Get Mystery Box with random crypto!

በማለዳ ንቁ !

የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaleda_neku — በማለዳ ንቁ !
የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaleda_neku — በማለዳ ንቁ !
የሰርጥ አድራሻ: @bemaleda_neku
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 20.09K
የሰርጥ መግለጫ

(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 13)
----------
11፤ በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ደኅና ሁኑ። ፍጹማን ሁኑ፥ ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
14፤ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን፡፡
@bemaledaa_neku_bot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-06 09:10:07 ጽንስ እንዲቋጠር፥ የወንድ ዘርና የሴት ደም ግዴታ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ጤናማ ካልሆኑ ጽንሱም አይሆንም፡፡ ዘር ከውጪ መጥቶ ደምን ይዋሐደዋል፡፡ በቅደም ተከተል ብናየው፥ ቀዳሚው የዘር ጤናማት ነው፡፡ ወይ ዘር የመዋሐድ አቅም ከሌለው፥ ደግሞ ቢኖረው ወደመዋሐድ አድራሻ መድረስ ካቃተው፥ ጽንስ አይፈጠርም፡፡ /አንባቢ የመጀመሪያው ሂደት፣ የእምነት ጉዞ፣ ከሥጋ ወደ ነፍስ ወደ መንፈስ የሚሄደው መንገድ፥ ከፅንሰት እንደሚነሣ በተደጋጋሚ የተነገረው እንዳይረሳ፤/

ለምእመናን በዘርነት የሚሰጠው ከወንጌል የሆነው አስተምህሮት ነው፡፡ ሕግና ትእዛዛት አስተምህሮቱን ይጠብቁታል፤ አምልኮት ወዲህ በምእመኑ ሕይወት ያዋሕደዋል፤ ከማይታየው ትስስር ያገናኘዋል፡፡ አስተምህሮት፥ በዕውቀትነት ሕግና ትእዛዛቱን ጨምሮ አምልኮቱንም ያስተምራል፡፡ ሚናው ወሳኝ ነው፡፡ ታዲያ አስተምህሮት ከተባለሸስ? ከወንጌል (ከእውነት) ማዕከል ፈር ከለቀቀስ? ዘር አቀባዩ ጤናማ ካልሆነስ? .. /አናብራራም፤ ኑሮአችን ስለሆነ እያንዳንዳችን ስለ እዚህ የምናውቀው፣ የምንለው ብዙ አለን፡፡/

የጥንቶቹ፥ ትምህርት ከሦስት ወገን ነው ይላሉ፡፡ ከመጽሐፍት፣ ከመምህራንና ከልቦና ነው ይላሉ፡፡ በተዋሕዶ ጉባዔ፥ ምእመናን ከመምህራን ወደ መጽሐፍት፣ ከመጽሐፍት ወደ ልቦና እንዲዘልቁ ታላቅ መስመር ተዘርግቶ ነበር፡፡ ሁለቱ፥ መምህራንና መጽሐፍት፥ ምእመናንን የሕይወት ውኃ እያጠጡ፥ ከልቦናው ሆድ ወንዝ እንዲያፈልቅ ተሰይመው ነበር፤ .. ነበር፡፡ ያው እንደምናየው ነው፡፡ /በመሠረቱ የመምህራን የአስተምህሮት ድርሻ፥ የምእመንን አስተሳሰብ ካነቁ በኋላ በወንጌል ወሳጅነት ራሱ ወደ ልቡ እንዲገባ ማገዝ ነበር፤ ግን ጌታ እንዳለው ነው፤ "እናንተ የዕውቀትን መክፈቻ ተቀበላችሁ ወይ አትገቡ ወይ አታስገቡ" እንዳለው፤/

ዘር በጤና ቢያልፍ፥ ሁለተኛው ደም በበኩሉ ጤናማ መሆን አለበት፡፡ ዘርን መቀበል፥ ተቀብሎም መዋሐድ ለጽንስ መኖር ግዴታ ነው፡፡ ጽንስ የሚቋጠረው በሴቷ ነው፡፡ ጽንሱን የመጠበቅ፣ የመሸከም፣ የማሳደግ ተፈጥሯዊው ባሕርይ እርሷ ጋር ነው፡፡ ካልቻለችስ? ብእሲት ምእመን ቃልን መዋሐድ እምቢ ካላትስ? ቃልን እንደሰማቺው መኖር ከሸሸችስ? .. /የዚህ ጥያቄ መልስ ከሁላችን ነው፡፡ እንደየራሳችን እንመልሰው እንጂ ስለ ልባችን ነገር ምን ተብሎ ምኑን ትቶ ይወራል?/

ሌሎቹ ከነዚህ ሥር የሚዘረዘሩትን የውጊያ ክፍሎች፥ ሁለቱን፥ መሠረታዊያኑን ስናልፋቸው እናወሳቸው ይሆናል፡፡ ጽንስ ሳይቋጠር ስለ አስተዳደጉ አንጨነቅምና፡፡

ለማንኛውም፥ ስናረዝመው የጀመርነው ይጠፋል፡፡ ስለዚህ በተወዳጅ ሰው፥ በጳውሎስ ሃሳብ እንጨርስ? /ታዲያ እስከ አሁን ባየነው ጉባዔ መሠረትነት የሃሳቡን አተረጓጎም እንዳናርቀው፤ ሰማይ በነፍስነት እኛ ውስጥ ነው፤ ምድርም በሥጋነት የኛው አካል፤/

            "በዚህ ውስጥ በእውነት እንቃትታለንና፥ ከሰማይም የሚሆነውን መኖሪያችንን እንድንለብስ እንናፍቃለንና ለብሰን ራቁታችንን አንገኝም። በእውነትም የሚሞተው በሕይወት ይዋጥ ዘንድ ልንለብስ እንጂ ልንገፈፍ የማንወድ ስለ ሆነ፥ በድንኳኑ ያለን እኛ ከብዶን እንቃትታለን። ነገር ግን ለዚሁ የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን።" (2ኛ ቆሮ. 5)


ተፈጸመ!

ማስታወሻ ፦ ከመጀመሪያው ጀምሮ እየተያያዘ ወደታች ቢነበብ በጎ ነበር፡፡

@bemaleda_neku
926 views06:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-06 09:08:18 የቀጠለ ...

           "ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል" (ዮሐ. 7፥38)

እንዴት? ሊጠጣ እንኳ የተጠማ አንድ ሰው፥ መልሶ ወንዝን ያህል ከሆዱ ያፈልቃል? ጉዳዩ ሚሥጢርነት ያለው ይመስላል፡፡

በመነሻችን፥ ለሁለት የከፈልነውን ጉባዔ ማስታወሱ እዚህ ይጠቅማል፡፡ ከፅንሰት - ሞት እና ከሞት - ዕርገት ብለን በኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ጉዞ በኩል ያየነው መንገድ አለ፡፡ የመጀመሪያው ሂደት የማንኛውም በሥጋ ያለ ሰው ጉዞ ነው፡፡ የሰው ልጅ ኑሮ በመፀነስ ተጀምሮ በመሞት ይገባደዳል፡፡

ስለዚህ አምላክ ሰውን ሲሆነው፥ የተገለጸውን የሰው ልጅ የኅልውና  ሂደት ሳያስቀር ይሄድበታል /በባሕርይ ተዋሐደ የሚሉት ይሄን ነው፤ ካልተዋሐደ ሰው እንደሆነው አይሆንም፤ አለመዋሐድ (ምንታዌ) ሂደቱን ያገድፋል፤/፡፡ በመሆኑ ይፀነሳል፣ ይወለዳል፣ ቋንቋ ይማራል፣ ያድጋል፣ ..  ለሰውነት የባሕርይ ሕጎች ይታዘዛል፡፡ ይሄ መታዘዝ እስከ መስቀሉ ድረስም ይቀጥላል፤ ለመስቀል ሞት እንኳ ታዘዘ እንዳለ!

በእምነት ጉዞ ውስጥ ላለውም ምእመን ሂደቱ ከላይ የተገለጸው ነው፡፡ በ'እንደ ቃልህ ይሁንልኝ' አሜንታ፥ ወንጌልን እየሰማ በልቡ ያኖራል፡፡ ይወለድ ዘንድ ይፀንሰዋል፡፡ ወንጌል በጽሩይነት ከተቀበሉት ከሰው ልቦና የሚጸነሰው ሕይወትነት ስላለው ነው፡፡ ሕይወት ስላለው፥ መጸነስ፣ መወለድ፣ ውህደት ፈጥሮ በጊዜ ጊዜ ማደግ፣.. ይችላል፡፡

እንግዲህ "የተጠማ ይምጣና ይጠጣ" ይኸው ቀዳሚ ጉዞ ነው፡፡ ንጹሕ ቃሉ ውኃ ነው፤ ከውኃም የሕይወት ውኃ፡፡ ምእመን ይህን ውኃ ከጥልቁ /ወንጌል በተፈጥሮ፣ በፍጥረታት፣ በሰው ባሕርይ፣ በመጽሐፍ ተጽፋ ያለች መሆኗ ጥልቅ እውነት ያሰኛታል፤/ እየጨለፈ ይጎነጫል፡፡ ስብዕናውን የሚሠራውን፣ ከየትኛውም ባርነት የሚገላግለውን፣ አስቀድሞ ማንነቱን ተከትሎ ሁሉን የሚያሳየውን ቃል እየተዋሐደ ወደፊት ይቀጥላል፡፡ አካሄዱን ዘርዝረነዋል፤ አንደግመውም፡፡ .. ምእመን ይቀጥላል፡፡

ጥሩ ምሳሌ ለዚህ የሚሆኑልን የመጀመሪያዎቹ የሕይወት ውኃ ተጎንጪዎች ደቀመዛሙርት ናቸው፡፡ ኢየሱስ፥ ሕያው ቃልን በማውጣት ማውረድ አስደምጧቸዋል፡፡ በየዋህነት፣ በደስታ፣ በእምነት፣ በተስፋ፣ በግርታ ሰምተውታል፡፡ ኋላም፥ እርሱ የሚያዝበት ጊዜው ደረሰና ተይዞ ተወሰደ፡፡ ተገደለም፡፡

በዚሁ አንጻር፥ እየፈሰሰላቸው ይጠጡት የነበረው የሕይወት ውኃ፥ በሚታየው ደረቀባቸው፡፡ "ከእኔ ትለፍ" ሲል ያሳለፋትን መሪር ጽዋ ቀመሷት፡፡ ከገዳይ ጎዳና ጠፍተው፣ ሥጋ ደሙን ወስደው፣ የቀጠራቸውን ረስተው (የሰሙትን ያህል ሞተው) ተሸሸጉ፡፡ ግን የሞተባቸው ወዳጅ፥ ከሞትም በኋላ የእንገናኛለን ቀጠሮን ሰጥቷቸው ነበር፡፡

              "ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ገና ጥቂት ዘመን አለ ከዚህም በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና እናንተ ደግሞ ሕያዋን ትሆናላችሁ።" (ዮሐ.14፥19)

ወይም፥

            "እንግዲህ እናንተ ደግሞ አሁን ታዝናላችሁ፤ ነገር ግን እንደ ገና አያችኋለሁ ልባችሁም ደስ ይለዋል፥ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም።" (ም. 16፥22)

'ዓለም ሳያየኝ እናንተ ታዩኛላችሁ፥ እንደገና አያችኋለሁ' የሚላቸው ያልሞተው፣ ከፊታቸው በሥጋ ሕግ የሚያዩት ኢየሱስ እንደሆነ ያጤኗል፡፡ ስለዚህ እንዴት ከዓለሙ ተሰውሮ ለነርሱ እንደሚገለጥ እንግዳ ሆኖባቸዋል፡፡ በዚያውም ላይ ማንኛውም በሥጋ ያለ ሰው ሃሳብ እስከ ሞት ድንበር ይረዝማል፤ እነርሱም ሲያስቡ እስከዚህ ጫፍ ድረስ ነው፡፡ ከመቃብር ባሻገር፥ አለቀ፣ ደቀቀ፣ ተጠናቀቀ የሚል የነበርነትን ታሪክ እንጂ፥ ሕይወትን አግኝቶ የሚቀጥል ኅልውና አያውቁም፡፡ በመሆኑ ከሞት ወዲያ ቀጠሮ ይሉት ጉዳይ አይገባቸውም፡፡ ከመካከላቸው አንዱ እንግዳውን ንግግር እንዲያስረዳቸው ጠየቀ፥

              "ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው?"

