Get Mystery Box with random crypto!

ጡባ ሊል ጉረባእ የሰለፍዮች መድረሳ ቻናል

የቴሌግራም ቻናል አርማ tubaliligurebae — ጡባ ሊል ጉረባእ የሰለፍዮች መድረሳ ቻናል
የቴሌግራም ቻናል አርማ tubaliligurebae — ጡባ ሊል ጉረባእ የሰለፍዮች መድረሳ ቻናል
የሰርጥ አድራሻ: @tubaliligurebae
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.15K
የሰርጥ መግለጫ

ጡባ ሊል ጉረባእ የሰለፍዮች መድረሳ በሀበሻ ቻናል
https://t.me/tubaliligurebae
https://t.me/tubaliligurebae
قال ابن تيمية رحمه الله:
ولا يحل لأحد أن يتكلم في الدين بلا علم، ولا يعين من تكلم فيه

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 17:39:28 ሸር አድርጋችሁ አሰራጩት

#ዘመንመለወጫ!!?

ማነሽ እንቁጣጣሽ..!!?

http://t.me/nuredinal_arebi
961 views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 17:39:00
#ዘመን_መለወጫ።
▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ዘመን መለወጫ የለንም ወዳጄ፡
ኮተት አልፈልግም ዘወር በል ከደጄ፡
ሙሉ ፅድት ያለ ሐቅ ነው መንሀጄ፡
ከሉቃስ ዩሀንስ ከማርቆስ ክርስቶስ፡
ከሰውች ወደሰው ከቄርቆስ ቆሮንጦስ፡
ኸረ ለቀቅ አርገኝ አያልቅም ያንተ ጦስ?
ወደ ሰው መጠጋት ሙስሊሞች አንወድም፡
ከአንድ አምላክ በስተቀር ለማንም አንሰግድም፡
ለማርቆስ ለሉቃስ አናጎበድድም፡
ምንክንያቱም ሙታን ምንም አይፈይድም፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ስለዚህ ራቂኝ ማነሽ እንቁጣጣሽ፡
ወደኛ አትጠጊ ዞር በይ እስከ ሻንጣሽ፡
እኛ እናውቅሻለን ከየት እንደመጣሽ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
በእስልምናችን የለም እንቁ ጣጣሽ፡
ዘመን መለወጫ የሽርክ ብጥስጣሽ፡
የድግምት የመተት ክፋት መተግበሪያ፡
የክፋት የሴራ ተንኮል መቀመሪያ፡
እውነታ የሌለሽ የኩፋር መመሪያ፡
እውነትን ሰርዘሽ ውሸት ማስተማሪያ፡
ሐቅን ባጢል ብለሽ ጥመት ማበጠሪያ፡
ውስጥሽ ውጭሽ ቦድ ግድግዳሽም ጣሪያ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ኢብሊስ የገነባሽ የጭፍሮቹ መተት፡
አማኞች አያውቁም እንድህ አይነት ኮተት፡
ሐቁ መመሪያችን ካላፀደቀልን፡
ውዱ ነብያችን ካልመሰከረልን።
በነሉቃስ ቀመር ተጓዥ አይደለንም፡
ዘመን መለወጫ ፈፅሞ የለንም፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
የአመፅ የበደል የወንጀሎች ቅርጫ፡
የሸይጣን የአጋንንት የጥመት መፈንጫ፡
የመጥፎነት ማዕረግ የሙሽሪኮች ዋንጫ፡
ሽርክን ክህደትን በጥብጦ መጠጫ፡
ሙስሊሞች የለንም ዘመን መለወጫ፡
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
[ ኑረዲን አል አረቢ 01/26/1443
922 viewsedited  14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 16:39:25 ሸርሑ ሱና ደርስ









ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም ተከታተሉ ሼር ሼር አድርጉት

https://t.me/tewhidfirst29
815 views13:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 16:26:13 ከ5 ደቂቃ በጟላ የሸርሁ ሱና ደርስ ይጀምራል ።
ገባገባ በሉ።
https://t.me/tewhidfirst29
726 views13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 15:32:59 ሸይኽ/ ሱለይማን አሩሐይሊ حفظه الله

