Get Mystery Box with random crypto!

ATC NEWS

የቴሌግራም ቻናል አርማ atc_news — ATC NEWS
ርዕሶች ከሰርጥ:
Dambidollouniversity
Dv
Scamalert
Fastmereja
የሰርጥ አድራሻ: @atc_news
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 116.34K
የሰርጥ መግለጫ

#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-04-01 21:45:03
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ቅሬታ


ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ነባር ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተናን ከመጋቢት 30 ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን ይፋ ባደረገው የፈተና ፕሮግራም አሳውቋል። ከዚህ የፈተና ፕሮግራም ጋር በተያያዘ የዩንቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች በዒድ አል-ፈጥር በዓል ቀን ወይም በአንድ ቀን ልዩነት ፈተና ትቀመጣላቹህ መባሉን ተቃውመው ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን ለዩንቨርሲቲው በተለያዩ መንገዶች ማሳወቃቸውንና አጥጋቢ ምላሽ ሊሰጣቸው እንዳልተቻለ ገልፀውልናል።

በዛሬው ዕለት ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ በባህርዳር ዩንቨርሲቲ ዋና ግቢ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎች እንደነበሩና ዩንቨርስቲውም በበጀት እጥረት ምክንያት የፈተናው ፕሮግራም በተጠቀሱት ቀናት እንዲሰጥ እንደተወሰነ ተነግሮናል ብለውናል።

ተማሪዎቹ በተጨማሪም የረመዳን ፆምን ራሳቸውን በራሳቸው እያስተናገዱ፣የሚጠቀሙባቸውን እቃዎች እያጠቡና ሲጨርሱም ሁሉን ነገር ራሳቸው አፅድተው እየፆሙ እንደሆነ ነግረውናል።

የሚድ ፈተና ከወሰድን ከሁለት ሳምንት በኋላ የማጠቃለያ ፈተናን መውሰድ አግባብ አይደለም ያሉት ተማሪዎቹ ብዙ ኮርሶች ከቨር እንዳልተደረጉም ገልፀዋል።

የእስልምና እምነት ተከታዮች የዒድ አል-ፈጥር በዓል የፊታችን ሚያዚያ 01/2016 ወይም ሚያዚያ 02/2016 ይውላል ተብሎ ይጠበቃል።

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.6K viewsMuJa. M, edited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 19:25:45 በብሉቱዝ አማካኝነት ከሚመጡ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነቶችን እንዴት እራሳችንን መጠበቅ እንችላለን?

ብሉቱዝ (Bluetooth) በተንቀሳቃሽ ስልኮች ላይ የምናደርጋቸውን የመረጃ ልውውጦች ያለ ውጫዊ መረጃ ማስተላላፊያ (External data transmission Device) ስልካችንን ከድምጽ፣ ከማፈላለጊያ እና ኤሌክትሮኒክስ ጋር በበይነ-መረብ ቁሶች አማካኝነት የሚያገናኝ ገመድ አልባ ቴክኖሎጂ ነው፡፡

ብሉቱዝ ምቾት የሚሰጥ እና ሥራን ለማቀላጠፍ አመቺ ቴክኖሎጂ ቢሆንም ዋና ዋና የደህንነት ሥጋቶችንም ሊያመጣ ይችላል፡፡

ከዚህ በታች ለተንቀሳቃሽ ስልክዎ የደህንነት ሥጋት ሊሆኑ የሚችሉ የብሉቱዝ ተጋላጭነቶችን እና የመጠበቂያ መንገዶች አቅርበንላችኋል፡፡

• አጠቃላይ የሶፍትዌር ተጋላጭነት መከላከል
ብዙዎቹ በብሉቱዝ መሣሪያዎች ውስጥ የሚገኙ ሶፍትዌሮች ሙሉ በሙሉ አስተማማኝ አይደሉም፡፡ በብሉቱዝ አማካኝነት አዲስ እና የማይታወቅ የደህንነት ተጋላጭነት በተንቀሳቃሽ ስልኮቻችን አንዲሁም በሌሎች መገልገያዎቻችን ላይ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ከደህንነት ስጋት ነጻ የሆነ ሶፍትዌር የሌለ በመሆኑ ሁልጊዜም ጥንቃቄ ማድረግ ተገቢ ነው፡፡

