Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethmedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-01-10 21:58:30
አስታውሱኝ አስታውሳችኋለውና ለኔም አመስግኑ አትካዱኝም። እናንተ ያመናችሁ ሆይ!! በትእግስትና በሶላት ታገዙ(ተረዱ)። አላህ (በእርዳታው) ከታጋሾች ጋር ነውና።


https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
54 viewsedited  18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 19:44:16
ሰሞኑን በሀዲያ ክልል ጥቃት የተፈፀመባቸው ሙስሊም ወገኖቻችን ናቸው ጴንጤዎች ድምበር አልፈዋል መጅሊሱ ምን እየሰራ እንደሆነ አላቅም በግለሰብ ደረጃ ሰው ሄዶ እስከሚያጣራና እስከሚጠይቁ ድረስ ጥቃት ፈፃሚዎቹም እስካሁን አልተያዙም አላህ ይድረስላቹ ወገኖቼ ።



https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
122 viewsedited  16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 18:17:55
86 views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 18:17:44 የዓለም  አቀፉ ሙስሊሞች ሊግና የአወልያ እርዳታና ልማት ድርጅት ጋር አብረዉ ለመስራት ተስማሙ።


ጥር 2/2015 ማክሰ ኞ

የዓለም  አቀፉ ሙስሊሞች ሊግ  رابطة العالم الاسلامي በአውሮፖ የአሜሪካ ዋና ዳይሬክተር  እና በሊጉ የዋና ፀሐፊው  የዶክተር ሙሐመድ  አብዱል ከሪም አል ጊሳ  አማካሪ በሆኑት በዶክተር  አብዱል አዚዝ ሰርሃን የተመራውን  ልዑክ በዛሬው እለት የአወሊያ እርዳታና ልማት ድርጅትን ጎበኙ።

የሙስሊም ወርልድ ሊግ ልዑክ አወሊያ ሲገባ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። በዉይይቱ ፕሮግራም ላይ
አወሊያ እርዳታና ልማት ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ጀማል ሙሀመድ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እንዲሁም በድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰይድ አስማረ ራቢጣ ለአወሊያ የነበረውን ታሪካዊ አበርክቶ ከምስጋና ጋር አቅርበዋል። አወሊያ ከመቸውም በላይ ራቢጣን እንደሚፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል።

የዓለም  አቀፉ ሙስሊሞች ሊግ  رابطة العالم الاسلامي ቀድሞ ያስተዳድረዉ ወደ ነበረው አወሊያ ተቋም በግፍ ከተባረረ ከ12 አመት በኋላ ዛሬ ተመልሶ ጉበኝት አድርጓል።

የቀድሞ መጅሊሶች የድጋፍ ደብዳቤ ለመጻፍና ሊጉ ድጋፍ እንዲያደርግ ፍቃደኛ ባለመሆናቸዉ በርካታ ነገሮች ተሰናክለው ቆይተዋል።

በእነ ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ የሚመራዉ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም አመራሮች በአካል ሄደዉ በተደረገላቸዉ ግብዣ መሠረት የልዑካን ቡድኑ ወደ ሚወዷት አወሊያ ለመምጣት ችለዋል። ለዚህም ድጋፍ ጠቅላይ ምክር ቤቱን እጅግ እናመሰግናለን።

