Get Mystery Box with random crypto!

Natnael Mekonnen

የሰርጥ አድራሻ: @natnaelmekonnen21
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 174.19K
የሰርጥ መግለጫ

በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ሲፈልጉና ማስታወቂያ ማሰራት ከፈለጉ 👉 @NatnaelMekonnen7
Facebook.com/natnaelmekonnen.et
Instagram.com/natnaelmekonnen21

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 386

2022-05-23 22:40:40
ተወርዋሪው ፋኖ!

#Ethiopia : እዙን ጨምሮ አደረጃጀቱና ምደባም በመከላክያ ስር የሆነውና ትክክለኛው ለሃገር የሞተው እየሞተም ያለው የወሎ ፋኖ ከወልዲያ ወደ ራያ ግንባር በዚህ መልኩ ደርሶ ቦታውን ይዟል!
15.7K viewsedited  19:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 19:44:25

28.3K views16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 19:02:46
" የMokeypox በሽታ መስፋፋት ለኢትዮጵያም ስጋት ነው "

በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የቅድመ ማስጠንቀቂያ እና መረጃ ስርዓት አስተዳደር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዘውዱ አሰፋ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል የተናገሩት ፦

" ቫይረሱ ከዚህ በፊት ፈንጣጣ መሰሉ በሽታ ተጠቂ የሌለባቸው ሀገራት ሳይቀር እየተስፋፋ ነው፡፡

እንደማንኛውም ሀገር እኛም በቫይረሱ ስርጭት ስጋት አለን። በኢትዮጵያ የመግቢያ እና መውጫ በሮች ላይ የተለመደው ክትትል እየተደረገ ይገኛል።

በሀገሪቱ የየብስ እና የአየር ትራንስፖርት መግቢያ እና መውጫ ላይ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እና ወደ ሌሎች ሀገራት እንዳይሄድ የተላላፊ በሽታዎች ክትትል እየተደረገ ነው።

የበሽታው ተጠቂ በኢትዮጵያ ቢገኝ ማድረግ ስለሚገባን ስራዎች፣ ለህብረተሰቡ መሰጠት ስለሚገባው የግንዛቤ ፈጠራ መልዕክት እና የህክምና ክትትል ስራዎችን ለመለየት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራት ላይ ነው "
31.1K views16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 18:03:18 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በ2022 የታይምስ መጽሔት 100 ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ። መጽሔቱ ይፋ ባደረገው የ100 ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ዝርዝር በአመራር ዘርፍ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መካተታቸውን አስታውቋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፈረንጆቹ 2019 የመጽሔቱ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ አንዱ እንደነበሩ የሚታወስ ነው።

https://time.com/collection/100-most-influential-people-2022/6177683/abiy-ahmed-leaders/
32.1K views15:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 17:03:45
በሀሰት ከሚሰራጩ አፍራሽ ተልዕኮዎች እንጠንቀቅ።

#Ethiopia : የአማራ ህዝብ በከፈለው ወደር የለሽ ተጋድሎ ያስመዘገበውን ድል በመቀልበስ ለጠላቶቹ አሳልፈው በመስጠት ለዳግም ባርነት ሊዳርጉት የውስጥ እና የውጭ ሃይሎች ሲሰሩ መቆየታቸው የሚታወቅ ነው። አማራውን ለማዋረድ ተቀናጅተው እየሰሩ የሚገኙ እነዚህ ሃይሎች በተለያዩ ጊዜያት የውሸት ሰነዶችን እያዘጋጁ ሲያሰራጩ የነበረ ሲሆን ዛሬም እንደትናንቱ መንግስት እውቅና የሰጣቸውን የምንጊዜም የኢትዮጵያ ጀግኖች የሆኑትን የአማራ ፋኖዎች እርምጃ ሊወስድ መሆኑን የሚገልጽ “የኦፕሬሽናል አፈጻጸም ዝርዝር ግዳጅ” የሚል የዳቦ ስም የሰጡት የበሬ ወለደ የፈጠራ ሰነድ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ።