ተመለሰለት፤

             "የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።" (ም. 14፥23)

ይሄ ቃል የሕይወት ውኃ ነው፡፡ አንዲት ሳምራዊት ሴት እንደሰማቺው፥ ከዚህ ውኃ የሚጠጣ ዳግመኛ አይጠማም፡፡ ምክንያት?

ሐዋሪያቱ ጉዟቸው በቀራኒዮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ውስጣቸውን ሲዋሐድ የኖረው ቃል፥ ከውጪ ሲያገኙት የቆዩት ነው፡፡ በትምህርት፣ በምሳሌ፣ በሥራ፣ .. ሲቀበሉት ሰንብተዋል፡፡ ውኃው ወደነርሱ በመግባት ይፈስ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ውኃው ውስጣቸውን አጥለቅልቆ ሲሞላ /ይሄ በወቅቱ ለነርሱ ባይገለጥላቸውም፤/፥ ከሚታየው ይመጣ የነበረው ተቋረጠ፡፡ በድምፁ፣ በድርጊቱ ይሰሙት የነበረ ቃል ዝም አለባቸው፤ እንደነርሱ ባለ ውስን ሥጋና ነፍስ ሆኖ ይናገራቸው የነበረ መምህር፥ በአደባባይ ተገድሏልና፡፡

ሆኖም፥ እንደቀጠራቸው፥ ከሞቱ እንደተነሣ ወደነርሱ ሄደ፡፡ ከዓለም በሞቱ ተሰውሮ ግን ለነርሱ በትንሣኤ ተገልጦ አገኛቸው፡፡ "እኔው ነኝ" እያለም የሞተውን ቀሰቀሰላቸው፡፡ አሁን ሐዋሪያት ጌታቸውን ባለመጥፋት ያውቁታል፡፡ ህያውነትን አስረግጠዋል፡፡ ስለዚህ ትምህርቱን፣ ያሳየቸውን ሁሉ ከእንግዲህ በነበር አያስቡትም፤ መቃብርን አልፎ አግኝቷቸዋልና፡፡

በዚህ ሥርዓተ ትንሣኤ ለ40 ቀናት ተመላልሶላቸው፥ ወደ አባቱ ሊሄድ ወደ ዕርገቱ ወጣ፡፡ ወደ አብ (ዋናው ልብ) ከፍ ከፍ አለ ስንል፥ ከእነርሱ የኖረ ቃልነቱ ወደ ውስጥ አስኳላቸው፣ ወደ ልባቸው ዘለቀን እናስተውላለን፡፡ ልብ፥ ባሕርያዊ ግብሩ መውለድ ነው ይላሉ ሊቃውንት፡፡ አንባቢ አንተስ ልብ ብለሃል?

ቃል ወደ ወለደው ከሄደ፥ ውኃውም ወደ ምንጩ ተመልሷል፡፡ እነሆ ከውጪ የሚመጣው ከውስጥ የሚፈልቅ ሆኗል፡፡ ያ ሊጠጣ የተጠማ ሰው፥ ሌሎችን የሚያጠጣ የሕይወት ውኃ ወንዝን እንዲህ ባለ የሕይወት ጉባዔ ከሆዱ ያፈልቃል፡፡

የአብን ወላዲነት በወልድ መንገድነት በኩል በእውነት ያገኘ፥ ሃብታት፣ ሚሥጢራትን ይወልዳል፤ አዲስ ሃሳብ ያስገኛል፤ ጥበብን፣ ዕውቀትን ከማይታየው እየገለጠ ያመጣል፡፡ ይኸውም መገለጥ ጠርዝ፣ ማብቂያ የለውም፤ በየዕለቱ ይነጋል፡፡ ማለዳ ማለዳ ወጋገኑ የሚጨምር ዕፁብ ብርሃን ነው፡፡ ስለዚህ ወንዝ አለው፤ ቢፈስ ቢፈስ ገደብ የሌለው፣ ያለማቋረጥ የሚወርድ አንጸባራቂ ውኃ ስለሆነ፡፡ እናስ ማነው? ይህን ያፈልቅ ዘንድ ጠጥቶ ሳለ ዳግም የሚጠማው? ..

አሁን ጥቅል ውጊያው ግልጽ ሆኖ ይገባናል፤

                   "ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።" (2ኛ ቆሮ. 4፥4)

ምእመን ቀዳሚውን ጉዞ በአስተምህሮት፣ በአምልኮት፣ በሕግ ትእዛዛት (በጥቅሉ ቃሉን በመጠበቅ) ይሄድበታል፡፡ የሚሄደው ምእመን፥ ሦስቱን የሃይማኖት ዐላባውያን የሚቀበለው ከርሱ ውጪ እንደሆነ ግልጽ ነው /በርግጥ አምልኮት መተሳሰሪያ ስለሆነ ከርሱ ውስጥ የሆነንም ይጠይቃል፤/፡፡ እነሆ ውጊያ ቁጥር አንድ ከዚህ ይጀምራል፡፡
873 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 07:21:10 በሥጋ ወራት በተወሰነ ቦታና ጊዜ ውስጥ ይንቀሳቀስ የነበረው አንድ ኢየሱስ፥ በትንሣኤው ምክንያትነት ከመወሰን ማዕቀፍ የወጣ ኅልውና ሆኗል፡፡ አንዲቱ የዘር ቅንጣት፥ አፈር ገብታ ስትበቅል አንድ ሆና አትወጣም፡፡ ትበዛለች፡፡ የተነሣውም ክርስቶስ ጊዜና ቦታ (የሥጋ ሕግ) ስለማይገዛው፥ ውስንነት የማይዘው ሁለንተናዊ ሆኖ በዝቷል፡፡ እንደማንኛውም ሰው በአንድ ሃገር፣ በአንድ ስፍራ፣ ከአንድ ሥጋና ነፍስ የተወለደው እርሱ፥ እስከአሁን ስንነጋገርበት በመጣንበት መልኩ በትንሣኤው ኃይል በሚቀበሉት ሁሉ ውስጥ የሚወለድ ረቂቅ ሆኗል፡፡ /ቃል ሥጋ ሆነ - ቀዳሚው ልደት፤ ጸጋና እውነትን ተመልቶ በእኛ አደረ - ደኃራዊው ልደት፤ አንባቢ ወንጌላዊ "እኛ" ብሎ አንዱን ኢየሱስ በክርስቶስነት ሲያበዛው አስተዋልክ?/

ስለዚህ ከትንሣኤው በኋላ፥ ክርስቶስን በሥጋ እንደሆነ አናውቀውም (እንደ መግደላዊት)፡፡ ይልቅ በእኛ ይኖር ዘንድ ባስቀመጠው፥ "አባ (ዳግም ከመንፈስ የተወለዱት)፣ አባት (ከሥጋ ተወልደው በመንፈስ ሊወለዱ የሚተጉት)" ስንል አብን በምንጠራበት የልጅነት መንፈስ እናውቀዋለን፡፡ ወይም በዚህ መንፈስ ባሕርያችንን በሚጎበኝበት ልዩ ቃሉ!

ቃል ካለ ሃሳብ አለ፡፡ ሃሳብም አስተሳሰብን ይሆናል፡፡ እንኪያስ ከላይ የጠቀስነው ብርቱ አሳዳጅ ይህን አስተሳሰብ መግደል ላይ ትኩረት ሰጥቷል፡፡ ሰው እንደየአስተሳሰቡ ክበብ ይኖራልና፤ አስተሳሰቡን እንደሠራው ቃል ያስባል /የሰውን ሕይወት ለመምራት አስተሳሰቡን መምራት ነው፤/፡፡ በመሆኑ ባለ ራሶቹ ዘንዶውና አውሬ፣ ነቢያቸውም የምድሩ አውሬ፥ ዘመቻቸውን በዚህ ክርስቶስ ኢየሱስ ሠርቶ፣ ለክቶ ባለሰበን መንፈስ ላይ ካደረጉ ዓመታት ከርመዋል፡፡ ይሄ ማስረጃን የማይጠይቅ የአኗኗራችን መረጃ ነው፡፡ አንባቢ፥ ለመሆኑ አሁን በዚህ ሰዓት፣ በዚህ ደቂቃ ምን እያሰብክ ነው?

በጀመርንበት እንጨርስ ዘንድ፥ ወዲህ ከመጽሐፍት፣ ከሰው ልብና አእምሮ፣ ከታሪክ፣.. አጠቃላይ ከዓለም ይሰደዳል ስላልነው አስተሳሰብ ግልጽ መረዳት ይኖረን ዘንድ፥ ተከታዩን የጌታ ሃሳብ ለመጠቅለያነት እናነሣው፥

              "ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ። በእኔ የሚያምን መጽሐፍ እንዳለ፥ የሕይወት ውኃ ወንዝ ከሆዱ ይፈልቃል" (ዮሐ. 7፥38)

እንዴት? ሊጠጣ እንኳ የተጠማ አንድ ሰው፥ መልሶ ወንዝን ያህል እንዴት ከሆዱ ያፈልቃል? ጉዳዩ ሚሥጢርነት ያለው ይመስላል፡፡

*14 - ዓለሙ፥ ክርስትናን የተገነጠለ ሃይማኖታዊ መልክ ሰጥቶ በተቋምነት ብቻ ያውቀዋል፤ ሆኖም እርግጡን አደንድነን ከተነጋገርን ክርስቲያን መባል የሰው ልጅነት በከፍተኛ ክብርና ልዕልና ሲገለጥ የሚያገኘው የብቃት ስም ነበር፤ ክርስትና ክርስቶስን በመምሰል አያበቃም፤ በመሆን ይፈጸማል እንጂ /"መምሰል ላይ የሚያቆመው ዓለም አቀፎቹ የክርስትና ርእዮቶች ናቸው፤ ዓለሙ የሚያውቃቸው ዝነኛ ሃይማኖቶች የልዕልናይቱን ጽዋ ወደ ውስጥ እንድንጎነጭ አያሰናብቱንም፤ እያየናት ከደጅ ቆመን እንድናደንቃት እንጂ፤/፡፡ ኢየሱስ ተከታዮችን ሊያፈራ ለዓለም አልታየም፤ በእርሱ የተገለጠው ሁለንተናዊነት ማንነት በሁሉ እንደሁሉ እንዲሆን እንጂ፡፡ .. ህዝብ የሚከተላቸው የአደባባይ ሃይማኖቶች (main stream religions) በማወቅም ሆነ ሆን ብለው የሚያሳድዱት፥ ይህን የሰው ልጆቾ ሁሉ እውነትና መዳረሻ ነው፡፡


ይቀጥላል ...

@bemaleda_neku
4.5K views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 07:20:07 የቀጠለ ...