ሚስት ባሏን በተመሳሳይ መንገድ የማስተናገድ መብት አላትን? ለምሳሌ መምታትን ይመስል?
299 views12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 12:44:40 Abu hafsua(أبو حفصة:
ማስታወሻ: ዛሬ ሀሙስ
የሸርሁ ሱና ደርስ ክ57 : 10:30

ላይ እንጀምራለን።
በቦታው ለማይገኝ

https://t.me/tewhidfirst29


መእና ላኢላሃ ኢለሏሁ ደርስ ክ5: 11:30
ላይ ይጀምራል።
በቦታው ለማይገኝ
https://t.me/Abuhafsua1443

ማስታወሻ 2:
የመእና ላኢላሃ ኢለሏሁ ደርስ የሚተላለፈው በዚህ መሆኑን አትርሱ

https://t.me/Abuhafsua1443
855 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 09:35:05 የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። ታዲያ ይህን ክስተት ተከትሎ የሚፈፀሙ ከሃይማኖትችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ጥፋቶች አሉ። ከነዚህም ውስጥ
1. ቀዳሚው ድግምትና ጥንቆላ ነው፡፡ በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሀሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት እጅግ ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ። ጥንቆላና ድግምት:-

* ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል።} [አሶሒሐህ፡ 3387]

* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን እንዲህ ይላል፡- “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም።” [ጦሃ፡ 69]

* ደጋሚዎች የሰዎችን ገንዘብ በማታለል የሚበዘብዙ መዥገሮች ናቸው። ገንዘቡን ለነሱ የሚሰጥ አካልም አላህ ፊት ተጠያቂ ነው። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- {የኣደም ልጅ በቂያማህ ቀን አምስት ነገሮችን ሳይጠየቅ እግሮቹ አይንቀሳቀሱም። እድሜውን በምን እንዳጠፋው፤ ወጣትነቱን በምን እንደጨረሰው፤ ገንዘቡን ከየት እንዳመጣው፤ እንዲሁም በምን እንዳወጣው፤ ባወቀው ምን እንደሰራ።} [አሶሒሐህ፡ 946]

* ደጋሚዎች የነገር ቋቶች የማህበራዊ ህይወት ጠንቆች ናቸው። የተቸገረ ደንበኛቸው መፍተሄ ፈልጎ ሲመጣባቸው በብዛት የችግሩ መንስኤ የሆነው ወይ ጎረቤቱ፣ ወይ ዘመዱ ወይ ደግሞ የቤተሰቡ አባል እንደሆነ በመጠቆም ሰዎች ውስጣቸው እንዲሻክር አለመተማመን እንዲነግስ ያደርጋሉ። በድግምቶቹ ምክንያት የጤና መጓደል፣ የትዳር መፍረስ፣ የዝምድና መቆራረጥ፣ የጎረቤቶች በጎሪጥ መተያየት አልፎም ደም የሚያቃባ ግጭት እንዲከሰት ሁሉ ሰበብ ሊሆኑ ይችላሉ።

* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡- {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም።} [ሙስሊም፡ 5957]

2. ሌላው በ “ዘመን መለወጫ” አካባቢ የሚፈፀመው ጥፋት በአንዳንድ አካባቢ ያለው ጳጉሜን ተከትሎ ለዱዓህ መሰባሰብ ነው። እነዚህ አካላት የጳጉሜ ዱዓህ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) በማለት ነው ወቅቱን በዱዓእ የሚያሳልፏት። በጣም የሚገርመው ለዱዓህ የሚጥጠሩት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ማለታቸው ምንኛ የሚደንቅ ሐቅ ነው?! ዲን ያስተምራሉ ተብለው የሚታሰቡት አካላት ክርስቲያናዊ አቆጣጠርን መሰረት ያደረገ ዒባዳህ እየፈፀሙ ሰዎችን ወደ ጥፋት ሲወስዱ በገሃድ ይታያሉ።

3. ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ በከንቱ የሚዳክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ሲበዛ ግልፅ ከመሆኑ ጋር በዚህ ላይ የሚሸወድ መኖሩ እጅጉን የሚደንቅ ነው። ብቻ ለማንም እንደማይሰወር ባስብም ለማስታወስ ያክል:-

* አቆጣጠሩ ወደ ሀገር ውስጥ የገባው በሚሲዮናውያን መሆኑ፣
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” መባሉ፣
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ መሞገታቸው
* እንዲሁም ይበልጥ ለማረጋገጥ የ “ዘመን መለወጫ” ወቅት ላይ ለምሳሌ “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በአሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡ ይህንን ስንል የሚደብራቸው ክርስቲያኖች አሉ። እኛኮ ዒድን አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ሰው እንዴት የኔን እምነት ካልተከተላችሁ ብሎ ሌሎችን በአክራሪነት ይፈርጃል?!
የእምነታችንን ጉዳይ ለኛ ብትተውልን። እምነታችን ሌሎች ህዝቦች በሚልለዩባቸው እምነቶች፣ ባህሎችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 26/2007)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
1.0K views06:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:47:39 እንዳይመሳሰልባችሁ እና እንዳትሸወዱ ያጀመዓ ይህ የፊትናው ቡድን አዲስ ግሩፕ ነው እንጂ የኮምቦልቻ ሰለፍዮች ግሩፕ አይደለም።
1.0K views20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:43:44
የኮምቦልቻ ሰለፍዮች ሳይሆን የኮንቦልቻ በጥባጮች ሰለፍያን አደፍራሾች ረባሾች ማለቱ ሀላችሁን ይገልፅላችሁ ነበር።
የረድ ጉረኞች የለተሜ ሙሪዶች ።
ማንኛውም ሰለፍይ የሆነ ሰው የነዚህን ሰዎች ፈተና አብሮ ሊያሯሩጥ አይገባም አራግፎ ሊጥላቸው ይገባል።
አቡ ሑዘይፋ ኢብኑ ሙሐመድ አስሰለፍይ

ፅሁፉ እኔ እና እኔን ብቻ ነው የሚመለከተው

https://t.me/tubaliligurebae
https://t.me/tubaliligurebae
قناة طوبى للغرباء مدرسة السلفيين
1.1K views20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 23:33:15 ይድረስ
ኢንተርኔት ለምትጠቀሙ እህቶች

በኢንተርኔት ከንቱ ምኞት ትዳርዋን የተበላሸባት፤ ህይወቷን የጨለመባት እንስት አስተማሪ ታሪክ…

ወጉ ወዲህ ነው
ሚስት አላህ ይጠብቀንና በኢንተርኔት ሱስ የተጠመደች ናት። ባለቤትዋ ከዚህ ተግባርዋ እንድትቆጠብ በተደጋጋሚ ቢመክራትም ልትቀበለው አልቻለችም። ብዙ ለመናት ብዙ አስመከራት "አሻፈረኝ" አለች። የምትጠቀምበትን ስልክ ሳይቀር ወስዶባታል። እሷም ሌላ ስልክ በመፈለግ ኢንተርኔት ላይ መዘውተሯን ቀጠለች።

በዚህ ጊዜ ባል አንድ ዘዴ ይዘይዳል
ወደ facebook በመግባት እንደ ሚባለው "fake acount" (የውሸት አድራሻ) በመክፈት ስሙን ይቀይርና ፕሮፋይሉ ላይ ሀብታምና ቆንጆ የሚመስል የወንድ ምስል ያስቀምጣል። ከዝያ በኋላ የሚስቱን የ facebook አድራሻ በመፈለግ ያናግራት ጀመረ።