የአማራን ህዝብ እንደ ህዝብ ኢትዮጵያን እንደ አገር ፊት ለፊት ገጥሞ ማሸነፍ እንደማይችል የተረዳው አሸባሪው ትህነግና ወኪሎቹ እያሰራጩት ያለው የፈጠራ ሰነድ የአማራ ክልል መንግስት የማያውቀው መሆኑን እየገለጽን ጠላት በቀጣይነትም በፈጠራ እና ውሸት የተሞሉ ሰነዶችን እያዘጋጀ ማሰራጨቱን መቀጠሉ አይቀሬ በመሆኑ መላው ሰላም ወዳድ የሆነው የክልላችን ህዝብ ከመሰል የፈጠራ ሰነዶች እራሱን እንዲጠብቅ እናሳስባለን።

የህዝባችን ተደጋጋሚ ጥያቄ የሆነውን የሰላም እና ደህንነት ጥያቄ ለመመለስ ምልዓተ ህዝባችንን በማሳተፍ የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ እርምጃ እየወሰደ የሚገኝ ሲሆን በዚህም እርምጃ አንጸባራቂ ድል ተገኝቷል። ህዝባችን ከጸጥታ አካላት ጎን በመቆም ለዘመቻው መሳካት አኩሪ ተጋድሎ እያበረከተ የሚገኝ ሲሆን ይኸንን ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል የክልል መንግስት በአክብሮት ያሳስባል።

የአማራ ፓሊስ ኮሚሽን
34.5K views14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 16:38:01
ሰበር መረጃ ወሎ ፋኖ !!!

#Ethiopia : በነ ጀኔራል ሀሰን ከረሙ ፤ ሞገስ ከበደ ፤ ሻለቃ ደምሌ አራጋው ፣ ምስጋን ደስየ ፣ ሙሃመድ ጎብየ ፤ የወርቄው ትንታግ በላይ እያሱ ፣ ሰይድ አፋሩ እና ሰለሞን ሰማው ፣ የሚመራው የወሎ ፋኖ ምርቃቱን ጨርሶ በትላንትናው እለት መከላከያ ሰራዊቱ በሰጠው የግዳጅ ቀጠና ወደ ወሎ ግንባር በዚህ መልኩ ገብቷል።

ይህ ነው ለሀገር ደጀንነት !!!
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ጀኔራል ሀሰን እና ሙሉ አመራራቸው ከመከላከያ ከሰራዊቱ፣ ልዩ ሃይሉ እና ሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር ተናበው እየሰሩ እንደሆነ ጀኔራሉ በስልክ ጠዋት ላይ አረጋግጠውልኛል።

አይሱዙው ላይ ምን እንደሚል አንብብልኝ !!
በርቱልን !!!
34.5K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 15:35:22
#Ethiopia : ወልዲያ ላይ ስልጠናቸው ሲከታተሉ ቆይተው የተመረቁት የወሎ ፋኖ አባላት ትናንትና ወደ ግንባር መሸኜታቸው ተሰምቷል።ዛሬ ደግሞ በሀገር መከላከያ ሠራዊቱ ምድብ(ግንባር) ቦታ እንደተሰጣቸው ታውቋል!!


ጀማል አማን
35.2K views12:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 14:09:18 #Ethiopia : መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊሰማው የሚገባ! ይህን ፕሮግራም ለአደማመጥ እንዲመች ብዬ ቆራርጨ ላቀርበው አስቤ ነበር ግን ምኑን ከምኑ ልቁረጠው?! አንዳችም የሚቆራረጥ ነገር የለውምና 49 ደቂቃ ነች ግዜ ሰታችሁ አድምጡት!

37.3K views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 14:08:56 ከድባጤ እና በቂዶ ሚሊሻዎች ጋር በመተባበር የአሸባሪው ህወሓት ተላላኪዎችን መደምሰሱን የመተከል ኮማንድ ፖስት አስታወቀ

በመተከል ዞን በድባጤ እና በቂዶ ወረዳዎች የሚገኙ የጉሙዝ የሚሊሻ አባላት ከመከላከያ ሰራዊት ጎን ተሰልፈው ለአሸባሪ ቡድኖች የሚላላኩ ሽፍታዎችን መደምሰሳቸውን የመተከል ኮማንድ ፖስት የተቀናጀ ግብረ ኃይል ተወካይ ኃላፊ ብርጋዴር ጀኔራል ዋለልኝ ታደሰ ተናገሩ፡፡

