Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.12K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-05-10 10:56:47 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.6K views07:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 14:13:47 Ethio Fm 107.8 pinned a photo
11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 14:13:39
2.9K views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 11:43:00 ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል ተባለ፡፡

ኢትዮጵያ ማር ለማምረት የሚያስችል ያላትን ከፍተኛ ጸጋ በሚገባ እየተጠቀመች እንዳልሆነ ተነግሯል፡፡

ሃገሪቱ በአመት 500 ሚሊዮን ቶን ማር የማምረት አቅም ቢኖራትም እያመረተች ያለችው ግን 10 በመቶ ብቻ ነው ተብሏል፡፡
ይህም ሆኖ የምትመረተዋ አነስተኛ የማር ምርት በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ እየወጣች መሆኑን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል፡፡

በተለያዩ የሃገሪቷ አካባቢዎች ገበሬዎች የሚያመርቱት የማር ምርት በትክክለኛው መንገድ ወደ ገበያ እየቀረበ ባለመሆኑ እና በኮንትሮባንድ ወደ ውጭ ስለሚወጣ ሃገሪቷን ገቢ እያሳጣት ይገኛል ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት ምክትል ዳሬክተር አቶ ታሪኩ ተካ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ደላሎች አዛዥ በሆኑበት የማር ምርት ሃገሪቱ ማግኘት የሚገባትን ገቢ እንዳታገኝ አድርጓታል ብለዋል፡፡
የማር ምርት እና ግብይትን የሚመለከት መመርያም ሆነ አዋጅ ባለመኖሩ፣ የማር ምርት እና ግብይት አደጋ ላይ ወድቋል ሲሉም አክለዋል፡፡


ከዚህ በፊት ኢንስቲትዩቱ ለዘርፉ መመርያ እና አዋጅ እንደሚያስፈልገው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቦ እንደነበረ አስታውቆ፣ በምን ደረጃ ላይ እንደረሰ አይታወቅም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ይህ አለመፈጸሙ ደግሞ በግብይት ሂደቱ ላይ አሉታዊ ጫና እያደረሰ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በንብ ሃብት ኢትዮጵያ ከዓለም አስረኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ ቀዳሚ ብትሆንም የምታገኘው ገቢ ግን እጅግ አነስተኛ እንደሆነ አቶ ታሪኩ አንስተዋል፡፡
የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግም ሆነ ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ህገ-ወጥ የግብይት ሰንሰለቱም መቁረጥ እንደሚገባም ጠቅመዋል፡፡

በሔኖክ ወ/ገብርኤል

ግንቦት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
3.0K viewsedited  08:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 10:50:33
ከ40 ሺ በላይ ሰዎች የአስተዳደር በደል ተፈጽሞብናል ሲሉ ቅሬታ አቀረቡ።

በ2015 ባለፉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ከ 40 ሺ በላይ አቤቱታዎች ቀርበውልኛል ሲል የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ለኢትዮ ኤፍኤም አስታውቋል።

40 ሺ 486 ሰዎች ከስራ፣ ከጡረታ፣ ከይዞታ፣ከካሳ ጥያቄ ከአገልግሎት ማጣት እና በሌሎም ጉዳዮች ላይ የአስተዳደር በደል ተፈፅሞብናል በማለት ነው ቅሬታቸውን ለተቋሙ ያሰሙት።

ተቋሙ በዚህ ዙሪያ ያደረገውን ምርመራ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ያስታወቀ ሲሆን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ምርመራ እንዲደረግባቸው ከተመረጡ 1 ሺ 174 አቤቱታዎች ውስጥ 741 አቤቱታዎች እልባት ማግኘታቸው ተነግሯል፡፡

ቀሪ 433 መዝገቦች ምርመራቸው ባለመጠናቀቁ በሂደት ላይ ይገኛሉ ሲል ተቋሙ አስታውቋል::

የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ፤ ተቋሙ የማይመለከተውን አቤቱታ የመመርመር ግዴታ እንደሌለበት እና
በፍርድ ቤት የታዩ የወንጀል ጉዳዮች እንዲሁም በግል ድርጅቶች ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች በተቋሙ ስልጣን ስር የማይወድቁ መሆናቸውንም ገልፃል፡፡

