Get Mystery Box with random crypto!

በማለዳ ንቁ !

የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaleda_neku — በማለዳ ንቁ !
የቴሌግራም ቻናል አርማ bemaleda_neku — በማለዳ ንቁ !
የሰርጥ አድራሻ: @bemaleda_neku
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 18.24K
የሰርጥ መግለጫ

(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ምዕ. 13)
----------
11፤ በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ደኅና ሁኑ። ፍጹማን ሁኑ፥ ምክሬን ስሙ፥ በአንድ ልብ ሁኑ፥ በሰላም ኑሩ፥ የፍቅርና የሰላምም አምላክ ከእናንተ ጋር ይሆናል።
14፤ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን፡፡
@bemaledaa_neku_bot

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-06-10 11:47:24 ወዳለንበት ዓለማዊ ሥርዓት የመጣነው በሥጋ ፈቃድ በመሆኑ ዓለም ላይ በመታየት የሚመላለሱት ብዙ ነገራት ለሥጋ ሕዋሳት የቀረቡ ናቸው፡፡ መንፈስ ደግሞ ሥጋና ደም የሌለው እንደ መሆኑ ከላይ የተዘረዘሩትን ክፉ መገለጫዎቹን ለመግለጥ፣ ለመወከልና ለማስተዋወቅ የሚያስችል ማደሪያ የሚሆነውን ግዙፍ አካል ይፈልጋል (ከጥንት ጀምሮ ምስል ቀርጸው ጣዖት የሚሠሩለት ለዚህ ነበር፥ ነውምም)፡፡ በዚህ ሐቲት መሠረት ክፉ መናፍስት በሥጋዊ አካላችን ሲያድሩ ክፉ መገለጫዎቻቸውን በተጨባጭ በኛ በኩል ይገልጻሉ ማለት ይሆናል፡፡

ዲያቢሎስን መዋጋት ክፉ ማንነትን መዋጋት ነው ያስባለኝ ይሄ ጉዳይ ነው፡፡ ይሄንን በውል ያልተረዱ አንዳንዶች መናፍስትን ለማስወጣት ጸበል ይጠመቁና በመመለሻቸው መንገድ እያቀኑ ሳለ ሐሜት ያወራሉ፡፡ ክፉዎቹን ለመዋጋት ጾም ጸሎት ይይዙና በጎረቤታቸው ስኬት ይቀናሉ፡፡ ዲያቢሎስን ለማድከም ሲሰግዱ ይውሉና ቤታቸው ያለች ሠራተኛቸውን ያመናጭቃሉ፡፡ እንዴት ነው ነገሩ! በዚህ ክፉውን ለመዋጋት በዚያ ክፉውን ስንገልጠው፥ የትኛውን ክፉ ነበር ልንቃረን የፈለግነው?

ይሄን ልብ እንበለው..

ክፉ መንፈስ የማንነት ክፉ መገለጫዎቹን በሥጋ ላይ ለመግለጥ በአብዛኛው መቼትን (መቼ እና የት) አድብቶ ይጠብቃል፡፡ ቦታና ጊዜን ማለት ነው፡፡ አጋጣሚን የሚጠብቅበት ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች አሉት፡፡ አንደኛ የእግዚአብሔር ቦታና ጊዜ በሆነበት ሁኔታ ውስጥ የእርሱን ለማከናወን ቢሞክር ሥራው እንደማይሰምርለት ያውቃል፡፡ ስለዚህ የጽድቅ ሰዓት ለክፋት ለሊት ዑደቱን እስክታቀብል ያደባል፡፡ ሁለተኛ በተለይ መንፈስ በሥጋ ተከልሎ ሊቀመጥና ሊንቀሳቀስ እንደሚችል በደንብ ያወቁ ምእመናን እርምጃዎቹን ከሥር ከሥር እየተከተሉ እንዳያስተውሉበት ንቃት የሚበታተንበትን ምቹ ገጠመኝ አድፍጦ ይጠባበቃል፡፡