Mujib amino



https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
85 views15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 16:36:10 የሀድያ ሙስሊሞችን የሚወክለው ተቋም ማነው?
..
ከአመት በፊት በሀድያ ዞን ሆሳዕና ከተማ ውስጥ ያለው ጥምቀተባህር በስማችን የይዞታ ማረጋገጫ ይሰጠን በሚል ከኦርቶዶክስ ምዕመናን ጋር ዞኑ እሰጣገባ ገብቶ ነበር። ቦታው የህዝብ መገልገያ ስለሆነ በአመት አንዴ ቦታው ላይ ስለሚከበርበት ብቻ ተብሎ ለአንድ እምነት ይዞታ አልሰጥም ብሎ ተሟገተ። በተቃራኒው ወገን በኩል ጉዳዩን በጥንካሬ ይዞ የታገለው የከተማው አልያም የዞን ወይንም የክልሉ የቤተ ክህነት አደረጃጀት ብቻ አልነበረም። በጉዳዩ ላይ ግንባር ቀደም ትግል ያደረገው ላዕላይ ስልጣን ያለው ሲኖዶሱ እራሱ ነበር። ዞኑ ቦታውን አልሰጥም ብሎ በግትርነት ሲቀጥልም ጥምቀት በዞኑ እንዳይከበር ከማዘዝ ጀምሮ ጠንካራ መልዕክቶችን የሚመለከታቸው አካላት ዘንድ በመቅረብ የታገሉት በሲኖዶሱ የተሾሙ የበላይ አባቶች ናቸው። ልብ በሉ ምዕመን እንዳያመልክ ተደብድቦ አልያም ታስሮ አይደለም፥ ቦታ ይሰጥ ለሚለው ጥያቄ ብቻ ነው።
...
የሀድያ ሙስሊሞች ላለፉት አመታት አይደለም የማምለኪያ ቦታ ሊያገኙ ይቅርና ወቅፍ ባደረጉት የግል ቤት እንኳን እንዳይሰግዱ ወቅፍ ያደረጉትን የ90 አመት ሽማግሌ ከማሰር ጀምሮ ምዕመኑን እስከመደብደብ ያልተሰራ ግፍ አልነበረም። ይህንን ግፍ ጉዳይ ብሎ የሚከታተል የሙስሊም ተቋም ባለመኖሩ ተራ የወረዳ አመራር "አልሐምዱሊላህ" ብላችኃል ብሎ ወጣቱን የሚደበድብበት ድፍረትና ንቀት ውስጥ ተገብቷል። ህገ-መንግስታዊ መብታቸው ለሆነው ዳዕዋ ሳይቀር ጉቦ ካልሰጡ ዳዒዎችን አምጥተው ማስተማር የማይችሉበት አፈና ውስጥ አሳልፈዋል። 50 ሺ እና 100 ሺ ካሬ መሬት እያነሳ ነብይ ነን ለሚሉ ሰዎች የሚሰጡ የዞን አመራሮች ለሙስሊሞች ግን ለምን በገዛ መሬታችሁ ሰገዳችሁ ብለው ዱላ የያዘ ፖሊስ ልከው ሴትና ህፃናትን ሳይቀር ያስደበድባሉ።
...
ይህ ጉዳይ ግድ የማይሰጠን ከሆነ ከቶ የትኛው ጉዳይ ነው እንደ ኡማ የሚያስጨንቀን? የእነዚህ ህዝቦች የዕለት ተዕለት ስቃይ ለውግዘት እንኳን መጅሊሱን ግድ ካልሰጠው ስለየቱ የገዘፈ ጉዳይ ሊታገልልን ነው? መንጋው ሲበላ ግድ የማይሰጠው እረኛ እንዴት ተብሎ መልካም እረኛ ይሆናል? በዚህ ዙሪያ ድምጽ የሚሆንልንና መንገዱን ቃኝቶ መፍትሄ የሚፈልግልን ተቋም እንዲመጣ ከታገልንም በኃላ ጩኸታችን እንደድሮው ከፌስቡክ አለመዝለሉ ልብ ይሰብራል።
...
የሀድያ ወገኖቻችን፥ አሏህ ከናንተ ጋር ይሁን..!

Abdurehim ahmed



https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
80 views13:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 15:13:51
አስቸኳይ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

ዳዕዋ ቲቪ ከዚህ በታች ያሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል ፡፡

የ ስራ መደብ ፡ ቪድዮ ኤዲተር
የት/ት ደረጃ ፡ ከሙያው ጋር ተያያዥነትያለው ሰርትፍኬት
የስራ ልምድ ፡ ከ 1 አመት ያላነሰ
ደሞዝ ፡ በ ስምምነት
ብዛት ፡ 2

