Get Mystery Box with random crypto!

Ayu Zehabesha-Official (አዩ ዘሀበሻ)

የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabeshaofficial
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 182.82K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2024-05-02 10:19:59
ድጋሚ ታስሯል ተብሏል
ለምን መፈታትህን አሳወክ ተብሎ ዳግም እንዲታሰር ተደርጓል
እራሱ የፌዴራል ፓሊስ አስሬዋለው ብሎ መግለጫ አወጣ። በወታደራዊ ዲስፕሊን እና ተቋማዊ ሥነ ስርዓት ህግ መሰረት ቀጣው። በስተመጨረሻም ቅጣቱን ጨርሶ ተፈቶ ወደ መደበኛ ሥራው ተመለሰ።
ይህንንም "ተፈትቻለው" ብሎ ለህዝብ አሳወቀ።ስለተጨነቃችሁልኝ አመሰግናለው ብሎ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ለጥፎ ነበር።
መፈታቱን በማኅበራዊ ሚዲያ ማሳወቁ እንደ ወንጀል ተቆጥሮበት ዳግም አስረውታል። ምክንያት ሲባል "መፈታትህን ለምን አሳወክ " በሚል ነው ተብሏል።
"ፈጣን እና እውነተኛ ሀገራዊ መረጃ እንዲደርሳችሁ የቴሌግራም ቻናላችንን ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ያድርጉ"
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
16.6K viewsAyu, 07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 11:50:06 << ተግባር ከሌለ መወያየት ብቻውን ባዶ ተስፋ ነው >> - ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ << መወያየት ብቻውን በቂ አይደለም፤ መተግበር እንዳለበት >> ተናግረዋል።
ፕሬዝደንቷ ይሄን ያሉት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሴቶችን ተሳፎ በተመለከተ በትናንትናው ዕለት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው።
<< በኢትዮጵያ መናናቅ እና የት ይደርሳል ማለት ችግር ሲፈጥር እየታየ መሆኑንም >>  ፕሬዝደንቷ አመልክተዋል።

<< መወያየት ብቻውን በቂ አይደለም >> ያሉት ፕሬዝደንቷ << መተግበር መቻል እንደሚኖርበት በግልፅ ቋንቋ ተናግረዋል። 

አክለውም << እንደ ሀገርም የመወያየት ችግር ባይኖርም መሠረታዊ ችግሩ አፈፆፀም መሆኑንም >> አብራርተዋል።

ውይይቶች ተሞክሮዎች ሁሉ መሬት ወርደው  ካልተተገበሩ ባዶ ተስፋ መስጠት ነው ያሉን ሳህለወርቅ የምክክር ሂደቱ ችግሮችን በዘለቄታዊነት ለመፍታት የሚደረግ ጥረት እንጂ ለተወሰነ ጊዜ የተወሰኑ ሲሉ የጠሯቸውን ሁኔታዎች ለማስተገሻ እንዳልሆነ  ግልፅ ማድረግ  ይገባል ብለዋል።

የማይሆን ተስፋ ሆኖ እንዳይታይም በጣም ሲሉ በገለፁት ደረጃ  መጠንቀቅ እንደሚያስፈልግም አመላክተዋል።  << ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ መስራት ያስፈልጋል በማለትም ብዙ ጊዜ የሚስተዋለው  እንወያይ እንጋገር ከማለት የዘለለ አይደለም >> ሲሉ ተችተዋል።

ሳህለወርቅ እንደሚሉት << አሁን በተለይ መናናቁ እና የት ይደርሳል መባባሉም ለሀገሪቷ ችግር እየሆነ መጥቷል >> ሲሉ አንክሮ ሰጥተዋል።

በመሆኑም እንደሀገር ያለብንን ችግር ለመቅረፍ የሚረዳው አማራጭ ሰው ያለውን ሁሉ ሓሳብ እንዲያዋጣ ማበረታታት እና መረዳት ብሎም መግባባት ነው ብለዋል።