አዲስ ፍጥረት የመሆን ጸጋ የተሰጠው በክርስቶስ ትንሣኤ ነው፡፡ አዲስ ፍጥረት ያሰኘውም፥ የሚታየውን ዓለም የተሻገረ ልዩ ኅልውና በመሆኑ ነው፡፡ የመጀመሪያው የፍጥረታት መገኛ የዘፍጥረቱ እሁድ፥ የክርስቶስ የትንሣኤው ዕለትም መሆኑ ይህን እውነት ያጸናዋል፡፡ ሁለተኛው እሁድ የአዲሱ ፍጥረት መገኛ ሁለተኛው ልደት ነው፤ ወይም የሁለተኛው መንገድ መነሻ ነው፤ ከሞት - ዕርገት ያልነው መንገድ፡፡ የማርቆስ ወንጌል 13፥31፤

              "ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም።"

አስቀድመን እንዳልነው፥ ልደት ካለ የሚዘለቅበት ዓለም አለ፡፡ ልደት ማለፊያ በር ነው፡፡ እና፥ ከሥጋ የተወለደ ሁሉ ወደሥጋው ዓለም ይገባል፤ ከመንፈስ የተወለደ ደ'ሞ ወደረቂቁ ዓለም ይሻገራል፡፡፡ የሥጋ ልደት - የዚህ ዓለም ሂደት - በዘፍጥረቱ እሁድ - በመጀመሪያዎቹ ሰማይና ምድር ተይዞ እስከ እልፈቱ ይቀጥላል፡፡ ዳግም ልደት - የማይታየው ዓለም - በትንሣኤው እሁድ - በአዲሱ ሰማይና ምድር ይጀምራል፡፡ (ራእ. 21፥1) ይሄ ትንሣኤና ልደት አንድ መሆናቸውን ይነግረናል፡፡

እነሆ ኢየሱስ በሥጋ ልደቱ፥ ከታተመች ማኅፀን ወጥቶ ወደዚህ ዓለም መጣ፡፡ በትንሣኤ፥ ከታተመች መቃብር ወጥቶ ወደዚያኛው ሄደ፡፡ የሄደበት ዓለም፥ በጊዜ ልኬቱና በአውታሩ አሁን ከምናውቀው ይለያል፤ በአካሉም መንፈሳዊ ነው፡፡ ይሄን ያለንበትን ዓለም የሚገናኘውም በመንፈሳዊ ትስስር ነው፡፡ ለምሳሌ ከተነሣ በኋላ መግደላዊቱ አስቀድማ እንዳየቺው ተጽፏል፡፡ ሆኖም በመልኩ ወዲያውን አላወቀቺውም፡፡ ለምን?

እርሷ እየተመለከተች ያለቺው በዚህኛው ዓለመ ገጽ ጊዜና አውታር ውስጥ ሆና ነው፡፡ በአጭሩ፥ በሥጋ ነው፡፡ ሥጋ ደ'ሞ መንፈሳዊን አካል ወይንም በመንፈሳዊ ዓለም ያለን አካል በቀጥታ አያየውም፡፡ ወይ የተዋሐደ የመንፈስ እይታ ያስፈልገዋል አሊያም መንፈሳዊው አካል ራሱን በግዝፈት ለዚህ ዓለም መግለጥ ይኖርበታል፡፡

               "ስለዚህ ማንም በ(ትንሣኤ)ክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።" (2ኛ ቆሮ. 5፥17)

እውነት ነው! አሮጌው ሰማይና ምድር ያልፋሉ፤ በየዕለቱ እያለፉም ነው፡፡ በነዚህኞቹ አንጻር ያሉት ሥጋና ነፍስ (ፊተኛው አዳም፣ መሬታዊው ሰው) እንዲሁ ያልፋሉ፡፡ የሥጋና ነፍስ ማለፍ ደግሞ፥ እስከአሁን ወዳወሳነው ወደ ትንሣኤ ሥርዓት ነው፡፡ በትንሣኤ ዳግም የተገለጠው ማንነት፥ ከሞቱ በፊት የነበረው (አሮጌ) አይደለም፡፡ ይልቅ የመንፈስ ሕይወትን ያገኘ አዲስ ማንነት ነው፤ አዲስ ፍጥረት እንደማለት! ስለዚህ?
    
             "እኛስ ዘወትር በሚያስፈራ ኑሮ የምንኖር ስለ ምንድር ነው? በጌታችን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለኝ በእናንተ ትምክህት እየማልሁ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ።" (1ኛ ቆሮ.15፥31)

ደ'ሞም በሌላ ስፍራ፥

             "እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን። የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና።" (2ኛ ቆሮ. 4፥9-11)

በእዛው መጽሐፍ ወረድ ብሎ፥

           "ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል።" (ቁ.16)

ይሄ እንዲሁ የጽድቅ የኩነኔ ስብከት አይደለም፡፡ ወይም ያልተጨበጠ ተስፋ አሊያ ሩቅ ሕልም አይደለም፡፡ የሰዎች ሁሉ የባሕርይ መሻት በአንድም በሌላም ዘወትር በፍርሃት አስሮ ከሚያኖር፥ በሥጋ ልደት አማካኝነት ከገባንበት ከዚህ የድካም ዓለም አርነት መውጣት አይደል? ይሄ ታመነም አልታመነም የማንኛውም ሰው ውስጣዊ መቃተት ነው፡፡ የፍርሀቶች ሁሉ መንስኤ ደ'ሞ የሞት ነገር ነው፡፡ መታመምም፣ መራብም፣ መቸገርም፣.. የሚያስፈሩት በሞት ምክንያት ነው፡፡ የሥጋ ማንኛውም ዓይነት ጉስቁልና ሟች ከመሆኑ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ጳውሎስ ግን እንደዘበት "ወንድሞች ሆይ፥ ዕለት ዕለት እሞታለሁ" ይላል፡፡ ምን እያለ ነው?

አንባቢ ዕለት ዕለት ሞት የሚታወጅበትን እውነተኛ ምእመን አስታወስከው? በመጨረሻው ቀን እንዲነሣ ኪዳን (ቃል፣ ቁርባን) የተሰጠው? .. እርሱን እኮ ነው አሁን የምንነጋገር፡፡

እንዲህ ያሉ ምእመናን ሐዋሪያው እንደሚለው፥ የኢየሱስን ሞት በሥጋቸው ተሸክመው የሚዞሩ የዚህ ዓለም ባዕዳን ናቸው፡፡ ክርስትና ከተመሠረበት መነሻው ጀምሮ እስከዛሬ እንደዘለቀበት ጠቅላይ እውነታ፥ ሂደቱ በሞት መንደር መካከል ነው፡፡ መጥፋት፣ መሰደድ፣ ቦታ ማጣት፣ .. የዚህ፥ በተዋኅዶ ስም የተገለጸ የሰው ልጅ እውነት፥ ኑሮ ነው፡፡ ከግለሰብ እስከ መንግሥት፣ ከሃይማኖት እስከ መናፍስት ባለው ስብስብ፥ በትንሣኤ መሠረትነት ለታነጸው ክርስትና ሁነኛ ጠላቶች ናቸው *14፡፡ ያገኙት ያሳድዱታል፡፡ ከያዙት አያራሩለትም፤ ይገድሉታል፡፡

ይሁን እንጂ ከክርስቶስ እውነት የተነሣ ሊሞት የሚታወጅበት ምእመን፥ ከክርስቶስ ሕይወትነት የተነሣ ቢሞትም ይነሣል፡፡ በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለው ያለው ቃል በራሱ ሕይወት ነው፤ ስለዚህ በአማኙ ኑሮ ላይ በፊቱ ተገልጦ ይከወናል፡፡

የምእመን አነሣሱ እንደ አማሟቱ ነው፡፡ የገደሉ(በ)ትን ነገር፣ ሃሳብ፣ ግብ፣.. ያህል ይነሣል፡፡ ሞቶ በተነሣ ልክም የሞተው ከፍ ከፍ ወደማለት ለጥቆ ይሄዳል፡፡ ወደትንሣኤ ጥልቀት ይጠልቃል፡፡ የዚህ ዓለም ግንዛቤዎች ወደማይደርሱበት ጥግ ይገሰግሳል፡፡ እነሆ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም የሚያስብለው ይሄ ነው፡፡ /ዓለም በተለይ በዚህ ሰሞን 'ሊነጋ ሲል ይጨልማል'ን የስኬት ማበረቻ፣ የስሜት ማነቃቂያ አድርጋ የራሷን "ትንሣኤ" ትሰብካለች፤ በመጥፋት በኩል የመትጋት ሃሳቡ ግን፥ ሕይወት ሆኖ፥ ከዛሬ ፪ሺዎች ዓመት ጀምሮ ሰዎች በእውነት ኅልውና ሲመላለሱበት ቆይተዋል፤/

የዚህ ዘመን የእውነት ገዳይና አስገዳይ እንደቀደመው ብዙም በሥጋ ግድያ አያምንም (ከስሕተቱ ተምሮ ይሆናል¡)፡፡ ከዚህ ይልቅ የሞት ሥልጣኑን የሚነጥቀውን፣ እንደ ጳውሎስ 'ምን በሚያስፈራ ኑሮ ያባትለኛል?' ሊያሰኝ ትውክልት የሚሰጠውን አስተሳሰብ፣ መንፈስ (የውስጥ ሰውነት) ላይ ማተኮሩ አዋጭ ሆኖለታል፡፡ በሚከተለው መሠረታዊ ምክንያት፥

             "ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም።" (2ኛ ቆሮ. 5፥16)

እንኪያስ እንደምን እናውቀዋለን? ጳውሎስ መልሱን ይቀጥላል፥

            "ልጆች ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።" (ገላ. 4፥6)

ወሳኝ ነውና እንድገመው፥

           " ... በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና። አባ አባት ብለን የምንጮኽበትን የልጅነት መንፈስ ተቀበላችሁ እንጂ እንደገና ለፍርሃት የባርነትን መንፈስ አልተቀበላችሁምና። የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል።" (ሮሜ 8)
3.5K views04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 08:35:15 ሐዋሪያቱ አስቀድሞ በቅፍርናሆም ይሄን ፍቅር አድምጠዋል፡፡ ኋላ ብዙም ሳይቆይ ኪዳን የሰጣቸው እርሱ ተይዞ ተገደለ፡፡ እነርሱም በሥጋ ተስፋ ያደረጉበት፣ የተለሙት ሁሉ አብሮ ሞተባቸው፡፡ ውስጥ ነገራቸውን ባማከለ አገላለጥ፥ ቃሉን በሥጋ የተረዱበት፣ የተረጎሙበት፣ የጠበቁበት አስተሳሰባቸው ከሞቱ የተነሳ ሞተ፤ ተለያቸው፡፡ የሞተባቸው መሪ እዚያው በተገደለበት ተቀበረ፡፡ በዚያው ትይዩ የትምህርቱ ሚሥጢር /በወቅቱ ያልተገለጠላቸው ሀሳብ፤/፣ በቁርባን የወሰዱትም ሥጋ ደም፥ ከሰውነታቸው ውስጥ ተቀበረ  *13፡፡ ደግሞ ከውስጥ ያለው በውጪኛው ይገለጻልና፥ በሚታየውም ረገድ በራቸው ዘግተው ከገፋቸው ዓለም ሸሽተው ተቀመጡ (ከዓለም ተቀበሩ)፡፡

