Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Fm 107.8

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8 E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiofm107dot8 — Ethio Fm 107.8
የሰርጥ አድራሻ: @ethiofm107dot8
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.32K
የሰርጥ መግለጫ

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

3

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 12

2023-04-27 11:22:02
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ስርቆት በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ የሚወሰደው የቅጣት እርምጃ ሊሻሻል ይገባል ተባለ

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ስርቆት እና ውድመት የሚፈፅሙ አካላት መረጃ  እና ማስረጃዎች ተገኝቶባቸው ለህግ ቢቀርቡም የሚወስደው የህግ እምጃ  ከሚያደርሰው ጉዳት አንፃር ተመጣጣኝ  እንዳልሆነ  የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን ዳይሪክተር መላኩ ታዪ ለኢትዮኤፍኤም ተናግረዋል።

ከ60 እስከ 70 በመቶ የሚሆነው የኤሌክትሪክ  መሰረተ ልማት ግብአት ከውጭ በምንዛሬ በከፍተኛ በጀት ወደ ሀገር የሚገባ ሲሆን ፤ለደንበኞች  አስተማማኝ  አገልግሎት ለማድረስ እና ተደራሽነትን ለማስፋት ለሚደረገው ጥረት በሀገር ሀብት ላይ የሚደርሱ ስርቆች እና ውድመት እንቅፋት እንደሆነ ገልፀዋል።


በኢነርጂ አዋጁ ላይ እንደተቀመጠው ማንኛውም በመሰረተ ልማት ላይ ውድመት ያደረሰ አካል ከአምስት አመት እስከ 25 አመት ድረስ ሊቀጣ እንደሚገባ ይደነግጋል ያሉት ዳይሪክተሩ፤ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ውድመት እና ስርቆት የሚፈፅሙ አካላት በዋስ  እንዲሁም  አነስተኛ ፍርድ ሲፈረድባቸው ለሌሎች አስተማሪ አይደለም ብለዋል።


ህብረተሰቡም  የመሰረተ ልማቱን እንደ ግል ሀብቱ ተመልክቶ በዚህ እኩይ ተግባር ላይ እሚሳተፉ አካላትን ለህግ የማቅረብ ስራ ላይ ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል።

እሌኒ ግዛቸው
ሚያዝያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም
3.4K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:20:48
ከሃሰተኛ ሰነድ ጋር በተያያዘ  በሚመጡ ዛቻ እና ማስፈራሪያ መቸገሩን የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ

ከሃሰተኛ ሰነድ ጋር በተያያዘ  ወደ ፍርድ ቤት ደርሰው በዋስትና ከሚወጡ ሰዎች መካከል  በሚመጡ ዛቻ እና ማስፈራሪያ  መቸገሩን  የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ  የሆኑት አቶ መኑር መሃመድ  ለኢቲዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

እንደ ሀላፊው ገለጻ ከሃሰተኛ ሰነዶች ጋር በተያያዘ  ክትትል እና  ፍተሻ  ሲደረግ እንደሚገኙ ና ተጠርጣሪ  ሰዎችን ወደ ህግ ወስዶ ጉዳዩ ላይ ወሳኔ እስኪሰጠው ክትትል የማድረግ ስራ እንደሚሰሩም  አቶ መኑር ነግረውናል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ  ፍርድ ቤት በፍትህ ሂደቱ አንድ ሰው ወንጀለኛ  መሆኑ እስካልተረጋገጠ ድረስ  የሚታሰርበት  መንገድ እንደሌለ አስታውሰው ሰዎቹ በዋስትና ሲለቀቁ የማስፈራራት እና ዛቻ መሰል ጉዳዮች  እየመጡ  ተቸግረናል ስራችንንም እየረበሸው ነው ብለዋል፡፡

