Get Mystery Box with random crypto!

ፈትህ አባቦራ መስጂድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fethmedia — ፈትህ አባቦራ መስጂድ
የሰርጥ አድራሻ: @fethmedia
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.07K

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-01-10 07:34:49
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አሱለሳዒ 17 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
107 viewsedited  04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 07:34:09 "አቡ በክረት (ረ.ዐ) እንዳወሱት የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡- ‹‹ሁለት ሙስሊሞች በሰይፋቸው ሲገናኙ ገዳዩም ተገዳዩም የእሳት ናቸው፡፡›› ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ገዳዩስ ይሁን! ተገዳዩ (የእሳት የሚሆንበት) ምክንያት ምንድን ነው?›› ‹‹እሱም ቢሆን ወንድሙን ለመግደል ፍላጎት (ኒያ) ነበረው፡፡›› በማለት መልስ ሰጥተዋል፡፡

(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
111 views04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 15:03:14
144 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 15:03:03 የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሳውዲ የሀጅና ዑምራ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ጋር ተፈራረመ።


ጥር 1/2015 ሰኞ

በዛሬዉ እለት በሳውዲ እስልምና ጉዳዮች ሚኒስትር መስሪያ ቤት የሀጅና ዑምራ ምክትል ኃላፊ በኩል ዶክተር አብዱልፈህ ሱለይማን ማሻት (Dr. Abdulfattah bin Sulaiman Mashat)፣ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በመወከል የጠቅላይ ምክር ቤቱ ምክትል ፕሬዝደንትና የሐጅና ዑምራ ዋና ተጠሪ በሆኑት ሸይኽ አብዱልአዚዝ አብዱል ወሌ ሙሀመድ በሀጅና ዑምራ ጉዳይ የማስተባበርና የአፈጻጸም ውል ተፈራርመዋል።

ይሕ ውልና የፊርማ ስነ ስ ርዓት ለኢትዮጵያውያን ሑጃጆችም የተቀላጠፈና ዘመናዊ አገልግሎት ለመስጠት ያለመ በመሆኑ እጅግ የሚበረታታ ተግባር ሆኖ ተገኝቷል።

በተለያዩ አለማት የሚገኙ ተወካዮች በሚገኙበትና ውይይት በሚደረግበት የ2023 የሐጅ ኤክስፖ #Hajj_Expo መድረክ በዛሬው እለት ምሽት የሚካሄድ ሲሆን ልዑክ ቡድኑም ተሳትፎ ያደርጋል።

Mujib amino



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
142 views12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-09 07:14:36 "ጁንዱብ (ረ.ዐ) እንዳወሱት ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹አንድ ግለሰብ ቆስሎ ሳለ (ህመሙን መታገስ ተስኖት) በፍጥነት ራሱን አጠፋ፡፡ አላህም እንዲህ አለ፡- ባሪያዬ ለራሱ ሞት ምክንያት ሆኗል፡፡ በመሆኑም ገነትን እርም አድርጌበታለሁ፡፡››
(ቡኻሪ ዘግበውታል) - ቡኸሪ ዘግቦታ"
==========================================
ይህን ሐዲስ ያገኙውት ከ ኢትዮ ቢላል ሃዲስ አፕ ነዉ ።


https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
16 views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 16:47:49 ተቋማዊ አሰራርን በማጎልበት ከግለኝነትና ከስሜታዊነት ከፍ እንበል!!!