የ ስራ መደብ ፡የ ማርኬቲንግ ባለሙያ
የት/ት ደረጃ ፡ ከሙያው ጋር ተያያዥነት ባለው የ ትምህርት ዘርፍ ሰርትፍኬት እና ከዚያ በላይ ያለው።
የስራ ልምድ ፡ ከ 1 አመት ያላነሰ
ደሞዝ ፡ በ ስምምነት
ብዛት ፡

ቦታ፡- ጀሞ 3 ሰዒድ ያሲን አዲሱ ህንጻ 2ኛ ፎቅ በአካል መተው ማመልከት ይችላሉ

ሰልክ :- 0912 97 27 69 / 0975 97 97 90



https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedi
73 viewsedited  12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 14:04:14
ሰሞኑን በበኒ (ኑር)መስጂድ የተፈጠረው ነገርን በተመለከተ ቢላል ቲቪ ከኡስታዝ መሀመድ አባተ ጋር ያደረገው ቆይታ ነው አዳምጡት ።



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedi
https://t.me/fethmedia
84 viewsedited  11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 13:44:46 በሐይማኖት ማስገደድ ሊኖር አይገባም!!

በደቡብ ክልል በሀድያ ዞን  ሙስሊሞች በብዛት በሚኖሩበት በጭንጎ ቀዴ ቀበሌ ባሳለፍነው ቅዳሜ በቀበሌው ነዋሪ ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመው ድብደባ እና ጥቃት ፍፁም ተቀባይነት የሌለው ፣ከኢትዮጵያውያን እሴት ያፈነገጠ በሁሉም ሀይማኖት ተከታዮች ዘንድ ሊወገዝ የሚገባው ወንጀል ነው::

በተመሳሳይም በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን በጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎችን በሂጃብ ምክንያት ከትምህርት ማገድ እና ይህን በአግባቡ የጠየቁ ወላጆችን እና ታዳጊዎችን ማዋከብ እና ማሰር አግባብ አለመሆኑ ለመግለፅ እወዳለው ::

በሀገራችን ኢትዮጵያ የሐይማኖት ነፃነት በይፋ ከታወጀበት ጊዜ አንስቶ ዜጎች የፈለጉትን ሀይማኖት የመከተል፣ የማምለክ፣ የሌሎችን እምነት ሳይጋፉ ስብከት ማካሄድ እና በመረጡበት እምነት ላይ ፀንቶ የመቆየት መብታቸው የተጠበቀ ነው::

የአንድ ሀይማኖት ተከታዮች በብዛት በሚኖሩበት አካባቢ የሚኖሩ ቁጥራቸው አናሳ የሆኑ የሌላ እምነት ተከታዮችን መብት እና የሀይማኖት ነፃነት መጋፋት ሀይማኖተኛ ከሚባል ማህበረሰብ የማይጠበቅ ፅንፈኝነት ነው::

በሀድያ ዞን በጭንጎ ቀዴ ቀበሌ የተፈፀመውም ሃይማኖትን ለይቶ የተፈፀመ ጥቃት ከፅንፈኝነት አስተሳሰብ የመነጨ፣ ባጭሩ ካልተቀጨም ሀገር የሚያጠፋ እሳቤ ነው::

ሀይማኖት ሰላምን፣ መተዛዘንን እና መከባበርን የሚሰብክ ሆኖ እያለ ከሀይማኖት እሴት ባፈነገጠ መልኩ የራስን ሀይማኖትን በግዳጅ ሌሎች እንዲቀበሉ ማስገደድ እና ማጥቃት ኢ ሞራላዊ እና ህገ ወጥ የሆነ ወንጀልም ነው::

ይህን በእምነት ሽፋን የተፈፀመን ወንጀል ከማንም በላይ የሀይማኖቱ አባቶች፣ ሰባኪያን እና ማህብረሰቡ ሊያወገዘው እንዲሁም ዳግም እንዳይፈፀምም በስህተት አካሄድ ላይ ያሉ ሰዎችን የቤተ እምነቱ መምህራን ተከታዮቻቸውን ሊገስፁ ይገባል::

ይህን አስነዋሪ ጥቃት በሙስሊሞች ላይ ያደረሱ ወንጀለኞችንም የሐድያ ዞን አስተዳደር እና የፀጥታ ክፍሉ ባስቸኳይ ለህግ በማቅረብ ፍትህን እንዲያሰፍን ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለው::