ጨዋታው የተጀመረው እዚህ ቦታ ነበር
በሰላምታ የተጀመረው ንግግር ወደ ትውውቅ ይሸጋገርና ያለችበትን የኑሮ ሁኔታ ጨርሳ ትነግረዋለች። እሱ ግን እየዋሻት እሷን በምትፈልገው አይነት ራሱን እየገለፀ ያጫውታታል።
ባለ ትዳር እንደሆነችና ነገር ግን በትዳሯ ላይ ደስተኛ እንዳልሆነች ስትነግረው
"እንግዲያውስ ባልሽን ይፍታሽና ከእኔጋ እንደመር" ይላታል።
ባቀረበላት ሀሳብ ደስተኛ ሆና ከባልዋ ጋ በምን ዓይነት መልኩ መፋታት እንዳለባት መላ ይፈልጋሉ። እሱም "በቃ ሳትጎዳዱና ሳትጨቃጨቁ እንድትለያዩ ችግር በማይፈጥር መልኩ ባህሪሽን ቀይሪበት" ይላታል።

ባል ስራ ውሎ ማታ ሲገባ የሚስቱ ባህሪይ ከቀን ወደ ቀን እየተቀያየረ ይመጣል። ሚስት የማታውቀው ባል የፈጠረው ጨዋታ ነውና ቀን እያወራት ማታ ገብቶ ይታዘባታል። [አላህ ይጠብቀን]

ጨዋታው ሲጧጧፍ ባል ማታ ይገባና
"ሰሞኑ እያየሁብሽ ያለው ነገር እያስደሰተኝ አይደለም ምን ተፈጥሮ ነው?" ይላታል
"ምንም" ትለዋለች
"ንገሪኝ ችግርሽ ዝምታ መፍትሄ አይሆንም" ሲላት
"ምንም አልሆንኩም" ትለዋለች
"ሀሳብሽ በግልፅ ንገሪኝ ከእኔ መለየት ትፈልጊያለሽ ያልተመቸሽ ነገር አለ እንዴ?" ሲላት
"ቢሆን አይከፋኝም" ብላ ፍላጎትዋን ገለፀችለት።

ፍላጎቷን ግልፅ ካደረገች በኋላ ባልየው ቀጥታ ወደ ፈለገው ጨዋታ ይገባና ያናግራታል
"እንግዲህ መለያየታችን አይቀሬ ከሆነ አንቺም የሄድሽበት እንዲቀናሽ እኔም ቤቴና ንብረቴ ተበታትኖ ህይወቴ እንዳይበላሽ ከመሄድሽ በፊት ሁለተኛ ላግባና ልክ እንዳገባኋት ለእሷ አስረክበሽ ትሄጃለሽ" ይላታል።
  ሚስትም ያሳሰባት ሁለተኛ ማግባቱ አለ ማግባቱ ሳይሆን የእሷ መፈታት ነበርና "ምንም ችግር የለውም" ብላ ትስማማለች።

ባልየው በማግስቱ ወደ ሚስቱ ቤተሰቦች በመሄድ የተነጋገሩበት ነገር ያጫውታቸውና ሁለተኛ ሊያገባ መሆኑ ይነግራቸዋል።
ሁለተኛ ሚስት ፍለጋ ተ ጀ መ ረ

ባል ሊያገባት ሚስት ደግሞ አስረክባት የምትወጣዋ ሁለተኛ ሚስት በሁለቱም ብርቱ ፍለጋ "ትሆናለች፣ ትመጥናለች" የተባለችዋን አፈላልገው አገኙ።
ያዝ እንግዲህ……

የሁለተኛዋ ሚስት የኒካህ ቀጠሮ ይያዛል። ልብ በሉ ሁለተኛዋ እንደ መጣች የመጀመሪያዋ ተሸኝታ ያ በኢንተርኔት መንፈስ ብቻ የምታውቀው ባልዋ ሊያገባት ነው።