የሐጂ መንሱርን ጉዳይ በተመለከተ:-
1)የወረዳው እስልምና ጉዳዮች ሐጂ መንሱርን በመስጂዱ አስተዳደራዊ ጉዳይ ሊያነጋግራቸው ቢሮአቸው ድረስ ቢሄድም ፍቃደኛ አልነበሩም።
2)የአራዳ ክፍለ ከተማ መጅሊስ በተመሳሳይ ጉዳይ ሊያወያያቸው ወደ ቢሮአቸው ቢያቀናም ኢ-ስነምግባራዊ በሆነ መልኩ እንዲመለሱ አድርገዋል።
3)የክፍለ ከተማው መጅሊስ እና የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት ኃላፊና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ሐላፊ ወደ ቢሮአቸው ያቀኑ ቢሆንም በተመሳሳይ ከኢስላማዊ አደብ ውጪ እንዲመለሱ አድርገዋል።
4)የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች በተደጋጋሚ:-በመስጂዱ ልማት ዙሪያ፣በፍርድ ቤት ክርክር፣እንዲሆም በካርታው ጉዳይ ቢያወያያቸውም በውይይቱ (በሹራው) መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
5)አዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በሪፎርሙ መሰረት በስሩ የሚያስተዳድራቸውን ሰራተኞች ለመለየት እና ህጋዊነታቸውን ለማረጋገጥ ሰራተኞቹ የም/ቤቱ ሰራተኛ ለመሆናቸው የሚስረዱ ሰነዶቻቸውን እንዲያቀርቡ ያዘዘ ቢሆንም እሳቸው መረጃም ሆነ ማስረጃ ማቅረብ አልቻሉም።ወይም ፍቃደኛ አልሆኑም።
6)በመጨረሻ የም/ቤቱ ሰራተኛ ለመሆናቸው ያቀረቡት ብቸኛ መረጃ በራሳቸው የተፈረመ መሆኑ።
7)ከተራ ቁጥር 1-6 በተጠቀሰው መልኩ ህጋዊነትን እና ኃላፊነትን በአግባቡ ካለመወጣታቸው ባሻገር በምን አግባብ ወደ ስራ እንደገቡ ማረጋገጥ ባለመቻላቸው ወይም መረጃና ማስረጃ ለመስጠት ተባባሪ ባለመሆናቸው ምክንያት የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት አስተዳደር ለግለሰቡ የስንብት ደብዳቤ ለመፃፍ ተገዷል።
8)በኑር መስጂድ ያሉ ሌሎች ሰራተኞች ፎርማሊቲውን በሟሟላታቸው በስራቸው ላይ እንዲቀጥሉ ተደርጓል።
9)የስንብት ደብዳቤ አልቀበልም በማለታቸው ህጋዊ አካሄድን ተከትሎ በሚመለከተው አካል እንዲያደርሳቸው ተደርጓል።
10)የስንብት ደብዳቤው በእጃቸው መግባቱን ካረጋገጥን በኃላ የርክክብ ደብዳቤ የተፃፈላቸው ቢሆንም አልቀበልም በማለታቸው በአራዳ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሰፋ ያለ ውይይት አድርገን በመጨረሻ ዛሬ ታህሳስ 30/2015 ጠዋት 3:00 እሳቸው ብቻ እንደ አስተዳደር ተገኝተው ለመጅሊሱ አመራር ሊያስረክቡ ተስማምተን በቃለ ጉባኤው ላይ ሁላችን እሳቸውም ጭምር ፈርመው ተለያይተናል።
11)በመጨረሻ ቃላቸውን አጥፈው ስልካቸውን አጥፍተው ተሰውረዋል።
12)የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤትም በቀጠሮው መሰረት በቦታው ዋና ፀሐፊው እና ከፍተኛ አመራሩ የተገኙ ቢሆንም ከስምምነቱ ውጭ የተደረጉ አላስፈላጊ መሰባሰቦች ህዝበ ሙስሊሙን የማይመጥኑ ከመሆናቸውም ባሻገር ለሁከትና ብጥብጥ ምክንያት እንዳይሆኑ በማድረግ ማንኛውም ግለሰብ ከህግ በላይ ሊሆን እንደማይችል አፅንኦት በመስጠት ነገሩ ለማረጋጋት ተችሏል።--- ወዘተ
----
በመጨረሻም ተቋማዊ አሰራርን ማጎልበት ለሁላችንም የሚጠቅም መሆኑን አውቀን ከግለኝነት ከፍ እንል ዘንድ እራሴንም ሁላችንንም በመምከር መልእክቴን እቋጫለሁ።

Ustaz Mohammed Abate




https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
94 views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 13:43:46
101 views10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 13:43:26 አቶ መንሱር ዘይኑ ይፈለጋሉ!

