Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethmedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-12-31 17:54:53
#ታላቅ_የደዕዋ_ፕሮግራም
ነገ እለተ እሁድ 6ኪሎ አል አቅሳ መስጂድ
የአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት
ከአፍሪካ ቲቪ ጋር በመተባበር
-ሼኽ ዶ/ር ሙሐመድ ሓሚዲን
-ሼኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ
-ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ እና ሌሎችም



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
126 viewsedited  14:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 17:52:33
103 views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-31 17:52:02 በሼህ አደም ቱላ ፋውንዴሽ ከስድስት ቢሊየን ብር በላይ የእስልምና ሀይማኖት መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ ሊገነባ መሆኑ ተገለጸ፡፡
**
የሼህ አደም ቱላ ፋውንዴሽን ከሀረሪ ክልል ፣ከምስራቅ እና ምዕራብ ሀረርጌ ዞን ከድሬደዋ ኢላሞች እና ሀጢቦች ጋር የጋራ የውይይት መድረክ አካሂደዋል፡፡

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሀረሪ ክልል እስልምና ጉዳዮች መጅሊስ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ሼክ አብዱሰላም ጅብሪል እንደተናገሩት በሼክ አደም ቱላ የተጀመረው ፋውንዴሽን መንገድ ላይ እንዳይቀር እንደ ሀረሪ ክልል አባላቶችን በማደራጀት ከእስልምና ሐይማኖት አባቶች ጋር ሰፊ ስራዎች እየሰራን እንገኛለን ብለዋል፡፡

በድሬደዋ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ተወክለው በመድረኩ የተገኙት ሼኽ አሊዪ አህመድ በበኩላቸው የድሬደዋ መጅሊስ በሼክ አደም ቱላ የተጀመረውን ፋውንዴሽን በበጀት እና በሰው ሀይል የመደገፍን ስራ እንደሚሰሩም ገልፀዋል፡፡

በምስራቅ ሀረርጌ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምክትል ሀላፊ የሆኑት ሼክ ኡመር እስማኤል በመድረኩ ላይ በሰጡት አስተያየት የሼኽ አደም ቱላ ፋውንዴሽን ጉዳይ የክልል ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጉዳይ ስለሆነ በእርሳቸው ስም የተጀመረው የእስልምና ዲን ከግብ ለማድረስ የድርሻውን እንደሚወጡም ተናግረዋል፡፡

በመድረኩ በሼኽ አደም ቱላ ፋውንዴሽን ላይ ያጠነጠነ የጥናታዊ ፁሁፍ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን የፋውንዴሽኑ ዋና አላማ ላይም የተለያዩ ሀሳቦች ተነስተዋል፡፡

የሼኽ አደም ቱላ ፋውንዴሽን ከግብ ለማድረስ የእስልምና ዩንቨርስቲ በስድስት ቢሊየን ብር ለመስራት እቅድ ተይዞ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል ተብሏል፡፡

በመድረኩ ላይ የተሳተፉ ሼኾችና ኡላማዎች ወደ መጡበት ሲመለሱም የሼኽ አደም ቱላን ፋውንዴሽ ለማሳካት የድርሻቸውን ጥረት እንደሚያደርጉም ገልፀዋል፡፡

በመድረኩ ከምስራቅ ሀረርጌ ከድሬደዋ አስተዳደር ምእራብ ሀረርጌ እና ከሀረሪ ክልል የተወጣጡ እስልምና ሀይማኖት መሪዎች እና ሼኾች ተገኝተዋል፡፡

ዘጋቢ አብዲ ኡስማን
22 / 04 / 2015



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
113 views14:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 09:07:52
በቁርአን የተዋቡ መድረኮች ላይ መታደም መታደል ነው። እንዳያመልጦ
27 views06:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-29 04:49:36 "አቡ ጁሐይፋህ ወሀብ ኢብኑ ዐብደላህ (ረ.ዐ) እንዲህ ሲሉ አስተላልፈዋል፦

"ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ሰልማንን እና አቡ ደርዳዕን (ረ.ዐ) በወንድማማችነት አቆራኙ። ሰልማን አቡ ደርዳዕን ለመጉብኘት ሲሄድ ኡሙ ደርዳዕ ራሷን ጥላ ተመለከታት፥ "ምን አገኘሽ?" ሲል ጠየቃት። "ወንድምህ አቡ ደርዳዕ ለዚች ዓለም ቅንጣት ያህል ግድ የለውም" አለችው። አቡ ደርዳዕ መጣ። ምግብ አዘፋጀለትና "ብላ እኔ ፆመኛ ነኝ" አለው። "አንተ ካልተመገብክ አልመገብም" አለ ሰልማን። ተመገበ-አቡ ደርዳዕ ። አመሻሽ ላይ አቡ ደርዳዕ የሌሊት ሶላት ለመስገድ ተዘጋጀ። "ተኛ" አለው። ተኛ። እንደገና ለሶላት ተነሳ።"ተኛ" አለው። በሌሊቱ መጨረሻ ላይ "አሁን ተነስ" አለው። ሁለቱም ሰገዱ። ሰልማን እንዲህ አለ "ጌታህ በአንተ ላይ መብት አለው፥ ነፍስህ በአንተ ላይ መብት አላት፥ ቤተሰቦችህም በአንተ ላይ መብት አላቸው፥ ለእያንዳንዱ ባለመብት መብቱን አድርስ።" ነብዩ(ሰ.ዐ.ወ) ዘንድ መጣና ይህንኑ አወሳላቸው፡፡ "ሰልማን እውነቱን ነው" አሉ መልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ)፡፡"
(ቡኻሪ ዘግበውታል)
- ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
50 views01:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 19:59:48 #ኪታቡ አቂደቱ አህሊ ሱነቲ ወልጀመዓቲ
#በፈትህ አባቦራ መስጂድ
#ዘወትር ረቡዕ እና ጁመዓ ከመግሪብ- ዒሻ #በኡስታዝ ካሚል ጣሃ   ደርስ በድምፅ ክፍል #7 መከታተልና መቅራት ትችላላችሁ። #እንዳያመልጥዎ

https://t.me/fethmedia
80 viewsedited  16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 16:32:14 #ከነቢዩ (ﷺ) ጥቅል ዱዓዎች…

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለው ዱዓ ያደርጉ ነበር፦

﴿اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذ بِكَ مِنْ جَهْدِ البلاءِ، ودَرَكِ الشقاءِ، وسوءِ القضاءِ، وشماتةِ الأعداءِ﴾

“አላህ ሆይ! እኔ ከመከራ ብርታት፣ ከዘቀጠ ክፉ ዕድል፣ ከመጥፎ ፍርድ፣ በጠላት ከመሳለቅ በአንተ እጠበቃለሁ።”

ሙስሊም ዘግበውታል: 2707



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
95 views13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 16:21:47 መቀሌ ከተማ የስልክ አገልግሎት ዛሬ ማግኘቷ ባንኮች፣ የአየር ትራንስፖርት እንዲሁም እጅግ በርካታ ሌሎች የቢዝነስ እንቅስቃሴዎች እንዲቀጥሉ ያደርጋል።

የቴሌኮም ጥገና ፈታኝ እንደሆነ አይተናል፣ ይህን በአጭር ግዜ ላሳኩት መላው የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኞች እና ለዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬህይወት ታምሩ ምስጋና።

#ሰላም 

ፎቶ: ኢብኮ

Elias meseret



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
88 views13:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 08:08:48
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልዓርቢዓዐ 04 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ
110 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-28 05:56:13 "ዑመር ኢብኑ አል- ኸጧብ (ረ.ዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)፦

"አንድ ሰው ዘወትር ሌሊት የሚያከናውናቸውን (የዒባዳ) ተግባራት ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ሳያከናውን ከተኛና ከሱብሂና ከዙህር ሶላቶች መካከል ባለው ጊዜ ካከናወነ ሌሊት እንዳከናወናት (ተቆጥሮ) ሙሉ (ምንዳ) ይፃፍለታል።"
(ሙስሊም ዘግበውታል)
- ሙስሊም ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
108 views02:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