Get Mystery Box with random crypto!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለመናፍቃንና ለአህዛብ መልስ አላት!

የቴሌግራም ቻናል አርማ yemerejawechsibesebchannel — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለመናፍቃንና ለአህዛብ መልስ አላት!
የቴሌግራም ቻናል አርማ yemerejawechsibesebchannel — ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለመናፍቃንና ለአህዛብ መልስ አላት!
የሰርጥ አድራሻ: @yemerejawechsibesebchannel
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

እዚህ ቻናል ውስጥ አህዛብ እና መናፍቃን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች በክርስቶስ አምላካችን ፣ በቅዱሳኑ ትሩፍት እና በስርዓተ ቤተ ክርስትያን ላይ ስለ ሚነሱ የስህተት ና የቅሰጣ ትምህርቶች ሙሉ መልስ የሚሰጥበት ቻናል ነው። በተመሳሳይ፦
* የቤተ ክርስትያን ቀኖና፣ዶግማ፣ትውፊት፣ታሪክ
* ነገረ ቅዱሳን
ይዳስሳሉ ይነገራሉ።
ለማንኛውም አስተያየት በዚህ ታገኙናላችሁ
@Selamawitttttttt

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-18 19:27:55
ዲያቆን አለን ➻መመዘኛ መስፈርቱስ

#ዲያቆናዊት ማለት ለሴት ጾታ ሆኖ ኣገልጋይ ማለት ነው
•••ዲያቆናዊት ለመሆን በክርስትያናዊ ሰነ ምግባር የተመሰከረላቸው እንግዳን በአግባቡ በመቀበል ፡ የቅዱሳን እግር በማጠብ ፡ የተቸገሩትን በመርዳት ፡ ለመልካም ስራዎች ንቁ በመሆን፡በመልካም ስራዎችዎ የታመነባቸው ፡ ከነገር የራቁ ፡ ልጆቻቸው በስርአት ያሳደጉ፡ ዕድሜያቸው ከስድሳ (60) ዓመት በላይ የሆኑ ፡ በአንድ ባል ፀንታ የኖረች፡ ሁለተኛ ያላገባች መሆን አለባት። ስለዚ በዚ ስነ ምግባር የተመሰከረላቸው ዲያቆናዊት ተብለው ይሾማሉ ። (ፍት.ክ.ኣን.8 ፡ 2ይ ዲዲስቅልያ 17 ፡ 1ይ ጢሞ 5፡9-11)

➻ስርዓተ ሲመት (የሹመት ስርዓት)

ሕገ ቤተክርስቲያን በሚፈቅደው መሰረት ይህን መመዘኛ አሟልታ የተገኘች ወደ ኤጲስ ቆጶስ ቀርባ የቡራኬ ጸሎት ከተፀለየላት በኋላ ኤጲስ ቆጶስ በኣንብሮት እድ ሳይሆን በቃል ብቻ ዲያቆናዊት ብዬሻለሁ ይላታል ።
➻የዲያቆናዊት ኣገልግሎት

በሴቶች መግቢያ በር ማስተባበርና መቆጣጠር ፡ከኤጲስ ቆጶስ፡ካህን አና ዲያቆን ወደ ሴት ምእመናን ትላላካለች። በንኡስ ክርስቲያን ጥምቀ አካላቸው ደግሞ ዲያቆናዊትዋ ትቀባቸዋለች።

በአጠቃላይ በስርዓተ ቤተክርስቲያን ሴቶችን የሚመለከት ለሴቶች ማስተማር መምከር እና ማገዝ ይገባታል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን
277 viewsDawit Asfaw, 16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 16:27:08

232 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 13:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 01:09:20

395 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 22:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 14:06:21
476 viewsDawit Asfaw, 11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 12:08:25
631 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 12:08:06 ከመልካም ወጣትነት ወደ ለየለት ዕብደት ከተድላ ደስታ ወደ ልቅሶና ዋይታ
መልካም የነበረው ወጣት በዕብዶች፣ አጭበርባሪዎችና ዕውራን መሪዎች እየተጭበረበረና እያበደ ወደ ገደል እየገባ ነው።
በኦርቶዶክሳዊ እምነቱ ለዘመናት በሥነ ምግባር ታንጾ ደስተኛ የነበረው ትውልድ ወደ ለየለት ዋይታና ልቅሶ እየገባ ነው።

ዕውራን መሪዎቻቸው በዘረፉት ገንዘብ እየሳቁና እየተሳለቁ ትውልዱን ግን እየሳቁበትና እየተሳለቁበት፣ ብሎም እያሳቀቁት ነው።
ዛሬ ላይ ሃይማኖት-አልባ የሆነው የትናንቱ የአውሮፓውያኑ የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ መጀመሪያ ላይ እንደዚህ ነበር። አሁን ላይ በሥነ ምግባር ጉድለት በዓለም ላይ አንደኛ ሆኗል። የአምልኮ ቦታዎቻቸው እየተዘጉ ነው። ትውልዱ የዕለት ከዕለት ኑሮው ገደብ አልባ ኃጢአት መሥራት ላይ ያተኮረ ነው።

ምክንያቱ ደግሞ ዕውራን መሪዎች በባዶ ቅዠት ስለመሯቸው ነው። መጨረሻ ላይ እንደተጭበረበሩ ሲገባቸው የአምልኮ ቦታቸውን ሽጠው ለጭፈራና ለዳንኪራ መሰብሰቢያ አደረጉት።
የእኔ ትውልድ መልካም ወጣትም የነገ እጣ ፈንታው ይኼው ነው።
እጅግ በጣም ያሳዝናል።