በንግግር ፋንታ ቂምንና ማግለልን ብሎም መሰል ነቀፌታዎችን  ማስወገድ ያስፈልጋል ሲሉ መክረዋል።

በሌላ በኩል ህዝብ ማዕከል ያደረገ ውሳኔ ሲሰጥ ሴቶችን አካታች ማድረግ ግዴታ መሆኑን አስቀድመው በህወሓት ሃይሎች እና በፌደራሉ መንግስቱ መካከል  የነበረውን ጦርነት በቋጨው የፕሪቶርያ ዘላቂ ግጭት ማቆም ስምምነት ሴቶች አለመወከላቸውን ጠቁመዋል። 

በጦርነቱ ሂደት ውስጥ ሴቶች ደርሶባቸዋል ያሉትን  ከፍተኛ ጉዳትም እስታውሰዋል።

ይሁን እንጂ አሁን ላይም  በተመሳሳይ መልኩ ሀገሪቷ ውስጥ ውጊያዎች፣ ጦርነቶች፣ መገዳደልና  መፈናቀል መኖሩን አስቀድመው በጥቅሉ  ከጦርነት ካለመግባባት ጋር ተያይዘው የሚመጡ ችግሮች መኖራቸወን ገልፀዋል።

በመጨረሻም በርትቶ መስራት፣የተናገሩትን መኖር እንደሚገባ አስገንዘበው ስራችን የሚወሰነውም የህዝቡን ኑሮ በመለወጥ ላይ፣ ሰላምን ለማስፈን መሆኑን አስቀድመው  ሰለም  ደግሞ << በመደለል >> ብቻ የሚገኝ አይደለም ብለዋል።

ምንም እንኳን ሳህለወርቅ ከመወያየት ባሻገር ተግባር ግድ እንደሚል አፅዕኖት ቢሰጡም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን < ምክክርሩን > ሲያጠናቅቅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ምክረሃሳቡን ከማቅረብ በዘለለ የመተግባር ስልጣን እንደሌለው በታህሳስ 2014 ዓ.ም የጸደቀው የማቋቋሚያ አዋጅ ያስረዳል።
"የቴሌግራም ቻናላችንን ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ያድርጉ"
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
12.7K viewsAyu, edited  08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-28 10:31:54
ማስታወቂያ
ጥራቱ የተመሰከረለት ሻሎም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ
አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እና
ኮተቤ 02 ጆሲ  ሙል ላይ በሚገኙ ክሊኒኮች የተሙላ የጥርስ ህክምና እየሰጠ ይገኛል።
የሚሰጣቸው አገልግሎቱች
የቁሸሾ ጥርስ   ማጠብ
የተቡረቡሮ ጥርስ መሙላት
በአበቃቀል የተበላሹ ጥርሳችንን ብሬስ ማስተካከል (በተመጣጣኝ ዋጋ እና አከፋፈል አማራጮች )
የጥርስ ስር ህክምና
የድድ  መድማት ችግር ላለባቸው
ሁሉንም አይነት ሰው ሰራሽ ጥርስ አንተክላለን ፤ ለተተከለዉም ዋስትና እንሠጣለን
ታክመው የማይድኖ ጥርሶች እንነቅላለን
አድራሻ   ቁጥር-4 ኪሎ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ
,ቁጥር 2 - ኮተቤ 02 ጆሴ ሞል
ለበለጠ መረጃ  0911424242
ስለ ጥርስ ንፅህና አጠባበቅ እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት Telegram join

https://t.me/shalomdentalclinic
https://t.me/shalomdentalclinic
https://t.me/shalomdentalclinic
13.4K viewsAyu, 07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-27 16:28:17
650 ሺ ብር የተጠራው ሰንጋ
አንድ ሰንጋ 650 ሽህ ብር ተጠርቷል።ሌላው 550 ሽህ ጥሪ ተሰምቷል።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እነዋሬ ከተማ አስተዳደር በአመት አንድ ጊዜ የሚውለው የሆሳዕና ገበያ ዘንድሮም የተለየ ነገር ታይቶበታል።
ይህ በምስሉ ላይ የሚታየው ሰንጋ 650 ሽህ ብር ተጠርቷል ።የሰንጋው ባለቤት ወጣት ሚጥዬ ታደለ ይባላል።650 ሽህ ብር የተጠራው የጅሩ ሰንጋ ገና አልተሸጠም።