• በስውር ማዳመጥ መከላከል

የብሉቱዝ ምስጠራ (encryption) ወንጀለኞች መረጃዎችን እና የስልክ ጥሪዎችን እንዳያዳምጡ ለማድረግ ያስችላል ፡፡
ስለዚህ ጊዜያቸው ያለፈባቸው የብሉቱዝ መሣሪያዎች ለደህንነት ተጋላጭ የሆኑ ክፍተቶች ሊኖራቸው ስለሚችል ወቅታዊና የዘመኑ ብሉቱዝ ምርቶችን መጠቀም ተገቢ ነው፡፡

• የአገልግሎት ማቋረጥ እንዳያጋጥም ጥንቃቄ ማድረግ
በአጥፊ ቫይረሶች ተንቀሳቃሽ ስልኮቻችንን በመጉዳት ጥሪ እንዳንቀበል እና የባትሪያችን ኃይል በማዳከም የምናደርጋቸውን ግንኙነቶች ሊያስተጓጉሉን ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ብሉቱዝ በማንጠቀምበት ወቅት ብሉቱዛችንን ልንዘጋ ይገባል፡፡

• ብሉቱዝ የሚያካልለውን ስፋት ታሳቢ ማድረግ
ብሉቱዝ ዲዛይን ሲደረግ በግል አውታረ-መረብ ስፋት ነው፡፡ ይህም ማለት ብሉቱዝ ከመሣሪያዎቻችን ጥቂት የእግር እርምጃዎች ርቀት በኋላ ተደራሽ አይሆንም ማለት ነው፡፡ ነገር ግን እኛ ባለንበት እና ጥቃት ሊፈፅም በሚችል ማንኛውም አጥቂ አካል መካከል ያለንን ርቀት እርግጠኛ መሆን አንችልም፡፡ ምክንያቱም ጥቃት ፈጻሚዎች ክፍት ብሉቱዝ መኖሩን ከርቀት የሚያመለክቱ መተግበሪያዎችን ሊጠቀሙ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም በማንጠቀምበት ጊዜ ብሉቱዛችንን ማጥፋት ተገቢ ነው፡፡

• ብሉቱዝ የሚጠቀሙ ጆሮ ማዳመጫዎች (earphones) ላይ ጥንቃቄ ማድረግ
በርካታ ብሉቱዝ የጆሮ ማዳመጫዎች አደገኛ የደህንነት ክፍተት ማስተናገጃ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ አጥቂዎች ይህን ተጋላጭነት በመጠቀም ንግግሮቻችንን ሊያዳምጡ ይችላሉ፡፡ በቫይረስ የተጠቃ መሣሪያ የሚያገኘውን መረጃ ለጥቃት ፈጻሚው ያስተላልፋል፡፡ ይህን ለመከላከልም በቀላሉ የሚገመት የፋብሪካ ምርት ፒን ኮድን /PIN code/ ለመገመት አዳጋች በሆነ ኮድ መቀየር ጠቃሚ ነው፡፡

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.1K viewsMuJa. M, 16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 19:25:32
በብሉቱዝ አማካኝነት ከሚመጡ የሳይበር ጥቃት ተጋላጭነቶችን እንዴት እራሳችንን መጠበቅ እንችላለን?


https://t.me/atc_news/23864
14.9K viewsMuJa. M, edited  16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 19:24:47
#GTSTv1_Round_6

"Geez tech Ethical Hacking course" በ6ተኛ ዙር ተመልሷል!!!

አሁኑኑ ተመዝገቡ!!!
እንዲሁም SHARE አድርጉት

ለ 100 ሰው ቦታ ነው ያለዉ
ትምህርት መጋቢት 30 ይጀመራል

ለበለጠ መረጃ + Registration

LINK: https://forms.gle/ebDiZ9ab8hr8gT1X7

For contact: @geeztechsupport
#geeztech #gtstv1 @geeztechgroup
14.2K viewsMuJa. M, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 19:24:33
ትምህርቶን በውጭ ሀገር ሄደው ለመከታተል አስበዋል


አይከን ስኮላር አካዳሚ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ International Student Festival ይዞላቹሁ መጣ

በፌስቲቫሉ ላይ ከአሜሪካ፣ ከአውሮፓ፣ ከመካከለኛው ምስራቅ እንዲሁም ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡ የዩንቨርስቲ ዳይሬክተሮች( ተወካዮች) በቀጥታ አግኝተው የስኮላርሺፕ ፕሮሰሶን የሚጀምሩበት እድል ይኖሮታል



ሚያዝያ 5 እና 6
በ ጊዮን ሆቴል
ከ ጠዋቱ 2:00 እስከ 11:00

ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ የመማር ፍላጎት ያላችሁ በሙሉ የዚህ ፕሮግራም ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችሁአል።