ነገር ግን ሰዎች ዲያቢሎስን ለመቃወም ማድረግ የሚጠበቅባቸው በራሳቸው ላይ ያሉትን ክፉ ነገሮች ሁሉ ማስወገድ እንደሆነ በማወቅና በማመን ራስን የመለወጥ ሥራ ከጀመሩ፥ መንፈስ አንዳች ማከናወን የሚችልበትን የመቼት ዕድል ይነጠቃል፡፡ ለምሳሌ ሐሰትን መዋጋት ዲያቢሎስን መዋጋት ነው ብሎ ያለመዘናጋትና ያለማቋረጥ የሚያስብ ግለሰብ እንዲዋሽ የሚያስገድድ ምንም ዓይነት ቀላልም ሆነ ከባድ ሰበብና ግፊት ቢከበውም፥ ጊዜውን ከሐሰት ጊዜ ቆጥቦ ይጠብቀዋል፡፡ በዚህ ጊዜ በውሸት ምክያትነት ኃይልን መሰብሰብና የበለጠ የመደበቂያ ምሽግን መሥራት የሚችለው የዲያቢሎስ መንፈስ፥ መኖሩም አለመኖሩም ያው የሆነ ያህል የሚሠራውን ያጣል፡፡

እያልን ያለነው ዲያቢሎስን ለማሸነፍ ራስን ማሸነፍ ያስፈልጋል ነው (የውጊያ ዓላማውም እርሱ ነው)፡፡ መናፍስትን ለማሸነፍ ቅድሚያ እኛ ለእግዚአብሔር መሸነፍ ያስፈልገናል፡፡ ትንሽ የማይባል ብዛት ያላቸው ሰዎች መንፈሳዊውን ጦርነት የተመለከተ አንድ የተሳሳተ እሳቦት አላቸው፡፡ ይኸውም፥ በእግዚአብሔር ኃይል በኩል ቅድሚያ መናፍስቱ እንዲሸነፉ ይፈልጋሉ፡፡ ይሄ ትክክለኛ ያልሆነ በሃይማኖት ጓዳና ላይ ሩቅ የማያስጉዝ አስተሳሰብ ነው፡፡

በእግዚአብሔር ስለእግዚአብሔር አስቀድመን መሸነፍ ያለብን እኛ ነን፡፡ እኛነትን የተጋራው ዲያቢሎስ፥ የኛ በእግዚአብሔር መሸነፍን ተከትሎ የሚሸነፍ ሁለተኛ ተሸናፊ ነው፡፡ እኛ ለእግዚአብሔር ፍቅር፣ ቃልና ሥርዓት ሳንገዛ፥ ለኑሮአችን ባላንጣ የሆነው ስውር ጠላት በእግዚአብሔር ኃይል ይገዛልን ማለት አካሄዱን የሳተ የውጊያ ምሪት ነው፡፡

መናፍስት ጥፋት እንዳያደርሱ ከመታሰራቸው በፊት፥ እኛ ስለ እምነት፣ ትሕትና፣ የዋህነት፣ በጎነት፣ ታጋሽነት መታሰር አለብን፡፡ መናፍስት ተጋልጠው ከሕይወታችን ተለይተው እንዲወጡ ቅድሚያ ከዘልማድ አሰተሳሰብና ጠባይ፣ ከሥጋ ዝንባሌ፣ ከስንፍና እና ከሰበበኝነት አመክንዮ መውጣት አለብን፡፡ መናፍስት በሃይማኖት ጦር ዕቃ እየተቀጠቀጡ እንዲዳከሙ፥ እኛ ሁለንተናዊ የሆነ መንፈሳዊ አኗኗርን ዕለት ዕለት ለመኖር በየቀኑ ንቁ ሆነን ስለቅድስና መድከም አለብን፡፡

እኛ በእግዚአብሔር ስለ እግዚአብሔር በተሸነፍን ቁጥር እኛ ውስጥ ያሉት መናፍስትም በዛው ልክ ይሸነፋሉ፡፡ ልዩነቱ፥ እኛ በፍቃደኝነት ስንሸነፍ፥ አጥፊዎቹ በግዴታ ይሸነፋሉ፡፡

ይቀጥላል..

