህ በጣልነው ልክ ነው::

ማርቲን ሉተር እንዲህ ይሉ ነበር:-

"ካላንደሬ ላይ ሁለት ቀኖች ብቻ ናቸው ያሉት - this day and that day”

እውነታቸውን ነው!
ነገር ግን that dayአችን በ this dayአችን ይወሰናል::

ትሞታለህ ትሞቻለሽ እሞታለሁ እንሞታለን

ዕብራውያን 12 ፡ 1 - 2

እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።

ከyilu danu fb የተወሰደ
@nazrawi_tube
2.1K viewsΒενιαμίν, 09:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 08:31:45 ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤

¹²-¹³ ይህም ጸጋኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደንየተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል


¹⁴ መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።

@nazrawi_tube
1.8K viewsΒενιαμίν, 05:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-15 10:15:38 https://telegra.ph/የማርቆስ-ወንጌል-አራት-ነጥቦች-05-14
2.4K viewsΒενιαμίν, 07:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-13 20:16:02
ቁልፉን ትቶ ዳቦውን?!
_____________
በምስሉ የምንመለከተው ሰው በታሰረበት ክፍል ሆኖ በፊቱ ሁለት አማራጮች ቀርበውለታል፤ አንድ ዳቦና የእስር ቤቱ በር መክፈቻ ቁልፍ። ሆኖም የእርሱ ምርጫ ለዘላቂው ከእስር ቤቱ የሚያወጣውን የበሩን ቁልፍ ሳይሆን ወቅታዊ ረሃቡን የሚያስታግስበትን ቁራሽ ዳቦ ማግኘት ሆኗል። ግን ለምን?

የብዙዎቻችንስ የምርጫ ዝንፈት ይሄው አይደለምን?! ለወቃታዊ ችግሮቻችን ፈጣን ማስታገሻ የሚሰጥ የሚመስለንን ቁራሽ "ዳቦ" ፍለጋ እንውተረተራለን እንጂ ዘላቂ መፍትሄ የሚቸረውን ቁልፍ (የእውቀት መክፈቻ) ለማግኘት እምብዛም እኮ አንተጋም። ከግብፅ የዘመናት እስራት ነፃ የወጡትን የእስራኤልን ልጆች ልብ ይሏል... ከምድረ በዳ ነፃነታቸው ይልቅ የግብፅ ሽንኩርት(የእስር ቤቱ ጥጋብ) ሲናፍቃቸው... ዘይገርም አሉ! ... ግን ለምን?

"ነፃነት" የሕይወት ወሳኝ እቅምና ውበት መሆኑን አለማወቅ አይመስላችሁም?

ስለዚህ ከውስጣዊና ውጫዊ እስራት ለዘላቂው ነፃ ከማያወጣ "የቁራሽ ዳቦ" ማስታገሻ ፍለጋ ፥ ነፍሳችንን አስገዝተንም ቢሆን እስከ ወዲያኛው አርነት ወደሚሰጠን የእውነት እውቀት "ቁልፍ" ፍለጋ ነፍሳችንን እናተጋ ዘንድ ይሁንልን እያልኩ ላብቃ።

#ነፃነት የሕይወት ወሳኝ አቅምና ውበት ነው!
---
Pastor abby
@nazrawi_tube
2.6K viewsΒενιαμίν, 17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-12 22:07:59 በእግዚአብሔር ተስፋ አይቆረጥም!

እግዚአብሔር አዲስ ጅማሬንና አዲስ ዕድልን በመስጠት የታወቀ ነው፡፡ እግዚአብሔር የእንደ ገና አምላክ ነው፡፡ የሐዋርያው ጳውሎስን ሕይወት ስናይ፣ ከዚያ ከሞተ ሃይማኖታዊ የጥፋት ወጥመድ (ያለ ኢየሱስ) አውጥቶ፣ ታሪክ እንዲሠራ አድርጐታል፡፡ ሁለት ሦስተኛው የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በእርሱ የተጻፉ አይደሉምን? ሐዋርያው ጴጥሮስም ከዚያ ውድቀትና መሪር ኀዘን በኋላ፣ በባለ ሃምሳ ቀን አስደናቂ ሰባኪ ሆኖ አልተገለጠምን? ለምን? እግዚአብሔር ለሰዎች እንደ ገና አዲስ ዕድል መስጠት ያውቅበታልና ነው፡፡