ረድኤት ገበየሁ
ሚያዝያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
3.1K viewsedited  08:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:15:27 በአዲስ አበባ ከ2ሺ 600 በላይ ግለሰቦች ያለመንጃ ፍቃድ ሲያሽከረክሩ መገኘታቸው ተገለፀ፡፡

በአዲስ አበባ ያለመንጃ ፍቃድ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እየተበራከቱ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዘጠኝ ወራት ውስጥ በዚህ ላይ የተገኙ ከ2ሺህ 638 በላይ ግለሰቦች ያለመንጃ ፍቃድ ሲያሽከርክሩ በመገኘታቸው ቅጣት ተላልፎባቸዋል ተብሏል፡፡

በአዲስ አበባ ፖሊስ ትራፊክ ቁጥጥር መመሪያ የትራፊክ ሙያና ህዝብ ግንዛቤ ዲቪዥን ሀላፊ የሆኑት ኢንስፔክተር ሰለሞን አዳነ ለጣብያች በሰጡት ቃል በዘጠኝ ወራት ውስጥ በርካታ የደንብ መተላለፎች ያጋጠሙ ሲሆን  የአሽከርካሪ ማረጋገጫ ብቃት ሳይኖራቸው የሚያሽከረክሩ ግለሰቦች መበራከታቸውን ገልፀዋል፡፡

ኢኒስፔክተር አዳነ አክለውም በዚህ ዘጠኝ ወራት ውስጥ 320 በሀሰተኛ መንጃ ፍቃድ ሲያሽከርክሩ የተያዙ ግለሰቦች ላይ ክስ እንደተመሰረተባቸው ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

ሁሉም የትራፊክ ደንብ መተላለፎች የትራፊክ አደጋ የሚያስከትሉ ቢሆንም ዋና የሚባሉት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በከተማዋ ስልክ እያወሩ የሚያሽረክሩ በርካቶች አሉ ያሉት ኢንስፔክተር ሰለሞን በዚህ ዘጠኝ ወር ውስጥ ብቻ 73ሺህ 490 አሽከርካሪዎች ስልክ እያወሩ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ሲሆን 81 ሺህ የሚሆኑ ደግሞ ያለደህንነት ቀበቶ ሲነቀሳቀሱ በመገኘታቸው ቅጣት ተላልፎባቸዋል ተብሏል፡፡

አቤል ደጀኔ
ሚያዝያ 19 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.5K views08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:11:45 የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
2.6K views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 15:22:35 80ሚሊዮን ብር በኤልክትሮኒክስ ስርአት ተዘዋውሯል፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር የነዳጅ ግብይት በኤልክትሮኒክስ ስርአት ካስጀመረበት ሰአት አንስቶ እስካሁን ድረስ 80 ሚሊዮን ብር ግብይት መፈጸሙን አስታወቀ፡፡

የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ የክፍያ መንገድ እንዲሆን ከወሰነበት እለት ጀምሮ ከ43ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች መስተናገዳቸውን ገልጻል፡፡

የሚኒስትሩ የታለመለት የነዳጅ ድጎማ ስርአት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሳልማን ሞሃመድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት ከኢትዮ ቴኮም ጋር በመተባበር የነዳጅ ግብይት በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል፡፡

ገና ጅምር ላይ በመሆኑ የተወሰኑ ችግሮች ሊያጋጥሙ ግድ ይላል ያሉት አቶ ሳልማን በሂደት ሁሉም ይስተካከላል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ተጠቃሚዎች ወደ ነዳጅ ጣበያዎች ሲመጡ እንደ ሞባይል ባንኪንግ የመሰሉ የኤልክትሮኒክስ ስርአት የሚያስጠቅሙ መተግበርያዎችን ዳወን ሎድ በማድረግ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ ተብሏል፡፡

በአንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ላይ ፍቃደኝነት ይጎላል ያሉት አቶ ሳልማን ነዳጅ ማደያዎች በመንግስት በኩል የተላለፈውን ውሳኔ ሊያከብሩ ግድ ይላል ብለዋል፡፡

ሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
3.2K views12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 14:37:38
ኢትዮጵያ ከግጭት በኋላ የምታደርገውን መልሶ ግንባታ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የኢትዮጵያ መንግስት ለአገሪቱ ሰላም ሂደት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ክብር ለመስጠት አዲስ አበባ ላይ የዕውቅና ዝግጅት ማካሄዱ ይታወሳል ፡፡

የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ቀንድ ጉዳዮች ልዩ መልዕክተኛ ሹዌ ቢንግ በዝግጅቱ ላይ ተገኝተው ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የእውቅና ሰርተፍኬት ተቀብለዋል ።

ኢትዮጵያ ካለፈው ዓመት ህዳር ወር ጀምሮ የውስጥ ውዝግቧን ገታ አድርጋ የሰላም ሂደት መጀመሯ ጥሩ መሻሻል መሆኑን የጠቀሱት ቃል አቀባይ ማኦ ኒንግ ‹‹ይህ የአንድነት ድል ነው›› ብለዋል።

በተጨማሪም በኢትዮጵያ ተቀናቃኝ ወገኖች መካከል የሚደረግ ውይይት የሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ጥቅም የሚያስከብር እንደሆነ አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ቁልፍ ሚና እንደምትጫወት የገለጹት ማኦ ሰላም ያላት እና የተረጋጋች ኢትዮጵያ ለቀጠናው ዘላቂ ሰላምና ደህንነት ትልቅ ፋይዳ አላት ብለዋል ሲል ዥንዋ ዘግቧል ።

"ቻይና ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድቷን ለማስጠበቅ የምታደርገውን ጥረት በጽኑ ትደግፋለች። ከዚሁ ጎን በድርድር ሰላም ለማምጣት እና መግባባትን ለመፍጠር በንቃት ስንሰራ ቆይተናል" ብለዋል ማኦ።

ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
3.0K viewsedited  11:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 14:13:39
ሩሲያ የአዉሮፓ ህብረትን አስጠነቀቀች

ሞስኮ የአዉሮፓ ህብረት የጦር ጎራ ከመሆን ሊታቀብ ይገባል ስትል አስጠንቅቃለች፡፡

የሩሲያዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ የአዉሮፓ ህብረት እራሱን ወደ ጦር ጎራ እየለወጠ ነዉ ሲሉ በኒዮርክ በነበረ መድረክ ላይ ተናግረዋል፡፡

ህብረቱ እራሱን የጦር መሳሪያ እያስታጠቀ ለሩሲያ ስጋት እየሆነ እንደመጣም የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አስታዉቀዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜ በአዉሮፓ ህብረትና በኔቶ መካከል የተወሰነ ልዩነት ብቻ እንዳለም ላቭሮቭ አንስተዋል፡፡
በመሆኑም ህብረቱ ወደ ጦር ጎራነት ከመለወጠ እንዲታቅብ ሲሉ አሳስበዋል፡፡

የአዉሮፓ ህብረት አባል ሀገራትና የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት ኔቶ መስፋፋታቸዉን እንዳልገቱም ሞስኮ ገልጻለች፡፡

ለዚህም ላቭሮቭ እንደማሳያ ያነሱት የፊንላንድንና የስዊዲንን የአባልነት ጥያቄ ነዉ ሲል የዘገበዉ አልጄዚራ ነዉ፡፡

አባቱ መረቀ
ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
2.6K views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 14:10:38
በከተማዋ 80 በመቶ የመኪና አደጋ እግረኞች ላይ የሚደርስ ነዉ ተባለ።

ከ2009 ዓ.ም  ጀምሮ በትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስተባባሪነት የ13 ዓመት የመንገድ ደህንነት ስትራቴጂ በመንደፍ በከተማዋ ከንቲባ የሚመራ የመንገድ ደህንነት ምክር ቤት መቋቋሙ የሚታወስ ነዉ።

