Get Mystery Box with random crypto!

Ayu Zehabesha-Official (አዩ ዘሀበሻ)

የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabeshaofficial
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 193.66K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-23 12:59:53
የካናዳ ኤምባሲ በሰሜን ፣ መካከለኛ እና በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢዎች ዜጎቹ እንዳይቀሳቀሱ መክሯል
ኤምባሲዉ በአዲስአበባ ጭምር ዜጎቹ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል
የካናዳ መንግስት ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ በጥቅሉ አስፈላጊ እና አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር እንዳይጓዙ ሲል ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ዳጉ ጆርናል ታዝቧል። ኢትዮጵያ የሕዝባዊ አመፅ ፣ ብጥብጥ ፣ በትጥቅ ግጭት እና የወንጀል ድርጊት በዞቶባታል ሲል ባስቀመጠው ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ዜጎቹ አላስፈላጊ ጉዞን ያስወግዱ ሲልም አሳስቧል።

በዋነኛነት በሰሜን ኢትዮጵያ አማራ ፣ ትግራይ (ከመቐለ ከተማ ዉጪ ወደ አዲግራት ፣ አቢ አዲ ፣ አድዋ ፣ ሽሬ እና ማይጨዉ አካባቢዎች) እንዲሁም ወደ ቤኒሻንጉል ክልሎች ዜጎቹ አይጓዙ ሲል አስጠንቅቋል።

በተጨማሪም መካከለኛዉ ኢትዮጵያ ክፍል ጋምቤላ እና ሲዳማ ክልሎች እንዲሁም ሰሜን እና ምዕራብ ሸዋ እና ወደ አራቱ የወለጋ ዞኖች ዜጎቹ እንዳይጓዙ ጠይቋል። እንዲሁም ኢትዮጵያን ከኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣ ሱዳን ፣ ሶማሊያ እና ኤርትራ ጋር በሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎችም ዜጎቹ እንዲጠበቁ መክሯል።

ኤምባሲዉ የካናዳ ዜጎች በአዲስአበባ ጭምር ዜጎቹ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ከፍተኛ የተባለ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
Join @ayuzehabeshaofficial
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ @ayulaw
20.8K viewsAyu, edited  09:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:33:44 ራያ
ከአላማጣ እና የራያ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሺህ መድረሱን ተመድ አስታወቀ
ግጭት ከተነሳባቸው የአላማጣ ከተማ፣ ዛታ እና ኦፍላ የራያ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሺህ መድረሱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
ተፈናቃዮቹ የተጠለሉባቸውን የዞን ባለሥልጣናት ዋቢ አድርጎ ጽህፈት ቤቱ ሰኞ ሚያዝያ 14/2016 ዓ.ም. ባወጣው ሪፖርት መሠረት ከተፈናቃዮቹ መካከል 42 ሺህ የሚሆኑ በሰሜን ወሎ በምትገኘው ቆቦ ከተማ እንዲሁም 8300 የሚሆኑት ደግሞ በሰቆጣ እና ዋግ ኽምራ ዞኖች ተጠልለዋል ብሏል።
በአብዛኛው ሴቶች፣ ህጻናት፣ ታዳጊዎች እና አረጋውያንን ያሉበት ተፈናቃዮች በማኅበረሰቡ ባሉ ቤቶች ለመጠለል እየሞከሩ እንደሆነ ገልጾ፣ ሌሎች ደግሞ ከቆቦ ከተማ ሦስት ኪሎ ሜትር ርቀት በሚገኝ ጋራ ሌንጫ በተሰኘው የኢንዱስትሪ መንደር ክፍት ቦታ ላይ ተጠልለው ይገኛሉ ተብሏል።
በዚህ ስፍራ የተጠለሉ ተፈናቃዮች በአስቸጋሪ ሁኔታ ለበልግ ዝናብ መጋለጣቸውን የጠቀሰው የመንግሥታቱ ድርጅት መግለጫ የተወሰኑትን ተፈናቃዮች ወደ ሌላ ስፍራ ለማዘዋወር እየተሞከረ እንደሆነ መሬት ላይ ያሉ አጋሮቹን ዋቢ አድርጓል ጠቅሷል።
የፌደራል ኃይሎች ጣልቃ መግባታቸውን ተከትሎ በአላማጣ፣ ወልዲያ እና ቆቦ ከተሞች አካባቢ ከትናንትና ሚያዝያ 14/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ የፀጥታው ሁኔታ የተረጋጋ መሆኑም ተገልጿል።
ከአላማጣ ወደ ቆቦ የሚወስደው እንዲሁም ከአላማጣ ወደ ማይጨው የሚወስዱ መንገዶች ለትራንስፖርት ክፍት መሆናቸውን እንዲሁም ባንክን የመሳሰሉ ሕዝባዊ አገልግሎቶች እንደገና ሥራ መጀመራቸው ተጠቁሟል።
በትግራይ ክልል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ወደ አማራ ክልል እንዲጠቃለሉ በተደረጉ የአላማጣ ከተማ እና ራያ ወረዳዎች እንደ አዲስ የተቀሰቀውን ግጭት ተከትሎ በአዲስ አበባ መቀመጫቸውን ያደረጉ የካናዳ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ጃፓን፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ አሜሪካ ኤምባሲዎች ውጥረት እንዲረግብ ጥሪ አቅርበዋል።
አዩዘሀበሻ
Join @ayuzehabeshaofficial
21.9K viewsAyu, edited  08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:33:42
19.7K viewsAyu, 08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:33:32
ማስታወቂያ #የቻናል_ጥቆማ
ለኢንጅነሮች ተማሪዎች እናconstruction ዘርፍ ለይ ለተሰማሩት ሁሉ