ወደ ተቋሙ የሚመጡ አቤቱታዎች ሲኖሩም ደረጃቸውን ጠብቀው መቅረብ ይኖርባቸዋል ያለው ተቋሙ ደረጃቸውን ጠብቀው ካልቀረቡ ምርመራ እንደማያካሄድባቸው አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በዜጎች ላይ የሚደርሱ አሰተዳደራዊ በደሎችን የመመርመርና ውሳኔ ሃሳብ የመስጠት ሃላፊነት ያለበት ተቋም ነው፡፡

በየውልሰው ገዝሙ
ግንቦት 01 ቀን 2015 ዓ.ም
2.6K views07:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 10:45:59 የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶች ዲጂታል መታወቂያ ለመውሰድ ፍላጎት እያሳዩ አይደለም ተባለ::


በአዲስ አበባ በአሽከርካሪ ተሽከርካሪ ፍቃድ እና ቁጥጥር ባለስልጣን ተመዝግበው የሚገኙ 18ሺህ እና በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ጂፒኤስ አስገጥመው የተመዘገቡ 11ሺህ የሚጠጉ የሞተር ብስክሌቶች መኖራቸውን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጀመንት ኤጀንሲ የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኩማ ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥ 2 ሺህ የሚሆኑት ብቻ ናቸው ዲጂታል መታወቂያውን ያስቀየሩት ብለውዋል።
የተለያዩ ወንጀሎችን ለመፈፀም አመቺ የሆነውን ቀድሞ ለመንቀሳቀስ ሲጠቀሙበት የነበረው ወረቀታቸው የአብዛኞቹ ፎርጂድ( ህገ-ወጥ ) መሆኑንም ነግረውናል።


ለዚህም ወደ ዲጂታል ሲቀየር ከዚህ ቀደም ወንጀል ሰርተው የተመዘገቡትን እና አዲስ የህግ ጥሰት የተጠቆመባቸውን በቀላሉ አጣርቶ በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።

ነገር ግን አብዛኛዎቹ ሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች በፎርጅድ እየተንቀሳቀሱ በመሆኑ፣ ወደ ዲጂታል ለመምጣት ፍላጎት እያሳዩ አለመሆኑን ለጣቢያችን ተናግረዋል።
መታወቂያው ጂፒኤስ ያስገጠመ እና ያላስገጠመን የሚለይ ፣ የመንቀሳቀሻ ፈቃዱ ህገ-ወጥ ነው ኦርጂናል የሚለውን ጨምሮ የታደሰ ነው ያልታደሰ እንዲሁም ከዚህ ቀደም የህግ ጥሰት ፈፅሟል አልፈፀመም የሚለውን የሚለይ ነው ሲሉ አቶ ብርሃኑ ነግረውናል።

ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ግንቦት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የቀድሞ መታወቂያቸውን በዲጂታል እንዲያስቀይሩ የተራዘመ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ከግንቦት 10 በኋላ ግን ቁጥጥር ይጀመራል ብለዋል።

በረድኤት ገበየሁ
ግንቦት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.6K viewsedited  07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 12:01:26 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
3.3K views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 15:24:49
አንድ ነጥብ አምሰት ቢልየን ብር የፈጀው ስቴይ ኢዚ ፕላስ ሆቴል ሥራ መጀመሩን አስታወቀ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው ስቴይ ኢዚ ፕላስ ሆቴል ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት ተመርቆ ወደ ሥራ ገብቷል።


የሆቴሉ ግንባታ ከአንድ ነጥብ አምስት ቢልየን ብር በላይ እንደፈጀ ባለቤቶቹ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።


ሆቴሉ አሁን ላይ በአጠቃላይ ከ 250 ዜጎች በላይ የስራ ዕድል እንደፈጠረም ታውቋል።

የኤሌትሪክ መኪና ይዘው ለሚመጡ ደንበኞቹ ኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ ቦታ እንዳለውም በመግለጫው ተነስቷል።