በተመሳሳይ ጉንችሬ ባሉ ትምህርት ቤቶችም ላይ እየተስተዋለ ያለው ከሂጃብ ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ችግሮችም የትምህርት ቢሮ እና የትምህርት ቤቱ አመራሮች ከሀይል አማራጭ ይልቅ ከተማሪዎች እና ከወላጆች ጋር  ውይይት በማካሄድ የነገ ሀገር ተረካቢ የሆኑት ተማሪዎች በሀይማኖታቸው ምክንያት የማግለል እና ከትምህርት ገበታ እንዲርቁ የተደረገበትን አግባብ በማረም የመማር ማስተማር ሂደቱ እንዲቀጥል ሊያደርጉ እንደሚገባም ለማሳሳብ እወዳለው:

በመጨረሻም በሀገራችን በሁሉም ቦታዎች ሀይማኖትን፣ ብሄርን እና ማንነትን ኢላማ ያደረጉ ጥቃቶች፣ ግድያዎች፣ ጭቆናዎች እና ማፈናቀሎች በዘላቂነት ያበቁ ዘንድ የተናጠል ውግዘት  ብቻ ሳይሆን ሁሉም ሰው እምነት እና ብሄር ሳይለየው በጋራ ግፍን ለመቃወም እና ለማስቆም በአንድነት መቆም ይገባል::

የአንዱ መጠቃት ለሌላው ህመም መሆን ሲችል፣በማንም የሰው ልጆች ላይ የሚፈፀም በደል እና ጭቆና በራስ ላይ የተፈፀመ ጭቆና እና ግፍ መሆኑን ማመን መቻል ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ነው::

ይህን አስተሳሰብ ማምጣት ከተቻለ አጥፊዎንም ለማጋለጥ፣ ጭቆና እና በደሎችን፣ ግድያዎችን እና መፈናቀሎችን ለማስቆም ያግዛል ብቻ ሳይሆን ይቻላልም!

በሀገራችን በሰላም እና በመከባበር እንዲሁም እውቅና በመሰጣጠት በፍትህ እና በእኩልነት ለመኖር በጋራ እንስራ!
ኡስታዝ አቡበከር አህመድ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
89 views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 10:10:46 ስለ ጠንካራ ስብእና መኖር
አጠር ያለች ወሳኝ ማስታወሻ ዳእዋ ነው በኡስታዝ ማህሙድ ሀሰን አዳምጡት ።

ኡስታዝ ማህሙድ ሀሰን
Strong persenality
ስለ ጠንካራ የሆነ ስብእና መኖር

  መጥፎ ነገርን በእጅህ አስቁም
           በምላሱ  …
        በቀልቡ…   የኢማን ድክመት ነው"
ስብእናው ደካማ የሆነ ሰው
ባመነበት አይፀናም
#ኸይር ስራ ቢሰራም አጅር አያገኝም

ፂሙን የሚያሳድገው በዙሪያው ያሉት ስለሚያሳድጉ ነው
   የሚላጨውም በዙሪያው ያሉት ስለላጩ ነው  ባያምንበትም
  
   #ህፃናት ልክ ያለፈ ስብእና አላቸው
ያልተገባ ተርቢያ ግን የራሳቸውንም እንዳይጠይቁ ያደርጋቸዋል ።
አህሉል ኢማን ሀሜተኛ አይደለም እዛው ነው የሚናገሩት
  #ሀቅ በድምፅ ብልጫ አይደለም

በጀማዓ ስገዱ እንጂ በጀማዓ አስቡ አልተባልንም
   #አብዛኞቻችን አቅላችንን ሽጠናል…!

     ገጠሬዎች ኩፍርና ኒፋቅ ውስጥ የበለጠ  የሚገቡት ድንበሩን ስለማያውቁ ነው ።
  
    ሰኞ   1/5/15
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
114 viewsedited  07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 08:22:41 ተቋሙን ለማሳጣት እየተደረገ ያለው የግለሰቦች የጥፋት መንገድ ግለሰቦቹን ከባድ ዋጋ ያስከፍላል!

