Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.12K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-06-12 13:11:10
ሌተናል ጄነራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ፡፡

ሌተናል ጄነራል ይልማ የቀድሞ የአየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቄን በመተካት ነው የአየር መንገዱ ቦርድ ሰብሳቢነት የተሾሙት፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.3K viewsedited  10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 12:30:31
የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ሞተዋል የሚለውን ዜና አስተባብለዋል፡፡

የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ እሁድ ምሽት በትዊተር ገፃቸው ከኮቪድ 19 ጋር በተገናኘ ለቀናት ራሳቸውን ማግለላቸውን አሳውቀዋል፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ መግለጫቸው በኮቪድ-19 መያዛቸውን ተከትሎ ህይወታቸው አለፈ መባሉን አስተባብለዋል፡፡

ሙሴቬኒ በፈረንጆቹ ሰኔ 7 በቫይረሱ መያዛቸውን እና ራሳቸውን ማግለላቸውን አሳውቀዋል፡፡

"ሰላም፣ አሁን የኮሮና ሁኔታዬ አምስት ቀን ሆኖታል፣ ትላንት ምሽት እስከ ሌሊቱ 10 ሰአት ድረስ በደንብ ተኝቻለሁ" ሲሉ የዩጋንዳው መሪ በረዥሙ የትዊተር ጹሁፋቸው አስፍረዋል፡፡

ኡጋንዳውያን ለኮቪድ ክትባት እና ለተጨማሪ ክትባቶች በተለይም ለአረጋውያን ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል፡፡

ሙሴቬኒ ወደ ከፍተኛ ህክምና መወሰዳቸው እና መሞታቸውን በትዊተር ላይ ባለፉት ጥቂት ቀናት ሲዘዋወር ሰንብቷል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት ባለፈው ወር ኮቪድ-19 በይፋ ከአሁን በኋላ የአለም የጤና ድንገተኛ አደጋ እንዳልሆነ ገልጾ፣ ቫይረሱ ግን ባህሪውን መለዋወጡን ቀጥሏል ማለቱን ቢቢሲ አፍሪቃ ዘግቧል፡፡

በያይኔአበባ ሻምበል
ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.4K views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 12:05:07
የቀድሞዉ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲልቪዮ በርሉስኮኒ በ 86 ዓመታቸዉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የቀድሞ የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሲርቪዮ ቤርሌስኮኒ በደም ካንሰር ምክንያት በ86 አመታቸው በሞት መለየታቸው ታውቋል፡፡

ከሳምታት በፊት ሆስፒታል ገብተው የነበሩት ስሊቪዮ ቤርሌስኮኒ እየታከሙበት በነበረው ሳን ራፋኤል ሆስፒታል መሞታቸው ተዘግቧል፡፡
ቤርሌስኮኒ የጣሊያን ሴርኤ ላይ የሚገኝው የኤሲሚላን ባለቤት የነበሩ ሲሆን ከአመታት በፊት ክለቡን ለሌላ ባለሃብት መሸጣቸው ይታወሳል፡፡

በርካታ ካምፓኒዎች እና ድርጅቶች በስማቸው እንዳላቸው ይታወቃል፡፡
በአወዛጋቢነታቸው የሚታወቁት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ቤርሌስኮኒ ለሶስት ተከታታይ አመታት ጣሊያንን በጠቅላይ ሚኒስትርነት አገልግለዋል፡፡

ቢሊዮነሩ በርሉስኮኒ ጣሊያንን ከፈረንጆቹ 1994 እስከ 2011 በጠቅላይ ሚንስትርነት አገልግለዋል፡፡

(በእስከዳር ግርማ)

አርቲ ኒዉስ

ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.2K viewsedited  09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:46:04
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ማለዳ ጅቡቲ ገብተዋል፡፡


የኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎች “ወሳኝ” የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመገኘት በጅቡቲ እየተሰባሰቡ ነው፡፡

የኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎች ለ14ኛው የኢጋድ የመሪዎች ጉባኤ በጅቡቲ ዋና ከተማ ጅቡቲ ተገናኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ማለዳ ጅቡቲ ገብተዋል፤ ኤርትራ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ ኦስማን ሳሌህ ተወክላለች፡፡