ይህ እንደዚህ ሳለ፥ የሞተው እርሱ በአካል ተነሥቶ ወዳሉበት መጣላቸው፡፡ ስለዚህ በሞቱ የሞተባቸው ቃሉ፣ በመነሣቱ ተነሣላቸው፡፡ በመብል መጠጥነት የተዋኀደ ሥጋ ደሙ ከሰውነታቸው መቃብር ተነሣ፡፡ በተዘጋ በር አልፎ አግኝቷቸው ሲያበቃ፥ በተዘጋ ሥጋቸው አልፎ ረቂቅ ዕውቀታቸውን ከፈተው፡፡ የህሊናቸውን፣ የልቡናቸውን ሕዋሳት ሁሉ ከፈተላቸው፡፡ ስለዚህ ባሕርያቸው የትንሣኤውን ብርሃን በርግጥ አየ፡፡ ይሄ ብርሃን፥ በዚህ ይፋው ዓለም የሚያውቁት አልነበረም፡፡ ይለያል፡፡ አዲስ ነው፤ ልዩ ነው፡፡ እንዲህ መባሉ የፀሐዩን ብርሃን አያዩትም ለማለት አይደለም፤ እርሱን በሥጋ ዓይናቸው ያዩታልና፡፡ ለፀሐይ ብርሃን የሆናትን ብርሃን ግን ውስጠ ልቦናቸው ይመለከተዋል፡፡ አሁን፥ በሞትና በህይወት፣ ወደፊትና ወደኋላ፣ በሚታየው በማይታየው፥ ኅልውናን ያገኘ አዲስነት፥ ማንነታቸውን ተዋሕዷል፡፡ እነርሱ ከእርሱ የተነሣ አዲስ ሰዎች ሆነዋል፡፡ ግሩም ሰው ጳውሎስ፥

           "እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥" (ኤፌ 2፥14-15)


___
*8 - በእርግጥ አብዛኛው ሰው ፍጥረታዊ (ሥጋዊ ደማዊ ሃሳብ ያለው) ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በአግባብ አስተምህሮትና ለሥነ ምግባር መግፍኤ በሚሆኑ ሕግና ትእዛዛት ሥር መኖሩ በቂው ሊሆን ይችላል፡፡ ወደ ትንሣኤ ሥርዓት የሚሻገሩት ጥቂቶች ናቸው፡፡ አብዛኛው፥ በጌታ ዓይን እንደታዩት፥ እረኛ እንደሚያስፈልጋቸው ተበታትነው ያሉ የበጎች መንጋ ናቸው፡፡ እውነት ከፊት እየቀደመ ተከተሉኝ የሚላቸው አሉ፤ ደ'ሞ የሚያስፈልጋቸውን በረከት ወስደው ወደየቤታችሁ የሚባሉ አሉ፤ ዋናው ነገር በክርስቶስ አባት ቤት (በጠቅላዩ ሃሳብ ዘንድ) ያሉት ክፍሎች ሰፋፊና ብዙ መሆናቸው ነው፤ ስለዚህ ለሁሉም የተዘጋጀ በቂ ማረፊያ አለ፡፡

*9 - እዚህ'ጋ ወንጌል ሲባል ሃይማኖታዊ የሆነው ገጽና ልማድ ብቻ የሚታያቸው አሉ፤ ደ'ሞም እስከአሁን ሰፍቶ እንዳለው ግንዛቤ ከዚህ መልኩ ባሻገር ሊታይም "አይችልም"፤ ይሁን እንጂ ወንጌል፥ የጽዮን ሕግ፥ የሰው ልጆች ሁሉ ምጥ ፍለጋ ናት፤ የትኛውም ዓይነት ዘውግ ያላቸው በጎ፣ ኃያልና ሰዋዊ ታላላቅ ሃሳቦች የወንጌልነት አንድምታ አላቸው፡፡

*10 - ይሁን እንጂ አስቀድሞ እንዳልነው፥ መሬት በረገጠው እውነታ ይሄ አስተሳሰብን የማንቃት ደረጃ ሆን ተብሎ ማዕቀብ ወድቆበታል፤ ወጥና ልሙጥ የሆነ ሲያክልም ቁንጽል አእምሮአዊ አተያየት በዓለሙ ሕዝብ የጋራ ናላ ላይ እንዲሰፍን በላይኛዎቹ ይፈልጋል፡፡

*11 -  ለማሳጠር ያህል ቆርጠን እንጂ፥ በርግጥ ገና ከጅምሩ የሚወለደው እንዳይፀነስ ቀድሞም ይታወጅበታል፤ ጳውሎስ እንዳለ በተለይ በመጨረሻው ዘመን ለዚህ ፅንስ ምክንያት የሚሆነው መንፈሳዊ ጋብቻ ሆን ተብሎ ይሰነካከላል፡፡

*12 - የሚገርመው ከሰባቱ አንዱ በሃይማኖቱ ክፍል ብርቱ ስፍራን መያዙ ነው፤ እንደውም ከስድስቱ ይሄኛው ይከፋል፤ ግብዝነትና ቅናት በዚህ ቦታ የሚቆምባቸው ሁለት እግሮቹ ናቸው፤ ራስ ቅሉ (ማሰቢያው) ሐሰት ይሆናል፡፡

*13 -  ቅዳሴ፥ በአምልኮ ሥርዓቱ ጠቅልሎ ይህንን ዕለት ዕለት ያውጀዋል፡፡ በቁርባን የሚሰጠው ሥጋ ደም ነፍስ የተለየው መለኮት ያልተለየው ነው፡፡ ወይም ሥጋ ደሙ የተሰጠው በሞቱ ነው፤ ስለዚህ ሕብሥትና ወይኑ ይሄን ሞቱን በምእመን ውስጥ ያውጃሉ፤ ሥጋ ደሙ በምግብና መጠጥነት በሰውነት ይቀበራል፡፡


ይቀጥላል ...

@bemaleda_neku
5.4K views05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-26 08:30:06 የቀጠለ ...

ምንም እንኳ ለሃይማኖት፥ ትምህርት፣ ሕግጋትና አምልኮት መሠረቶቹ ቢሆኑም፥ ለሁለቱ መሠረታዊያን ደግሞ ሥርዓተ አምልኮት መሠረታቸው ነው፡፡ በግልጽ አገላለጽ አስተምህሮትና ሕግጋት ምንጫቸው ከአምልኮት ነው፡፡

አምልኮት መንፈሳዊ ክንውን እንደመሆኑ፥ ከመንፈሳዊ ዓለም ጋር የሚደረግ ግንኙነት ነው፡፡ ማንኛውም ዓይነት አምልኮ ራሱን የቻለ መንፈሳዊ ትስስር ይኖረዋል፡፡ ከሌለው ልማድ ወደመሆን ይወርዳል፡፡ አምልኮት በሚፈጥረው ግንኙነት የተነሣ፥ ለአስተምህሮትና በአስተምህሮቱ ዙሪያ ለሚኖሩ ሕግጋት ምንጭ የሚሆኑ ሀሳቦችን ከማይታየው ወስዶ ያመጣል፡፡

በአስተምህሮት መንገድነት፣ በሕግጋት ጠቋሚነት እየተጓዘ ያለ ምእመን ታዲያ፥ የሂደቱን ዓላማ የሚቀርጸው፣ ወደ መዳረሻው በሚራመድበት ጉዞው የሚገጥሙትን ተግዳሮቶች የሚያልፈው፣ እንዲሁም በአስተምህሮት በኩል የተቀበለውን ቃል በጊዜው ውስጥ የሚተረጉመው በአምልኮት ረዳትነት ነው፡፡ መንፈሳዊ ትስስር መፍጠር የሚችሉ መንፈሳዊ ልምምዶችን እየፈጸመ ካልሄደ ወደ ቀጣዩ የዕድገት ክፍል መዝለቅ አይችልም፤ ይልቁን ዝንት ዓለሙን ከመምህራንና መጽሐፍት እየወሰደ፣ ከሕግና ትእዛዛት በታች ሆኖ ሊወሰን ይገደዳል፡፡ *8

ወደ ሥር ነገራችን ስንመለስ፥ በአስተምህሮትና ሕግጋት ዕድገቱን የቀጠለው ምእመን በአምልኮት በኩል እየተረዳ፥ ባገኘው ማስተዋል ልክ በእምነት የሰማቸውን ቃላት እንደገና በውስጡ ይሰማቸዋል፡፡ አስተሳሰቡን በወንጌል ቅኝት ይዋጃል *9፡፡ ፈጣሪውን፥ እንደሚነገረው ብቻ (ከውጪ፣ በሌሎች) ሳይሆን እንደሚያስበውም (ከውስጥ፣ በራሱ) ሊያገኘው ይጥራል፡፡ እውነትን ከወረቀት ብቻ ያይደል ከሕይወትም ሊያነባት ይጀምራል፡፡ አሜን ያለውን የእምነት ቃል፥ በራሱ ማውጣት ማውረድ ውስጥ በኑሮው አሚንነት ይፈትሻል፡፡ በሃሳብም፣ በሕይወትም መውጣት መውረድ ዕለቶቹን ይመራል፡፡ *10

በቤተክርስቲያን ዋነኛውና ወንጌሉን ህይወት የሚሰጠው ሥርዓተ አምልኮ ቅዳሴ ነው፡፡ ቅዳሴ በአጭሩ ወንጌል ተተርኮ ማለት ነው፡፡ እዚያ ሥርዓት ውስጥ በተለያዩ መሥዋዕቶች ቃሉ በመንፈስነት ወደተሳታፊው እየደረሰ ይቆይና በመጨረሻም ሁላቸውን መሥዋዕቶች የሚጠቀልላቸው መሥዋዕት ይቀርባል፤ ይኸውም ሰማያዊው ማዕድ - ቅዱስ ቁርባን ይባላል፡፡

ቅዱስ ቁርባን የሐሙስ ሥርዓት ነው፤ ፍጻሜውን ያገኘው ግን በአርብ ዕለት ነው፡፡ እንካችሁ የሚፈስ ደሜን ጠጡ እያለ የወይኑን ጽዋ ጌታ ለወዳጆቹ ሐሙስ ቢያድላቸውም፥ ደሙ ግን የፈሰሰው አርብ ላይ ነው፡፡ አርብ ነገረ መስቀሉ ነው፡፡ ወይም ሞቱ ነው፡፡ አስቀድመን እንዳወሳነው ደ'ሞ በዚህ ዓለም ተገልጦ የሚኖረው የሥጋ ኅልውና፥ ከልደት እስከ ሞት ይጓዛል፡፡ ይሄም ነው ከሴት የተወለደ "ሁሉ" ሞትን ያያል የሚያሰኘው፡፡ ሰው ሲወለድ ሞትንም ይዞት ይወለዳል፡፡

በምእመንነት ያለው ይህ ነው፡፡ በእምነትነት ተጸነሰ ያልነው ቃል፥ በተቀበለው ውስጥ ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ሞት ይከተለዋል *11፡፡ ቃሉ ሕይወት ነው የተባለውን አልረሳንም፡፡ ሕይወትነቱም የኢየሱስ በመሆን ነው፡፡ እርሱ ደ'ሞ በመዋለ ሥጋው ሞት ከብቦት ነው የኖረው፡፡ በመጨረሻ በመስቀል ተገደለ፤ ከነበረበት ትውልድ ተወገደ፡፡

አማኝም ተቀብሎ በውስጡ ካዋሐደው በሞት መካከል ከኖረ ከዚህ ቃል የተነሣ ሞት ከብቦት ይኖራል፡፡ በትምህርት መግቦት፣ በሕግጋት ሞግዚትነት የሚያድገው ሐዲስ ባሕርይ፥ ሲሆን እንዳይወለድ፥ ቢወለድ ከዚህ ዓለም እንዲወገድ፥ የግድያ ትእዛዝ ከየአቅጣጫው ይወጣበታል፡፡ ስላንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን እንግዲህ ይኸው ነው፡፡ በማይታየው ሆነ በሚታየው የሚገለጽ የጥፋት ስደት እውነተኛ ምእመንን ያሳድደዋል፡፡ እንዲጠፋ ይፈርድበታል፤ ዐወጅ ይነገርበታል፡፡

