Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethmedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-01-04 08:40:48
ሴቶችዬ ተጋብዛቹሀል
ወንዶችን አይመለከትም
107 views05:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 06:29:53
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልኽሚስ 11 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ
110 views03:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 06:29:30 "አቡ የዚድ መዕን ኢብኑ የዚድ ኢብኑ አል-አኽነስ (ረ.ዐ) እርሳቸውም ፣ አባታቸውም ፣ አያታቸውም ሶሐባዎች ነበሩ እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፡-
‹‹አባቴ የዚድ ለምፅዋት የተወሰኑ ዲናሮችን አወጣና መስጊድ ውስጥ ለአንድ ሰው መፀወተ። መጣሁና አነሳኋቸው ወደርሱም ይዣቸው መጣሁ፡፡ ‹‹በአሏህ እምላለሁ! ለአንተ አላሰብኳቸውም ነበር›› አለ፡፡ መልእክተኛው (ሶ.ዐ.ወ) ዘንድ ሞገትኩ፡፡ ‹‹የዚድ ሆይ! ለአንተ ያሰብከው አለህ (የኒይያህን ዋጋ ታገኛለህ) መዕን ሆይ! ለአንተ ደግሞ የያዝከው አለህ›› አሉ፡፡
(ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል) - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበዉታል"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።


https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
106 views03:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 22:31:59
115 views19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 22:31:54 ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የሠላም አባት!

የኢ/እ/ጉ/ጠ/ም ዋና ፕሬዝደንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንና የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤን በበላይነት አስታረቁ።


ታህሳስ 25/2015 ማክሰኞ

ከሰሞኑ በተፈጠረዉ ወቅታዊ ጉዳይ ማለትም ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር በተያያዘ አስተምህሮቱ የሚያጠለሽና መከባበርን የሚያደፈርስ ስብከቶች ተፈጽመዉብኛል በማለት ለቀረበዉ አቤቱታ ጉባዔዉ አስፈላጊ እርምጃ ባለመውሰዱ ምክንያት ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመውጣት ማሳሰባቸዉን ተከትሎ የተፈጠረዉን ጉዳይ እንደአባት ኃላፊነት በመውሰድ፣ እርቅና ሠላም እንዲሰፍን የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤ/ም ዋና ፕሬዝደንት የሆኑት ሸይኽ ሀጅ ኢብራሂም ቱፋ ድርሻቸዉ ከፍ ያለ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ ከጤናቸዉ አኳያ ከቦታ ወደቦታ መዘዋወር ስለማይችሉ በእሳቸዉ ቢሮ ውይይት የተካሄደ ሲሆን  የጋራ ውይይቱን በመምራትና በማስታረቅ በሠላም፣ በፍቅርና በመከባበር እንዲሰምር ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የአባትነት ሚናቸዉን ተወጥተዋል።

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠ/ም/ቤ/ም ዋና ፕሬዝደንት ሸይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባላትንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችን በማስታረቅና በጉባዔዉ እንዲቀጥሉ በማሳለጥ ወደ ፊትም ችግሮችን በጋራ ለመፍታት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አድርገዋል።


ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
112 views19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 21:09:06
115 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 21:09:00 ለብልጽግና መጅሊስ አልታዘዘም፣ ከአስተዳደርነት አልነሳም ሲል አቶ መንሱር ዘይኑ በኑር መስጂድ ቅጥር ጊቢ ህገ ወጥ የሆኑ የመስጂዱ ሰጋጅ ያልሆኑ አካላትን በማሰባሰብ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት መሞከሩ ታውቋል።

ታህሳስ 25/2015 ማክሰኞ

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከ/ም/ቤ ባለፉት ወራት በአዲስ መልኩ ሕዝባዊና ሕጋዊ አደረጃጀት በመፍጠር በመላው ከተማ ያሉ የመጅሊስ የወረዳና የክ/ከ አመራሮችን ስራ ማስጀመሩ ይታወቃል።

በዚህ ሕጋዊና ሕዝባዊ ውክልና መሰረት መላዉ ሕዝባችን በሚፈልገዉና በመረጠዉ መልኩ መዋቅሩ በመውረዱ እጅግ ደስተኛ መሆኑን ከፍተኛ ድጋፍ አሳይቷል።

ይሁንና በርካታ የከተማዉ ምዕመን በሚሰግድበት በአራዳ ክ/ከ የሚገኘዉ ኑር/በኒ መስጂድን አስተዳድራለዉ የሚለዉ በአቶ መንሱር ዘይኑ የሚመራዉ የቀድሞ ሕገ ወጥ መጅሊስ በሠላም  ከመልቀቅና ከማስረከብ ይልቅ ረብሻ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በዛሬው እለትም የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በሰጠዉ አቅጣጫ መሰረት የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ካሊድ መሀመድ  ፣የአራዳ ክ/ከ ና የወረዳ አመራሮች የኑር መስጂድ አስተዳድር በአዲስ መልኩ እንዲያዋቅሩ በቅጥር ጊቢ ቢገኙም አቶ መንሱር ዘይኑ ባደራጃቸዉ ህገ ወጦች ምክንያት ሁከትና ብጥብጥ ለማሳነሳት ጥረት አድርጓል።