፨ ያለ ምንም ቅድመ ክፋያ
፨ ያለ ምንም አይነት መግቢያ ፈተና
፨ 100%የተረጋገጠ ቅበላ
፨ በሀይ ስኩል ፣በመጀመሪያ ዲግሪ እንዲሁም በማስተርስ

እኛጋ ሲመጡ ምን ያስፋልጎታል፦
ፓስፖርት/ የልደት ሰርተፍኬት
ትራንስክሪፕት /ቴምፖ


ይህንን እድል ለማግኘት ተማሪው መመዝገቡ ብቻ በቂ ነው ።

የዚህ እድል ተሳታፊ በመሆን የወደፊት የትምህርት ጉዞዎን ይጀምሩ

ይፍጠኑ ያለን ቦታ ውስን ነው፧

መግቢያ በነፃ

ለመመዝገብ ይህንን ሊንክ #ይጫኑ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScKTVR6WoXPAivB1RUae_0qYuEjbvwBq_FvIxMzOhMp-fdWkw/viewform
#አይከን_ስኮላር_አካዳሚ
#አለም_አቀፍ_የተማሪ_ዝግጅት
#ትምህርት
#ዕድል
14.3K viewsMuJa. M, 16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 13:15:02
ለልዩ ፍላጎት ትምህርት የሚረዱ 14 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት ወደ ሥራ ገብተዋል
**********

የልዩ ፍላጎት ትምህርትን ለማጠናከር የሚረዱ 14 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት በመገንባት ወደ አገልግሎት ማስገባቱን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በቢሮው የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት እና መደበኛ ትምህርት ዳይሬክተር አቶ ዳንኤል አስራት ለኢፕድ እንደገለጹት፤ የልዩ ፍላጎት ትምህርት በመዲናዋ ተደራሽ እንዲሆን ቢሮው የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ቀደም ብሎ በከተማዋ 72 የድጋፍ መስጫ ማዕከላት የነበሩ ሲሆን፤ አሁን ላይ አስራ አራት ማዕከላት ተገንብተው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ መደረጋቸውን ጠቁመዋል።

(ኢ.ፕ.ድ)
ሙሉውን ለማንበብ
https://press.et/?p=124724

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
16.4K viewsMuJa. M, 10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 13:13:46 Safari English Academyዎች ነን በonline ለሁለት ወር ያክል እንግሊዘኛ የመናገር ችሎታችሁን ለማሳደግ ሁለተኛ ዙር ምዝገባ ጀምረናል።

መሉ በሙሉ online በመሆኑ በቤታችሁ ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ

ጥቂት ተማሪዎችን ብቻ ስለምንፈልግ ምዝገባው የምቆየው ለ4 ቀን ስሆን በመጀመሪያዎቹ 2 ቀናት ለሚመዘገቡ የ50% ቅናሽ አለው።

ለመመዝገብ @Private_Airport

Telegram Channel: safarienglish

https://t.me/+RBn3SqI-LTkwODdk
16.8K viewsMuJa. M, 10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 22:28:42 በተማሪ ምገባ ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ መመለስ መቻሉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር አስታወቀ።

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ከ15 ሺህ በላይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገድደዋል።

ይሁን እንጂ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ድርቅ ለተከሰተባቸው አካባቢዎች አልሚ ምግቦች በመላክ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ገልጿል።

ተማሪ ልእልት ብርሃኑ በአበርገሌ ወረዳ ማዓርነት ትምህርት ቤት ተማሪ ናት። በወረዳው በተከሰተው ድርቅ ምክንያት ፍየሎችን ለመጠበቅ ከትምህርት ገበታ ርቃ እንደነበረ ገልጻለች። የተማሪ ምገባ በመጀመሩ ወደ ትምህርቷ እንድትመለስ እንዳገዛት ተናግራለች።

ተማሪ ናትናኤል ሹመት በርካታ ተማሪዎች የዕለት ምግብ በማጣታቸው ምግብ ለመፈለግ ከትምህርት ገበታ ርቀው ነበር ብሏል።

አንድ ክፍል ላይ ከ20 ያልበለጡ ተማሪዎች ይገኙ እንደነበርም ነው ያስረዳው። አሁን ግን በአንድ ክፍል ከ50 በላይ ተማሪዎች ይማራሉ ብሏል። መንግሥት የጀመረውን ድጋፍ እስከ ሰኔ እንዲቀጥል እንደሚፈልጉም አስረድቷል።

የአበርገሌ ወረዳ ኒየረ አቑ ከተማ ነዋሪ እና የትምህርት ቤቱ የወመህ አባል አቶ ወርቁ አየነው "ከችግሮች ሁሉ ክፉው ልጅህን የምታበላው ማጣት ነው፤ አሁን ግን ተመሥገን ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታቸው በመመለሳቸው ደስተኞች ነን” ብለዋል።