ዮሐንስ በራእዩ አንዲትን ሴት ዘንዶው ሲያባርራት፣ ሳይዛትም ሲቀር ከዘርዋ የሚወለዱትን ሊያገኛቸው ሲጣጣር ተመልክቷል፡፡ ለዚህ ጽሑፍ ጭብጥ ትርጓሜ፥ ሴቲቱ በሚሥጢር ቅድስቲቱ ወልድ ናትን እንይዛለን፤ ዘር የሚሰኘው ደ'ሞ ቃል እንደሆነ ራሱ ተርጉሞልናል፡፡ (ማቴ. 13፥18) ስለዚህ በቃሉ ዘርነት ሊወለዱ የተጸነሱትንና የተወለዱትን ሁሉ ሊበላቸው በሰባት አቅጣጫ ከፊታቸው ይቆማል *12፡፡ ክፉው ወደ ስብዕናቸው ፍጻሜ ሊደርሱ እየተጉ ያሉትን በሚታየው (የሥጋ ነገራቸውን) ይዞ ይገድላቸዋል /ለዚህ ነው አይደል 'ሥጋችሁን የሚገድሉትን.. ' የሚለው?/፡፡ የራሱ ከሆነው ሁሉ እየፈለገ ያጠፋቸዋል፤ በዚህ ሳይበቃው ዙሪያቸውን ጭምር ተከታትሎ ያጠፋል፡፡ አንተም ከነርሱ አንዱ ነህ እያለ የተጠጓቸውን ያስጨንቃል፡፡ እንዳልነው ይሄ በክርስቶስ ሕይወት ንጣፍነት ለሚመላለሱት የሆነና የሚሆን ኑሮ ነው፡፡ ሆኖም ግን ስለ ቁርባን ደ'ሞ በአንድ ቦታ እንዲህ ይነበባል፥

            "ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።" (ዮሐ. 6:54)

በመጨረሻው ቀን?

በሥጋ ወራት ላለ ማንም ሰው መጨረሻ ቀኑ ዕለተ ሞቱ ናት፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ከታየ፥ የመስቀል ሞቱ የዚህ ዓለም መጨረሻው ነው፡፡ ይሁን እንጂ "መጨረሻው" የሆነ ሥጋን እንደገና በትንሣኤው አስጀምሮታል (አድሶታል)፡፡ እንዲሁ፥ 'ሥጋዬን የሚበላ ደሜን የሚጠጣ፥ ቢሞትም እንኳ እንደኔ ይነሣል' የሚል ቃሉን ደ'ሞ በእርሰነቱ ላሉት ሰጥቷል፡፡
4.2K views05:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 09:51:04 በመጽሐፍ ታሪክ፥ በናዝሬት ገሊላ ከተማ የተፈጸመውም ይኸው ነበር /የሥጋን እያወራን ነን፤/፡፡ ድንግል ማርያም "እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" ካሰኛት ጽሩይ እምነት ባሻገር፥ ቃልን የምትቀበልበት ሌላ መንገድ አልነበረም፤ ሊኖርም አይችልም፡፡ መሬት ያለ ዘር የምታፈራበትን ጥበብ ቅድሚያ በእምነት እንጂ በምን ይቀበሉታል? መልአኩ ወደ እርሷ መጥቶ 'ተቀበይው' ያላትን ቃል በእምነት ተቀበለቺው፡፡ በተቀበለች ቅጽበት፥ ጸነሰቺው፤ ወለደችውም፡፡ ፊተኛው ሂደት፣ የዚህ ዓለም ጉዳይ፣ የኢየሱስ ልደት ይሄ ነው፡፡

የተወለደው ልጅ ትምህርት እየተማረ ማደጉን ይቀጥላል፡፡ በወላጆቹና በአምላኩ ፊት በሥጋና በዕውቀት (በነፍስ) ከፍ ከፍ ይላል፡፡ የዕድገቱን ደረጃ በመቀጠል ወደሚቀጥለው ይጓዛል፡፡ እስከአሁን በዕውቀትነት ከውስጡ የኖሩትን ሃሳቦች ራሱ ማብላላት፣ ማሳመክ ይጀምራል /አሁን አሁን እንኳ ይሄ የእድገት እርከን ታላቅ ማዕቀብ ተጥሎበታል፤/፡፡ ለምሳሌ እናቱን፥ እስከዛሬ ስለ እርሷ ከራሷና ከሌሎች በተቀበለው ዕውቀት በኩል ሲያገኛት ቢቆይም፥ በራሱ ማውጣት ማውረድም ውስጥ ያገኛት ይጀምራል፡፡ ይሄ ጊዜው፥ ነፍስ አወቀ (አስተሳሰቡ ነቃ) የሚባልለት ዕድሜው ነው፡፡ በመሆኑ ክፉና ደጉን ራሱ በራሱ ትርጓሜዎች መለየት ይጀምራል፤ ፍላጎትና ጠባያቱን እንደ አተያየቱ ይቀርጻል፤ ተሠርቶ የመጣ ስብዕናውን በራሱ አሠራር ያጸናል፤ ያፈርሳል፡፡ በዚህ ደረጃ ላይ ሳለ፥ አስቀድሞ በእምነት ከውጪ ያገኛቸው ዕውቀቶች፥ ማንጸሪያዎቹና ማሰቢያዎቹ ሆነው ያገለግሉታል፡፡ /አስተዳደግ እጅጉን ወሳኝ ነው የሚባለው ለዚህ ነው አይደል? ወላጆች ከወለዳችሁ አይቀር .. /፡፡

የተዋህዶ ሃይማኖታዊው አካሄድ ወይም ክፍል (ከወንዙ በፊት ያለው የሕይወት ዛፍ አውድማ) የምንለው፥ እነሆ ይሄ ከላይ በሥጋ ልደት አማካኝነት የዳሰስነው በዚህ ዓለም ስላለን ብቻ የምናውቀውን ሂደት ነው፡፡ አንድ አማኝ፥ "እንደ ቃልህ ይሁን" እያለ ቃልን በንጹሕና የዋህ እምነት ከመቀበል ይጀምራል፡፡ ተወላዲ ቃልን በእምነት ተቀበለው ማለት ይወለድ ዘንድ ጸነስነውም ማለት ነው /ድንግል ማርያምን ያዩአል፤/፡፡ ምእመን የሚጸንሰው በልቡ ነው፤ ቃልን በእምነት መቀበል የልብ ነውና፡፡ ጽንስ ደ'ሞ እስከ ጊዜ ልደቱ ድረስ ያድግ ይለወጥ ዘንድ ግድ ይለዋል፡፡ እነሆ ከውስጣችን በእምነት ጽንስነት የተቋጠረ ቃል፥ ትምህርትን ከመጽሐፍትና መምህራን እየተመገበ ያድጋል፡፡ ከፍ ከፍ ይላል፡፡ ዕድገት ደ'ሞ ወዳስፈላጊው ደረጃው እንዲደርስ ጥበቃ ያስፈልገዋል፤ መፈጸም የሚያስፈልጉና የማያስፈልጉ ነገራት ይኖራሉ፡፡ ሕግና ትእዛዛት እዚህ ይመጣሉ፡፡ አድርግ አታድርግ ወደተፈላጊው ስፍራ የሚደረገውን ጉዞ አቅጣጫ የሚያሲዙ ጥቆማዎች ናቸው *5፡፡ እና በአስተምህሮቱ መግቦት የሚያድገው ልጅ፥ አስተምህሮቱን መሠረት ባደረጉ ሕግ ትእዛዛት እየተመራ ከፍታውን ይቀጥላል፡፡

ምእመን በአስተምህሮት መልክነቱ እየወሰደ የሚያሳድገው የእውነት ቃል፥ ጌታ እንዳለው ለሚሰሙት ሕይወትም መንፈስም ነው *6፡፡ ሕይወትነቱ የኢየሱስ ክርስቶስ በመሆን ነው፡፡ ስለሆነ ቃልን ሰምተው እንደሰሙት ባዩት ልክ፥ በርሱ ኑሮ የሆነው በአማኙም ኑሮ ይሆናል፡፡ ይሄ በአማናዊ ትንሣኤው ምክንያት የሆነ ነው፡፡ ከሞት ሲነሣ ከሞቱ በፊት የኖረው ጭምር ነው አብሮ የተነሣው፡፡ ስለዚህ የሕይወተ ሥጋው ጉዞ፥ ከተያዘበት ጊዜ አጥር ውጪ የመሆን ሕያውነትን ነሥቷል፡፡ እንኪያስ ለሚቀበሉት ሁሉ፥ በስሙ ለሚያምኑት፥ የኢየሱስ ኑሮዉ ትናንት ያለፈ ታሪክ ሳይሆን አሁን የሚያዩት ህይወት ሆኖ በፊታቸው እየተገለጠ ይሄዳል *7፡፡ ወንጌልን በመረጃነት ለሚያጠናት ድሮ ናት፥ እንደማኅተም በልቡናው ክንድ ለሚያስራት ግን ዘንድሮ ናት! ለዚያውም አሁንነት ያላት ዘንድሮ!

__
*4 -
ክርስትና፥ በተለይ በሩቅ ምሥራቁ ዓለም ውስጥ ከሚዘወተሩ የዳግም ልደት (reincarnation) ሃሳቦች የሚለይበት አስተምህሮት ይሄ ነው፤ በዳግም ልደት በኩል የሚከሰተው ሌላ ማንነት ሳይሆን በቀዳሚው ልደት የመጣው ራሱ ነው ይላል፡፡ ኢየሱስና ኒቆዲሞስ ሲጨዋወቱ፥ ኒቆዲሞስ ይሄ ገብቶት ይመሰላል "እንዴት ሰው ወደእናቱ ማኅፀን ዳግመኛ ተመልሶ ሊወለድ ይችላል?" ሲል የጠየቀው፡፡ ክርስትና በሥጋ ልደት የተገለጠው አካላዊ ማንነት ወደ መንፈስ ልደት ይሻገራል እንጂ በሥጋ እንደገና አይወለድም እያለ ያስተምራል፡፡ የሩቅ ምሥራቅ እምነቶች በበኩላቸው ወደ ሌላ አካል፣ ወደ ሌላ ፍጡርነት በመቀየር ዳግም ልደት ይከናወናል ይላሉ፤ ከሥጋ ወደ ሥጋ አልሸሹም ዘወር አሉ ነገር፡፡