ሌላው በዚሁ ገበያ የሞረትና ጅሩ ወረዳ የማንጉዶ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ አበበ በፍቃዱ  ለ1 አመት ያክል እንደ ልጄ ስንከባከበው ነበር ያሉትን ሰንጋ በ550 ሽህ ብር ሲሉ ጠርተዋል ሲል የከተማ አስተዳደሩ ሚዲያ አስነብቧል።የሁለቱም ሽያጭ ገና አልተፈፀመም።
የቴሌግራም ቻናላችንን ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ያድርጉ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
24.2K viewsAyu, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 14:18:16
በርካታ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ጥቆማዎች እየደረሱኝ ነው - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን
በርካታ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግር ጥቆማዎች እየደረሱት መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ የጥቆማ መቀበያ ነጻ የስልክ መስመር ይፋ ካደረገ በኃላ በርካታ ጥቆማዎች እየደረሱት መሆኑን የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለኢቢሲ ሳይበር ተናግረዋል፡፡

የሚመጡ ጥቆማዎችን ተገቢነት በማጣራት ጥፋተኞችን ለሕግ ለማቅረብ ከፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑንም ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

የጥላቻ እና ሐሰተኛ ንግግሮች በአዋጁ መሰረት ከገንዘብ እስከ እስራት ቅጣት እንደሚያስከትሉ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ጠቁመዋል፡፡

ባለስልጣኑ የማህበራዊ የትስስር ገጽ አገልግሎት ሰጪዎች የኢትዮጵያን ሕግ እና ስርዓት አክብረው እንዲሰሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

ህዝቡ ለሀገራዊ ሰላም እና ለህዝቦች አንድነት ፀር የሆኑ የሐሰተኛ እና የጥላቻ ንግግሮችን ሲመለከት በ9192 ነጻ የስልክ መስመር ጥቆማዎችን እንዲሰጥ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አሳስበዋል፡፡
የፌስቡክ ገፃችንን ከስር ባለው ሊንክ Follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/ayuzehabesha.1999
21.2K viewsAyu, edited  11:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 13:41:19
“በኢትዮጵያና ኤርትራ የሰብአዊ መብት አያያዙ እንደከፋ ነው” - ዩኤስ
የዩናዩትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሀገራትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በተመለከተ የሚያወጣውን ዓመታዊ ሪፖርት ከትናንት በስተያ ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ትላንት ሚያዚያ 14/2016 ዓ.ም ባወጣው የሃገራትን የሰብአዊ መብቶች አያያዝ በሚተነትነው ሰፊ የአውሮፓያኑ የ2023 ዓመታዊ ሪፖርቱ፤ ፣የኢትዮጵያ መንግሥት ወይም የመንግሥት ወኪሎች፣ ከሕግ ውጪ የዘፈቀደ ግድያ መፈፀማቸውን፣ በርካታ የሃገር ውስጥና የውጪ ሃገራት የሰብአዊ መብት ቡድኖች ሪፖርት ጠቅሶ ይፋ አድርጓል።