የኮንስትራክሽ፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ አርክቴክቸር
      ተማሪ ነዎት?
በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?
በአማርኛ እና እንግሊዘኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መፅሀፍቶች፣ ቪድዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን እውቀቶች ለማግኝት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ሌክቸር የምታገኙበት

እንግዲያውስ ለርስዎ የሚሆን ምርጥ እና ጠቃሚ  ቻናል እንጠቁመዎት

Join us :-

on Telegram

https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1

on tiktok

tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons
18.7K viewsAyu, 08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:27:05
ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክር መድረክ እንዲመጡ ተጠየቀ፤ ጥበቃ ይደርግላቸዋል ተብሏል
ትጥቅ አንግበው የሚታገሉ አካላት ወደ ሀገራዊ ምክክሩ መድረኮች እንዲመጡ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡ ኮሚሽኑ ለሚሳተፉ ታጣቂዎች ጥበቃ እንደሚደረግላቸውም ገልጿል።

የኮሚሽኑ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገ/ሥላሴ፤ ግጭት ሕይወትና ንብረትን ያጠፋል እንጂ ችግርን አይፈታም ሲሉ ገልጸው፤ “ታሪካዊ አጋጣሚ” በሆነው ሀገራዊ ምክክር በመሳተፍ ሐሳብን በማቅረብ መግባባት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ኮሚሽነሯ አሁንም ታጣቂዎቹ ወደ ምክክሩ እንዲመጡ በመጠየቅ ሲመጡም ጥበቃ እንደሚደረግላቸው አረጋግጠዋል ተብሏል፡፡

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር እና የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስን ጨምሮ ሌሎች የሲቪክ ድርጅቶች በሀገራዊ ምክክሩ ከመሳተፍ እራሳቸውን አግልለዋል።

የ #ኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ስራ አስፈጻሚ ኪሚቴ አባል የሆኑት ሱልጣን ቃሲም በቅርቡ ከአዲስ ስታንዳርድ ጋር ባደረጉት ቆይታ ፓርቲያቸው የኮሚሽኑ ምስራታ ሂደት እና እያከናወነው ያለው ስራ ላይ ቅሬታ እንዳላቸው አስረድተዋል።
Join @ayuzehabeshaofficial
17.2K viewsAyu, edited  08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 11:26:50
ማስታወቂያ
ፂም የለዎትም፡ ፀጉሮ እየሸሸ ነው ወይስ ራሰ-በራ ኖት ?
Call 0712148785
                  0909812211
አስደናቂው የፀጉርና ፂም ማሳደግያ
                MINOXIDIL