የአ/አበባ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት የተቋሙን ህልውና ለማስጠበቅ ለአንድም ሰኮንድ ወደ ኋላ አይልም

የአ/አበባ ከተማ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት የህግ ክፍል ሀላፊ ኡስታዝ ሱፊያን ኡስማን


የኑር መስጅድን ተገን በማድረግ የግል ፍላጎትን ማሳካት አይቻልም፡ህግና ስርዓት ይከበራል፡የጊዜና የጉልበት ዋጋ ካሳ በግለሰቡ ላይ በህግ ይዳኛል።

ተቋም ከግለሰብ በላይ ነው፡ግለሰብ ከማሕበረሰብ ጋር ራሱን አቆራኝቶ የግል ፍላጎትን ማስኬድ በፍፁም አይችልም፡ሀገራዊ ለውጥ የጋራ እንጂ የግለሰቦች ሊሆን አይቻለውም፡በተቋም ውስጥ ሌላ ተቋም፡በመንግስት ውስጥ ሌላ መንግስት፡በሀገር ውሰጥ ሌላ ደሴት መፍጠር ፈፅሞ አይታሰብም።

በበኒ ኑር መስጅድ ውሰጥ ተወሽቆ የሕዝበ ሙስሊሙ ተወካይ በመምሰል የተቀመጠው ግለሰብ፡ሕዝበ ሙስሊሙን ሲከፋፍል የነበረ፡አንድነት አይጠቅምም የሚል ከመሆኑ በዘለለ፡የልማት ስራውን በማደናቀፍ ለአመታት የመስጅዱን ሚናራ ሞሽሮ በማስቀመጥ በዋና ከተማ እንብርት ላይ ያለን ግዙፍ መስጅድ ያኮሰሰ ስው ከመሆኑ አንፃር፡በአስተዳደርነትም ደካማ የሆነና የኦዲት ሪፖርት የሌለው ሰው መሆኑ ይታወቃል፡የእምነት ተቋምን የኑሮ መግፍያ ማድረግ ደግሞ ነውርም ነው።

አስተዳደር ተብየው ከቦታው መነሳቱን በቃለ ጉባዔ አስይዞ በራሱ እጅ የፈረመበትን ሰነድ ያልተቀበለ ከሆነ፡የሚያሸሸው ገንዘብና ሌላ ተጨማሪ ሴራ መጎንጎን ላይ ስለመሆኑ የሚያመለክት ከመሆኑ አንፃር ተቋማዊ እርምጃ ወሳኝ ነው።

መስጅድ ተቀማ፡ኢማም ተባረረ፡ደምወዝ ተቆረጠ የሚል የውሸት ዘመቻ ጊዜና ቦታ የለውም፡አንድም ሰው በዝህ ጉዳይ ላይ የተነካ እንደሌለ እየታወቀ ብዙ ማስጮህ ተችሎ ነበር፡ነገር ግን የውሸት መንገድ ሁሌም አጭር ነውና ተጋለጠ።

መጅሊስ የቡድን ወይም የተወሰኑ ሰዎች ተቋም አይደለም፡ሁሉንም በእኩል የሚያገለግል ተቋም ነው፡የተቋም ክብርን ማስጠበቅ ደግሞ የተቋሙን ህልውና ማስቀጠል ነው፡ ስለዝህም ተቋሙን ለማሳጣት እየተደረገ ያለው የግለሰቦች የጥፋት መንገድ ግለሰቦቹን ከባድ ዋጋ የሚያስከፍላቸው መሆኑ መታወቅ አለበት፡ይህን ደግሞ አብረን የምናየው ጉዳይ ይሆናል፡በእስልምናና በቡድን ስም መነገድ አይቻልም፡አበቃ።

የአ.አበባ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት የተቋሙን ህልውና ለማስጠበቅ ለአንድም ሰኮንድ ወደ ኋላ የማይል ጠንካራ ተቋም መሆኑን ሁሉም ማወቅ ግድ ይለዋል ።



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
101 views05:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