ብርጋዴር ጀኔራል ዋለልኝ ታደሰ እንደተናገሩት፥ የሚሊሻ አባላቱን ከግል ፍላጎት ወደ ቡድን አንድነት አደረጃጀት በመቀየር በአጭር ጊዜ ውስጥ የአሸባሪው ህወሓት ተላላኪ ሽፍታዎች በመደምሰስ እና የጦር መሳሪያዎችን በመማረክ የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውን በተግባር አረጋግጠዋል።

የሚሊሻ አባላቱ ቡድን መሪ ብድኡከም በታሐኒ እንደገለጹት÷ የአሸባሪው ህወሓት ተልዕኮ አስፈፃሚዎችን ሙሉ በሙሉ ለመደምሰስ እና ሕዝቡን ከጥፋት ቡድኖች ለመታደግ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ተቀናጅተን እንሠራለን ብለዋል፡፡

ሌሎች የሚሊሻ አባላት በበኩላቸው÷ ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ሰላም ለማደፍረስ ቀን ከሌሊት የሚደክሙ የአሸባሪ ኃይሎች ላይ አስፈላጊውን የኃይል እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጅተናል ማለታቸውን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
34.7K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 14:08:07 ‘‘‹‹በሸኔ ቁጥጥር ስር የነበሩ ቦታዎች አልነበሩም ፤ ነጻ የሚወጡ ቦታዎችም የሉም››’’:- ኮሎኔል አበበ ገረሱ ኦሮሚያ አስተዳደርና ጸጥታ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

የክልሉ አስተዳደርና ጸጥታ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ ለኢፕድ ሕብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን እየወሰደ ባለው እርምጃ የሸኔ እንቅስቃሴ ለሀገር ስጋት በማይሆን ደረጃ ላይ ደርሷል ብለዋል::

እንደ ኮሎኔል አበበ ገረሱ ገለጻ ሸኔ በሚንቀሳቀስባቸው የኦሮሚያ አካባቢዎች መንገድ በመዝጋት ና ከመኪና አውርዶ ሰውን በመግደል በተወሰነ መልኩ በሕዝቡ እንቅስቃሴ ላይ ፍርሃትና ስጋት እንዲፈጠር አድርጓል:: ሆኖም በድርጊቱ የተማረረው ሕዝብም ከጸጥታ አካላት ጋር በመሆን ቡድኑ የሚንቀሳቀስባቸውን ቦታዎች በመከታተል እርምጃ እየወሰደበት ይገኛል::

እስከ አሁን ድረስ ሸኔ ላይ በተወሰደው እርምጃ የተገደሉና የተማረኩ መኖራቸውን ገልጸው በተገኘው ውጤት የሕዝብ እንቅስቃሴ ወደነበረበት ቦታ እየተመለሰ መሆኑን ገልጸዋል ::

እንደ ኃላፊው ገላጻ ሸኔ የታጠቁ የመንግሥት ኃይሎች በማይገኙበት ቦታ ጨለማን ተገን በማድረግ በጫካ ውስጥ እየተሽሎከለኩ ጥቃት ፈጽሞ ከመሸሽ ውጪ የመንግሥት አቅም አሸንፎ የተቆጣጠረው ቦታ የለውም :: ‹‹በሸኔ ቁጥጥር ስር የነበሩ ቦታዎች አልነበሩም ፤ ነጻ የሚወጡ ቦታዎችም የሉም›› ብለዋል። ሸኔ ፊት ለፊት ጦር ግንባር ላይ የሚደረግ ጦርነት የሚከተል ሳይሆን ሽምቅ ውጊያ ሥልት የሚከተል አጥፊ ቡድን ነው::

የሸኔ እንቅስቃሴ ለሀገር ስጋት አይሆንም ሲባል እንደተለመደው ተሸሽገው ህዝቡ ላይ ጥቃት አያደርሱም ማለት እንዳልሆነ ምክትል ቢሮ ኃላፊው አመላክተዋል:: ሆኖም ይህንን የቡድኑን አጥፊ ድርጊት ለመከላከል መንግሥት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንደሚያደርግ ኮሎኔል አበበ ገረሱ አብራርተዋል::
31.5K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