የመዓርነት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምክትል ርእሰ መምህር ሲሳይ ታደሰ በትምህርት ቤቱ ከሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ጀምሮ ምገባ እንደተጀመረ ገልጸዋል።

የተመዘገቡ ሁሉም ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል ያሉት ምክትል ርእሰ መምህሩ በምገባ ሥራው ለሦስት ሥራ አጥ ወጣቶችም የሥራ እድል መፍጠር ተችሏል ብለዋል። የተማሪዎች የመማር ፍላጎትም በእጥፍ ጨምሯል ነው ያሉት።

የአበርገሌ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ገብረሃና ኪሮስ በበኩላቸው በወረዳው በ12 ትምህርት ቤት ምገባው የተጀመረ ሲኾን ከ6ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባው ተጠቃሚ ስለመኾናቸው አብራርተዋል።

በሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ያቋረጡ ከአንድ ሺህ 150 በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ ተመልሰዋል ነው ያሉት፡፡

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ፍታለሽ ምህረቴ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ባደረገው ድጋፍ በዞኑ 64 ትምህርት ቤቶች የምገባ ተጠቃሚ እንደኾኑ ገልጸዋል።

በዚህም ከ30 ሺህ በላይ ተማሪዎች የምገባው ተጠቃሚ እንደኾኑ የገለጹት ምክትል ኀላፊዋ ምገባው እስከ ትምህርት ዓመቱ መገባደጃ ድረስ የሚቀጥል ነው ብለዋል።

የተማሪ ምገባ በብሔረሰብ አሥተዳደሩ መከፈቱ ሁለንተናዊ ፋይዳው የጎላ እንደኾነም ነው ያስገነዘቡት፡፡ መምሪያ ኀላፊዋ በምገባ ሥራው ከ200 በላይ ሥራ አጥ ወጣቶች ጊዜያዊ የሥራ እድል እንደተፈጠረላቸው ነው ያስገነዘቡት፡፡ ተማሪዎችም ትምህርታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

[ዘገባው የአሚኮ ነው]
ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
19.2K viewsMuJa. M, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 22:28:23
በተማሪ ምገባ ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ገበታ መመለስ መቻሉን የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሥተዳደር አስታወቀ።
17.9K viewsMuJa. M, 19:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-31 13:25:02 ከሥራ አጥነት ወደ ቀጣሪነት የተሸጋገሩ የቸሃ ወጣት አርሶአደሮች

ከተንጣለለው የቃሪያ ማሳ ደርሰናል። በስተቀኝ ደግሞ ሽንኩርት፣ ኪያር፣ ጥቅል ጎመን፣ ዝኩኒና ሌሎችም የጓሮ አትክልቶች በስፋት ተተክለው ይታያሉ። በቅርብ ርቀት ደግሞ በርከት ያሉ ሴቶችና ወጣቶች የቀሩ ምርቶችን በመሰብሰብ ሥራ ተጠምደዋል። ይህ ከ30 ሄክታር በላይ የሚልቀው ማሳ ታዲያ ከዓመታት በፊት ከባህር ዛፍ ውጪ ምንም አገልግሎት የማይሰጥ ሜዳ እንደነበር ከአካባቢው አርሶ አደሮች ነግረውናል።

ወጣት ዳንኤል ሽፈታ እዚሁ ቸሃ ወረዳ ወድሮ ቀበሌ ላይ ነው ተወልዶ ያደገው። ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ በሆርቲካቸር ትምህርት ዘርፍ ተመርቆ በእርሻ ሥራ ለመሰማራት ከአራት ጓደኞቹ ጋር ይመክራል፤ የራሳቸውን ሥራ ለመጀመር የሚያግዛቸውን 70 ሺ ብር ከቆጠቡ በኋላ ከቸሃ ወረዳ 28 ሺ ብር ብድር፣ ምርጥ ዘርና እንደ የውሃ ፓምፕ የመሳሰሉ ግብዓቶችን በማግኘት በአንደኛው ጓደኛቸው አባት ጓሮም ሽንኩርትና ሌሎች አትክልቶችን ማልማት ይጀምራሉ።