አቶ መንሱር ዘይኑ ለጸጥታ አካሉና ለመጅሊስ በፊርማዉ ያረጋገጠዉን ቃል በማጠፍ በመስጂዱ ቅጥር ጊቢ ሳይገኝ ቀርቷል።


ታህሳስ 30/2015

ረቡዕ ታህሳስ 26/2015 በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳድር ፀጥታ ቢሮ ውስጥ- የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ፣ የክ/ከ ፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ፣ የወረዳዉ ፀ/ዘ/ኃ፣ የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንትን ጨምሮ የተለያዩ አባላቱ በተገኙበት ቃል ጉባዔ ተይዞ ለእሁድ አቶ መንሱር አስተዳዳሪ አካል ለሆነዉ መጅሊስ አስተዳደርነቱን እንዲያስረክብ በፊርማ ጭምር አረጋግጦ ነበር።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በደብዳቤ ቁጥር 0044/15 በቀን 20/3/2015 በፃፈዉ የስንብት ደብዳቤ መሰረት በዛሬው ቀን በመስጂዱ ቅጥር ጊቢ ተገኝቴ የፀጥታና የመንግሥት አካላት ባሉበት አቶ መንሱር አስተዳደርነቱን እንዲያስረክብ ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ሲሆን የሁከትና ብጥብጥ ጠንሳሹ አቶ መንሱር እምቢታዉ ላይ በመግፋት ሳይገኝ ቀርቷል። ለመጨረሻ ጊዜ ለሰላም ሲባል የተሰጠዉን እድል አምክኗል።

አቶ መንሱር በሕገ ወጥነት በአስተዳደርነት በቆየባቸዉ ጊዜያት ያሉት ንብረቶችና ቢሮዎች እንዲሁም ዶክሜንቶች ራሱ ባለበት አጠቃላይ ሁኔታዎችን በማስመዝገብ በቃለ ጉባዔዉ መሰረት ርክክብ ማድረግ ሲገባዉ ርክክቡን አደናቅፏል።

አቶ መንሱር ዘይኑ ስልኩን አጥፍቶ ተሰውሯል። የመንግስትና የፀጥታ አካላት ርክክብ ለማድረግ የቢሮ ቁልፎችን ይዞ ስለተሰወረ በዚሁ ምክንያት ማረካከብ አልተቻለም። በፀጥታ አካላት እየተፈለገ ሲሆን ያለበትን የሚያዉቅ ማንኛዉም አካል አቅራቢያ ላለ ፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ እናሳስባለን።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተገቢዉን ሕጋዊና ሰላማዊ አካሄድ አሟጦ እየተጠቀመ ሲሆን፤ ከዚህ ቡኃላ የፀጥታ አካሉ ሕግና ስርዓትን የማስፈጸም ስራዉ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል።

በዛሬዉ እለት በመስጂዱ ቅጥር ጊቢ ከፈጅር ሶላት ጀምሮ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር የተዘጋጁ ወጣቶች መኖራቸዉ የታወቀ ሲሆን የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፀጥታ አካሉ ጋር በመምከር በከተማዉ እንብርት ላይ ረብሻ ፈጥሮ ገፅታን የማበላሸት እቅድ በመሆኑ ይህንኑ የማምከን ስራ ተሰርቷል።

የሁከትና ብጥብጥ ጥንስሱና በማን እንደሚመራ በግልጽ ታውቋል። አላማዉና መስመሩ በገሀድ የታየ በመሆኑ የፀጥታ አካሉ የተናጥል እርምጃ በመውሰድ ሕግና ስርዓትን እንደሚያስከብር እሙን ነው።

ሙጂብ አሚኖ



https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
https://t.me/fethmedia
96 views10:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 09:18:21
#በሂጅራ የቀን መቁጠሪያ ማስታወሻ
#አልአሃድ 15 #ጀማዱል አኽር 1444 ሂ
103 views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 09:17:43
101 views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