የመጽሐፍ ቅዱሷን ሩት ያየን እንደሁ፣ ባሏ የሞተባት፣ መሄጃ የሌላት ሴት ነበረች፡፡ ሕይወቷም ተስፋ የማይጣልበት እጅግ ባዶ ነበር፡፡ ነገር ግን ከምትገምተውና ከምታስበው በላይ የሆነ አዲስ ሕይወትን አግኝታለች፡፡ ለምን?

አምላካችን እግዚአብሔር "በዚህ ብቻ ነው የሚሠራው" ስለዚህም "አለቀ" ብሎ መደምደም አይቻልም፤ እጅግ ብዙ መንገዶች አሉትና፡፡ በፍጹም ያልጠበቅነውን መስመር ዘርግቶ፣ ሕይወታችንን እንደ ገና ማስዋብ ይችልበታል፡፡

በግሌ ከዚህ በኋላ አበቃልኝ ያልኩባቸው እጅግ በርከት ያሉ ጊዜያት እንደ ነበሩ አልደብቃችሁም፡፡፡ የተዘጉ በሮችን አይቼ “በቃ፣ ከዚህ በኋላ የእኔ ነገር አበቃ” ብዬ አውቃለሁ፡፡ ያኔ በአእምሮዬ እንደ ሰው መውጫ አማራጮችን ፈታትሼ፣ ዝርክርኬ የወጣባቸው ጊዜያት ነበሩ፡፡ ነገር ግን ወደ ልቤ ተመልሼ፣ የእኔ መፍትሔ ከላይ ብቻ እንደ ሆነ ገብቶኝ፣ በፊቱ በቂ ጊዜ ወስጄ በማሳለፍ፣ በማልቀስ፣ በመቃተትና በመጮኽ ለረጅም ጊዜ በማሳለፍ የሚደንቁ ትንሣዔዎችን አይቼአለሁ፡፡

ወገኖቼ ሕይወት ባዶ ሆኖባችሁ፣ ልትሄዱባቸው ያሰባችሁባቸው መንገዶች ተዘጋግተውባችሁና ሕይወት አስጠልቷችሁ ካላችሁ፣ የምነግራችሁ አንድ ነገር ብቻ ነው፡፡ ምንም ሳታወላውሉ፣ ምንም ሳታመነቱ፣ በመሐሪው አምላክ ፊት ውደቁ፡፡ እናም "የተበጠሱ ጅማቶች እንደ ገና ሙዚቃ የሚያሰማ ድምፅ ይሰጣሉ (Chords that were broken will vibrate once more) !!

መልካም ጊዜ ተባረኩ!
Dr. Bekele brihanu
@nazrawi_tube
2.3K viewsΒενιαμίν, edited  19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 11:20:18
የእግዚአብሔር ዐብሮነት ከሁሉ ይበልጣል - ጳውሎስ ፈቃዱ
11.05.2023
07:17

@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
494 viewsΒενιαμίν, 08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 11:55:25 ወንጌል ምንድን ነው? (ከቴብል ወግ ፌስቡክ ፔጅ የተወሰደ)
በዶ/ርበርክ ፓርሰንስ