አቶ መንሱር "እናንተ የብልጽግና መጅሊስ ናችሁ፣ ደም ይፈሳል እንጂ ከቦታዬ አልነሳም፣ መስጂዳችንን ልትነጥቁን ነው፣..." እንዲሁም እድሜዉን የማይመጥኑ ስድቦች ሲሳደብ የመጅሊስ አመራሮቹ ሁኔታዉን በትዕግስት  አሳልፈዋል።

አቶ መንሱር ያሰባሰባቸዉ ወጣቶች ከጠሮ፣ ከ01፣ እና ከኑር መስጂድ አከባቢ ተሰባስበዉ የመጡ መሆናቸዉን ለማወቅ ተችሏል። እነኚህ ወጣቶች በቀደመዉ ጊዜ በተለያዩ መስጂዶች ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸዉ ልብ ይሏል።

የአ/አ ከተማ መጅሊስ ለአቶ መንሱር የስንብት ደብዳቤ መጻፉ ይታወቃል።

ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
117 views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 18:07:57
አስላሙ ዐለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ
ወድ የተፍሲር እና ዐረበኛ ት/ት ፈላጊዎች ምዝገባ ለጠናቀቅ የቀሩት 3 ቀን ብቻ ስልሆነ  ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ቅዳሜ ባሉት ውስን ክፍት ቦታዎች መታችሁ እንድትመዘገቡ ለናሳስብ እንወዳለን፡፡


  ኢማም አል ቡካሪ ኢስላሚክ አሶሴሽን
120 views15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 15:08:09 ኧረ ጉንችሬ ምን እየተካሄደ ነው??
---------------------

ፍትህ ለጉራጌ ዞን ለጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎች  ሹፌሮችና ነጋዴዎች!!

በጉራጌ ዞን እነሞር ወረዳ ጉንችሬ ላይ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ተፅእኖ እየተደረገበት ይገኛል!!!
ተማሪዎችን ሂጃብ ካላወለቃችሁ አትማሩም በሚል ካለፈው አመት ማገባደጃ ጀምሮ በትምህርት ቤት ከባድ ተፅእኖ ሲያደርጉባቸው መቆየቱ ይታወሳል። በሰሞኑም ይህን ርእስ ከበላይ አስተዳደር እልባት ከተሰጠው በኋላ ዳግም ሙስሊም ተማሪዎችን ያለ ሂጃብ እንዲማሩ የማስገደድ ስራ ሴት እህቶቻችን ላይ እየሰሩ ነው። ዛሬ ደግሞ ይህን ግፍ አሻፈረኝ በማለት ለተማሪዎቹ የመማር መብታቸው እንዲከበር ድምፅ የሆነው ይህ ግፍ ያልተዋጠለት የአካባቢው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ ድብደባና እስራት በማድረስ ስልጣንን ጉልበት በማሳየት ያለአግባብ እየተጠቀሙ ሲያሳዩ እንደዋሉ የአካባቢው ነዋሪዎች መረጃ አድርሰውናል።  በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን መንገላታት በመቃወም ላይ ነው ያሉትን ሁሉ እያሰሩ ነው። አሳሪዉ አሁንም የዞኑ የፍትህና የፀጥታ ሀላፊ ቀጭን ትእዛዝ አማክኝነት መሆኑን ጨምረው አሳውቀውናል። የፌደራል መንግስት ጉዳዩን በአፅንኦት እንዲመለከትላቸውም ጥሪ አቅርበዋል!  

ሀገራችን በየአቅጣጫው እየገጠማት ካለው አለመረጋጋት ጋር ተደምሮ ይህን የመሰለ ያፈጠጠ በደል በሙስሊሙ ላይ ማድረስ እንኳንስ ተምሮ በመንግስት መስሪያ ቤት ወንበር ከተቀመጠ የዞን መሪ ቀርቶ የሀገሪቱን ተጨባጭ ካልተረዳ ተራ ግለሰብ እንኳ የማይጠበቅ ነው።

#ፍትህ_ለጉንችሬ
#ፍትህ_ለተማሪዎች
#ፍትህ_ለሙስሊም_ተማሪዎች
#ፍትህ_ለጉንችሬ_ሙስሊም_ተማሪዎች



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
129 views12:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 06:44:28
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 10 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ
29 views03:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