@bemaleda_neku
9.0K viewsedited  08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:35:20 የቀጠለ... መናፍስትን መዋጋት የወንጌልን ዘንድሮ ማሳየት ብቻ ሳይሆን የወንጌልን ቃላት በሕይወት መረዳት ተገንዝበን ምግባር እንድናደርገውም ያግዘናል፡፡ ለምሳሌ ያህል፦         "ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም…
8.1K viewsedited  08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 11:23:08 በክፍል አንድ፥ ዲያቢሎስን መዋጋት ሰውነትን የማስጠበቅ ጦርነት ነው ያልነውን እዚህ እናምጣ፡፡ ስብዕናን የሚቃወመው ፍጥረት ክፉው መንፈስ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን የሰው ተጻራሪ መጻረር፥ ሰው ከመሆን ሚዛን እንዳንወርድ ልክ የሚያሰምር ድንበር ነው ማለት ነው፡፡

ከእግዚአብሔር አሳብ የጠፋች ሰውነት የተገኘቺው ደግሞ በእግዚአብሔር ቃል በኩል ነው፡፡ በወንጌል!

ከላይ በጻፍናቸው አንቀጾች ዲያቢሎስን መዋጋት ወንጌልን እንድንኖር ያደርጋል ካልን፥ ወንጌልን ስንኖር ደግሞ ሰውነትን እየኖርን ነው ማለትም ይሆናል፡፡ በመሆኑም ቀደም ሲል የተባለው ትክክል ነው፡፡ መናፍስትን መዋጋት ሰውነትን የመጠበቅ ሂደት ነው፡፡ በሌላ አነጋገር ከርኩሰት ሁሉ ርቆ የመለኮት ቤተመቅደስነትን በማስጠበቅ፥ ሕልውናን በእግዚአብሔር ፈቃድ የማስጠለል መንፈሳዊ ተጋድሎ ነው ብንለውም እንችላለን፡፡

የዚህ ጽሑፍ ዝግጅት መሠረታዊ ፍላጎት ምእመናን ዲያቢሎስን የመዋጋትን ነገር ከአንድ ልዩ ጉዳይና ነባራዊ ችግር ጋር አስተሳስረው፥ በውጊያ ውስጥ ያሉ ራስን የማሻሻል፣ እምነትን የመጨመር፣ መንፈሳዊ ማንነትን የማጠንከር፣ ሃይማኖታዊ አስተሳሰብን የማስፋት፣ ዕውቀትን የማጎልበት ትሩፋቶችን ካለማወቅ እንዳይተዉ ማሳሰብ ነው፡፡

እስካለን ድረስ ያለብንን የዓለም መከራ ለመገላገል ስንል መናፍስትን መዋጋት ሩቅ አያስኬደንም፡፡ ብቻም ሳይሆን ወቅታዊ ችግርን ለመፍታት በሚል የምንጣጣረው ጥረት፥ ሳናውቀው መናፍስትን የሚያግዝ አመለካከት እንዲቀረጽብን ያስገድዳል፡፡

የተዘጉብን እስኪከፈቱ አሊያ የተከፈቱብን እስኪዘጉ ድረስ በምንጀምረው መንፈሳዊ ጦርነት ውስጥ፥ በወንጌል ዕውቀትነት የመመራት፣ በወንጌል ሕይወትነት የመኖር ዕድሉ ሲበዛ ጠባብ ነው፡፡ ዕድሉ እንዲስተካከልለት ብቻ የኃጢአትን ኃይል ለሚፋለም አማኝ፥ የማርቆስ ወንጌል ምኑም አይደለም፡፡ በቤተሰብ ያለው ፈተና እንዲቀረፍ ብቻ ክፋትን ለሚጋደል ግለሰብ፥ የጴጥሮስ መልእክት ቢመለከተውም አይመለከተውም፡፡ የሥጋ ፈውስን ፍለጋ ወደ መንፈሳዊ ትግል የመጣ ሰው፥ የእርሱን ፈውስ ከተመለከቱ ትምህርቶች ውጪ የመማር በጎ ፈቃድ አይኖረውም፡፡

እነዚህ ሰዎች በአብዛኛው የዲያቢሎስ ውጊያ እስከ መጨረሻው የሕይወት ቀናቸው እንደማያባራ ያልተረዱ ናቸውና፥ አጥብቀው የፈለጉትን አግኘተው ጥቂትም ሳይቆዩ ሌላ ፍላጎት በሚያስቸግራቸው ጊዜ፥ መዛል፣ መሰልቸት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ማማራር የሚጠብቃቸው ፈንታ ይሆናል፡፡