የአሥራ ዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን የፕሪንስተን የሥነ መለኰት ሊቁ ቻርለስ ኾጅ፣ "ወንጌል ትናንሽ ልጆች ሊረዱት የሚችሉት በጣም ቀላል ሲሆን፤ በአንጻሩ ደግሞ ምጡቅ የሆኑት የሥነ መለኰት ጠቢባን በውስጡ ያለውን ሀብት ጨርሰው ሊያውቁት የማይችሉት ነገር ነው" ብሏል። ወንጌል አምነናል ብለን ለምንላቸው ነገሮች ሁሉ ሙሉ በሙሉ መሠረታዊ ነገር ከመሆኑ በተጨማሪ፣ የክርስቲያንነታችን ምንነት እና ማንነት ማዕከላዊ እምብርት ነው። ነገር ግን፣ ብዙ አማኝ ክርስቲያኖች "ወንጌል ምንድን ነው?" ለሚለው ቀላል ጥያቄ መልስ ለመስጠት ይቸገራሉ። በማስተማር ላይ ሆኜ ተማሪዎቼ ወንጌል ምን እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ትክክለኛ ማብራሪያ መስጠት ኣለመቻላቸው በጣም ይገርመኛል። ከዚህም ባለፈ፣ ወንጌል ምን እንዳልሆነም መግለጽ ይቸግራቸዋል። ወንጌል ምን እንደሆነ ካላወቅን፣ እኛ ከሰዎች ሁሉ ይልቅ በጣም የምናሳዝን ምስኪኖች ነን። ምክንያቱም ወንጌልን የማስረዳት አቅም ከሌለን፣ በምስክርነት ወንጌሉን ሰብከን ምናልባት ኃጢአተኞች ደኅንነትን ያገኙ ዘንድ ማድረግ ኣንችልም ማለት ነው። እንዳውም እኛው እራሳችንም እንኳን ደኅንነትን ላናገኝ እንችል ይሆናል።

በጊዜያችን ለቊጥር የሚታክቱ ሐሰተኛ ወንጌሎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥም ሆነ ከቤተ ክርስቲያን ውጭ አሉ። በክርስቲያን ቴሌቪዥን ፕሮግራሞችና በክርስቲያን የመጻሕፍት መደብር መደርደሪያዎች ላይ ያሉት ብዙዎቹ ነገሮች ወንጌልን ሙሉ በሙሉ የሚያጨልሙ ናቸው። በዚህም፣ እነዚህን ነገሮች ጭራሽ ወንጌል ያልሆኑ ልዩ ወንጌል ያደርጋቸዋል። ሰይጣን ወንጌልን ሊያጠፋው ስለማይችል፣ ጄሲ ራየል እንደጻፈው "በመደመር፥ በመቀነስ ወይም በመተካት ብዙ ጊዜ ጠቃሚነቱን ዋጋ ቢስ ያደርገዋል።" አንድ ሰባኪ ስለ ኢየሱስ፣ ስለ መስቀሉ እና ስለ መንግሥተ ሰማያት ስለተናገረ ብቻ ወንጌልን እየሰበከ ነው ማለት እንዳልሆነ ማስተዋል በጣም አስፈላጊ ነው። እንደዚሁም ሁሉ፣ በየጥጋ ጥጉ ቤተ ክርስቲያን ስላየንም በየጥጋ ጥጉ ወንጌሉ እየተሰበከ ነው ማለትም ኣይደለም።

በመሠረቱ ወንጌል ዜና ነው። የምሥራች፣ መልካም ዜና ነው—የምስራቹም ሥሉሱ አምላካችን በጸጋ ለሕዝቡ ስለ አከናወነው ሥራ ነው። እርሱም፦ አብ ወልድን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ሥጋ የለበሰው አምላክ መላኩ፤ እርሱም በፍጹምነት መኖሩ፣ ሕግን መፈጸሙና መሥዋዕት ሆኖ መሞቱ፤ ለኃጢያታችን ስርየትን ማድረጉ፣ በዘላለማዊ ሞት እንዳንጠፋ በላያችን የነበረውን የእግዚአብሔርን ቊጣ እንዲከልከል ማድረጉ፣ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ከሞት መነሣቱ ነው። ወንጌል እግዚአብሔር ኃጢያተኞችን እንደሚያድን አመልካች የድል አዋጅ ነው። ምንም እንኳን የኢየሱስ ጥሪ “መስቀሉን ተሸክመህ ተከተለኝ”፣ “ንስሐ ግባ እንዲሁም እመን”፣ “እራስህን ካድ”፣ “ትእዛዛቴን ጠብቁ” የሚሉት የወንጌሉን አዋጅ በቀጥታ የሚከተሉ ትእዛዛት ቢሆኑም፤ እነዚህ ግን በእራሳቸው ኢየሱስ ያከናወነው የምሥራች ኣይደሉም። ወንጌል እግዚአብሔር እኛ ጋር ለመድረስ እንዴት ሁሉን ነገር ለበጎ እንዳደረገው የሚያሳይ ታላቅና ክቡር መልእክት እንጂ—እግዚአብሔር ጋር ለመድረስ በብርታት እንድንጥር ጥሪን የሚያቀርብ ኣይደለም። ወንጌል ጥሩ ዜና የምሥራች ነው እንጂ ጥሩ ምክር ኣይደለም። ጄ ግራሻም ማከን እንዲህ ብሎ ጽፏል፦ "ከሁሉ በፊት የሚያስፈልገኝ ነገር ወንጌሉ እንጂ ልባዊ ምክር ኣይደለም። እግዚአብሔር እንዴት እንዳዳነኝ እንዳውቅ እንጂ፣ ራሴን እንዴት እንደማድን መመሪያን ማግኘቴ ኣይደለም። አንዳች የምስራች አለህን? የምጠይቅህም ጥያቄ ያንን ነው።”