ከአንድ ሄክታር በማይልቀው መሬት ላይ አልምተው 70 ሺ ብር ሲያገኙ ልባቸው የበለጠ ለማልማት ተነሳሳ፤ እናም ከአንድ ሄክታር ወደ ሁለት፤ ከሁለት ወደ ሦስት ሄክታር መሬት አሰፉ። የምርት አይነታቸውንም ከዚህ ቀደም በአካባቢው ኅብረተሰብ ብዙም ያልተለመዱ ግን ደግሞ በከተሞችና በውጭ ገበያ ተፈላጊ የሆኑ እንደ አበባ ጎመን፣ ብሮኮሊና ኪያር ያሉ የጓሮ አትክልቶችን እንዲያለሙ ወረዳው ሰባት ሄክታር መሬት አመቻቸላቸው። እነዚህ ብርቱ ወጣቶች ታዲያ ሳይታክቱ ማልማታቸውን ቀጠሉና እድገታቸውን ጨመሩ። ይህን ያየው የወረዳው አስተዳደርም የብድር አቅርቦቱን ወደ 300 ሺ ብር ከፍ አደረገላቸውና አቅማቸውን አጎለበቱ።

‹‹በአሁኑ ጊዜ የእርሻ መሬታችን 30 ሄክታር ሲሆን በዚህም ጎመን፣ ቲማቲም፣ ሽንኩርት፣ ብሮኮሊ፣ አበባ ጎመን፣ ሃብሃብና ሌሎችም ተፈላጊ ምርቶችን በስፋት በማልማት ለገበያ እናቀርባለን›› የሚለው ወጣት ዳንኤል፤ በተለይም በወረዳው አማካኝነት በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር በመጠቀም ያለ ብዙ ድካምና እንግልት ምርታቸውን ወደ ተጠቃሚው እንደሚያደርሱ ይገልጻል። በአሁኑ ወቅት ካፒታላቸውን ወደ አስር ሚሊዮን ብር ማድረሳቸውን አመልክቶ፤ ከ100 በላይ ለሚልቁ የአካባቢው ወጣቶች በቋሚነት የሥራ እድል መፍጠራቸውን ያመለክታል።

በተጨማሪም በየቀኑ ከ100 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች በእርሻው ላይ በጊዜያዊነት ተቀጥረው የሚሰሩበት ሁኔታ የተመቻቸላቸው መሆኑንም ይጠቅሳል።
ወጣት ዳንኤል እንደሚገልጸው፤ ምርቶቻቸውን አጎራባች ወረዳዎችና የክልሉ ዞኖች በስፋት ከማቅረብ በዘለለ፤ በኢትዮጵያም ሆነ በውጭ ገበያ ተወዳዳሪ ሆነው ለመቅረብ ተግተው እየሠሩ ነው። በአሁኑ ወቅትም ጥሩና ምርታማ ዘሮችን በማባዛት ለአዳዲስ ማህበራትና አርሶአደሮች ያሰራጫሉ፤ ይህንንም ዘር የማባዛት ሥራቸውን በማጠናከር ክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ ነው ያሉት።

በተጓዳኝም የእርሻ ተረፈ ምርታቸውን በማቀነባበርና መኖ በማዘጋጀት ከብቶችን የማደለብና የወተት ልማት ሥራ ለመሥራት ማቀዳቸውን ወጣቱ አርሶአደር ይናገራል። ውጥናቸው መሳካት ግን አሁን ያለው የብድር መጠን ሊሻሻል እንደሚገባ ሳይጠቁም አላለፈም። በሌላ በኩል ደግሞ ከተለያዩ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው ቁጭ ያሉ ወጣቶች ከተስፋ መቁረጥ ውስጥ ወጥተው እንደእነሱ መንግሥት ያመቻቸውን ምቹ እድል እንዲጠቀሙ ነው የመከረው።
የጉራጌ ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኃላፊና የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አክሊሉ ካሳ እንደሚናገሩት፤ ዞኑ በዋናነትም በበጋ መስኖ ልማት ከ30 ሺ ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ ሰብሎችን እያመረተ ይገኛል።

ከዚህም ውስጥ ወደ 5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታን ምርት መሰብሰብ ችሏል። ዞኑ በስሩ ባሉ የወረዳና ቀበሌ መዋቅሮች የሚገኙ አርሶአደሮችን የመደገፍ ሥራ እያከናወነ ነው። በተጨማሪም እንደእነ ዳንኤል ድህነትን ታሪክ የሚያደርጉ በርካታ ወጣቶችን በመፍጠር የአካባቢውን ብሎም እንደሀገርም በምግብ እህል ራስን የመቻል እንቅስቃሴ ከግብ እንዲደርስ እየተሠራ ነው።

አዲስ ዘመን

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news
13.4K viewsMuJa. M, edited  10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