ነገር ግን ረቂቁ ጦርነት፥ ሰውነት በልዕልና ኃይል እንዲገለጥ መግፍኤ እንደሚሆን ክርስቲያኖች ሲያስተውሉ፥ ጉዳያቸውን ወደ እግዚአብሔር ጉዳይ ለማስተለቅ እይታቸውን ሰፋ ያደርጋሉ፡፡ ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም ያስባሉ፡፡ በመከራ ውስጥ እያገኙ የመጡትን ዕውቀት ያከብራሉ፡፡ ፈተና ወደ ቀጣይ የሕይወት ምዕራፍ የሚሻገሩበት የለወጥ መዘወሪያ እንደሆነ ይረዳሉ፡፡ ከዛ "ክርስቶስን እንደምመስል እናንተም እኔን ምሰሉ" ያለውን ሐዋሪያ መስለውም እንዲህ ይናገራሉ ፦

      "እስከዚህ ሰዓት ድረስ እንራባለን፥ እንጠማለን፥ እንራቆታለን፥ እንጐሰማለን፥ እንንከራተታለን፥ በገዛ እጃችን እየሠራን እንደክማለን፤ ሲሰድቡን እንመርቃለን፥ ሲያሳድዱን እንታገሣለን፥ ክፉ ሲናገሩን እንማልዳለን፤.. እንግዲህ እኔን የምትመስሉ ሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።"

                                                            (1ኛ ቆሮ. 4፥11-16)

ይቀጥላል..

@bemaleda_neku
10.7K viewsedited  08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 11:16:19 ክፍል - ፬                   የወንጌልን ዘንድሮ ያሳየናል ዓለም በቅርጿ አራት ማዕዘን ናት ብዬ አስባለሁ (የተዘረጋውን የዓለም ካርታ ዐይቼ አይደለም)፡፡ በእርግጥ መሬት በቅርጿ ክብ እንደሆነች የተረጋገጠ ነገር ነው፡፡ ብቻ ሳይሆን ክቧ ምድር በክብ ዛቢያ ላይ እንደምትሽከርከር ብዙ አሳማኝ የሆኑ ሥጋዊም መንፈሳዊም ማስረጃዎች አሉ፡፡ የኔ ጉዳይ ግን ከክብ ቅርጹና ዛቢያው ጋር የተያያዘ አይደለም፡፡…
8.9K viewsedited  08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-03 19:59:51 ተሞክሮ 130

እህታችን ነፍሰ ጡር ሳለች እንዴት ባለ ድካም በሕይወት ያየቺውን እንደምትነግረን ታስተውላላችሁን?

እንዲህ ያለውን የሕይወት ነገር እየሰሙ ምንም የማይመስላቸው ጆሮዎች ምንኛ ይደንቃሉ? ..ለመንፈሳዊው ሕይወት የተመረጡ ሰዎች አሉ'ዴ የሚያሰኙ የተለያየ ዓይነት አስተሳሰቦች ገጥመውኛል:: ወዲህ ግን አባቶቻችን ይላሉ:: እግዚአብሔር ይመርጣል መባሉ ለይቶ የሚመርጥ ሆኖ አይደለም: ይልቅስ ለመመረጥ የተመቹ ሆኖ መገኘት እንጂ ይላሉ:: ይህ ማለት የእግዚአብሔር ሥራ በኛ እንዲገለጽ ፈቃዳችን አስቀድሞ ራሱን ለአምላክ ሥራ አሳልፎ መስጠት አለበት:: ስጡ ይሰጣችኋል የሚለው: በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ጥልቅ ትስስር ጠቅለል ባለ አገላለጽ ይሄ ነው:: ጳውሎስም "ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) ጋር አብረን የምንሠራ ነንና" ያለው ይህንኑ ጉዳይ ነው:: (1ኛ ቆሮ. ፫፥፱)

እነዚህ: ከእግዚአብሔር ጋር አብረው ለመሥራት ራሳቸው ላይ ስለ በጎ መሻት የሠሩ ሰዎች የእግዚአብሔር በጎች ይባላሉ:: መልካሙ እረኛ ክርስቶስ ስለነዚህ በጎች "ድምፄን ይሰማሉ፤ እኔም አውቃችኋለሁ፤ ይከተሉኛማል" ይላል:: (ዮሐ. ፲፥፳፯)