በተጨማሪም ሆቴሉ የሚጠቀመውን የከርሰ ምድር ውሃ ለአካባቢው ነዋሪዎች ውሃ በነፃ እያደለ መሆኑም ተጠቅሷል።

በቅርቡም ለአካባቢው ነዋሪዎች ዳቦ በተመጣኝ ዋጋ ያቀርባል ተብሏል።

በአባቱ መረቀ

ሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast
Website https://ethiofm107.com/
ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።
ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
4.2K views12:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 11:32:54
ሬናሰንት የተሰኘ የአዕምሮ ጤና እና የሱስ ተሃድሶ ማዕከል ተመርቋል።

በሱስ እና የአዕምሮ ጤና ችግሮች ዙሪያ መፍትሄ ለመሆን በሱስ የስነልቦና ባለሙያዎች ፣ በኤክስፐርት የስነልቦና ባለሙያዎች እና በስነልቦና ነርስ ባለሙያዎች አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋመው ማዕከል ነው በትናንትናው እለት በይፋ የተመረቀው።

ማዕከሉ አገልግሎቱን መስጠት ከጀመረ ጥቂት ወራትን ያስቆጠረ ነው ያሉት የማዕከሉ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ፕሮፌሰር ሰለሞን ተፈራ ናቸው።

ፕሮፌሰሩ ማዕከሉ አገልግሎት መስጠት በጀመረበት አጭር ጊዜ ውስጥ ከመቶ በላይ ተገልጋዮች ተኝተው ህክምና ያገኙ መሆናቸውን ገልፀው ፣ አብዛኞቹ እድሜያቸው ከ30 አመት በታች የሆኑ ወጣቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እና የሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተገኝተዋል።

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ የእንደዚህ አይነት ማዕከላት መገንባት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ሙሉ ድጋፍ የሚያገኝ እና ሌሎች ተመሳሳይ ማዕከላት እንዲገነቡም መንገድ የሚከፍት ነው ብለዋል።

ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ በበኩላቸው እንደ አገር ወደ ሶስት ሺህ የሚጠጉ የወጣት ማዕከላት መኖራቸውን አንስተው ትናንት ከተመረቀው ማዕከል ጋር በጋራ መስራት እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

በ2007 ዓ.ም በተደረገው እና በአገር አቀፍ ደረጃ ከ10ሺህ ሰዎች በላይ የተሳተፉበት ጥናት፣ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆኑት እድሜያቸው ከ15-65 የሆኑ ወንዶች የአልኮል ሱሰኞች ነበሩ ተብሏል፡፡
16 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ የጫት ሱስ እና 5 በመቶ የሚሆኑት የትምባሆ ሱሰኞች እንደነበሩ ጥናቱ ያሳያል።

በእስከዳር ግርማ
ሚያዝያ 28 ቀን 2015 ዓ.ም
3.9K views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-05 12:44:08
ሙዚቀኛው ዳዊት ፍሬው ሀይሉ በአረፈበት ሆቴል ሞቶ ተገኘ
...
በመሳሪያ የተቀነባበሩ አልበችሞን በማሳተም እንዲሁም በርካታ መድረኮች ላይ የሙዚቃ መሳሪያ በመጫዎት ከፍተኛ አድናቆትን ያተረፈው የአንጋፋው ድምፃዊ ጋሽ ፍሬው ሀይሉ ልጅ ሙዚቀኛው ዳዊት ፍሬው ለስራ በሄደበት ጣሊያን ሮም ትላንት ምሽት በአረፈበት ሆቴል ተነግሯል ።

ሙዚቀኛው በኢትዮጵያ ኤምባሲ በጣሊያን ሮም ከተማ ስራዎቹን አቅርቦ ወደ አረፈበት ሆቴል ከገባ በኋላ ምክንያቱ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ማረፉን የጣሊያን ፖሊሶች ተናግረዋል።

በጣሊያን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እና የሞያ አጋሮቹ ከሀገሪቱ ፖሊስ ጋር ተነጋግረው የአርቲስቱን አስክሬን በሀገሩ ለማሳረፍ እንቅስቃሴ መጀመራቸውም ታውቋል::

ዳዊት ፍሬው የክላርኔት የሙዚቃ መሳሪያውን እየተጫወተ የሰራው ሶስት የሙዚቃ አልበም ያለው ሲሆን የአንጋፋው ድምፃዊ ፍሬው ሀይሉ ልጅም ነው።
3.9K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