“ ዕውሮችን የሚመሩ ዕውሮች ናቸው፤ ዕውርም ዕውርን ቢመራው ሁለቱም ወደ ጉድጓድ ይወድቃሉ።”
— ማቴዎስ 15፥14
522 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 09:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 21:44:20
532 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 21:43:58 መልካም ወጣት ማለት ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖት ወጥተህ በመ*ቅ አዳራሽ መክተም አይደለም።
መልካም ወጣት ማለት ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል ከአንገትህ ላይ በጥሶ መጣል አይደለም።
መልካም ወጣት ማለት ቅድስት ድንግል ማርያምን መካድ ማለት አይደለም።
መልካም ወጣት ማለት ለሰዎች ይታዩ ዘንድ በምድር ላይ ባለጠግነትንና ዝነኝነትን ማካበት አይደለም በምድር ላይ ሁሉ የከንቱ ከንቱ ነው።

ይልቁንስ መልካም ወጣት ማለት ወንጌል ነው
ወዳጄ ወንጌል ማለት በሽንገላ ከንፈር ኢየሱስ ያድናል ማለት አይደለም። ወንጌል ማለት ክርስቶስን አምኛለውኝ ብሎ በግላዊ ግብር ለክርስቶስ ያለመታመንም ማለት አይደለም። ወንጌል ማለት መከራ መስቀልን መሸከም ነው። ወንጌል ማለት ክርስቶስ የተጓዘበትን የኩርንችት መንገድ በደስታ መራመድ ነው ። ወንጌል ማለት ለማዕተብህ ትሞታለህ ሲባል ከስጋው ይልቅ ነፍስን አስበልጦ ቀድሞ መሰለፍ ነው። ወንጌል ማለት ስለክርስቶስ ፍቅር ስጋህን እና ምኞትህን ገድለህ ለሞተልህ አምላክ መሰጠት ነው። ወንጌል ማለት ነፍስን መግደል በማይችሉት ፈርዖኖች ፊት በክብር ማሸብሸብ ነው ።
ወንጌል የምታወራው ልብ ወለድ ሳይሆን የምትላላክለት መወደድ ትዕዛዝ እንጅ። ወንጌል ማለት ክርስቶስ በደሙ የዋጃት ቤተክርስቲያን ክብር ላይ ዕጣ ሲጣጣሉባት እንደ 44 ታቦት ብላቴናዎች ቀድሞ የመገኘት ጥሪ ነው። ወንጌል የምትታዘበው እና ከአውደምህረት ላይ የምትወረውረው የማትኖርበት ቃል አይደለም። የምታልፍበት የመከራ ኮረብታ እንጅ ።
ከእዚህ አማናዊ ወንጌል ከሆነው ህዝብ ተማር። በጣምም ተማር!
ልጆቻችሁን ወንድም እኅቶቻችሁን "መልካም ወጣት አዳራሽ" የምትልኩ ኦርቶዶክሳውያን ጊዜያዊ መላ ፍለጋ ልጆቻችሁን ለዘለዓለማዊ ሞት አሳልፋችሁ እየሰጣችሁ እንደሆነ ዕወቁ።
አዎ ልክ ነው ዘፋኙ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው አዎ ልክ ነው ሰካራሙ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው አዎ ልክ ነው ሱሰኛው ኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው አዎ ልክ ነው ተሳዳቢው ተራጋሚው ተደባዳቢው አመጸኛው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነው ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቷ እና ሀይማኖቷ አጥብቀው ያወግዛሉ።
የአባ ዘጋስጫ ሀይማኖት የአባ ኤፍሬም ሀይማኖት የቅዱስ ያሬድ ሀይማኖት የቅድስት አፎሚያ ሀይማኖት የአቡነ ተክለ ሀይማኖት ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቡነ አረጋዊ ሀይማኖት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ነው ትልቅ እምነት እና ከክርስቶስ ቀጥሎ በክርስቶስ መንገድ የሄዱ ቅዱሳን የተጠሩባት ሀይማኖት (1ቆሮ᎐11:1) እኔ ስጠራበት በመጥፎ ስራዬ ላፍር በሀይማኖታችን ግን ልኮራ ይገባል።
ይህ ሰበብ ሊሆነን አይገባም እኔ መልካም ወጣት እንድሆን መ*ቅ መሆን በፍጹም አይጠበቅብኝም!!
ኦርቶዶክሳውያን ሰባክያነ ወንጌል ማኅበረ ቅዱሳንና ሌሎች መንፈሳዊ ማኅበራት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ኦርቶዶክሳዊውን ወጣት የመጠበቅ ኃላፊነትና አደራ ከጌታ የተሰጣችሁ ነውና ትውልዱን ከጥፋት ለመጠበቅ ድጋማችሁን ሁሉ የነፍስ ዋጋ ያድርግላችሁ።
ዳሩ ግን ባለ ጠጎች ሊሆኑ የሚፈልጉ በጥፋትና በመፍረስ ሰዎችን በሚያሰጥምና በሚያሰንፍ በሚጎዳም በብዙ ምኞትና በፈተና በወጥመድም ይወድቃሉ።

ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና (፩ጢሞ ፮፣፲) አንዳንዶች ይህን ሲመኙ ከሃይማኖት ተሳስተው በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ።
አንተ ግን የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ከዚህ ሽሽ ጽድቅንና እግዚአብሔርን መምሰል እምነትንም ፍቅርንም መጽናትንም የዋህነትንም ተከታተል።

መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል የተጠራህለትንም በብዙም ምስክሮች ፊት በመልካም መታመን የታመንህለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ።
ደግሞ ሁለተኛ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው።" (ዮሐ 21:16-17 )

#ኦርቶዶክሳዊ_ወጣት
565 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:06:24

553 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 06:38:59

521 viewsSelam Ye Tewahdo Lij, 03:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