አዎ፤ በትክክልም ድምፁን የሚሰሙት: ይሰሙታል:: ድምፁን የሚሰሙት ስለ መንፈሳዊ ስበት አይጎተቱም:: ድምፁን የሚሰሙት ያውቁታል፡፡ አንድ ተነግሮአቸው ሁለት ይሄዱበታል፡፡ የፈቃዳቸው ክንፍ መንፈሳዊውን ዓለም ለማወቅ ዘወትር ይበራል፡፡ ከሕይወት ውኃ ለመጠጣት የተጠሙ ናቸው፡፡ እንደ ፍም እሳት የሚነድ ሃይማኖታዊ መሻት አላቸው፡፡ ሰኮንዶቻቸውን ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር ማስተሳሰር ታላቅ ምኞታቸው ነው፡፡ በእርግጥም እነዚህ በጎች: የእረኛቸውን አንድ ጥሪ [ያለ ጩኸት] ይሰማሉ: እርሱ በሄደበት እየሄዱም ይከተሉታል::

ተሞክሮ መላካችሁን ቀጥሉ
☞ @bemaledaa_neku_bot
9.9K viewsedited  16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 14:15:44 ውጊያን የማያውቁ ሰዎች የእግዚአብሔርን ቃል በሕይወትነትና በመንፈስነት ስለመረዳታቸው እጠራጠራለሁ፡፡ ዲያቢሎስ እንዴት በኑሮ ውስጥ ኑሮን መስሎ እንደሚፋለም ምእመናን ዕውቀት ካላገኙ የዓውደ ምሕረት ስብከት ወደ ጓጆአቸው ገብቶ ቤታቸውን ያስተካክላል ብዬ አላስብም፡፡ ይሄ በተለይ በኛ ዘመን የሚታይ ምስክርነት ያለው የአደባባይ እውነት ነው፡፡

መንፈሳዊ ትምህርቶች በተለያየ መንገድ ለአማኞች ይደርሳሉ፡፡ ትልልቅ ጉባዔዎችም እየተዘጋጁ ቁጥር ያላቸው ታዳሚዎች ሲሳተፉ በተደጋጋሚ ይስተዋላል፡፡ በንግሥ ክብረ በዓላት ላይ የሚታየው የምእመናኑና የአገልጋዮች ሃይማኖታዊ አከባበር በጣም ያስደስታል፡፡ አንድ ላይ ተሰብስበው የሚታዩ ነጠላዎችና የሚነዱ ጧፎች ውበታቸው ሌላ ነው፡፡ ግን ታዲያ በየግል በየግል ሕይወታችን ውስጥ ሲሆን የሚታየውም ነገር ሌላ ነው፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ መንፈሳዊ ሲሆን የሚነግረንም ስለ መንፈሳዊው ዓለም መሆኑን ረስተን፥ ከመጽሐፍ የሰማነውን ታሪክ ልክ እንደ ሥጋ ታሪክ "ይገርማል፣ ቃለ ሕይወት ያሰማልን" ለአፋችን ብለንለት፥ የኛን ሕይወት ከመጽሐፉ ታሪክ ውጪ አድርገን (የሆነ መስሎን) መኖር እንቀጥላለን፡፡

ምእመን ሆይ፥ አስተውል! ዘፍጥረት 3 "ዲያቢሎስ ወደ አዳም ቤተሰብ መጣ" ሲልህ፥ ወዳንተም እንዲሁ መጥቶአልን እየነገረህም ነው፡፡ ይኸውም ራእይ 12 "ዓለሙን ሁሉ (የአዳምን ልጆች ሁሉ) የሚያስተው ዲያቢሎስ" በማለቱ ተረጋግጦአል፡፡ እንኪያስ ክፉ መናፍስትን የሚጣላ የጽድቅ ኑሮን ለመያዝ በአቅምህ ስትውጀመጀም፥ ከመጀመሪያው አዳም እስከ መጨረሻው አዳም አንድ ሰውን እንኳ ሳይመርጥ (ሳይተው) ውጊያ የሚከፍተውን የሰው ጠላት ትለየዋለህ፡፡ ከለየህም በኋላ፥ ካንተ አስቀድመው ዲያቢሎስን ከወጉ ወይንም በዲያቢሎስ ከተወጉ ሰዎች የታመነ ተሞክሮ ለመውሰድ እንድትችል መጽሐፍ ቅዱስን ትመለከታለህ፡፡ አሁን የወንጌልን ትናንትና በአንተ ዘንድሮ ውስጥ አነበብህ ማለት ይሆናል፡፡

ይቀጥላል..