@nazrawi_tube
1.6K viewsΒενιαμίν, 08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 22:22:44
በእምነት ይኖራል ጻዲቅ
ፓስተር ታምራት ኃይሌ

@nazrawi_tube
484 viewsΒενιαμίν, 19:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 16:45:02 10 ለማስረጃነት የበቁ የትንሣኤው ተጨባጭ መረጃዎች!

ከ2 ሚሊንየም በፊት ኢየሱስ በአይሁድ ባሕል በታወቀ ሥፍራ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ እያየ በአደባባ ራቁቱን ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ከተቀበረም በኋላ፣ "ይነሣል" የሚል ወሬ ቤተመንግሥትን ስላሰጋ ትልቅ ድንጋይ በመቃብሩ ላይ ተደረገ፤ በማህተም ታትሞ ጥብቅ ቁጥጥርና ጥበቃ ይደረግ ዘንድ በመንግሥት መታዘዙን በወንጌላት ተጽፎአል፡፡ በቃሉ " እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አጥፍቶ አስነሳው፤ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለም"ና (ሐዋ. 2፡ 24) እንደተባለው የትንሣኤ በኩርና ጀግናው ኢየሱስ በሦስተኛው ቀን ከሞት ተነሣ፡፡ አሜን፡፡

የትንሣው ተጨባጭ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች

1. የተሰበረው የሮም መንግሥት ማህተም፡፡

2. እስከ ዛሬ አፉን ከፍቶ በየዓመቱ በሚሊዮኖች እየተጎበኘ ለእስራኤል መንግሥት ዋና የገብ ምንጭ እየሆነ ያለ ባዶ መቃብር/ ዛሬ ኢየሩሳሌም ሄዶ ማየት ይቻላል/፡፡ በዓለም ላይ ከተነሡ የሃይማኖት መሪዎች አንዱም የተነሣ የለም፡፡ መቃብሮቻቸው በተለያየ አገሮች እንዳሉ ናቸው፡፡

3. በሕግ የተቀመጠው ድንጋይ በመለኮት ኃይል መከባለል፡፡

4. የሮም ወታደሮች የነበሩና የኢየሱስ መቃብር ጠባቂዎች ብርቱ ድንጋጤ፣ ውድቀትና ሽሽት፡፡

5. አስከሬኑ የተጠቀለለበት ጨርቅ በመቃብር ውስጥ መገኘት፡፡

6. ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለሐዋርያት ደጋግሞ መገለጥ፣ ከዚያም ለ500 ሰዎች መታየትና በግልጽዳ አባቱ ማረግ፤

7. የኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መነሳቱን ከተለያዩ የዓይን ምስክሮች የሰሙትን ብቻ ሳይሆን በዓይኖቻቸው ያዩትን በጥንቃቄ ጽፈው ለእኛ ማስተላለፋቸውና ተጨባጭ መረጃዎች በእጃችን መኖሩ፡፡ በዚህም ላይ የርቫርድ ዩኒቨርሲቲ አንድ ዓለማችን ዕውቅ የሕግ ፕሮፌሰር መረጃዎቹን በሳይንሳዊ መንገድ በጥልቀት ካጠኑ በኋላ፡- "እምነታችን የተመሠረተው በጠንካራ እውነት ላይ ነው፡፡ እውነቱም በኢየሱስ ክርስቶስ ልደት፣ አገልግሎት፣ ሞትና ትንሣኤ መሆኑና ይህም በዚያ ዘመን በነበሩ በዓይን ምስክሮች ብቻ ሳይሆን በሕይወታቸው እርግጠኛ በሆኑ ጸሐፊውች የተጻፈ ከበቂ በላይ ማስረጃ መሆን የሚችል ዳጎስ ያለ መረጃዎች በእጃችን መኖራቸው ነው" ብለዋል፡፡

