2023-02-09 10:20:28
አንዳንድ ጊዜ የዱዓችን ተቀባይነት በተግባር የሚረጋገጠው ለኛ ይጠቅመናል ብለን ያሰብነውንና በጣም የምንፈልገውን ነገር ስናጣ፣ ለኛ ይጎዳናል ብለን ያሰብነውንና እንዳያገኘን የፈራነውን የማንፈልገውን ነገር ስናገኝ ሊሆን ይችላል።
አላህ ጥበበኛና ለባሮቹ እጅግ በጣም አዛኝ ስለሆነ ከኛ በላይ ለኛ የሚጠቅመንና እኛን የሚጎዳንን ያውቃል። ስለሆነም የሆነ በጣም የፈለግነውንና የጓጓንለትን ነገር ስናጣ ከበሳጨት ይልቅ የአላህን ውሳኔ ወደን እንቀበል። «በቃ! ለበጎ ነው። ለኔ ባይለው ነው። የማይጠቅመኝ መሆኑን አላህ አውቆ ነው!» ብለን እንለፈው።
በተቃራኒው የማንፈልገውን ነገር ስናገኝ ደግሞ «ይሄም ለበጎ ነው። ምንም እንኳ እኔን ባይመስለኝም አላህ ጠቃሚዬ መሆኑን አውቆ ነው!» የሚሉ ምክንያቶችን ወደ ውስጣችን እናምጣ። ይህንን የምንለው ራሳችንን ለማጽናናት ሳይሆን ሐቂቃ የእውነትም ስለሆነ ነው። ለወዳው ባይመስለንም የዚያን ነገር እውነታ ከሆነ ጊዜ በኋላ በተጨባጭ እንረዳዋለን።
አላህ እንዲህ ብሎናል፦
(…وَعَسَىٰ أَن تَكْرَهُوا شَيْئًا وَهُوَ خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰ أَن تُحِبُّوا شَيْئًا وَهُوَ شَرٌّ لَّكُمْ ۗ وَاللَّهُ يَعْلَمُ وَأَنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ)
«…አንዳች ነገርን እርሱ ለናንተ የበለጠ ሲሆን የምትጠሉት መኾናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አንዳችንም ነገር እርሱ ለናንተ መጥፎ ሲሆን የምትወዱት መሆናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አላህም (የሚሻላችሁን) ያውቃል ግን እናንተ አታውቁም፡፡»
[አል-በቀረህ: 216/٢١٦]
(… فَعَسَىٰ أَن تَكْرَهُوا شَيْئًا وَيَجْعَلَ اللَّهُ فِيهِ خَيْرًا كَثِيرًا)
«… አንዳችን ነገር ብትጠሉ አላህም በእርሱ ብዙ ደግ ነገርን ሊያደርግ ይቻላልና፡፡»
[አ-ን'ኒሳእ: 19/١٩]
አላህ ለሚወደው ተግባርና ንግግር ይወፍቀን።
@Islamic_direction
297 viewsNizal Ümu ªň€s, 07:20