@bemaleda_neku
10.3K views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-01 14:12:59 የቀጠለ.. እንግዲህ ክፉው መንፈስ በሃይማኖት መንገድነት ላይ ባየናቸው አቅጣጫዎች በኩል የሚቆም ከሆነ፥ እርሱን በመዋጋት ከቆመበት ቦታ ዘወር ማድረግ መንፈሳዊ ጉዞአችንን ያለ ችግር እንድንቀጥል ይረዳናል ማለት ነው፡፡ በቀላል አገላለጽ ዲያቢሎስን መዋጋት በሃይማኖት እንድናድግ ይረዳናል፡፡ ዲያቢሎስ ከነቃንበት ሃይማኖታችንን የሚያሳድግልን ከነቃብን ግን ሃይማኖታችንን የሚያቀነጭርብን የጽድቅ ጠላት ነው፡፡…
9.0K views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 12:19:24 መጎልመስ በጥሬ ቃል ፍቺው ማደግ፣ መሻሻል፣ ጥሩ ለውጥ ማምጣት ተብሎ ይተረጎማል፡፡ በሃይማኖት መጎልመስ በሃይማኖት ከመቆም ቀጥሎ የሚመጣ ነው፡፡

በዲያቢሎስ ላይ ከነቃህ በኋላ ትዋጋው ዘንድ እንዲቻልህ በቀደመቺው መንገድ ላይ ትቆማለህ፡፡ በዚህ ጊዜ ውጊያው ሲጀመር፥ ውጊያው በባሕሪዩ ከግዝፈት ወደ ርቅቀት እየሄደ የሚጓዝ ስለሆነ ወደ ሃይማኖት ጥልቅ እውቀቶች እየገባህ ትመጣለህ፡፡ በሃይማኖት መጎሎመስ የምንለው ይሄን የመንፈሳዊ እይታ ማደግና መስፋት ነው፡፡

ክፉ መናፍስትን መዋጋት በሃይማኖት እንድንጎለምስ ያደርገናል፡፡ ከላይኛው አንቀጽ እንደተጻፈው የመጋደሉ ጦርነት ከግዝፈት ወደ ርቅቀት እየጠለቀ የሚሄድ በመሆኑ፤ ውጊያው በግዝፈት አካል ላይ በሚታዩት መንፈሳዊ ክንውኖች፥ ማለትም በስግደት፣ በጸሎት፣ በጾም፣.. በኩል አድርጎ ወደ በውስጥ አካል ላይ ወደሚታዩት መንፈሳዊ ፍሬያት እንደ ፍቅር፣ ትሕትና፣ ደግነት፣ ይቅር ባይነት፣ ለጋስነት፣.. ጋር በመድረስ፥ በቀዳሚነት በእግዚአብሔር ታስቦ ወደ ተፈጠረው ንጹሕ አዳማዊነት ስውነታችንን እያሳደገው ይመጣል፡፡

በቀደሙት ክፍሎች ላይ እንደተወሳው በክፉው መንፈስ ውስጥ ምንም አይነት የእግዚአብሔር ነገር ባለመኖሩ፥ ይህንን ተቃዋሚ የምንዋጋው በእግዚአብሔር ነገራት በመታገዝ ነው፡፡ የአምልኮተ እግዚአብሔር የዘወትር ልምምዶች ውጊያውን እንድንጀምር ሲያደርጉ፥ እየተዋጋን ስንቀጥል፥ በየዕለቱ በውጊያው ምክንያትነት የምናገኛቸው ትምህርቶች፣ ተጨባጭ ተሞክሮዎችና የተፈተኑ ልምዶች፥ ትናንት ከነበርንበት ሃይማኖታዊ ደረጃ ከፍ ብለን እንድንወጣ የሚያግዙ ለውጦች ይሆኑናል፡፡ በቀላል ምሳሌ፥ ትዕግስት ያልነበረን ታጋሽነትን ገንዘብ እንድናደርግ፣ ግዴለሽነት የተጠናወተን አስተዋይነትን እንድናከብር፣ ንዴት የሚፈታተነን እርጋታን እንድንማር፣ ተስፋ መቁረጥ የከበበን ተስፋ እንዲሰማን ውጊያው በራሱ ያስተምረናል፡፡