በ 1 ወር ውስጥ ውጤት የሚያሳይ
ከ (3-6) ወር ውስጥ ድፍን ያለ ፀጉር/ፂም  እንደኖርዋ ያደርጋል፡፡

ልብ ይበሉ manufacturing 2024-2025
Made in USA የሆነ label ያለዉ orignal ምርት


ለ 1 ወር የሚቀባ 1700ብር
ለ 3 ወር የሚቀባ  1600*3 ብር
ለ 6 ወር የሚቀባ   1500* 6 ብር                                                                                                         

አዲስ አበባ ዉስጥ ነፃና ፈጣን የ delivery አገልግሎት እንሰጣለን።
                
Hair Regrowth Derma roller
የፀጉር ማሳደግያ ማይክሮ-ኔፕሊንግ
ዴርማ ሮለር  የደም ፍሰትን እና የፀጉር እድገትን ይጨምራል::
የፊት ቆዳ ጤንነት ለመጠበቅ እና  ብጉር እንዲሁም ጠባሳን ለማስወገድ ተመራጭ፡፡
ዋጋው 650 ብር  እጅግ በሚገርም ቅናሽ ከ ነፃ  delivery ጋር                                                                                                                 .inbox on @Rama_Technology_Agent or call 0712148785
         0909812211
18.6K viewsAyu, 08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 09:51:32
የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ስለሙስሊሞች በሰጡት አስተያየት ተቃውሞ ተነሳባቸው
ህንድ 1.42 ቢሊዮን ህዝብ ያላት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 200 ሚሊዮን የሚሆነው ህዝቧ ሙስሊም ነው
የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሞዲ ስለሙስሊሞች በሰጡት አስተያየት ተቃውሞ እንደተነሳባቸው ተገልጿል።
የህንዱ ዋና ተቃዋሚ ኮንግረስ ፓርቲ ምክርቤት የምርጫ ህጎችን በመጣስ በሙስሊሞች ላይ ተገቢ ያልሆነ አስተያየት ሰጥተዋል ባላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ላይ የምርጫ ኮሚሽን እርምጃ እንዲወስድ አቤቱታ ማቅረቡን ሮይተርስ ዘግቧል።
ለሶስተኛ ዙር የስልጣን ዘመን እየተወዳደሩ ያሉት ሞጄ ባለፈው እሁድ ባቀረቡት የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ሙስሊሞችን "ሰርጎገቦች" በሚል መጥራታቸው ከተቃዋሚዎች ከፍተኛ ትችት አስነስቶባቸዋል።
የሞዲ የሂንዱ ብሔርተኛ ባራቲያ ጃናታ ፓርቲ(ቢጄፒ) እና አጋሮቹ ሙስሊሞችን በህገወጥ መንገዱ ከፓኪስታን የመጡ ሰርጎገቦች ሲሉ ይጠሯቸዋል። ሙስሊሞችን ባላቸው ከፍተኛ የወሊድ ምጣኔ ምክንያት የሚተቹት የሞዴ ፓርቲ እና አጋሮቹ የህንድ ሙስሊም ህዝብ አብዛኛ ቁጥር ያለውን ሂዱን ሊበልጥ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።
ህንድ 1.42 ቢሊዮን ህዝብ ያላት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 200 ሚሊዮን የሚሆነው ህዝቧ ሙስሊም ነው።
የኮንግረስ መሪ አቢሸክ ማኑ ሲንግቪ እንደገለጹት  የሞዴ ያልተገባ ንግግር እጩ ተመራጮች፣ መራጮች እጩዎችን "በሀይማኖት" "በማህበረሰባዊ ማንነት" ወይም "በሀይማኖታዊ ምልክቶች" እንዲመርጡ ወይም እንዳይመርጡ እንዳይጠይቁ የሚከለክለውን የምርጫ ህግ ጥሷል።
የምርጫ ኮሚሽኑ ይህንን እንዲመለከተው ማመልከታቸውን ሲንግቪ ተናግረዋል።
የሞዲ መንግስት ሙስሊሞችን በማግለል በተደጋጋሚ ክስ ይቀርብበታል።ነገርንግን ሞዲ የሚነሱባቸውን ሁሉንም ክሶች አስተባብለዋል።
Join @ayuzehabeshaofficial
19.4K viewsAyu, edited  06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 09:40:15 5 ሰው ተገደለ 18 ቤት ተቃጠለ
በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር አምስት ሰዎች ሲገደሉ 18 ቤቶች መቃጠላቸውን ተገልጾአል።