ግድያዎቹ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል እየተካሄዱ ባሉ ግጭቶች እንዲሁም ትግራይን ጨምሮ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈጸሙ እንደሆነ አስታውቋል።
የፌስቡክ ገፃችንን ከስር ባለው ሊንክ Follow ያድርጉ
https://www.facebook.com/ayuzehabesha.1999
20.3K viewsAyu, edited  10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 13:36:41
ኬንያና ሶማሊያ የጎርፍ አደጋ ማስጠንቀቂያ አወጡ
በምሥራቅ አፍሪቃ አካባቢ ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ በመሆኑ፣ ሶማሊያ እና ኬንያ የጎርፍ አደጋ ማስጠንቀቂያ ለማውጣት ተገደዋል። የኬንያው ቀይ መስቀል ማኅበር እንደሚለው ከበድ ባለው ዝናብ ምክያት ባለፈው ሳምንት ስድስት ሰዎች ሲሞቱ፣ ከ11ሺሕ በላይ የሚሆኑ ደግሞ ተፈናቅለዋል።ሶማሊያም በወንዞች ዳርቻ የሚኖሩ ዜጎቿ ከፍ ወዳለ ቦታ እንዲዛወሩ ጠይቃለች።
ትናንት በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ ከ30 በላይ ሰዎች ሞተዋል። የኬኒያ የመረጃ ምንጮች በጎርፉ ምክንያት 40 ሺህ ሰዎች ተፈናቅለዋል ያሉ ቢሆንም ተመድ 130ሺህ ሰዎች ተፈናቅለዋል ብሏል።
"ለፈጣን መረጃ ቻናላችንን Join አድርጉ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
የማስታወቂያ እና መረጃ መቀበያ
t.me/ayulaw t.me/ayulaw
18.5K viewsAyu, 10:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 13:34:14
በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ስልክ እያነጋገሩ ያሽከረከሩ ከ6 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች መቀጣታቸው ተነገረ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጅመነት ባለስልጣን በ2016 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከፍጥነት ወሰን በላይ ያሽከረከሩ ከ25 ሺህ በላይ  አሽከርካሪዎችን መቅጣቱን አስታውቋል።
ባለስልጣኑ በበጀት ዓመቱ 9 ወራት ውስጥ በ33 መንገዶች ላይ ከፍጥነት ወሰን በላይ ያሽከረከሩ 25 ሺህ 888 አሽከርካሪዎች የደህንነት ቀበቶ ያላሰሩ 3 ሺህ 800 አሽከርካሪዎች በደንብ መተላለፍ መቀጣታቸው ተገልጿል ።

በተጨማሪም 204 ሞተረኞች የግጭት መከላከያ ቆብ ወይም ሄልሜት ሳያደርጉ ፣ 6504 አሽከርካሪዎች ስልክ እያነጋገሩ በመገኘታቸው በደንብ ቁጥር 395/2009 መሰረት ቅጣት እንደተጣለባቸው ተጠቁሟል ።

በዚህም የተነሳ የሞት አደጋ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ6 ነጥብ 34 በመቶ  መሻሻል መታየቱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ገልጿል።
"ለፈጣን መረጃ ቻናላችንን Join አድርጉ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
17.3K viewsAyu, edited  10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 13:32:29 ማስታወቂያ
አያት ( ዞን 2 ፣ 3፣ 8) የሚገኙ የአያት አክሲዮን ማህበር ቤቶች መረጃ
የመኖሪያ ቤቶቹ ስፋት
- ባለ 2 መኝታ   80፣ 85፣ 90 ፣ 95 እና
- ባለ 3 መኝታ   107፣ 110 ፣ 115 ፣ 120፣ 127 ፣ 138 እና 145

አብዛኞቹ 3 መኝታ ያላቸው የመኖሪያ ቤቶች ተጨማሪ የሰራተኛ ክፋል አላቸው።

ዋጋ:
102, 258 ብር እስከ 114,839 ብር / በካሬ እንደ ግንባታ ዓይነቱ (በከፊል /በሙሉ ግንባታ) እና ቤቱ እንደሚገኝበት የወለል መጠን የሚወሰን ሲሆን :

አከፋፈል

በ15% ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤትነትን እድል የፈጠረ ! ቀሪው እንደ ውለታው/ ስምምነቱ መሰረት የግንባታው ሂደት የደረሰበትን ደረጃ ተከትሎ የሚከፈል ይሆናል።

60% በ 7 ዙር  40% ቱን ቤትዎን ተረክበው እየኖሩበት ከ 15-30 ዓመታት በሚከፈል ብድር (በ9.5% ወለድ) የዱቤ አማራጭ ያመቻቸ ፣

ሙሉዉን ክፍያ በካሽ ለሚያጠናቅቁ የዋጋ ተመን ለውጥ ሳያገኛቸው በተዋዋሉበት የመጀመሪያ የዋጋ ስምምነት መሰረት  እንዲከፍሉ ተመቻችቷል::
የቅናሽ ፓኬጅ
100% ለሚከፍል የ 25% ቅናሽ
80% ለሚከፍል የ 20% ቅናሽ
60% ለሚከፋል የ 15% ቅናሽ
40% ለሚከፍል የ 10% ቅናሽ
25 % ለሚከፍል የ 6.5% ቅናሽ

በውጪ ምንዛሪ ለሚከፍሉ የ 5% ተጨማሪ ቅናሽ ያገኛሉ
"