የማይደርስ የለምና የኒካሁ ቀን ደረሰ። ባል ልክ የሁለተኛ ሚስቱ ኒካህ እንዳሰረ ያ ሚስቱን ሌላ ሰው መስሎ ያወራበት የነበረው የ facebook አድራሻ ዘግቶት ከኢንተርኔት መንደር ይወጣል።
لا إله إلا الله

የመጀመሪያዋ ሚስት ባልዋ ሌላ እንዳገባና ከባልዋ ተለያይታ አዲስ የተዋወቀችው ሰወዬ ልታገባው እንደሆነ ልታበስረው ስትገባ ያ በውሸት ሲያወራት የነበረው ባለ facebook አድራሻው ዘግቶ ከመንደሩ ጠፍቷል።

ዱንያ የት አትጥበባት?
"ምድር ዋጭኝ" ብትላት መች ልትውጣት? ህይወት ጨልሞባት፣ መኖር አስጠልቷት ራሷን እየረገመች አዝና ተክዛ ቁጭ ብላለች።

ባል አዲሷ ሙሽራው ጋ መቆየት ያለበትን ቆይቶ መጫወት ያለበትን ተጫውቶ ወደ ቀድሞ ሚስቱ ቤት ሲሄድ በሀዘን ተውጣ ተቀምጣለች።
"ምንድን ነው ሰላም አይደል እንዴ?" ሲላት
"ሰላም ነው" ትለዋለች
"ምን ሆንሽ?"  "ምንም"
ትቷት ይሄዳል።

አሁንም ተመልሶ ሲመጣ ሰውነቷ ከሳስቶ ፊቷ ተሸብሽቦ ያገኛታል
"ምንድን ነው የሆንሽው?"
"ምንም አልሆንኩም"
"ያስቀየምኩሽ ነገር አለ"
"ኧረ የለም"
"ሀሳብ መቀየር አስበሽ ነው?"
ፀጥ ረጭ አለች።

የዛኔ ባል አጠገቧ ቁጭ ብሎ እያፅናናት
"ምን ላርግ ታድያ? ከአንቺ መኖር እየፈለግሁ፣ ሳልጠላሽ፣ ሳላስከፋሽ በራስሽ ፍላጎት ያመጣሽው ሀሳብ ነው። እኔ ግን አሁንም ቢሆን የማከብርሽ የምወድሽ ባለቤቴ ነሽ። አንቺም ከእኔ የመለየት ፍላጎት ከሌለሽ ያመጣኋትም ሙስሊም እህትሽ ናት አብራችሁ ትኖራላችሁ። እሷም በቤቷ አንቺም በቤትሽ አብረን እንኑር።" አላት

በዚህ ሰዓት ካላይዋ ላይ የተጫናት ተራራ የተነሳላት በሚመስል መልኩ በደስታ ፈንጥዛ ባልዋን እየሳመችና እያመሰገነች እያለቀሰች ደስተኝነቷን ገለፀችለት።

በመጨረሻም ባልየው ባለ ሁለት ሲም ሆኖ ከሁለቱም ሚስቶቹ ጋ አብረው መኖር ጀመሩ።


NB: ታሪኩ ላይ የተጠቀሱ በሸሪዓ ክልከላ ያለባቸው ነጥቦች አሉ [ፎቶ መጠቀምና ውሸትን] ይመስል
ዘንግተናቸው ሳይሆን ከታሪኩ ብዙ ሰው ሊማር ይችላል ብለን ስላሰብን ነው።
ማስተላለፍ የተፈለገውም ባሎች እንዲህ እንዲያደርጉ ሳይሆን ሴቶች ከምንም ነገር በፊት ክብራቸውን (ትዳራቸውን) ማክበርና መታዘዝ እንዳለባቸው ለማስገንዘብ ነው።

ኮፒ!!

በጣም ገራሚ ትምህርት አለው አንብቡት በተለይ ሴቶች ወንዶችም እንደዛው።
https://t.me/tubaliligurebae/11431
https://t.me/tubaliligurebae/11431
1.2K viewsedited  20:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