2022-08-26 08:38:48
የመልካምነት ምላሽ
ሳውዲ አረቢያ
ጅዳ ኤርፖርት
ከሪም እና ሰኢድ ትውውቅ የላቸውም
ለሀጅ ጉዞ ጅዳ ኤርፖርት ነበር የተገናኙት..
ከሪም በማሌዥያ በህንፃ ተቋራጭ በኮንስትራክሽን የስራ ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን
ሰኢድ ደግሞ በኢንዶናዥያ በግል ሆስፒታል ውስጥ ፊዚዮ ቴራፒስት ሆኖ ያገለግላል
የኢስላማዊ ወንድማማችነት ጭውውት ይጀምራሉ
ከሪም ነበረ ጨወታ የጀመረው
" አላህ ወፍቆኝ ለአስረኛ ጊዜ ነው ሀጅ ዚያራ የመጣሁት "
ሰኢድ ፈገግ በማለት " ሀጅ መብሩር አላህ ይቀበልህ ወንጀልህንም ይማርህ .
አሜን ወንድሜ
.. አንተስ ስንተኛ የሀጅ ጉዞህ ነው ?
ሰኢድ መለሰ :- የመጀመሪያዬ ነው በመጨረሻዋ ሰአት የአላህ ተአምር ታክሎበት ተሳካልኝ እንጂ የሀጅ የጉዞ ፕሮግራሜ ተስተጓጉሎ ነበር
ፕሮግራምህ እንዲት ነበር ሊስተጓጎል የነበረው?
ታሪኩ ረጅም ነው ባልጀምረው ይሻላል
ግድ የለም ቀጣዩ ወደ መካ በረራችን ሰአታት ይቀሩታል
ታሪኩን አጫውተኝ መስማት ጓጉቻለሁ
ካልክ እንግዲህ ይኸውልህ
" እኔ በግል ሆስፒታል ውስጥ ፊዚዮ ቴራፒስት ነኝ ክፍያው ብዙም አጥጋቢ ባለመሆኑ የሀጅ ጉዞን ለማሳካት ለ20 አመታት ነበር ገንዘብ ሳጠራቅም የኖርኩት
እናም በዚህ አመት ሀጅ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ገንዘብ ስላኖርኩ በደስታ ነበር የሀጅ መሰናዶዬን በማጠናቀቅ ላይ ነበርኩ
በምሰራበት ሆስፒታል ሙሉ አካሉ ፓራላይዝ የሆነ ሚስኪን ታዳጊ ልጅ ክፍል ይዞ ህክምና ይከታተላል
ወደ ምሳ ሰአት አካባቢ ላይ ነው የታዳጊው እናት ወደ ቢሮዬ ዘለቀች
ለታዳጊው ለረጅም ጊዜ የህክምና አገልግሎት ከሚሰጡት ውስጥ በቀዳሚነት እኔ ኑኝ
በእርግጥም ብዙም ባይባል ከዕለት ዕለት በጤናው ላይ መጠነኛ መሻሽሎችን አይቻለሁ ..
እናቲቱ ፊቷ ላይ ጭንቀት እና መረበሽ ይታይባታል
በሀዘን በተዋጠ በሰለለ ድምፅ
ጋሼ ብላ ነው የምትጠራኝ
" ጋሽ ሰኢድ ልጄን ከእንግዲህ ለአላህ ልተወው ነው ዛሬ የመጨረሻችው የህክምና ዕርዳታ የምናገኝበት ቀን ነው " አለችኝ
ግራ ተጋባው
ለልጇ በምንሰጠው የህክምና አገልግሎት ደስተኛ ስላልሆነች ሌላ ሆስፒታል ልትቀይር ነው? በማለት በውስጤ አሰብኩ
እናቲቱ ቀጠለች " ጋሽ ሰኢድ አላህ ምስክሬ ነው አንተ ለልጄ ከአላህ በታች የተቻለህን እርዳታ አድርገሃል ብዙ መሻሻልም አሳይቷል አላህ ጀዛህን ይክፈልህ በማለት እንባዋን እያፈሰሰች ከቢሮዬ ወጣች ..
ታሪኩን ተመስጦ የሚሰማው ከሪም ግራ በመጋባት
" በምትሰጡት አገልግሎት ደስተኛ ከሆነች እና የልጇ ጤንነት መሻሻሉን ካመነች ታዲያ ለምን ሆስፒታሉን ለመልቀቅ ወሰነች ?