*5 - ህግና ትእዛዝ ግብ አስፈጻሚ ባለተልዕኮዎች መሆናቸው ተረስቶ በራሳቸው ግቦች ሆነው ካረፉ ትንሽ ሰነባብቷል፡፡ በዛሬይቱ ዓለም በሃይማኖታዊ ተቋማትም ሆነ በሌሎቹ ዘንድ፥ ለአንድ ሃሳብ የመጨረሻ ፍጻሜ ሲባል የተፈቀዱ ትእዛዛትና የተከለከሉ ህግጋት የሃሳቡን ፍጻሜ ከጥግ የሚያደርሱ መሆናቸው ተዘንግቶ ነገር ዓለሙ ሁሉ ደንቦችን ብቻ የመከተል ያለመከተል ግብዝነት ሆኗል፡፡ ህግ ምሪት ናት፤ በሙሴ ትወከላለች፡፡ ሙሴ ደግሞ አገልግሎቱ ወደ ከነዓን ነው፡፡ ከነዓን የሌለው ሙሴ የለም፡፡ አሁን ግን የሆነው፥ ሙሴን የምንከተለው በከነዓን ምክንያት መሆኑ ቀርቶ ትክክልነት ሙሴ በሄደበት መሄድን ማስመሰል "ስለሆነ ነው"፡፡ ህግ ያለ አንዳች ፍጻሜ ወግ ብቻ ናት፡፡ ተማሪ አታጥና እና አጥና በሚሉ ጥንድ መርሆች ወደፊት የሚሄደው ላሰበው ውጤት ካልሆነ ምን ጥቅም አለው? በተለይ ሃይማኖቶች ያው እንደምናየው የወግ መናህሪያ ሆነዋል፡፡ ጉዳዩ፣ ፍጻሜው፣ አድራሻው በውጪም በውስጥም ወደምትገለጽ ልዩ መንግሥት፣ ጠቅላይ ሥርዓት፣  ከምንም በላይ ምሉዕ ወደ ሆነ ፍቅር መግባት መሆኑ ከነአካቴው ጠፍቶ፥ በየዓመቱ ዓሣ ይበላል አይበላም በሚል መሰል የተራ ተራ ሙግት ውስጥ ለዝቅጠት መቧጠቅ ሆነ፡፡ 

*6 - ይህ ቃል፥ ወንጌለ እግዚእ ነው፤ ሌሎቹ አስተምህሮቶች ሁላቸው በወንጌል ማዕከላዊነት የተያዙና በዙሪያው የሚዞሩ ናቸው፡፡

*7 - ጳውሎስን "ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት፤" ያስባለው ይህ ነው፡፡ (1ኛ ቆሮ.15፥14) የእርሱ የሥጋው ወራት ኑሮ እንደማንኛውም ሰው በሞት ተደምድሞ ቢሆን ኖሮ፥ ነገሩ ከአግራሞት ባሻገር ምንም ነበር፤ ጠቢቡ ከፀሐይ በታች ሁሉ የከንቱ ከንቱ ነው ያሰኘው፥ ነገር ሁሉ በሞት ስለሚጠናቀቅም አይደል? በዓለም ውስጥ ብዙ ለሰው ልጆች የሚሆኑ ጠቃሚ ሃሳቦችን፣ ሥራዎችን ለየትውልዳቸው የሰጡ ብሩህ አእምሮዎች ነበሩ፤ ይኖራሉም፡፡ ይሁን እንጂ ያለፉቱ በሞት በመሸነፋቸው ምክንያት፥ ያሉትም ቢሆኑ በሥጋ ሕግ ከመያዛቸው የተነሣ፥ የህይወታቸው ውጤት በሆነ ሥራቸው መገልገል እንጂ በህይወታቸው መስመር ዘልቀን፣ በኑሮአቸው ጊዜ ገብተን የኖሩትን መኖር አንችልም፡፡ የልባቸውን ፍሬ እንጂ ልባቸውን ማግኘት አንችልም (የክርስቶስን ልብ ግን እንችላለን)፡፡ በሞትና በሥጋ ሕግ ተዘግተዋልና፡፡ የማርያም ልጅ የተለየው ይህን ዝግ ማኅተም በመክፈቱ ነው፡፡ ከሞት በመነሣቱ ምክንያት የተዘጋውን የኅልውና ቁልፍ ከፍቶት፥ በርሱ የኑሮ ጊዜ፣ የህይወት መስመር ውስጥ ገብተን የኖረውን እንድንኖረው ሆነልን፤ ታዲያ ወደርሱ ዓለምነት ማለፊያ በሩ ዳግም ልደት ነው፤ ለዚህ ልደት መጸ'ነሻዋ (ጥምቀት)፣ መጋቢዋ (ቁርባን፣ ትምህርት) እና መውለጃዋ (የመስቀል መከራ) መንፈሳዊቷ ማኅፀን ደግሞ ወንጌል ናት፡፡

ይቀጥላል ...

@bemaleda_neku
6.3K viewsedited  06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 09:50:10 የቀጠለ ..

               "ቃል ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ"፡፡ (ዮሐ. 1፥14)
            
ይሄ የአንድ ምእመን ኑሮ ነው፡፡ አንዳንዶች ምእመናን ሲሰበሰቡ ኅብረት ይፈጥራሉ፤ በዚያም ኅብረት በኩል ወደ አንድነት ያድጋሉ፤ ወደ ቤተክርስቲያንነት እንደማለት!

እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን ሙሉውን የተዋኅዶ ጉባዔ የምትኖርበት መክሊት አላት፡፡ ቃል ሥጋ ሆነ ብላ የጀመረቺውን ጉዞ በጸጋና እውነት ሙላት ትፈጽማለች፡፡ ከገሊላ እስከ በዓለ ኀምሳ የሚረዝመውን የሕይወት፣ የእውነት መንገድ ትሄድበታለች፡፡ ምእመንም እንዲሁ እንደ ልቡ ርዝማኔ ይጓዛል፡፡ መንገዱን ሙሉውን ከተጓዘ በጉ በሄደበት ሄዷል ማለት ነው፡፡ እርሱ የ144ሺው ልዩ ትውልድ አካል ነው፡፡ (ዮሐ. 14፥3)

ጉዞው በመካከሉ ላይ ወንዝ እንደሚገጥመው አውስተናል፡፡ ወንዙን በክርስቶስ ሕይወት ስናየው የመስቀል ሞቱ ነው፡፡ ኢየሱስ የተጎነጫትን ይህቺ ጽዋ ለተቀበሉት ሁሉ አሳልፏልና፥ ከኋላ የሚከተሉ ምእመናንም ከጽዋዋ ይጎነጫሉ፡፡ ልደቱን፣ ዕድገቱን፣ አገልግሎቱን በሕይወታቸው እያዩ ይቆዩና ሞቱንም እንዲሁ ያያሉ፡፡ በርግጥ የሞት ሽታ የሚከባቸው ከቤተልሔም ጀምሮ ነው /እንደተወለደ ስደት እንደተከተለው ያስቧል፤/፡፡ ይሄ፥ ቀዳማዊው፥ በጉባዔ "አምላክ ሰው ሆነ" ሲል መሠረቱን ያኖረው፣ በዓለማት አንጻር "ከሚታየው ወደማይታየው" የሚወስደው፣ በአንድ ሰው አእምሮና ልቦና ዐውድ ደግሞ "ከውጪያዊ ወደ ውስጣዊ ዕውቀት" ሊጠልቅ የሚጓዘው፥ ሃይማኖታዊው ሂደት ነው፡፡

ሃይማኖት በዋነኝነት በሦስት ነገሮች መልኩ ይገለጻል፡፡ አንድን ሃይማኖት ሃይማኖት የሚያሰኙት እነዚህ ሦስቱ የተሟሉ ሲሆኑ ነው፡፡ እነርሱም አስተምህሮት፣ ሕግና ትእዛዛት እና አምልኮት ናቸው /ሦስተኛውን መንፈሳዊ ሰውም ይጋራዋል፤/፡፡ እነዚህ ሦስቱ ለሃይማኖት መሠረቶቹ ናቸው፡፡ ያለነርሱ ሃይማኖት መኖር፣ መቀጠል አይችልም፡፡ አስተምህሮት ከሌለ፥ ሃይማኖት ሊታወቅ ብሎም ሊስፋፋ አይችልም፡፡ አድርግና አታድርግ የሚላቸውም ደንቦች ከሌሉት፥ መስመር እንዲሁም ግብ አይኖረውም፡፡ በመጨረሻ ኅልውናውን የሚያሳርፍበት፣ ከማይታየው የሚገናኝበት፣ በአስተምህሮትና በደንቦች ለምእመናኑ የሚያቀብለውን የሚያገኝበት፣ የሚያሠርጽበት ሲልም በኑሮና መንፈሳዊ ኃይል የሚተረጉምበት የአምልኮ ሥርዓት የግድ ያስፈልገዋል፡፡

በአስተምህሮቱ ዘርፍ ቅዱሳት መጽሐፍት ትልቁን ሚና ይጫወታሉ፡፡ ሕግና ትእዛዛትም በመሠረትነት ከነኚሁ መጽሐፍትና በመጽሐፍቶቹ የክብር ደረጃ ባሉ ሰዎች ከተሰጡ ደንቦች ይወጣሉ፡፡ በሥርዓተ አምልኮት በኩል፥ መሥዋዕት፣ ንዋየ ቅዱሳት፣ መንፈሳዊ ልምምዶች ተጠቃለው ይገኛሉ፡፡ ሃይማኖት ከብዙ በጣም ጥቂቱ ይሄን ይመስላል፡፡

ሃይማኖት በመንገድነት አብዛኛውን ይመሰላል፡፡ መንገድ ከሆነ አድራሽ እንጂ አድራሻ አይደለም ማለት ነው፡፡ መንገድ ሂደት ነው፤ በራሱ ጫፍ አይደለም፡፡ መንገድ ካለ መጓዝ አለ /መንገዱ በእምነት የሚሄዱበት ነው፤/፡፡ አስተምህሮት፣ ሕግጋትና የአምልኮ ሥርዓት ጉዞዎች፣ ወሳጆች ናቸው፡፡

ታዲያ 'ሁሉም' ሃይማኖቶች ወሳጅነታቸው ከሌሎች ዓለማት ጋር በጥብቅ ይገናኛል፡፡ እነ 'ገነት፥ መንግሥተ ሰማያት፣ ሲዖል፥ ገሀነም' ዋናዎቹ የተስፋ ጉዳዮች ናቸው፡፡ በመሆኑ የአንድ መደበኛ ባለ ሃይማኖት ሰው የመጨረሻ ሃሳብ፥ በማይታዩቱ ዓለማት ዕጣ ፋንታ ላይ የተመረኮዘ ነው፡፡ እስቲ በተዋሕዶ ቤት ያለን የሃይማኖት ዝርዝር ገጽታ ለመቃኘት እንሞክር፡፡

በተዋሕዶ፥ ከጽንሰት እስከ ሞት ያለው፥ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደመጣ የሚታመንበትን ክፍል፥ ሃይማኖታዊው ክፍል ነው፡፡ የዚህ ሃይማኖት አስተምህሮት፣ ሕግጋትና አምልኮት በቃል ላይ መሠረቱን ይጥላል (መሥራቹስ አካላዊ ቃል አይደለ?)፡፡ ባለ ቃሉ ስለ ከፍተኛው ዓለም ሲናገር ፦

            "እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት (የማይታየውን ዓለም) ሊያይ አይችልም .. ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህ አታድንቅ። .. ስለ ምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ፥ ስለ ሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ?" (ዮሐ. 3)

ዳግም ልደት ለአድራሻው ታላቅ ዓለም፥ እንደ ይለፍ ፈቃድ ሆኖ በዚህ ንግግር ተገልጿል፡፡ ዳግም ልደት ስያሜውም እንደሚገልጠው እንደገና መወለድ ነው፡፡ ይህ ሲብራራ ማለት፥ ሰው እንደገና ሲወለድ፥ በሥጋ የተወለደበትን የመጀመሪያ ልደት አስጠብቆ ወደ መንፈስ ልደት ይሻገራል (ይታደሳል) እንጂ፥ ተለውጦ ሌላ ሰው አሊያ ፍጡር አይሆንም /የተነሣው ክርስቶስ የሞተው ኢየሱስ ነውን አስታወስክ?/ *4፡፡ ወይም 'እንደገና' ከተባለ፥ በሥጋ ልደት የታየው በመንፈስ ልደትም ላይ ድጋሚ ይታያል ማለት ይሆናል፤ ወይም ምድራዊውና ሰማያዊው አወላለድ በይዘት አንድ ናቸው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ምድራዊው በደንብ ከገባን ሰማያዊውም የሚገባን ነውና ለመንፈሳዊው አወላለድ መረዳት የሚሆነንን ሥጋዊውን እንየው፡፡

