2023-05-27 08:35:38
+• 20 ወንድማዊ ምክሮች •+
1. ፈገግታ ጌጥ ነውና ከፊትህ ላይ አይለይህ::
2. ብዙ ማውራት ሰውን ያታክታልና በንግግርህ ቁጥብ ሁን::
3. የምትጀምራቸውን ነገሮች ሁሉ በጸሎት ጀምር::
4. ያልተገባ ነገር ተናግረህ ትዝብት ላይ እንዳትወድቅ የማታውቀውን ነገር አላውቅም ለማለት አትፈር::
5. በሁሉ ነገር ላይ አስተያየት ካልሰጠሁ አትበል::
6. በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትሆን "እግዚአብሔር ይመስገን" ማለትን አትርሳ::
7. በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ምጽዋትን የምትሰጥ ሁን::
8. ለመቀየም የዘገየህ ይቅር ለማለት የፈጠንክ ሁን::
9. ሕይወትህን በእቅድ ምራ::
10. በጥበብ ማደግ ገደብ የለውምና ትምህርትን በቃኝ አትበል፤ ሊያስተምርህም ፈቃደኛ ከሆነ ሰው ሁሉ ተማር::
11. ውሳኔን ለመስጠት ችኩል አትሁን::
12. በሰው እንዳትናቅ የዋህ ሁን እንጂ ጅል አትሁን:: ሰዎች እንዳይርቁህ ብልጥ ሁን እንጂ ተንኮለኛ አትሁን::
13. በሰዎች ፊት ያለ ፍርሃት እንድትቆም የምትማራቸውን ነገሮች አጥርተህ ተማር::
14. ክርስትና ሕይወት ነውና፤ የምታምነውን በሕይወትህ ለመተግበር የተጋህ ሁን::
15. የሚያስቀይምህን ነገር ልትሠማ ትችላለህና ሰዎች የሚያወሩትን በድብቅ አትስማ::
16. በአመጋገብህ ትዝብት ላይ እንዳትወድቅ ስትመገብ አትስገብገብ::
17. አዳማጭ ከማጣት የቆሰሉ ብዙ ሰዎች አሉና፤ ሰዎች ችግራቸውን ሲያዋዩህ ጆሮ ስጣቸው::
18. ምጽዋት ለጠየቀህ መስጠት ስንኳ ባትችል "እግዚአብሔር ይስጥልኝ" ማለትን አትርሳ::
19. በእንስሳት ላይ ጨካኝ አትሁን::
20. የሰዎችን ሁኔታ የበለጠ ለመረዳት "እኔ በእነርሱ ቦታ ብሆን ምን አደርግ ነበር?" ብለህ ራስህን ጠይቀው::
Fresenbet G.Y Adhanom
----------
የፌስቡክ ገጽ: https://www.facebook.com/fre.asalib
ቴሌግራም: https://t.me/fresenbett
2.6K viewsFre, edited 05:35