በጉባኤው መሪዎቹ የቀጣናውን ሰላም፣ ደህንነት እና ልማት በሚመለከቱ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ይጠበቃል፡፡

የኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኤርትራ እና ሌሎች የኢጋድ አባል ሀገራት መሪዎችን ያሳተፈዉ ጉባኤ የአፍሪቃ ህብረት፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የአውሮፓ ህብረት እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮችን እንደሚያስተናግድም ተሰምቷል፡፡

ልዑካኑ በአባል ሀገራቱ መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር፣ ክልላዊ ውህደትን ማጎልበት፣ ሰላምና መረጋጋትን ማስፈን፣ የኢኮኖሚ እድገትና ማህበራዊ ልማትን ማጎልበት በሚቻልባቸው ስትራቴጂዎች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ክልሉ በግጭቶች እና ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊ አለመረጋጋቶችን ጨምሮ ከበርካታ ተግዳሮቶች ጋር እየታገለ ባለበት ወቅት የሚደረግ ጉባኤ በመሆኑ “ወሳኝ” ነው ሲል ኦል አፍሪቃ ዘግቧል።

በያይኔ አበባ ሻምበል

ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.1K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 11:07:17 ከፍተኛ መጠን ያለው የዕርዳታ ምግብ እንደተመዘበረ ማረጋገጡን የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት አስታወቀ፡፡

የአሜሪካ መንግሥት የዓለም አቀፍ ልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ)፣ ባደረገው የምርመራ ውጤት ከፍተኛ መጠን ያለው የዕርዳታ ምግብ አቅርቦት ምዝበራ መፈጸሙን በማረጋገጡ፣ በኢትዮጵያ የሚያደርገውን ዕርዳታ እንዳቆመ አስታውቋል፡፡

ውሳኔውም አስቸኳይ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሃያ ሚሊዮን ዜጎችን እንደሚጎዳ ነው የተገለጸው፡፡ድርጅቱ እንደገለጸው፣ በፌዴራልና በክልሎች መንግሥታት አማካይነት ወታደራዊ ክፍሎች ከሰብዓዊ ዕርዳታው ተጠቃሚ ነበሩ ብሏል፡፡

ዩኤስኤአይዲ ባደረገው ምርመራ ደርሼበታለሁ እንዳለው ከሆነ፣ ባለሥልጣናት ለተረጂዎች ተብሎ የቀረበን የዕርዳታ ምግብ ወታደራዊ ኃይሎችንና የቀድሞ ተዋጊዎችን ለመመገብ ከመዋላቸው በተጨማሪ፣ ዱቄቱን ወደ ውጭ ለሚልኩ ድርጅት በግልጽ ገበያ ቀርቦ እንዲሸጥ ማድረጋቸውን አረጋግጫለሁ ማለቱን የሪፖርተር ዘገባ ያመለክታል፡፡

ይህን ተከትሎ የኢፌዴሪ መከላከያ ሚንስቴር ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቁልፍ እሴት ከሆኑት ቀዳሚውና ዋናው ከራስ በፊት ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መቆም መሆኑን አስምሮበታል፡፡
(USAID) ሰሞኑን አጣርቻለሁ ብሎ ባወጣው መግለጫ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣን እህል ከሌሎች መንግስታዊ አካላት ጋር በመሆን፣ መከላከያ ሰራዊታችንም እንደተጠቀመ አድርጎ ያቀረበውን ሪፖርት የተለያዩ ሚዲያዎች ሲዘግቡት ተመልክቻለሁ ብሏል፡፡



ይሁንና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በጥብቅ ድስፕሊን የሚመራ ዘመናዊ ሰራዊት ነው ያለው መግለጫው ፣ ሰብዓዊ ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖቹን ቀለብ ሊቀማ ቀርቶ፤ ከቀለቡ ቀንሶ የሚያካፍል ሰራዊት መሆኑን የሃገሩ ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሰላም ማስከበር በተሰማራባቸው ቦታዎች ሁሉ የዕለት ከዕለት ተግባሩ መሆኑን የደረሰላቸው ህዝቦች፤ መንግስታት እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሁሉ የሚያውቁት ሰመ ጥር ህዝባዊ ሰራዊት ሲል ገልጧል፡፡


የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት በቂ ሎጄስቲክ ያለው በዓለም አቀፍና በአገር ውስጥ ለተፈናቀሉትና በድርቅ ለተጎዱት፣ በዓይነትና በገንዘብ የሚረዳ እንጂ ተቸግሮ ከአሰራር ውጭ የሚጠቀም አለመሆኑም ሊታወቅ ይገባል ብሏል፡፡



ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.1K viewsedited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:43:58
በወልቂጤ ከተማ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የትራንስፖርት ስምሪት አሰጣጥ ስርአት (ኢ_ቲኬቲንግ) ተጀምሯል።

ህብረተሰቡ ከታሪፍ በላይ እንዳይከፍል፣ ተሳፋሪን ከእንግልት የሚታደግ ፣ትርፍ እንዳይጫን የሚያደርግ እና ዘመናዊ መናኸርያ እንዲፈጠር የጎላ ሚና ይኖረዋል የተባለለት አዲስ ቴክኖሎጂ መጀመሩ ታውቋል።

ቴክኖሎጂው ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ከመስጠቱ በተጨማሪ ሙሉ የመኪና መረጃዎችን የሚያሳውቅ ነው ተብሏል።

በወልቂጤ ከተማ የተጀመረው ይህ ቴክኖሎጂ(ኢ_ቲኬቲንግ) በደቡብ ክልል የመጀመርያው ነው።

የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ሲስተም አስተባባሪ አቶ ቢኒያም ፈቃዱ፣ ቴክኖሎጂው ለህብረተሰቡ በታሪፉ ልክ ቲኬት መቁረጥ፣ለመኪናዎች መውጫ መስጠትና ቅደም ተከተል የማሰያዝ ስራ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ቴክኖሎጂውን በተመለከተ ከአሽከርካሪዎች ማህበር፣ ከትራፊክና ከፖሊስ መዋቅሮች ጋር ውይይት ተደርጎ መግባባት ላይ ተደርሷል መባሉን ሄኖክ ወ/ገብርኤል ዘግቧል፡፡

ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.1K views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:42:02

2.0K views07:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 10:36:56
በ2016 በጀት ዓመት ሁሉንም ዩኒቨርስቲዎች ወደ ኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓት እንዲገቡ ይደረጋል ተባለ፡፡

በፀጥታ ችግር ሳቢያ ከመደበኛ አገልግሎታቸው ተስተጓጉለው ከነበሩ ዩኒቨርስቲዎች ውጪ ያሉት ዩኒቨርስቲዎች ፣ወደ ኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓት እንዲገቡ እንደሚደረግ የመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል።

እስካሁን 44 ከሚሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓትን ተግባራዊ ያደረጉት ሁለቱ ብቻ መሆናቸውንም የባለስልጣኑ የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አበበ አለሙ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ገልፀዋል፡፡

እነዚህም የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ መሆናቸውን ያስታወቁት ሃላፊው፣ በቀጣይ ቀሪ ዩኒቨርስቲዎችን በስርዓቱ እንዲካተቱ ይደረጋል ብለዋል፡፡

በሌሎች አገልግሎቶች የተሰማሩ ተቋማት 74 የመንግስት ተቋማት በኤሌክትሮኒክስ የግዢ ስርዓት ውስጥ እንደተካተቱም አቶ አበበ ገልፀዋል፡፡

በረድኤት ገበየሁ

ሰኔ 05 ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
2.4K views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 12:19:29
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባሕር ዳር ገቡ

በአቶ ጌታቸው ረዳ የተመራው ልዑክ ባሕር ዳር ከተማ መግባቱን ኢትዮ ኤፍ ኤም ከአማራ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ አረጋግጧል ።

የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ባሕር ዳር ሲደርሱ በአማራ ክልል ፕሬዚዳንት በዶክተር ይልቃል ከፋለ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የትግራይ ክልል ልዑክ በባሕር ዳር ከተማ በሚኖረው ቆይታ በሁለቱ ክልሎችና የህዝቦች ግንኙነት ዙሪያ ይመክራሉ ተብሏል።

በአባቱ መረቀ
3.1K views09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 00:00:05
በቱርክ አታቱርክ ስታዲየም የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ፍፃሜ

ማንቸስተር ሲቲ 1 - 0 ኢንተር ሚላን ጨዋታው ተጠናቋል።
1.1K views21:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