የሥጋ ማንኛውም ልደት፥ ማኅፀን እና ጊዜ የሚባሉ ዋነኛ ነገሮች አሉት፡፡ ሰው፥ በእናቱ የማኅፀን ጎዳና አልፎ፥ በልደት በኩል ወደ ጊዜ ይገባል፤ በሰማይ ብርሃናት የሚሰላ ዕድሜውን ይጀምራል፡፡ ለምሳሌ የኢየሱስን ዕድሜ 33 ዓመት ብለን የቆጠርነው፥ የቤተልሔም ልደቱን አንድ ብለን ጀምረን ነው፡፡ ይሄ ባሕርያዊ ህግ ነው፡፡ በማኅፀን ይቋጠራል፤ በልደት አድርጎ ወደዚህ ዓለም ይመጣል፤ የመምጣቱም መነሾ የጊዜውን ስፍር ያስጀምራል፡፡ ከሥጋ የሚወለድ ሥጋ ሁሉ፥ እንዲህ ይመላለሳል፡፡

እንዲሁ በመንፈስ ልደትም ማኅፀንና ጊዜ አሉ፡፡ ሰው ዳግም በሚወለድበት በመንፈስ ማኅፀን ተጸንሶ ሲያጠናቅቅ፥ በዳግም ልደት አልፎ ወደ ሌላኛው ዓለም ይሄዳል፡፡ ወይም የመንፈስ ልደት በሚያዘልቀው የጊዜ መስመር ውስጥ ይገባል፡፡

ልደት፥ የተወላጁ አካል ወደ ጊዜ መግቢያ በር ነው፡፡ ሃሳቡን ወደ ሥነ ፍጥረት ብንስበው፥ አንድ ነገር ተፈጠረ ማለት ወደ ጊዜ ገባ ማለትን ያመጣል፡፡ የእግዚአብሔር የመፍጠር ነገር፥ በፍጥረታት የመውለድ ነገር ተንጸባርቆ ይታያል፡፡ ፈጣሪ በእናትነት አንቀጽ የሚገለጽበትም ዋና ምክያት ይሄ ነው፡፡ ለማንኛውም ልደት ካለ፥ የሚገባበት ጊዜ (የሚዘለቅበት ዓለም) አለ፡፡

እንደሚታወቀው፥ በሥጋ ወደዚህ ዓለም የተወለደ ልጅ ዕውቀት ይዞ አይወለድም፡፡ ቃል (ቋንቋ) የለውም፡፡ ቃል ከሌለው ሃሳብ የለውም /ሃሳቡን አይገልጽም የሚለው ይመረጣል፤/፡፡ ውጨኛውን ዓለም የሚያውቅበት ዕውቀት ወደ ውስጡ አልገባም፡፡ ስለዚህ ቃል ከውጪ ወደ ውስጥ ይነገረዋል፡፡ ከቅርቡ ጀምሮ ያሉትን አንድ በአንድ እያገናዘባቸው እንዲሄድ ትምህርት ይሰጠዋል፡፡ እርሱም በእምነት እየተቀበለ ዙሪያውን እየተረዳ ያድጋል፡፡ ከእምነት በቀር ሌላ ቃልን የመቀበያ መንገድ የለውም፤ ለምሳሌ አንዲቱ ሴት እናትህ ናት ሲባል እናትነቷን በእምነት ተቀብሎ ያድጋል፡፡
4.9K views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:23:24 ከዚያ ለ40 ቀናት ያህል በትንሣኤው እየተገለጠ በመመላለስ ካገኛቸው ኋላ፥ ወደ ዕርገቱ ሥርዓት (ወደ ዐሥሩ ቀናት) ቀጥሎ ሄደ፡፡ "ወደ አባቴ እሄዳለው" እንዳለ፥ ወደ አብ ከፍ ከፍ አለ፡፡ እነርሱ ውስጥ በቃል፣ በሥጋ ደሙ የተነሣላቸው እርሱነቱም በዚያው አንጻር እንዲሁ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ወደ ባሕርያቸው ጥልቀት ዘለቀ፡፡ ቃል ወደ ወላጁ ወጣ፡፡ የቃል ወላጅ ልብ (አብ) ነው፡፡ በነርሱም ያለ የቃል ባሕርይው ወደ ልባቸው ምስጠት ገባ፡፡ ስለዚህ ጠቅላዩ ሃሳብ ታሰባቸው፤ ልዑሉን ፈቃድ ፈቀዱት፤ የመጨረሻው ጽሩይ ድምፅ ኅሊናቸውን ሞላ፤ የምልዓትን አስተሳሰብ በአርምሞ ከበሩበት፤ በመቼት ባልተገደበ እንዲህ እንዲያ ተብሎ በፍጡር ቋንቋ በማይገለጽ ጽማዌ ለ10 ቀናት ያህል ቆዩ፡፡ /ወይንም 10ሩን የጽድቅ (የመርቀቅ) ማዕረጋት ደረጃ በደረጃ ተመለከቱ፤/

በ10ኛው ቀን ቅዱስ አካላዊ መንፈስ ከሁሉ አባት ዘንድ ወረደ *3፡፡ በነርሱ ያለውን የሚገልጽ ለዓለም የተሰወረ አካል፥ ያለፈውን ሊያጸናላቸው፣ የሚመጣውን ሊያሳስባቸው ወረደ፡፡ በዚህ ስለዚህ መለኮታዊ ልዩ ምሪት፣ ልዩ ኃይል ተከናወነላቸው፡፡ ከልቡና የሚፈልቅ ህያው ዕውቀት ውስጣቸውን ሞላ፡፡ የማያባራ ንጋት አገኛቸው፡፡ ጸጋን ለበሱት፤ እውነትም ከፊት ታየቻቸው (10ኛውን ማዕረግ 'ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ' ይሉታል)፡፡ በሕይወት ውኃ ወንዝ ወዲያም ወዲህም የሚያብቡትን የብርሃን ፍሬዎች ለቀሙ፡፡ ስብዕና በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ አንቀጽ ተሠርታ እንዲህ ተፈጸመች፡፡ እነሆ ይህን ሙሉ ገባዔ የተካፈለ ከመካከላቸው የነበረም ሰው እንደሚከተለው ጻፈ፥

         "ቃል ሥጋ ሆነ፤ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ" (ዮሐ. 1፥14)
        

____
*1 - ስያሜ ከማንነትና በተሰየመው ማንነት ላይ ከሚገለጥ ግብር ጋር በዋናነት ይጎዳኛል፡፡ ኢየሱስ የሚለው፥ ቃል ሥጋ በመሆኑ ምክንያትነት ለተለገለጠው ግላዊ ማንነት የተሰጠ ልዩ የተጸውዖ ሰም ነው፤ ልክ ሰዎች በየራሳቸው መጠሪያ "አብርሃም፣ ዳዊት፣ ሰሎሞን፣ .." እንደሚሰኙት፡፡ (ሉቃ. 1፥31) ህይወተ ሥጋው ላይ የሚተርኩ አራቱ ወንጌላት "ኢየሱስ" የሚለው ላይ አትኩረው በየቦታው የሚጠቅሱ ለዚያ ነው፡፡ ክርስቶስ ሲባል ግን በዚህ በኢየሱስነት በተጠራ ማንነት ላይ ይገለጥ ዘንድ ላለው የሹመት ግብር፥ ስያሜው ነው፤ በትርጉሙ የተቀባ ማለት ነው፡፡ ይሄ ስያሜ፥ ከመስቀል ሞት አስከትሎ በቀጠለው የትንሣኤና የዕርገት ስውር ጉዞ ለተገለጠው ሁለንተናዊነት ማንነት መግለጪያ ሆኖ በተለይ በጳውሎስ ተደጋግሞ ይጠቀሳል (ጳውሎስ ከአራቱ ወንጌላት ቀጥሎ እንደሚመጣ ያስተውሏል፤ እርሱ ከህይወተ ሥጋው ታሪክ ይልቅ በትንሣኤው የሆነውን ያስተምራል)፡፡ በአጭሩ ኢየሱስ፥ ቃል እኛን የሆነበትን፥ ከቤተልሔም እስከ ቀራኒዮ ተገልጾ በሥጋ የታየውን አንድ ሰውነት በግላዊ ማንነት ይጠራል፤ ክርስቶስ፥ በዚህ ማንነት ላይ የተሾመውን ህያውና መንፈሳዊ አገልግሎት አማክሎ ይገልጻል፡፡ (ማቴ. 8፥29) ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉዉ ስያሜ ሲጠራም፥ ሙሉዉን ጉባዔ ከስሙ ኋላ ይዞ ይከስተዋል፡፡

*2 - እርግጥ 'በዚህ ዓለም ሕግ' ሥር ከተባለ፥ መስመሩ ከፅንሰት ሳይሆን ከልደት ነው የሚጀምረው፡፡ ያልተወለደ ፅንስ እስኪወለድ ድረስ የሚኖርበት ማኀፀን፥ ዓለሙ እንደሆነለት ያጤኗል፡፡ ሕፃኑ፥ ከዚህ የማኀፀን ዓለም በልደት በኩል አልፎ ወደዚህ ዓለም ይገባል፡፡ በመሆኑ አሁን ስላለንበት ተጨባጭ ዓለም ሕግ ከተነሣ፥ ከልደት እስከ ሞት ድረስ ያለውን ጎዳና ይመለከታል፡፡

*3 - መንፈስ ቅዱስ መውረዱ የተጠናቀቀው በ10ኛው ቀን ስለሆነ፥ በደፈናው "በሐምሳኛው ቀን (በዓለ ሐምሳ) ላይ መንፈስ ወረደ" ይባላል እንጂ፥ ጌታ ለደቀመዛሙርቱ "ወደ አባቴ እኔ ስወጣ ወደእናንተ ደግሞ መንፈስ ይመጣልና ጠብቁ" ካለበት ተነሥቶ ነው መውረዱ የጀመረው፡፡ (ሉቃ. 24፥49) በሌላ አቀራረብ፥ ኃይልን እስኪለብሱ ድረስ ሐዋሪያት የጠበቋቸው ዐሥሩ ቀናት፥ የመውጣትና የመውረድ ጊዜያት ናቸው፡፡ ነገርየው ትይዩ የዕርገትና የርደት ጉዞ ነው፤ ወደ ላይ ወደ አብ ቃል እየወጣ እየወጣ ሲሄድ፥ ወደታች ደግሞ ከአብ የሚወጣው መንፈስ እየወረደ እየወረደ ለሰዎች መጥቷል፡፡ ለመንፈስ እንደ ሥጋ ውጣ ውረድ የለበትም፤ መገለጽ ያለመገለጹን በሰው ሰውኛ ማውሳት ነው፡፡

ይቀጥላል ...