አያት አክሲዮን ማህበር በ2015 ዓ.ም 51.3% ትርፍ ሲያተርፍ

የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የገዛ 513,000 ብር አትርፏል

የ 100,000ሺ ብር የገዛ 51,300 ብር አትርፏል

የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር

ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የአክሲዮን መጠን 2,500

በብር 250,000 ብር

ከፍተኛ የ 20 ሚሊዮን ብር

40% ቅድመ ክፍያ ከፍለው ቀሪውን በሶስት ዓመት መክፈል ይችላሉ
አያት አ.ማ የተሰማራባቸው መስኮች:- በሪል እስቴት
በሆቴል እና ቱሪዝም
በማርብል ማምረቻ ኢንደስትሪ
በጠጠር ማምረቻ ኢንደስትሪ
በብሎኬት ማምረቻ ኢንደስትሪ
በእንጨት ብረታብረት ውጤቶች ማምረቻ ኢንዱስትሪ
በትምህርት ኢንቨስትመንት እና
በፋይናንሺያል ኢንቨስትመንት ናቸው።

ለበለጠ መረጃ እና ቤትዎን ለማስያዝ ፡ 0927715438/0903543582
ዬሴፍ
(የሽያጭ ተቆጣጣሪ)

አያት ዞሮ መግቢያዬ !
16.0K viewsAyu, 10:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-25 12:24:36 የጊብሰን ትምህርት ቤት የሰጠው ምላሽ ደርሶኛል
ለተከበራችሁ ውድ የጊብሰን ትምህርት ቤቶች ሥርዓት ወላጆች እና አሳዳጊዎች፣


ጉዳዩ: ለሁሉም የጊብሰን ት/ቤቶች ሥርዓት ወላጆች እና ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኝ  ተማሪዎች ወላጆች ወቅታዊ መረጃን ማሳወቅ ይሆናል ፡፡

በመጀመሪያ የከበረ ሰላምታዬን እያቀረብኩ በቅርቡ የተማሪዎቻችን ከተማ አቀፍ ፈተናዎች መሳተፍን በሚመለከት ያልተረጋጋ ሁኔታ እየተፈጠረ ቢሆንም እርስዎን እና ቤተሰቦች በጥሩ ጤንነት እና መንፈስ ሆነው ይህ መልዕክት እንደሚደርሶት ተስፋ አደርጋለሁ።

እንደሚታወቀው ከትምህርት ቢሮ ኃላፊ በተሰጠ መመሪያ መሰረት የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በተከበረው ጊብሰን ት/ቤቶች ስርዓት ስም ክልላዊ ፈተና እንዳይወስዱ አግዷል። ይልቁንም እነዚህ ተማሪዎች ቀድሞ ምንም ግንኙነት በሌላቸውና በማያውቋቸው የመንግሥት ትምህርት ቤቶች እንደሚመደቡ ተገልጿል። በቀላሉ ለመረዳት እንደሚቻለው፣ ይህ ያልተጠበቀ ድርጊት በትምህርት ቤታችን ማህበረሰቦች መካከል ግራ መጋባት እና ስጋት ፈጥሯል።

ይህ ውሳኔ ኢፍትሐዊ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ የማይታወቅ እና የተማሪዎቻችንን ህጋዊ መብት ያልተከተለ ነው የሚለው የትምህርት ቤታችን ጽኑ አቋም መሆኑን ለማሳወቅ እወዳለሁ። ይህንን እገዳ ከዚህ ቀደም ላላወቁ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የከፍተኛ ተቋማት ባለስልጣናት በማሳወቅ ይህ ሁኔታ ተስተካክሎ ተማሪዎቻችን ሰላማዊና ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ለክልላዊ ፈተና የመቅረብ መብታቸውን እንዲጠቀሙበት እንዲደረግ ቅሬታችንን አቅረበናል።