ሟቾቹ አራት ወንዶች እና አንድ ውሃ ስትቀዳ ነበር የተባለች ሕጻን መሆናቸው ተገልጿል።

በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ አጎና በተባለ ‘የቀበሌ ከተማ’ ባለፈው ሰኞ ሚያዚያ 7/2016 በፋኖ እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል የተካሄደ ግጭትን ተከትሎ፤ ነዋሪዎች መገደላቸውን እና በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን የተጎጂ ቤተሰቦች እና የዐይን እማኞች ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ጋይንት፣ ሞጃ፣ እስቴ እና ስማዳ ለተባሉ የደቡብ ጎንደር ወረዳዎች ማዕከል ናት በተባለችው አጎና የፋኖ ሀይሎች እና የመንግሥት ኃይሎች “በአጋጣሚ መንገድ ላይ ተገናኝተው” የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ተከትሎ ጥቃቱ መፈጸሙን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

ከእስቴ ወረዳ የመጡ ናቸው የተባሉ የፋኖ ታጣቂዎች እና ወደ ጋይንት ወረዳ በመጓዝ ላይ ነበሩ የተባሉ የመንግሥት ኃይሎች መጋጨታቸውን ተከትሎ፤ በንጹሃን ሰዎች እና በቤቶች ላይ ጥቃቱ መፈጸሙን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ሰኞ ሚያዚያ 7/2016 ጠዋት 3 ሰዓት አካባቢ ግድያው እንደተፈጸመ የተናገሩ አንድ የአካባቢው ነዋሪ፤ “በተኩስ ልውውጡ የመንግሥት ኃይሎች ጉዳት ስለደረሰባቸው ጥቃቱን እንደፈጸሙ” ተናግረዋል።

አንድ የአጎና ነዋሪ “በአጋጣሚ የመኪና መንገድ ላይ እና መንደር ላይ ያገኟቸውን ንጹሃን አንድ ሴት እና አራት ወንዶችን ነው የመቷቸው” ሲሉ ስለ ጥቃቱ ተናግረዋል።

“ከረምቡላ ቤት፣ ፑል ቤት ያሉትን እየከፈቱ እዚያ የሚጫወቱትን ነው ጨፍጭፈዋቸው የሄዱት” ያሉ ሌላ ነዋሪ ድግሞ፤ ይህ ሲሆን “የፋኖ ኃይሎች በቦታው አልነበሩም” ብለዋል።

በጥቃቱ የ22 ዓመት ወንድማቸው እንደተገደለባቸው ለቢቢሲ የተናገሩ አንድ የሃይማኖት አባት፤ ታናሽ ወንድማቸው ተደብቆ ከነበረበት ፑል ቤት ከሦስት ጓደኞቹ ጋር መገደሉን ተናግረዋል።

ወንድማቸው ከመሞቱ በፊት “ነፍሱ” ላይ ደርሼ ነበር ያሉት ይኚህ ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ ነዋሪ፤ ጤና ጣቢያ ማድረስ ባለመቻላቸው ወደ ቤታቸው ወስደው የህክምና እርዳታ ቢደረግለትም ሕይወቱ እንዳለፈ ተናግረዋል።

ሟቾቹ አራት ወንዶች እና አንድ ውሃ ስትቀዳ ነበር የተባለች ሕጻን እንደሆኑም የሃይማኖት አባት የሆኑት ነዋሪ ተናግረዋል።

የሁሉም ሟቾች ቀብር በማግሥቱ ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ 6 ሰዓት ላይ ‘አጎና ማሪያም’ ቤተ-ክርስቲያን እንደተፈጸመ የሃይማኖት አባቱ ተናግረዋል።