@bemaleda_neku
7.1K viewsedited  08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 11:22:49 ጉባዔ ዘተዋሕዶ

(የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 22)
----
1፤ በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ።
2፤ በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፥ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።

ሃይማኖትን መንገድ ይሉታል፡፡ ከየት ወደየት የሚወስድ? ከሚታየው ወደ ማይታየው፣ ከገዘፈው ወደ ረቀቀው፣ ከዚህ ዓለም ወደዚያኛው ዓለም፣ .. ፡፡ በሰው ማንነት ስናየው፥ የሚታየው፣ የገዘፈው፣.. የሚሰኙት ዐለባውያን የሥጋ ናቸው፡፡ በተቃራኒው የማይታየው፣ የረቀቀው እያልን ካወሳን ነፍስን፣ መንፈስን ወደተመለከተው እንሄዳለን፡፡ እስቲ ሐሳቡን ዘርዘር እናድርገው፡፡

በተዋህዶ ቤት የሚነገረው "አምላክ ሰው ሆነ፥ ሰውም አምላክ ሆነ" የሚለው ጉባዔ ከፅንሰት እስከ ዕርገት ድረስ የተዘረጋ ነው፡፡ ይሄ ጉባዔ በመሠረትነት ለሁለት የተከፈለ ነው፡፡ አምላክ ሰው ሆነ በሚለው ቀዳሚው፥ የእግዚአብሔር ልጅ የሰውን ልጅ ይሆን ዘንድ የተገለጠበትን ይተርካል፡፡ የሰው ልጅ የሥጋ ሕይወት በርዝማኔ ቢለካ፥ ከፅንሰት እስከ ሞት ይደርሳል፡፡ እንጸነሳለን፣ እንወለዳለን፣ እናድጋለን፣ .. ከዛ እንሞታለን፡፡ ይሄን የኅልውና ሥርዓት፥ ተፈጥሮአችን ያውቀዋል፡፡ በመሆኑ የአምላክ ልጅ የሰውን ልጅ ሆነው ስንል፥ እዚህ የባሕርይ መስመር ውስጥ ሳያዛንፍ ገባ እያልን ነው፡፡ ስለዚህ በሥጋ ማኅፀን ተጸነሰ፣ በሥጋ ተወለደ፣.. እያልን በሰው አንቀጽ ከገሊላ እስከ ቀራኒዮ የተጓዘውን ጉዞ እንተርከዋለን፡፡ /ታሪክ የሥጋ ነው፤/

ታዲያ ጎለጎታ ላይ ተፈጥሮአችን የሚያውቀው ይሄ የሰውነት ጉዞ በሞት ይዘጋል (ሕልም ብናይ፥ አእምሮአችን ሞትን በህልውና ስለማያውቀው ልንሞት ስንል ይነቃል፤ እንባንናለን)፡፡ ይሁን እንጂ ማንም የማይዘጋውን በሚከፍት ኀይለ ጥበብ የኢየሱስ የሞተ ሥጋው ከመቃብር ተነሥቷል፡፡ ይህ በመሆኑ ምክንያት፥ ከፅንሰት - ሞት የሚሄደው ባሕርያችን በዚህ ዓለም የማያውቀውን አዲስ እንግዳ ነገር ሊያይ ችሏል፡፡ እንደተነሣም አስቀድሞ ሲመራቸው ወደነበሩት ወዳጆቹ ገስግሶ ቀድሟል፡፡

የተነሣው ክርስቶስ የሞተው ኢየሱስ ነው *1፡፡ ግን የተነሣው እርሱ ሳይሞት ከነበረው የሚለይበት ዋነኛ ነገር አለ፡፡ ይኸውም ሞት የመጨረሻው የነበረ ሥጋው፥ ሕይወትን አግኝቷል፡፡ በፅንሰት ተጀምሮ በሞት የሚጠናቀቀው ሥጋ፥ የወትሮ ፍጻሜው፥ ልዩ መነሻው ሆኖለታል፡፡ ይሄ የትንሣኤ ሥጋ አዲስ አካል ነው፤ ከእንግዲህ የማይሞት፣ የዚህ ዓለም ማንኛውም ሕግ የማይይዘው አዲስ ማንነት ነው፡፡ እንግዲህ ደቀመዛሙርቱን ሊያገኝ በትንሣኤው ሥርዓት ሆኖ ወዳሉበት ሲሄድ፥ በዚህ ልዩ ኅልውናው ሆኖ ነው፡፡ አግኝቶም እንደገና ጠርቶ ለአንድነት ሰብስቧቸዋል፡፡ ለጥቆ ወደ ቢታንያ ኮረብታ አውጥቶ ባረኳቸዋል፡፡ በመጨረሻም እንደማይለያቸው ነግሯቸው እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ወደ ሰማያት ዐረገ (ወደ ዘላለምነት፣ ወደ ምልዓት ወጣ)፡፡ ይሄ ሁለተኛው ጉዞዉ ነው፤ ከሞት - ዕርገት የተለካው!

በመግቢያችን፥ በአደባባይቱ መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን፣ እንደ ብርሌ የሚያንጸባርቀውን የሕይወት ውኃ ወንዝ ዮሐንስ በራእይ ሲያየው አይተናል፡፡ በዚህ ወንዝ ወዲህና ወዲያ ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ አዝመራ አለ፡፡ ይሄ በወዲህና በወዲያ የሚያፈራው አዝመራ፥ ከላይ በመስቀል ሞት መካከልነት የከፈልነው የኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ጉዞ ነው፤ አንዱ የትሕትናው አንዱ የልዕልናው ጉዞ፡፡

 ከፅንሰት                                                  ከመስቀል
     እስከ                |       ወንዙ        |               እስከ
   መስቀል         | (ቁርባን ፤ ሞት) |             ዕርገት
(ለዚህ ዓለም የሚታየው)       (ለዚህ ዓለም የማይታየው) 
                    
በወንዙ ወዲህ ማዶ (ከሞቱ በፊት) ተዘርቶ የሚለቀመው ፍሬ፥ የሥጋውን ወራት በረከቶች ይመለከታል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ባሳደዱት ተይዞ እስኪገደል ድረስ በእርምጃዎቹ ሁሉ ፈውስን፣ ትምህርትን፣ እውነትን እየሰጠ ለብዙዎች አገልግሏል፡፡ የተጠሩት ተማሪዎቹም፥ በዋለበት እየዋሉ፣ ባደረበት እያደሩ ቃሉን ሰምተዋል፤ ሥራውን ታድመዋል፡፡

ሐዋሪያቱ እንደየትናንታቸው አስተሳሰብ የሚለውን፣ የሚያዩትን ለመረዳት ይጥሩ ነበር፡፡ ጥያቄ ይጠይቁታል፤ እርሱም ይጠይቃቸዋል፡፡ ያስረዳቸዋል፡፡ ደ'ሞ የምነግራችሁን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም ይላቸዋል፡፡ እነዚህ ተማሪዎች ከፊት ፊታቸው እንደሚቀድመው መምህራቸው በሥጋ ያሉ መሆናቸውን እዚህ ልብ የምንለው ጉዳይ ነው፡፡ ወይም ከፅንሰት - ሞት ብለን በዘረጋነው በዚህ ዓለም ሕግ ሥር ያሉ ናቸው *2፡፡ ስለዚህ አረዳዳቸው፣ አኳኋናቸው፣ ሁለንተናቸው በዚህ ዓለም ቅኝት የተቃኘ ነው፡፡ እንደሚበሉት፣ እንደሚጠጡት ግዘፍ የነሣ እህል ውኃ ግዘፉን ብቻ ያስባሉ፡፡ ከሚታየው ባሻገር ስለሆኑ ጉዳዮች የሚነግራቸው ነገራት እምብዛም አይገባቸው ነበር፡፡

በየሚሄድበት እየሄዱ የተከተሉ ደቀመዛሙርቱ፥ ጉባዔያቸው በጊዜ ሞቱ ተናጠቀቀ፡፡ አበው የዚህን ጉባዔ መጠናቀቅ "ትምህርት በሰው ልቦና ተከተተ" ሲሉ ይገልጹታል፡፡ እያወጣ እያወረደ፥ በሚሥጢር፣ በግልጽ፣ በምሳሌ ሕይወትነት ያለው መንፈሳዊ ቃሉን በልባቸው ሲዘራ ቆይቶ፥ በመስቀል ተገደለ፡፡ ሐዋሪያቱ ተስፋ ያደርጉበት አስተማሪያቸውን በአደባባይ ተነጠቁ፡፡ ተስፋቸው በሞቱ ሞተ፡፡ ተስፋ ከሞተ፥ የነገራቸውም ሃሳብ አብሮ እንደሚሞት አያጠይቅም፡፡ በልባቸው የተዘራ ቃሉ አፈር ገባ፤ ከመሬት ተሸፈነ፡፡ ስለዚህ ሰብሳቢያቸውን ካሳደደባቸው ዓለም ሸሽተው በር ቆልፈው ተቀመጡ፡፡ እነዚህኞቹ ሐዋሪያት፥ ማንኛውም በሃይማኖት አስተምህሮትነት እየተጓዘ፥ በሕግ በትእዛዛት እየተመራ፥ በአምልኮ ሥርዓት ውስጥ እስከ ሥጋ ደሙ (ቁርባን) የሚገሰግስን ትጉ አማኝ ይወክላሉ፡፡ /ሥዕሉን ይመለከቷል፤/

ይሁን እንጂ ሥጋ ደሙን ወስደው ደጃቸውን ዘግተው ከዓለም የጠፉት ደቀመዛሙርት፥ መሪያቸውን እንደገና በትንሣኤው ያገኙታል፡፡ በዝግ ደጅ ገብቶ ባሉበት ያገኛቸዋል፡፡ (ዮሐ 20፥19) 'በተዘጋ በር ሳይከፍት አለፈ' ከተባለ፥ ተጨባጭ የሚዳሰስ አካሉ በዚህ ባለንበት ጠጣር ዓለም የጊዜና የቦታ አውታር ሥር እንዳልተያዘ እረዳለን፤ ወይም በሌላ አነጋገር ሥጋው መንፈስነትንም እንደተዋሐደ እንገነዘባለን፤ ግዘፍነቱን ያለቀቀ ረቂቅ ሥጋ!

እንግዲህ ከሞት ከተነሣ በኋላ ወደነርሱ በመምጣቱ ምክንያት፥ የሞተባቸውም ተስፋ እንኪያስ ይነሣላቸዋል ማለት ነው፡፡ በልብ በአእምሮአቸው የታተመች እርሱነቱ፥ በመነሣቱ ተነሥታላቸዋለች፡፡ ከሞቱ ቀድሞ ያስተማራቸውም ሁሉ ኀልውናን በነርሱ አገኘ፡፡ በቁርባን ሥርዓት በሰውነታቸው የተቀበረ ሥጋው ደሙ ከባሕርያቸው ተነሣላቸው፡፡ እነሆ ስለዚህ፥ በሰውነት ያለን ሕያውነት ሊሰሙት ቻሉ፤ የሞትን አስፈሪነት ናዱት፤ ድንበርነቱንም ውስጣቸው ተሻገረው፡፡ በዚህ ሳያበቃ አእምሮአቸው ደ'ሞ ያስተውል ዘንድ ተከፈተ፡፡ (ሉቃ. 24፥45) አስቀድሞ በኅቡዕ የጻፈባቸው ሁሉ በዕውቀትነት ተተነተነላቸው፤ ሚሥጢር ተጨበጠላቸው፤ ምሳሌ ተፈጸመላቸው፡፡ እነዚህኞቹ ሐዋሪያት ቀድመው ከተሰበሰቡበት ይለያሉ፡፡ የማይሞት መምህር እንደገና ጠርቷቸዋልና የማይሞት ሃሳብን ተቀዳጅተዋል፡፡ ትንሣኤ ልቡናን፣ አእምሮ መንፈሳዊን አግኘተዋል፡፡ በስውር በግልጥ፣ በሥጋ በመንፈስ ላይ ሕዋሶቻቸው ሰልጥነዋል፡፡
6.0K viewsedited  08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