8. ከሞቱ በፊት ጥለውት የፈረጠጡ፣ እርሱ ሲያዝ ከእርሱ ጋር ለመታየት ፈጽሞ ያልፈቀዱና በአደባባይ የካዱት ተከታዮቹ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋለ በንስሐ ወደ እርሱ ተመልሰው፣ ለዓለም ሁሉ ያዩትን በድፍረትና በእምነት እየመሰከሩ በየተራቸው እርሱ ለእነርሱ ሰማዕት እንደሆነ እነርሱም ለእርሱ ሰማዕት በመሆን ወደ ቀጣዩ ሕይወት በድል መሻገር፡፡ ምናለባት ለውሸት አንድ ሁለት ምናልባት ይሞቱ ይሆናል፡፡ 12ቱም የእርሱ ሐዋርት በትልቅ ደስታና መሰጠት ለእርሱ ሰማዕት መሆን በትንሣኤው ብቻ ሳይሆን ለትንሣያቸውም ያላቸውን እርግጠኝነት ያመለክታል፡፡ ኢየሱስ ካልተነሣ ከመሞቱ በፊት ጥለውት የሸሹ እነዚህ ፊሪ የነበሩ ሰዎች ተመልሰው ትንሣኤውን በታላቅ ኃይል እየሰበኩ፣ እየኖሩ፣ እየጻፉ፣ እንዴት በተራቸው ለእርሱ ይሞታሉ?

9. በስሙ ዛሬም አጋንንትት ከሰዎች ይወጣሉ፤ ድውያንን ይፈወሳሉ፣ ሙታኖች ይነሳሉ ... ፡፡ ይህ የትንሣኤው አንዱ ማስረጃ ነው፡፡ በዚህ ዓለም ላይ በየትኛውም የሃይማኖት መሪ ስም ሞተው ተቀብረው ቀርቶ በሕይወትም እያሉ በስማቸው አጋንንትን ከሰዎች ማስወጣትና መፈወስ አልተቻለም፡፡ የትንሣኤ ንጉሥ በሆነው በኢየሱስ ስም ግን ተችሎዋል፡፡ ይህም የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ አንዱ ሕያው ማረጋገጫ ነው፡፡

10. ሌላው ጠንካራ ማስረጃ በእርሱ የሚያምኑ ሰዎች ሕይወት በትንሣኤው ኃይል መለወጥና ለዘላለም መዳን፡፡ ዛሬ ከ2 ቢሊዮን የሚበልጡ ሰዎች ይህን የትንሣኤ ጀግና ይከተሉታል፣ ያመልኩታል፣ ይገዙለታል፣ ይሰብኩታል፣ ይኖሩለታል አንተስ/አንቺስ? ያለ እርሰ ድነት፣ ሕይወት፣ ሰላምና ዕረፍት የለም!

አሜን

መልካም የትንሣኤ ኑሮ
ክብር ለታረደው በግ፤ ሞትን ድል አድርጎ ለተነሳውና በትንሣኤው ኃይል እያኖረን ላለው፡፡ አሜን።

ትንሣኤው ለዘላለም የምንኖረው ሕይወት እንጂ በዓመት አንድ ቀን የሚከበር በዓል አይደለም።

የትንሣኤው ምስክር ጸጋአብ ነኝ፡፡
@nazrawi_tube
318 viewsΒενιαμίν, 13:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 09:30:00
የዶክተር ዘገየ ቸርነት ደንቅ የህይወት ምስክርነት
አድምጡት
360p, 68.7MB,

@nazrawi_tube
49 viewsΒενιαμίν, 06:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