2022-08-27 17:56:21
አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ ራሱንም ለሁሉ ቤዛ ሰጠ፥ ይህም በገዛ ዘመኑ ምስክርነቱ ነበረ፤ (1ኛ ጢሞ 2፥5-6)
#መታረቃችን_በሞቱ_መዳናችን_በሕይወቱ!
ኢየሱስ የማዳንን ስራ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ ፈፅሟል ነገር ግን ዛሬም ድረስ ህያው ነው፨ የዛሬ 2000 ዓመት የተሰራው ስራ አሁንም ትኩስነቱ እንዳለ ነው፨#ከእግዚአብሔር_ጋር_መታረቃችን_በኢየሱስ_ሞት አንድ ጊዜ የተጠናቀቀና የተፈጸመ ቢሆንም #መካከለኛነቱ ግን ዛሬም ድረስ ነው ወደፊትም ይኖራል፨
በእርግጥ ክርስቶስ ኢየሱሰ ዛሬ ስለመታረቃችን አንዳች የሚያደርገው ስራ የለም፨ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ ያለው ሊቀ ካህናችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ቀደሙት የብሉይ ካህናት ዕለት ዕለት ስለ በደልና ስለ ኃጢአት የሚሆን ማናቸውንም ዓይነት መስዋዕት አያቀርብም፨ ለመስቀል ሞት ራሱን አሳልፎ ሲሰጥ ይህን አንድ ጊዜ ፈጽሞ አድርጎታልና፨ ስለዚህ የክርስቶስ የማስታረቅ ሥራ የተጠናቀቀ ነው ማለት ነው፨ ይህ ማለት መካከለኝነቱ ተጠናቋል ማለት ነውን? አይደለም!!! መጽሐፍ እንዲህ ይላል
" ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን " (ሮሜ 5፥10)
መታረቃችን በሞቱ መዳናችን ግን በሕይወቱ ነው፨ ለመታረቃችን መካከለኛ የነበረው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬም ለሰዎች መዳን መካከለኛ ነው፨
ሐዋርያው ሲናገር ከተናገርነውም ዋና ነገሩ ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፥ እርስዋም በሰው ሳይሆን በጌታ የተተከለች ናት። (ዕብ 8፥1-2)
በዚህ በማያልፍ ሕይወት ኃይል በመልከ ጸዲቅ ሹመት የዘላለም ሊቀ ካህን በሆነበት ሰማያዊ አገልግሎቱ ነው ሰዎች የሚድኑት! የማዳኑ ስራው ከማያልፈው ሕይወቱና በግርማው ዙፋን ቀኝ ካለው ሰማያዊ አገልግሎቱ ጋር የተወዳጀና የተቆራኘ መሆኑ ግልፅ ነው!
አሁንም ሐዋርያው በዚህ ከሰማያዊ አገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ሲመሰክር " ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። " (ዕብ 7፥25) ያለውም ለዚህ ነው!
#ትናንት_ያዳነን_ዛሬም_ነገም_የሚያድን_ኢየሱስ_ብቻ_ነው!
"ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው። " (ዕብ 13፥8)
https://t.me/lifeofGodzoe
ከ zoe ማስታወሻ ወዳጄን ኢየሱስን ኑና እዩት
192 viewsZoe , 14:56