የሰላማዊ ሠዎቹን ግድያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት እንደፈጸሙት የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ጥቃት ፈጻሚዎችን በደንብ ልብሳቸው እና በሚያሽከረክሯቸው መኪኖች መለየት እንደቻሉ ገልጸዋል።

ለግድያው ምክንያት ፋኖን ትደግፋላችሁ የሚል እንደሆነ የተናገሩ አንድ ነዋሪ፤ “እናንተ ባትኖሩ ፋኖ አይኖርም ነበር” በሚል ጥቃቱ እንደተፈጸመ ተናግረዋል።

የመንግሥት ኃይሎች ከተማዋን ጥለው ወጥተው [ከጋይንት መስመር] ሲመለሱ ከሰዓት በኋላ ሰንዝረውታል በተባለ ጥቃት፤ 18 ቤቶች መቃጠላቸውንም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

ቢቢሲ በአካባቢው የተቃጠሉ ናቸው የተባሉ ቤቶችን የሚያሳይ ቪዲዮ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያገኘ ቢሆንም፣ ስለትክክለኛነታቸው ግን ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጿል።

የአካባቢው ማኅበረሰብ ድጋፍ እያደረገላቸው እንደሆነ የተናገሩት ነዋሪዎች፤ ቤቶቹ ‘በጋዝ እና ላይተር’ እንደተቃጠሉ ተናግረዋል።

በስጋት የተሸበበው የአካባቢው ነዋሪ ከዚህ ቀደምም ተመሳሳይ ጥቃት በመድረሱ አካባቢውን ለቆ በተለይም ወደ ገጠር “እየተሰደደ” መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የፌደራል መንግሥት ኢመደበኛ ያላቸውን ታጣቂዎች ትጥቅ ለማስፈታት መወሰኑን ተከትሎ በአማራ ክልል የተከሰተው አለመረጋጋት በተለያዩ የክልሉ ክፍሎች ውስጥ ከተስፋፋ አንድ ዓመት ሊሞላው ተቃርቧል።
ቢቢሲ
Join @ayuzehabeshaofficial
18.8K viewsAyu, edited  06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 09:40:11
18.0K viewsAyu, 06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-23 09:18:43
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የቀሲስ በላይ ጉዳይ ከቤተክርስቲያኗ ጋር የሚያገናኘው ነገር እንደሌለ አስታወቀች
ከሰሞኑ ቀሲስ በላይ መኮንን በሀተኛ ሰነድ 6 ሚሊዮን 50 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ገንዘብ ለማዘዋወር ሞክረዋል በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርትያኗ ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር እንደሌለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ማስታወቋን ዶቸቬለ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ግለሰቡ በቤተክርስቲያኗ በከፍተኛ ኃላፊነት የሚያገለግሉ ቢሆንም፤ ተጭበርብሯል ከተባለው ሰነድ ጋር ግን ቤተክርስቲያኗን የሚያገናኛት ምንም ነገር እንደሌለ አስታውቃለች፡፡

መምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትሪያርክ ህዝብ ግንኙነት የሚዲያ ክፍል ዋና ኃላፊ “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር በዋሉበት ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያን ጉዳዩን የመከታተል ጥረት ላይ ትገኛለች ማለታቸውን  ሸገር ታይምስ ሚዲያ ከዜና ምንጩ ዘገባ ለመመልከት ችሏል።

ኃላፊው “እስካሁን በተደረገው ክትትል “ሊቀ አዕላፍ በላይ መኮንን በህግ ጥላ ስር የዋሉበት ጉዳይ ከቤተክርስቲያናችን ጋር የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ እንደሌለና በግል ህይወታቸው ውስጥ የገጠማቸው ነገር እንደሆነ ነው የተረዳነው” ብለዋል።

መምህር ዶ/ር አካለወልድ አክለውም በቀጣይ ጉዳዩ ቤተክርስቲያንን የሚጎዳ ነገር አለው ወይ? የሚለው በህግ ክፍል በኩል ማጣራት እንዲደረግ ትዕዛዝ መተላለፉንም አመልክተዋል፡፡
Join @ayuzehabeshaofficial
18.6K viewsAyu, edited  06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