ከዚህ ውሳኔ ጀርባ ያሉት ሁለቱ የትምህርት ቢሮ አመራሮች አቅጣጫቸውን በሌሎች ላይ በማድረግ ውሳኔያቸውን አስገድደው እየተገበሩ ይገኛሉ። ከሥነ ምግባር ውጭ የሆነ ተግባር እንድንፈጽም ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ በየደረጃው ከተጋለጠ በኋላ በአጸፋውን ተማሪዎቻችንን ከክልላዊ ፈተና ከመከልከል ባለፈ የሁሉም ተማሪዎች የሪፖርት ካርድ ውድቅ ለማድረግ እና በመቀጠልም የጊብሰን ት/ቤቶችን ስርዓትን ሙሉ በሙሉ እንዘጋለን በማለት በማስፈራራት የትምህርት ቤታችንን ማህበረሰብ እየጎዱ ይገኛሉ።

አሁን የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ለዚህ እገዳ ተጠያቂ የሆኑ አመራሮች ተግባራቸውን በማስፋፋት አስቀደመው ለክልላዊ ፈተና የተመዘገቡ በሌሎች የትምህርት ቤታችን ቅርንጫፎች በተለይም በቦሌ እና በሲኤምሲ ቅርንጫፎች ላይ ተግባራቸውን ቀጥለዋል። እነዚህ ኃላፊዎች ወላጆች ልጆቻቸውን ምንም ግንኙነት በሌላቸው እንዲሁም ባልተማሩባቸው የተለያዩ ትምህርት ቤቶች በድጋሚ እንዲመዘገቡ በመጠየቅ ላይ ናቸው። ይህም የልጆቻችን የረጅም ጊዜ  ጥረት እና ድካም መና በማስቀረት ከፍተኛ ጉዳት ይኖረዋል። በሌላ በኩል ግን የሀገሪቱን የትምህርት ደህንነት ማጎልበት በሚገባቸው ግለሰቦች የሚፈጽሙትን ሥነ ምግባር የጎደላቸው ድርጊቶች ማሳያ ነው።

ከእነዚህ ክስተቶች አንፃር ተማሪዎቻችንን በመደገፍ በአንድነት መቆም እና የእነዚህን መሪዎች የተሳሳቱ ተግባራት ማጋለጥ የጋራ ሀላፊነታችን ነው።ሁሉም የጂ.ኤስ.ኤስ ወላጆች ለመብታቸው እና ለልጆቻቸው መብት በሀገሪቱ ህጎችና ስርዓቶች መሰረት በሰላም እና በትዕግስት እንዲሟገቱ አሳስባለሁ። የህግ የበላይነት ሊሰፍን ይገባል ይህም ፍትህን ለማረጋገጥ እና  የተማሪዎቻችንን የትምህርት ጉዞ ተጨማሪ መስተጓጎልን እንዳይፈጠር ለመከላከል በጣም ውጤታማው እርምጃ ነው።

እያንዳንዳችሁ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ ከትምህርት ቤቱ ጋር በአንድነት እንድትቆሙ እና የከፋፍለህ ግዛ ስልታቸው ወጥመድ ውስጥ እንዳትገቡ አሳስባለሁ። በጋራ፣ የልጆቻችንን የትምህርት መብቶች እናስከብራለን ከዚህም ባለፈ በትጋት የሰሩባቸውን የትምህርት እድሎች እናረጋግጣለን። በህጋዊ መንገድ መብትን ለመጠየቅ እገዛ ወይም መመሪያ ከፈለጉ፣ እባክዎን የትምህርት ቤቱን አስተዳደር ለማግኘት አያመቱ። በእያንዳንዱ እርምጃች ላይ የእኛ ድጋፍ አይለያችሁም ፣ ለዚህም ዝግጁነታችንን እናሳውቃለን።

በአሳደራችሁት እምነትዎ እና እያደረጋችሁ ላላችሁት ትብብር ከልብ እመሰግናለን። በዚህ ፈታኝ ወቅት የሚኖሩ ለውጦችን በወቅቱ ለእርስዎ ለማሳወቅ ቃል እንገባለን። ለፍትሃዊነት እና ጥራት ላለው ትምህርት ባለን ታማኝነት የምናደርገውን ጥረት በተስፋ እና በቆራጥነት እንቀጥል።
የትምህርት ቤቱ ፕሬዚዳንት
"ለፈጣን መረጃ ቻናላችንን Join አድርጉ
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
http://t.me/ayuzehabeshaofficial
18.1K viewsAyu, edited  09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