የ2015 በጀት ዓመት የ6ወራት የትራፊክ አደጋ መረጃ  በብሉምበርግ ኢኒሼቲቭ አስተባባሪነት የመረጃ ትንተና ተካሂዷል።

ወ/ሮ ሜሮን ጌታቸዉ  በብሉምበርግ ኢኒሼቲቭ የዳታ ትንተና ባለሙያ እንደገለፁት ከሆነ 703ሺህ የተመዘገበ ተሽከርካሪ በከተማዋ ይገኛል ብለዋል።

በከተማዋ ከሚፈፀሙ የመኪና አደጋዎች 80 በመቶ የሚሆነዉ ደግሞ እግረኞች ላይ ነዉ ብለዋል።

ከሚያጋጥሙ የሞት አደጋዎች 78 በመቶ ወንድ ሲሆን 22 በመቶ የሚሆነዉ የሞት አደጋ ሴቶች ላይ የሚያግጥም መሆኑን ተገልፃል።

ጥናቱ በከተማዎ 20 የተለያዩ  አደጋ የሚያግጥማቸዉ ቦታዎችን ለይቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበዉ ሚደቅሳ  በከተማዋ በስድስት ወራት ዉስጥ 211 ሰዎች ህይወት በመኪና አደጋ ማለፉን ገልፀዉ ከሞቾች ዉስጥም በአብዛኛዉ ከ20 እስከ 49 ዕድሜ ክልል ያሉት ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

የመንገድ ደኅንነት ምክር ቤቱ  የምክር ቤቱ አባላት፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ አጋር ድርጅቶች፣አርቲስቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው ባለድርሻ አካለት በተገኙበት ተካሂዷል፡፡

አቤልደጀኔ
ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
2.3K views11:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 14:06:48
በኢትዮጵያ ተላላፊ ባልሆኑ ህመሞች ህይወታቸው የሚያጡ ዜጎች የሞት ምጣኔ 43 በመቶ መሆኑ ተነገረ

ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች በዜጎች ጤና እና ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በጤና ልማትና ፀረ ወባ ማህበር አማካኝነት ለሚዲያ ባለሞያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተከናውኗል ።

በስልጠናውም ጤናማ ያልሆነ አመጋገብን በተመለከተ የተለያዩ የዳሰሳ ጥናቶች ቀርበዋል፤ በሀገራችን ስድስት በመቶ የሚሆነው ሞት ጤናማ ካልሆነ አመጋገብ ጋራ በተያያዘ እንደሚከሰት በጤና ሚንስትር ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች ባለሞያ የሆኑት ዶክተር ሙሴ ገብረሚካኤል ተናግረዋል።

በ15 አመታት ውስጥ የጨው ይዘት ቅነሳ ላይ ካልተሰራ የ455 ሺህ ሰዎች ህይወት አደጋ ላይ እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን፤ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታውን ለመቆጣጠርም ከ242 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገልፆል።


ጤናማ ያልሆኑ ምግቦች ለመቆጣጠር የሚያስችል አስገዳጅ ህግ ማውጣት፣ በፋብሪካ የተቀነባበሩ ምርቶች የፊት ለፊት ማሸጊያዎች ላይ የማስጠንቀቂያ ምልክቶች እንኖሩ ማስገደድ ፣ የገበያ ቁጥጥር ማረግ፣ የማስታወቂያ ገደብ መጣል እና ከፍተኛ ታክስ መጣል፤ የአለም የጤና ድርጅት ሃገሮች ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞችን ለመቆጣጠር ይረዳል በሚል ያስቀመጣቸው የፖሊሲ ምክረ ሃሳቦች መሆናቸው ተገልፆል።

እሌኒ ግዛቸው
ሚያዝያ 18 ቀን 2015 ዓ.ም
2.1K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 16:34:45

1.4K views13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