" በወቅቱ እኔም ተመሳሳይ ጥያቄ ነበር ጭንቅላቴ ውስጥ የተመላለሰው
ከቢሮዬ ወጥቼ ቀጥታ ወደ ሆስፒታሉ አስተዳደር በመሄድ ሴትየዋ የነገረችኝን በመግለጽ ምን እንደ ተፈጠረ የሚያውቁት ነገር ካለ ብዬ ጠየቅኩኝ
አሳዛኝ መልስ ነበር የሰማሁት
የታማሚው ልጅ ወላጅ አባት ከስራ በመባረሩ ምክንያት ለቀጣይ የህክምና ወጪ የመክፈል አቅም ስለሌላቸው ሆስፒታሉን ለቀው እንዲወጡ ተነግሯቸው ነበር
በሰማሁት ዜና እጅጉን ተረበሽኩ
ሆስፒታሉ ወጪውን ሸፍኖ ታዳጊው ቀሪ ህክምናውን ይከታተል ዘንድ አስተዳደሩን ተማፀንኩት
" ይሄ የግል ሆስፒታል እንጂ የበጎ አድራጎት ድርጅት አለመሆኑን በመግለጽ ምንም ማድረግ እንደማይችሉ ነግሮኝ ጥያቄንዬ ውድቅ አደረገው ።
ልቤ በሀዘን እንደተሰበረ ቢሮውን ለቅቄ ወጣሁ።
ከነፍስያዬ ጋር ሙግት ገጥሜ ከውሳኔ ላይ በመድረስ
ለሀጅ ጉዞዬ በማለት ለ20 አመታት ሳስቀምጥ ወደ የነበረውን ገንዘብ አውጥቼ ተመለስኩ
" አላህ ሆይ የአንተን ቤት እንዲሁም የነብዩን (ሰ.ዐ.ወ ) መስጊድ ለመዘየር ህይወቴን በሙሉ ገንዘብ ሳጠራቅም መኖሬን ታውቃለህ የእናት ለቅሶ የታዳጊ ልጅ ስቃይ ቸል ብዬ በንፁህ ህሊና ጉዞ ማድረግ አይቻለኝምና ይህንን ገንዘብ ለእናት እና ልጅ ለመስጠት ወስኛለሁ " በማለት ከአላህ ጋር አውርቼ ቀጥታ ወደ ሆስፒታሉ ሂሳብ ክፍል ሄድኩኝ
ለቀጣይ 6 ወራት ህክምና በቂ የሚሆን ገንዘብ ነበር
ለገንዘብ ተቀባዩ
እባክህን ለልጁ እናት ክፍያውን እኔ መሸፈኔን አትንገራት ሆስፒታሉ ነው በላት አልኩ
በተመስጦ ሲያዳምጥ የነበረው ከሪም
" ለ20 አመታት ያጠራቀምከውን ገንዘብ በጠቅላላ ለበጎ ተግባር ካዋልከው ታዲያ እንዴት ወደ ሀጅ ልትመጣ ቻልክ ? በማለት በግርምት ጠየቀ
የሀጅ ዕድሌን በማጣቴ ብቆጭም ለጊዜውም ቢሆን ለእናት እና ልጅ በመድረሴ ልቤ በደስታ እና እርካታ ተሞልቶ ነበር ምሽት ወደ መኝታዬ የሄድኩት
በቀጣዩ ሳምንት ነበር
ከእንቅልፌ የስልክ ጥሪ ቀሰቀሰኝ
የሆስፒታሉ አስተዳደር ነበር የደወለው
የሆስፒታሉ መስራች እና ባለቤት የሆነው ግለሰብ የዲስክ መንሸራተት ችግር ስላለበት የግል ቴራፒስት ሁሌም አይለየውም ነገርግን
ሚስቱ እርግዝናዋ ዘጠኝ ወር ስለገባ በማንኛውም ሰአት ልትወልድ ትችላለች በሚል የግል ዶክተሩ እሷን ይከታተል ዘንድ አድርጓል
እሱ ደግሞ በአላህ ቤት ተገኝቶ ለሚስቱ እንዲሁም ለሚወለደው ህፃን ዱአ እና ሀጅ ለማድረግ ጉዞ አቅዷል
በመሆኑም
ሀጅ አብሮት የሚጓዝ የህክምና ባለሙያ አዘጋጅልኝ ስላለኝ አንተን ልጠይቅህ ነው የደወልኩት
ለአንተም ትልቅ ዕድል ነው በዛውም ሀጅ ታደርጋለህ አለኝ
ስልኩ ጆሮዬ ላይ እንዳለ ነበር ሱጁድ የወረድኩት
አየህ የአላህን ታላቅነት እና ተአምር
ያለምንም ወጪ በቅንጡ የአውሮፕላን ክፍል በመብረር ወደ ሀጅ እንድመጣ አደረገኝ
አላሁ ወክበር ..
በበረራ ላይ በነበረን ቆይታ ለሆስፒታለ ባለቤት.. ስለ ሚስኪኗ እናት እና ስለ ፓራላይዝ ልጇ ታሪክ ሁሉንም አጫወትኩት
በጣም ነበር ያዘነው
የታዳጊውን ህክምና ሙሉ ወጪ ለመሸፈን እና ከስራ ገበታው ለተፈናቀለው የልጁ አባት ስራ እንደሚሰጥ ቃል ገባልኝ
በተጨማሪም
ለሀጅ ጉዞ ለ20 አመታት አጠራቅሜ የነበረውን እና ለልጁ ህክምና የከፈልኩት ገንዘብ ሙሉ ቡሙሉ ተመላሽ እንደሚያደርግ ገለፀልኝ
ይህ የአላህ ውሳኔ እንጂ የማንም አይደለም
ታላቅ ውለታ ከታላቁ ጌታ ..
በሰማው ታሪክ ልቡ የተነካው ከሪም
በእርግጥም መልካም ሰው ነህ በማለት ሰአድ እቅፍ በማድርገ
" በእራሴ እንዳፍር ነው ያደረግከኝ
በየአመቱ ተመላልሼ ሀጅ ማድረጌ ትልቅ ጉዳይ መስሎ ይሰማኝ ነበር የአንተ ሀጅ ከእኔው ሺህ ተመጣጣኝ ነው ..
እኔ ወደ አላህ ቤት ስመጣ ኖሪያለሁ
አንተን ግን አላህ ቤቱን እንድትዘይር አመቻችቶልሃል ..
አላህ ሐጅህን ይቀበልህ
@ቢላል ዘይድ
https://t.me/ya_Allah_maran
773 views śmîle , edited 05:38