ጳውሎስ ጎልምሱ ብሎ አላበቃም፡፡ ጠንክሩ ሲል ደግሞ ሦስተኛውን ቃል ጽፎአል፡፡ ርእሳችን መናፍስትን መዋጋት እንዴት ለሃይማኖታችን ይጠቅመናል የሚል ነውና፤ የሐዋሪያውን መልእክት ለጀመርነው ርእሳችን ማስተንተንኛ አድርገን እንቀጥል፡፡

ዲያቢሎስን መዋጋት በሃይማኖት እንድንቆምና እንድንጎለምስ ብቻ ሳይሆን በሃይማኖት እንድንጠነክርም ያደርጋል፡፡

ክፉ መንፈስ ክፋቱን ወደ ሰው ልጆች ለማጋራት ሲንቀሳቀስ ዕረፍትን አያርፋትም፡፡ እየተሸነፈም እያሸነፈም ግብሩን ለመፈጸም እንቅልፍ የሌለው ባላንጣ ነው፡፡ ተንኮል ከማሰብ አይደክምም፣ ሐሰትን ከመናገር አይሰለችም፣ ጥፋትን ከማድረስ አይቆጠብምም፣ ችግርን ከመፍጠር አይለዝብም፡፡ የሚመጠሉትን አጋጣሚዎች በሚገባ ለሚፈልገው ዓላማና ውጤት ለማድረስ ጥቁር ልቦናው አይዘናጋም ነው፡፡ ሰይጣን ሥራ ፈትቶ አያውቅም!

ስለዚህ፥ ይሄን በክፋት ለክፋት የጸና ጠላት ለመጣል በጽድቅ ለጽድቅ መጽናት ደግሞ የምእመናን ፋንታ ነው፡፡ እያንዳንዷን ሰኮንድ ለተልዕኮው ማስፈጸሚያነት የሚጠቀምባት ዲያቢሎስ በሰፊ ርቀት አልፎ በመቅደም ፍላጎቱን እንዳያሳካብን፥ በእያንዳንዱ  ዘወትራችን ላይ መንፈሳዊ ልካችንን ጠብቀንና አስጠብቀን መሄድ አማራጭ የሌለው ግዴታችን ነው፡፡

ትናንት የሰገድከው ስግደት ዛሬም መቀጠል አለበት፡፡ ዛሬ ያሳየኸው መልካምነት ነገም ሊገለጥ ይገባዋል፡፡ ነገ ያቀድከው የመቀደስ ቀን ከዚያም በኋላ ሊለይህ አይገባም፡፡ ጠዋት የበላነው ቁርስ የማታ ራት እንደማይሆነን፥ ክርስትናም አሁናዊ መዳንን ትልቁ ጉዳዩ አድርጎ በመንቀሳቀሱ፥ በአሁኖቻችን ላይ ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ ነገሮች ሁሉ አሁኑኑ እንድናደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ያስተላልፋል፡፡ አሁኖችን ሁሉ በአሁንነታቸው አክብሮ አሁን መደረግ የሚገባውን እንድናደርግ የሚያደርገው ደግሞ፥ አሁንም ድረስ ቀጥሎ ያለው የዲያብሎስ ፈተና ነው፡፡

መናፍስት ሃይማኖትን ጠንክረው መታገላቸው በሃይማኖታችን እንድንጠነክር ያግዘናል፡፡ የማይቋረጥ አሳችነታቸው የማይተኛ ጥንቅቁነት እንዲኖረን ያበረታናል፡፡ ትናንት የጀመሩትን ሴራ ዛሬም መሸረባቸው፥ ትናንት የተጀመረው ስግደት እንዳይቋረጥ ያስገድደናል፡፡ ቅድም የተጠነሰሱት ተንኮል በኋላም መቀጠሉ፥ ዓለምን በማይሟጠጡ ትዕግስቶች እንድንታገሳት ያስተምረናል፡፡ በእውነትም መናፍስትን መዋጋት በሃይማኖት ያሳድገናል፡፡ ርእሳችንን በይሁዳ ምክር እንዝጋው፦

      "ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።"

                                                                        (ይሁ. 1፥3)


ይቀጥላል

ተሞክሮ መላካችሁን ቀጥሉ ☞ @bemaledaa_neku_bot
9.1K viewsedited  09:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-30 12:14:40 ክፍል - ፫                በሃይማኖት ያሳድገናል ባሳለፍነው መናፍስትን መዋጋት ምን ይጠቅመናል የሚለው የትምህርት ክፍሎቻችን ላይ ዲያቢሎስን መዋጋት በመጀመሪያ ምን ማለት እንደሆነ እና እርሱን በመዋጋትም ምክንያትነት የነፍስና የሥጋ መዳንን እንደምንጠቀም ተመልክተናል፡፡ በዚህኛው ርእሳችን ላይ ደግሞ ክፉውን መፋለም በሃይማኖት ለማደግ እንዴት እንደሚጠቅም እንመለከታለን፡፡ ሃይማኖት ማመንንና…
8.2K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-28 16:35:20 ክፉ መንፈስ ከሃይማኖት ፊት ሲቆም ቀድሞውኑ ሃይማኖትን እንዳታገኘው፣ አግኘተህ እንዳትቀበለው፣ ተቀብለህም እንዳታውቀው ሲል ነው የሚታገለው፡፡ ዞሮ መጥቶ ከኋላህ ከቆመ ግን (ወደኋላ ሄዶ የሚጎትተው ከፊት ሆኖ መዝጋት ሲያቅተው ነው፤ በሌላ አገላለጥ ሃይማኖትን ስታውቀውና አውቀህ መኖርን ስትጀምርበት ነው)፤ ስለ ሃይማኖት በሆነ ደረጃና መጠን ያወከውን እንዳትኖረው ይፋለማል፡፡ መንፈሳዊ እውቀቶችህ በልቦና መዝገብ እንዳይታተሙና በየመቼታቸው እንዳይተረጎሙ አስሮ ይይዛሃል፡፡ ሕይወትና መንፈስ የሆነቺው ወንጌል በኑሮህ ላይ እንዳትነበብ ይፋለምሃል፡፡

               3•  ዲያቢሎስ ከሃይማኖት ጎን ይቆማል

ከክርስቶስ የሕይወት ታሪክ እንደምንገነዘበው፥ አይሁዶች የዳዊትን ልጅ የገደሉት በዳዊት ስም ነው፡፡ የአብርሃምን አምላክ ያሳደዱት የአብርሃም ዘሮች ነን በማለት ነው፡፡ ይሄ፥ ዲያቢሎስ ሃይማኖት አለን የሚሉ ሰዎችን በመጠቀም ሃይማኖትን እንደሚፋለም ይነግረናል፡፡

አንድ ሰው ከጎኔ ቆሟል የምንለው አባባል ብዙ ጊዜ ወዳጅነትን ለመግለጽ የምንጠቀምበት አነጋገር ነው፡፡ እህሳ ዲያቢሎስ ከሃይማኖት ጎን ይቆማል ስንል፥ ሃይማኖትን እንደ ወዳጅ ተጠግቶ ነውን እንይዛለን፡፡ ሃይማኖት ከኛ ወዲያ ላሳር የሚሉ ወገኖችን በመጠቀም፣ ሃይማኖት በኛ ቢሮ ካላለፈች ተሳስታለች ከሚሉት ጀርባ በመከለል፣ የሃይማኖትን ሥርዓትና ወግ እናስጠብቃለን የሚሉ ፍቅር አልባ ሰዎችን በማሰለፍ፣ ሃይማኖትን ለሥጋ ትርፍና ለቁስ አምልኮት ከሚገለገሉባት የቤተ መቅደስ ነጋዴዎች አጠገብ በመሆን፣ ሃይማኖትን እንደ ቡድን መመደቢያ ወይንም እንደ ጎራ መለያ ድርጅት የሚቆጥሩ ተከታዮችን ተገን በማድረግ፥ ዲያቢሎስ የዓለምን ምሪት ወደርሱ የዓለማ አቅጣጫ እንዲያጋድል ተግቶ ይሠራል፡፡

ይቀጥላል..

@bemaleda_neku
8.9K viewsedited  13:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